Telegram Web Link
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ከላይ በፎቶው የተያያዘው የማኅበረ ቅዱሳን እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ወደ መስቀል አደባባይ ጉዞ ሲያደርጉ የሚያሳይ ነው።

Photo Credit - TMC

@tikvahethiopia
🔥ከባድ ትንቅንቅ የማያጣው የ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ቶተንሃም እሁድ መስከረም 19 በኦልድትራፎድ ይገናኛሉ!

🏆 ቀያዮቹ የሰሜን ለንደኑን ቶተንሃምን መርታት ይችላሉ?

ይህንን ደማቅ ፍልሚያ በጎጆ ፓኬጅ በቀጥታ ይከታተሉ

🎉ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ወደ ጎጆ በማራዘም ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
#MPESASafaricom

ከተለያዪ የውጭ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ በM-PESA ገንዘብ ስንቀበል 5% ተመላሽ አለን!

በM-PESA ገንዘብ እንቀበል ፣ 5% ተመላሽ እናግኝ!

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
 
#FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በአጠቃላይ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል " - የዞኑ ፖሊስ መምሪያ በወላይታ ሶዶ ዞን ዛሬ (ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ/ም) ከቀኑ 7 ሰዓት ደረሰ በተባለ የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ሕይወት ሲያልፍ በ47 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡ አደጋው…
#Update!

“ ከባድ ሁኔታ ላይ ያሉ ተጎጅዎች አሉ፡፡ የ26 ሰዎች አስከሬን ተለይቶ ወደ ዳውሮ ዞን፣ የሁለት ሰዎች ደግሞ ወደ ወላይታ ዞን ተሸኝቷል ” - ወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ

ከወላይታ ዞን ወደ ዳውሮ ዞን እየተጓዘ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ዲዳዬ ወረዳ ፓፓታ ቀበሌ ሲድረስ ትላንት በደረሰበት ድንገተኛ አደጋ በ48 ተሳፋሪዎች ላይ ሞት፣ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹን ነግረናችሁ ነበር፡፡

ፖሊስ፣ አስክሬን የመፈልግ ሥራው እንደቀጠለ፣ በተለይ በ8 ተሳፋሪዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ስለደረሰ ሪፈር እንደተባሉና በዚህም የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ነበር የገለጸው፡፡

ሪፈር የተባሉት ተጎጅዎች እንዴት ሆነው ይሆን ? ስንል ዛሬ በድጋሚ የጠየቅናቸው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ንጋቱ ጌታቸው ምላሻቸው፣ “ ተጎጅዎች ሕክምና እየተከታተሉ ናቸው፡፡ ጉዳቱ ከባድ ስለሆነ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል ” ብለዋል።

“ በክርቲያን ሆስፒታል፤ ኦቶና ሆስፒታልም ሕክምና እየተከታተሉ ነው፡፡ አንዳንድ ከባድ ሁኔታ ላይ ያሉ ተጎጅዎች አሉ ” ብለዋል፡፡

ኮማንደሩ የደረሰውን አደጋ ሂደት በተመለከተም፣ “ አስከሬን ወደ ቤተሰብ የመሸኘት ሥራ ተሰርቷል፡፡ የ26 ሰዎች አስከሬን ማንነታቸው ተለይቶ ወደ ዳውሮ ዞን፣ ሁለት ሰዎች ደግሞ ወደ ወላይታ ዞን ተሸኝቷል ” ነው ያሉት፡፡

“ ቀሪ ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው 22 ተሳፋሪዎች በኦቶና ወላይታ ሶዶ ሆስፒታል እየታከሙ ነው ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ አስክሬን የማውጣት፣ ምርመራ የማድረግ ሥራ ሌሊቱን ጭምር እስከ 11 ሰዓት ድረስ ወስዷል፡፡ ሕዝቡ፣ አመራሩ፣ የጸጥታ ኃይሉ፣ ሙያተኞች ሁሉ ተረባርበዋል” ብለው፣ በዛ በአስቸጋሪ ቦታ ርብርብ ላደረጉት የወገን ደራሾች ምስጋና አቅርበዋል።

° አሽከርካሪው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንደዋለ፣
° ቀላል ጉዳት እንደደረሰበት፣ ከሆስፒታል ክትትል አድረጎ እንደወጣ፣
° አሽከርካሪው ቃሉን ሲሰጥ የተለዬ መረጃ ካልተገኘ በቀር እስከሁን ባለው መረጃ በተሽከርካሪው ተሳፍረው የነበሩት ወደ 56 ሰዎች እንደነበሩ፣
° 6ቱ ተሳፋሪዎችም አደጋ ሳይደረስርባቸው እንደተረፉ አስረድተዋል።

“ የትራፊክ አደጋ ከገዳይ በሽታም በበለጠ የአገር ተረካቢ ትውልድን ጭምር እየጨረሰ፤ መተኪያ የሌለውን ሕይወትም እየቀጠፈ ነው " ብለዋል

" አሽከርካሪዎ፤ ባለንብረቶች፣ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የትራፊክ ደንብና ሕግን አክብረው እንዲሽከረክሩ ጥሪ አቀርባለሁ ” ሲሉ ኮማንደሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የተሳፋሪዎች ቁጥር ከ56ም ሊጨምር ይችላል የሚል ግምት እንዳለ፣ የአደጋው ቴክኒካል ምክንያት ገና በምርመራ ላይ እንደሆነ የተመላከተ ሲሆን፣ በህክምና ላይ ያሉት ተጎጅዎችን ሁኔታ ጭምር ተከታትለን መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፍቶ፦ የመስቀል ደመራ በዓል እየተከበረ ይገኛል።

በአዲስ አበባ ከሰዓታት በፊት ዝናብ ሲጥል ነበር።

ምንም እንኳን ሲዘንብ የነበረው ዝናብ ጠንከር ያለ ቢሆንም የበዓሉ ድባብ አልደበዘዘም።

#ኦርቶዶክስተዋሕዶ #መስቀልደመራ

Photo Credit : ኢቢሲ ፣ ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ፣ Tikvah Family AA

@tikvahethiopia
2024/09/27 07:34:12
Back to Top
HTML Embed Code: