Telegram Web Link
#እንድታውቁት

አዲስ አበባ ውስጥ ከነገ ማለዳ 12 ሠዓት እስከ ዓርብ ማለዳ 12 ሠዓት ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ተከለከለ።

የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ፥ " ለመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የመንገድ ትራንስፖርት ደህንነት ሲባል ከመስከረም 16 እና 17 ቀን 2017 ዓ.ም ማለዳ 12 ሠዓት ድረስ በመዲናዋ የሞተር ብስክሌት የትራንስፖርት አገልግሎት ተከልክሏል " ሲል አሳውቋል።

የትራንስፖርትና የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እና የትራፊክ ፖሊሶች አፈፃፀሙን ተግባራዊ እንዲያደርጉም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
#MPESASafaricom

በዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ቀኑን ሙሉ ፈታ እንበል! 🥳 በM-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው! 

በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በፈጣን ዳታ እንንበሽበሽ!

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቦታችንን https://www.tg-me.com/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#SafaricomEthiopia
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
" ወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በአጠቃላይ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል " - የዞኑ ፖሊስ መምሪያ

በወላይታ ሶዶ ዞን ዛሬ (ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ/ም) ከቀኑ 7 ሰዓት ደረሰ በተባለ የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ሕይወት ሲያልፍ በ47 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡

አደጋው የደረሰው መነሻውን ከወላይታ አድረጎ ወደ ዳውሮ ዞን ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ፓፓታ ቀበሌ ሲደርስ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል፡፡

በአደጋው የሞቱትና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ምን ያክል ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ንጋቱ በሰጡን ምላሽ፣ " በወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በ14 ሰዎች ከባድ፣ በ5 ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሷል " ብለዋል።

" አጠቃላይ ወደ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል " ብለዋል፡፡

" ከሕጻን እስከ አዋቂ ድረስ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ጉዳት የደረሰባቸው " ነው ያሉት፡፡

" የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል፡፡ አሁን ወደ 8 ሰዎችም ወደ ከፍተኛ ህክምና ሪፈር እየተላኩ ስለሆነ ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል " ሲሉ ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡

አደጋው የደረሰበት ምክንያት ታውቋል ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ " የቴክኒክ ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ነው የሚገለጸው፡፡ ለአሁን ግን ዳገት ተሽከርካሪው ዳገት እየወጣ እስክራፕ ነው የገጠመው፡፡ ከትልቅ ዳገት ላይ ወደ ቁልቁለትና ርቀት ባለው ወንዝ ውስጥ ነው አጠቃለይ ተሳፋሪዎችን ይዞ የገባው " ሲሉ መልሰዋል።

ተሽከርካሪው ስንት ሰዎችን ነበር ያሳፈረው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ፣ " አጠቃላይ ቁጥሩን እየመዘገብን ነው፡፡ እስካሁን ባለው መረጃ በ47 ሰዎች ላይ ነው ሞትና ጉዳት የደረሰው፡፡ ጉዳት ሳይደርስባቸው የተረፉ ወደ 6 ሰዎች አሉ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

" ጠቅላላ ተሳፋሪዎቹ ከ56 እስከ 60 ሰዎች ይደርሳል የሚል ግምት አለን " ነው ያሉት፡፡

" ቦታው ወንዝ ውስጥ ነው፡፡ የአካባቢው ማህበረሰብም የጸጥታ ኃይልም ተረባርቦ ጉዳት የደረሰባቸውን የማንሳት፣ የተጎዱ በፍጥነት ወደ ህክምና እንዲደርሱ እየተደረገበት ያለ ሁኔታ አለ " ነው የተባለው፡፡

ምን ያክል ሰዎች ናቸው ወደ ሕክምና የተላኩት ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ፣ " ጠቅላላ ወደ 21 ሰዎች ወደ ወደ ሆስፒታሎች ተልከዋል፡፡ 8 ሰዎች ከሆስፒታል ሪፈር ተብለው ወደ ክርስቲያን ሆስፒታል ተጭነው እየወጡ ያሉት ሁኔታ ነው ያለው " ተብሏል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

ነገ በአዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ተደርገዋል።

መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከረፋዱ 5:00 ሰአት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የሚከተሉት ናቸው።

- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ

- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)

- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ

- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ

- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ

- ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ

- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ

- ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ

- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከመስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ይዘጋል።

በተጨማሪም በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ ነው።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ መስጠት ይችላል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪውን የመስቀል በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኝ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡

እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉ፡፡

ይህንን ሽልማት ለማግኘት ዛሬ መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው የጥያቄ እና መልስ ውድድር እንድትሳተፉ እንዲሁም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የሽልማቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያድርጉ።

እርስዎም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!! ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡

[Telegram] (https://www.tg-me.com/LionBankSC) [Facebook] (https://www.facebook.com/LionBankSC)
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ
የስኬትዎ አጋር!

https://www.tg-me.com/LionBankSC
መልካም የመስቀል ደመራ በዓል ይሁንላችሁ !

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
#ደመራ

ዛሬ ከሰዓታት በኃላ ለሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ዝግጅቶች ወደመጠናቀቃቸው ነው።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ትላንት በዓሉን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈው ነበር።

በዚህም በዓሉ በድምቀት ፣ባማረና በሰመረ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሕዝበ ክርስቲያኑ በንቃትና በሕብረት በመሆን ከጸጥታ አካላትና ቤተክርስቲያኒቱ ለዚሁ ዓላማ ካቋቋመቻቸው የኮሚቴ አባላት ጭምር በመተባበር እንዲሰራ አደራ ብለዋል።

የመንግሥት የጸጥታ ተቋማት በዓሉ ያለ አንዳች የጸጥታ ችግር ተከብሮ መዋል እንዲችል ከጠቅላይ ቤተክህነት ዐቢይ ኮሚቴ ጋር በጥምረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በበዓሉ ወቅት ለሚደረግ ፍተሻ ፍፁም ክርስቲያናዊ ትብብር እንዲያደርግ አደራ ብለዋል።

የጸጥታ አስከባሪዎችም ጨዋነት በተሞላና ክብርን በሚገልጽ አግባብ የፍተሻ ሥርዓቱን እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።

ሕዝበ ክርስቲያኑ ከበዓላችን መንፈሳዊ ሥርዓት ውጪ የሆኑ መልዕክቶች፣ አለባበሶች እንዲሁም የቤተክርስቲያኒቱ መገለጫ ከሆኑ ዓርማዎች ውጭ መያዝ አይገባውም ብለዋል።

በዓሉ ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ እንደመሆኑ መጠን ቤተክርስቲያኒቱን ከማይገልጹ ሆታዎችና ጭፈራዎች እንዲርቅ አሳስበዋል።

" የመስቀል ደመራ በሚከበርባቸው ቦታዎች ሁሉ ያልተፈቀዱ ነገሮችን ይዞ መገኘት ፍጹም መንፈሳዊ የሆነውን በዓላችንን የሚያደበዝዘው ስለሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል " ብለዋል።

" ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ልጆቻችን ከሚያቀርቡት መንፈሳዊ ትርኢትና ዝማሬ ጎን ለጎን አካባቢያቸውን በመቆጣጠር በዓላችንን በሰላም እንዳናከብር የሚያደርጉ ሁኔታዎች እንዳይፈጠሩ በጥንቃቄ መጠበቅ ይኖርባቸዋል " ብለዋል።

" ብፁዕነታቸው ከንጉሰ ነገስት አጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት ወዲህ ተደርጎ በማያውቅ ሁኔታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሦስተኛ ጊዜ የመስቀል ደመራ በዓልን በድምቀት ማክበር የሚያስችል የስቴጅ፣ የድምጽ ማጉያና የክብር እንግዶች ማስተናገጃ ቦታዎችን በማዘጋጀት ተሳትፎ አድርጓል " ሲሉ ገልጸዋል።

ይህን ተሳትፎም አድንቀው የከተማ አስተዳደሩ እያደረገ ላለው ከፍተኛ አስተዋጽኦ በራሳቸውና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

" በዓሉን ስናከብር ፍቅር ሰላምንና አንድነትን እንዲሁም መግባባትን መርሕ ባደረገ አግባብ መሆን አለበት " ያሉ ሲሆን " በዓሉ ሥጋዊ ፈቃዶቻችንን የምንፈጽምበት ሳይሆን ፦
- ንስሐ ያልገቡ ንስሐ የሚገቡበት
- የተጣሉ የሚታረቁበት
- የተለያዩ አንድ የሚሆኑበት
- የተራራቁ የሚቀራረቡበት
- ፍፁም የደስታና የሰላም በዓል ሆኖ እንዲከበር ማድረግ ይኖርብናል " ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ደመራ ዛሬ ከሰዓታት በኃላ ለሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ዝግጅቶች ወደመጠናቀቃቸው ነው። ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ትላንት በዓሉን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈው ነበር። በዚህም በዓሉ በድምቀት ፣ባማረና በሰመረ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሕዝበ ክርስቲያኑ በንቃትና በሕብረት…
#EOTC

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፦

" ... አንዳንድ ጊዜ በዓልን ምክንያት በማድረግ መጠጦች ይኖራሉ።

በዓል ለመጠጥ ምክንያት ሊሆን አይችልም።

በዓል ስንል መንፈሳዊ በዓላት ሁል ጊዜ ምክንያቶቻችን ፦
- ለፅድቅ ነው
- ለሰላም ነው
- የተጣላ የምናስታርቅበት ፣
- የራቀውን የምናቀርብበት፣
- የተቸገረውን የምንረዳበት
- ያላመነውን እምነት እንዲኖረው የምናስተምርበት ፣
- ከእግዚአብሔር የራቀውን ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቅበትን ንስሃ የሚገባበትን ስራ ለመስራት የሚያስፈልጉን ነገሮች የተዘረዘሩ እንጂ መጠጥ አይደለም።

መጠጥ ክፉ ምኞትን ያመጣል፣ የጉልበት ስሜትን ያመጣል፣ መጠጥ ስካርን ያስከትላል፤ ከዚያ በኃላ የሚሰሩትንም የሚናገሩትንም አለማወቅ ይመጣል።

አንዳንድ ጊዜ በምንሰማው በመንፈሳዊ በዓላቶቻችን መንፈሳዊ ተብለው ሲከበሩ በመጠጥ ኃይል አላስፈላጊ ግጭቶች ተፈጥረው የብዙ ንጹሃን ህይወት ደም የሚፈስበት ጊዜ ይኖራል ፤ ይህ በየትኛውም ቦታ ነው ፤ ስለዚህ ይሄ ጥቅም ስለሌለው ጥቅማችን እኛ በዓሉን በማክበር ካላስፈላጊ ክፉ ምኞት ሳይሆን በጎ ምኞት ፦
° ያልቆረበ ለመቁረብ ፣
° ያልሰገደ ለመስገድ፣
° ከእግዚአብሔር የራቀ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ፣
° ሰላምን ያጣ ሰላምን ለማግኘት ፣
° የተጣላ ለመታረቅ ፣
° ያጣ ሰርቶ ጥሮ ግሮ እግዚአብሔር ስራውን ባርኮለት እራሱን ችሎ ከድህነት ተላቆ የሚኖርበትን እግዚአብሔርን የሚማፀንበት ስራ መስራት እስከተቻለ ድረስ ሁሉ ነገር ውጤታማ ያደርገናል። "

#EOTC

@tikvahethiopia
የዘንድሮው ኢሬቻ በዓል መቼ ይከበራል ?

የዘንድሮ ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 ቀን 2017 ዓ/ም ይከበራል።

የአባገዳዎች ህብረት ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

በዚህም መግለጫ ፥ መስከረም 25 ኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በማግስቱ መስከረም 26 ኢሬቻ ሆረ አርሰዴ እንደሚከበር ገልጿል።

#ኢሬቻ2017

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ : መንገዶቹ ተዘግተዋል።

በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ከላይ በምስሉ የተዘረዘሩት መንገዶች ከዚህ ሰዓት አንስቶ ተዘግተዋል።

ከቤት ለስራም ይሁን ለሌላ ጉዳይ የወጣችሁ አማራጭ መንገዶችን ተጠቀሙ።

@tikvahethiopia
2024/09/27 04:21:43
Back to Top
HTML Embed Code: