Telegram Web Link
Live stream scheduled for
Live stream started
TIKVAH-ETHIOPIA
#ውጤት : የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ ይገለጻል። የትምህርት ሚኒስቴር በውጤቱ ዙሪያ ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጥታ የሚያሰራጭ ይሆናል። ይጠብቁ ! #TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba @tikvahethiopia
#ውጤት : የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።

ሚኒስትሩ የፈተናው ውጤት ለሊት 6 ሰዓት ላይ ይፋ ይደረጋል ብለዋል።

መግለጫውን ከላይ በቀጥታ ይከታተሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አጠቃላይ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች 5.4 በመቶ ናቸው። @tikvahethiopia
ዘንድሮ ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑት ተማሪዎች 36,409 ተማሪዎች ናቸው ያለፉት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዘንድሮ ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑት ተማሪዎች 36,409 ተማሪዎች ናቸው ያለፉት። @tikvahethiopia
አዲስ አበባ 10,690 ተማሪዎች በማሳለፍ ከፍተኛውን ስፍራ ይዟል።

አዲስ አበባ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 21.4 በመቶ አሳልፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲስ አበባ 10,690 ተማሪዎች በማሳለፍ ከፍተኛውን ስፍራ ይዟል። አዲስ አበባ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 21.4 በመቶ አሳልፏል። @tikvahethiopia
ከፍተኛ ውጤት ስንት ተመዘገበ ?

በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በትግራይ ነው።

በትግራይ ፈተናው ከ700 ነው የተሰጠው።

ከቀላሚኖ 675 ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል ፤ በወንድ ተማሪ። ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል ከ700 ይሄን ያህል ውጤት ሲመዘገብ።

ሌላ በሀገር ደረጃ ከ600 ከተፈተኑት ውስጥ 575 ከፍተኛው ነው ከተፈጥሮ ሳይንስ ፤ የካቴድራል ተማሪ ናት።

ከማህበራዊ ሳይንስ 538 ተመዝግቧል። ከኢትዮ ፓረንትስ ትምህርት ቤት ናት።

በተፈጥሮም በማህበራዊ ሳይንስም ትልቅ ውጤት የመጣው በሴቶች ነው።

@tikvahethiopia
Live stream finished (55 minutes)
ሬሜዲያል ዘንድሮም ይኖራል።

" አምና ሰጥተናል። ዘንድሮ ከዓምናው የቀነሰ ቁጥር እንወስዳለን። የሬሜዲያል ፕሮግራም በሂደት እየቀነሰ ይሄዳል " ሲሉ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሬሜዲያል ዘንድሮም ይኖራል። " አምና ሰጥተናል። ዘንድሮ ከዓምናው የቀነሰ ቁጥር እንወስዳለን። የሬሜዲያል ፕሮግራም በሂደት እየቀነሰ ይሄዳል " ሲሉ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተግረዋል። @tikvahethiopia
#Amhara

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ " ዘንድሮ ሁሉም
ክልሎች አምና ካሳለፉት ተማሪ በላይ አሳልፈዋል " ብሏል።

" በፐርሰንቴጅም በአክቹዋል ቁጥርም ካለፈው የተሻለ ነው " ተብሏል።

ከአክቹዋል ቁጥር ያነሰው አንድ ክልል ነው እሱም የአማራ ክልል እንደሆነ ተገልጿል።

ክልሉ ያነሰው ደግሞ የተፈተኑት ተማሪዎች ቁጥር ከግማሽ በታች ስለነበር ነው ተብሏል።

ክልሉ ፈተና ካስፈተናቸው ውስጥ ግን 6.6 በመቶ ተማሪዎች አልፈዋል።

አምና ከተመዘገበው 4.1 በመቶ ዘንድሮ በልጧል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ውጤቱ በጣም ዝቅተኛ ነው !

" በ2016 ትምህርት ዘመን በወረቀትና በበይነ መረብ የተሰጠው ፈተና ውጤት እንድምታው ሲታይ ከ2014 ዓ/ም 30,034 (3.3%) ፣ ከ2015 ዓ/ም 27,267 (3.2%) ... (ዘንድሮ 5.4%) መሆኑ እያሽቆለቆለ እየሄደ ያለው ጉዞ የተገታ እና መጠነኛ የመሻሻል አዝማሚያ ያሳየ ቢሆንም አሁንም 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተፈታኞች ቁጥር በጣም #ዝቅተኛ ነው። " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር)

@tikvahethiopia
Jasiri is looking for young, motivated and impact driven women entrepreneurs to join our 13 month, fully funded talent investor program.

Apply today for a chance to make a change through high impact entrepreneurship.

👉🏾 https://bit.ly/3A8rxtV

For more information, Join our telegram channel 👉🏾 @Jasiri4Africa
#SafaricomEthiopia

🌻 አንዴ የበዓል ዝግጅታችንን ቆም አርገን 🏃🏼ወደ TikTok ሄደን ተሰጥዖአችንን እናሳይ!
እስከ መስከረም 18 ብቻ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ  እንዝፈን! እንላክ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!

#1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
#Oromia : በመሬት ናዳ የሦስት እህትማማቾች ሕይወት አለፈ።

በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ጅማ ሆሮ ወረዳ ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት አደጋ የአንድ ቤተሰብ አባላት የነበሩ 3 እህትማማቾች መሞታቸውን የዞኑ አደጋ መከላከል ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ኑራ መሐመድ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ህይወት የጠፋው በአንድ አባወራ መኖሪያ ቤት አፈር ተደርምሶ ነው።

የእናት እና አባት ህይወት ሲተርፍ ሶስቱ ልጆቻቸው ሞተዋል።

አደጋው የተከሰተው ጷጉሜ 2 ሌሊት ስምንት ሰዓት ላይ ሲሆን አስክሬናቸውን የአካባቢው ማህበረሰብ በነጋታው በማውጣት የቀብር ስነ ስርዓታቸው እንዲፈጸም መደረጉን የዞኑ አደጋ መከላከል ጽ/ቤት ገልጾልናል።

አደጋው በተከሰተባቸው አኮ ጅሩ፣ኢሉ ኩታዬ እና ኡነይ ቀበሌዎች ከሰው ህይወት ህልፈት በተጨማሪ በሰብል የተሸፈነ 20 ሄክታር ማሳ መውደሙ ተነግሯል።

በተጨማሪም ከጅማ ሆሮ ወደ ጊዳሚ የሚወስደው መንገድ በመሬት መንሸራተቱ መዘጋቱን እና ለማስከፈት ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ሃላፊው አክለዋል።

ችግሩ አሳሳቢ በመሆኑ ተጨማሪ ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ 10 ቤቶች ላይ የሚኖሩ አርሶ አደሮችን በማንሳት ወደሌሎች አካባቢዎች እንዲሰፍሩ እየተሰራ ነው ተብሏል።

Via @tikvahethmagazine
2024/09/30 16:25:28
Back to Top
HTML Embed Code: