Telegram Web Link
#Waryt

#ዋሪት

ውድ ደንበኞቻችን አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በውሃ ማጣሪያዎቻችን ላይ ከጳጉሜ 1 - ጳጉሜ5 /2016  የሚቆይ ልዪ ቅናሽ ማድረጋችንን  ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው እንዳያመልጥዎት ወደ ማሳያ ክፍሎቻችንን በመምጣት ይጎብኙን !

ስልክ ፦ 0911210706/07
#TPLF #እንዳስላሰሽረ

በሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ።

ህወሓት ሰላማዊ ስልፍ ለማካሄድ ከጳጉሜን 3 - 5 ባሉት ቀናት የጠየቀ ሲሆን ሰልፉ የሚካሄድበት ቦታ ደግሞ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ ነው።

የህወሓት ፅህፈት ቤት እንዳስላሰ ሽረ ቅርንጫፍ ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም በፃፈው የሰላማዊ ሰልፍ የፍቃድ ደብዳቤ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፁ ለማሰማት መፈለጉ ያትታል።

ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ፍቃድ በጠየቀበት ሰላማዊ ሰልፍ ፦

"
- ከባቢያዊ መለያየትና አገር የሚበትኑ ተግባራት ይቁሙ !
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ !!
- የፀለምቲና ራያ ተመላሽ ተፈናቃዮች ድህንነታቸው ይጠበቅ !
- የህዝበኝነት ፓለቲካ በትግራይ እንቃወማለን !
- የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር !
- ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመለት ዓላማ ይተግብር !
- ህወሓትን ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ ይቁም !
- ህወሓት ሰላምን ይደግፋል !
- ጦርነት የሚናፍቅ የህወሓት መሪ የለም ! "

የሚሉና ሌሎች መፈክሮች እንደሚያሰማ በፍቃድ መጠየቂያ ደብዳቤው ላይ ገልጿል።

ቅርንጫፍ ፅህፈቱ ለጠየቀው ' ሰላማዊ ሰልፍ ' የማካሄድ ጥያቄ መልስ የሰጠው የእንዳስላሰ ሽረ ከተማ አስተዳደር በወቅቱ ባለው የፓለቲካ ትኩሳት እና የአዲስ ዓመት መለወጫ በመሆኑ ምክንያት የፀጥታ ሃይሉ የተደራረቡ ስራዎች ስላሉበት ሰላማዊ ስልፉ እንዳልተፈቀደ አሳውቋል።

በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ልኡክ በተምቤን ዓብዩ ዓዲ ዓዲግራትን ማይጨው ካካሄዳቸው ህዝባዊ ውይይቶች በመቀጠል በአክሱምና በእንዳስላሰ ሽረ ከተማዎች ለማካሄድ አቅዶ የነበረ ቢሆንም አቶ ጌታቸው ባጋጣመቸው የጤና እክል ምክንያቱ ውይይቱ ለሌላ ጊዜ መዛወሩን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል መዘገቡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
🔈 #የሰራተኞችድምጽ

" ክፍያችን ከኑሮ ውድነት አንጻር በጣም የወረደ በመሆኑ ህይወት አስቸጋሪ ሆኖብናል " - በሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ ሰራተኞች

" በ1000 ብር ደሞዝ ኑሮን መቋቋም አቃተን "  ያሉ የሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ ሰራተኞች የሚከፈለን ገንዘብ ከቤት ኪራይ የማያልፍ በመሆኑ በረሀብ እየተሰቃየን ነው በማለት ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

የረከሰ ቤት ፍለጋ ከከተማ ወጣ ያሉ ሰፈሮች በመምረጥ ሶስት አራት ሆነዉ እንደሚከራዩና ጠዋት አንድ ሰአት ለመድረስ ከአስራ ሁለት ሰአት በፊት ተነስተዉ ያውም በባዶ ሆድና በእግር እንደሚመጡ የሚናገሩት ሰራተኞቹ " አሁን ግን ኑሮ ጣሪያ በመንካቱ በዚህ መልክ እንኳን መቀጠል አልቻልንም " ብለዋል።

" ምንም እንኳን የምሳ ድጋፍ ቢደረግልንም በአንድ ከተማ በአንድ የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ያለዉ ልዩነት ያሳዝናል " በማለት በፓርኩ ውስጥ እንኳን ልዩነት መኖሩን ይገልጻሉ።

አንዳንድ ሼዶች የትራንስፖርት አገልግሎትን ጨምሮ የትርፍ ሰአት ስራ የሚያመቻቹ ቢሆንም ሌሎች ደግሞ ከአንድ ሽህ ብር ደሞዝ ውጭ ምንም ትርፍ ነገር አይሰጡም።

" በዚህም ኑሮን መግፋት ተራራ ሆኖብናል " በማለት ያሉበትን የስቃይ ህይወት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

ሰራተኞቹ " በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አይደለም የቤት ኪራይ ከፍለንና የምግብ ወጭ ሸፍነን ለመኖር ይቅርና ሰርተዉ ይረዱናል ብለዉ በማሰብ ወደላኩን  ቤተሰቦቻችን ለመመለስ እንኳን አስቸጋሪ ሆኖብናል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን የሰራተኞች እሮሮ ይዞ ምላሽ ለማግኘት የሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክን ደጋግሞ ቢያናንኳኳም ለጊዜዉ ምላሽ ማግኘት አልቻልንም።

ይሁንና በቅርቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈጻሚው አቶ ዘመን ጁነዲን " የሰራተኛውን ምቹ ከባቢ መፍጠር የኛም ፕራይወሪቲ ነው " ብለው ነበር።

አሁን ላይ ከሚመለከታቸዉ አካላት በተለይም ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር እየተነጋገርሩ መሆኑን የገለጹት አቶ ዘመን ከክፍያ በተጨማሪ ትራንስፖርት ምግብና መሰል ድጎማዎች እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#DStvEthiopia

🌼 አዲስ ዓመት ደስ ይላል… እንደ አዲስ እናቅዳለን ፣ እናልማለን 🌼

የስራ ውጣ ውረዱን ፣ የኑሮ አባጣ ጎርባጣውን ፣ ደስታና ሐዘኑን ስናስተውል… በየቀኑ የምንተውነው ድራማ አጃኢብ ያስብላል… እንዲያውም የእያንዳንዳችን ሕይወት ቢፃፍ ምርጥ ፊልም ይወጣዋል!

ሕይወት ፊልም ናት!
ድራማውን በአቦል እዩት! በወር በ350 ብር ብቻ!

መልካም አዲስ ዓመት!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
#KABBA_TRANSPORT🚌

Safety is our priority !

ካባ በት/ቤቶች ውስጥ የተማሪ ሰርቪስ አገልግሎትን ለሚሰጡ አካላት በስልጠና እና በቴክኖሎጂ በመደገፍ ደህንነቱ የጠበቀ እና ቁጥጥር ያለው የተማሪዎች ትራንስፖርት ሰርቪስ አቅርቦት ለመፍጠር ከት/ቤቶች፣ወላጅ ኮሚቴ እና ወላጆች ጋር መስራት ይፈልጋል፡፡
አብረውን ሁለት አመታት የሰሩ ት/ቤቶች ምስክር ናቸው፡፡
የትምህርት ዘመን ከመከፈቱ በፊት ቀጠሮ ያስይዙ 0960009900 አዲስ ተመዝጋቢ ወላጆች መተግበሪያውን በማውረድ ይመዝገቡ👇 https://linktr.ee/Kabbatransport
ስልክ ፡ +2519 60 00 99 00
ካባ ትራንስፖርት
TIKVAH-ETHIOPIA
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳንት እና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት የፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ የቀብር ስንስርዓት እሁድ ጷጉሜን 3/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስትያን ይፈፀማል። በዕለቱ ከጠዋቱ 4:00-6:00 ሰዓት ባስተማሩበትና በሰሩበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ራስ መኰንን አዳራሽ የስንበት…
የፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ የቀብር ሥነ-ሥርዓት  ዛሬ ተፈጽሟል።

የፕሮፌሰር እንድሪያስ የቀብር ሥነሥርዓት የተፈፀመው በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ነው።

በቀብር ሥነሥርዓቱ ላይም ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ፣ የሀይማኖት አባቶች የፕሮፌሰር እንድርያስ ወዳጅ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

ከቀብር ሥነሥርዓቱ አስቀድሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ፊት ለፊት በተጣለ ድንኳን የሽኝት ሥነሥርዓት ተካሄዷል።

በዚያ የስንብት ዝግጅት ላይ ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የክልል ፕሬዚዳንቶች ፣የፕሮፌሰር እንድሪያስ ወዳጆችና ቤተሰቦች ተገኝተው እንደነበር ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።

ፕሮፌሰሩ በመምህርነታቸው ፣ በፍልስፍናቸው ይታወቁ ነበር።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ሆነው  ለ9 ዓመታት አገግለዋል። የየቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አማካሪም ሆነው ሰርተዋል።

በተወለዱ 79 ዓመታቸው ነሀሴ 23/2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ፕሮፌሰር አንድሪያስ እሸቴ  የአሉላ አንድሪያስ ወላጅ አባት ናቸው።

Photo Credit : Sheger FM, Abel G/Egziabeher, Addis Admas Newspaper

@tikvahethiopia
#ትንሳኤ70እንደርታ

" የመቐለ ከተማ አስተዳደር የፈቀድልን ህዝባዊ ስብሰባ ተከለከልን " ሲል ትንሳኤ 70 እንደርታ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን አሰማ።

የፓርቲው ሊቀመንበር ከበደ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በሰጡት ቃል ፥ _ እሁድ ጳጉሜን 3/2016 ዓ.ም በመቐለ ከተማ አስተዳደር ግቢ በሚገኘው አግኣዚ የስብሰባ አዳራሽ ህዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ ተፈቕዶልን አባልና ደጋፊዎቻችን ጠርተን ስናበቃ አዳራሽ እንዳንገባ በታጣቂዎች ተከልክለናል " ብለዋል።

" በህጋዊ መንገድ የተፈቀደ ህዝባዊ ውይይት መከልከልና ታዳሚዎች ማንገላታት ኢ-ዴሞክራሲያዊ ነው " ያሉት የፓርቲው ሊቀመንበር በተግባሩ ማዘናቸው በመግለፅ ከሚመለከተው አካል ግልፅ ማብራርያ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸው ተናግረዋል።

" የመቐለ ከተማ ፀጥታ ፅ/ቤት በፃፈልን ደብዳቤ መሰረት ስብሰባውን የፀጥታ ጥበቃ ለማድረግ ፓሊስ መድቦ በቦታው የተገኙ ሲሆን ማንነታቸውና ተጠሪነታቸው የማይታወቁ ሌሎች ሃይሎች ተሳብሳቢው ወደ ግቢ እንዳናሰግባ የአዳራሹ ሰራተኞች ሳይቀር እንዳይገቡ በር ላይ ለነበሩ የጥበቃ ሰራተኞች ትእዛዝ በመሰጠቱ ምክንያት ስብሰባው ሳይደረግ ቀርተዋል " ሲሉ አስረድተዋል።

" እንደምክንያት ያቀረቡትም የከንቲባ ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ለጋስ ማርያም ' እኔ ካልደወልኩኝ እንዳይገቡ ብለዋል ' የሚል ሲሆን ግለሰብዋ በደብዳቤ የፈቀዱትን ስብሰባ በዚህ መንገድ የከለከሉበት ምክንያት ለመጠየቅ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ብንደውልም ስላካቸውን በመዝጋታቸው ምክንያት ልናገኛቸው አልቻልንም " በማለት ገልጸዋል።

የመቐለ ከተማ ፀጥታ ዘርፍና ፓሊስ መንግስታዊ ሃላፊነቱን በአግባቡ ለመወጣት መሞከሩን አመልክተው " ምስጋና ይገባዋል " ብለዋል።

የመቐለ ከተማ አስተዳደርና ፓሊስ እስከ አሁን ሰዓት ስለ ክልከላው የሰጠው ይፋዊ ማብራርያም ሆነ መግለጫ የለም። 

ትንሳኤ 70 እንደርታ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ከአንድ ዓመት በፊት ሰላማዊ ፓለቲካዊ ትግል ለማካሄድ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ እውቅና አግኝቶ መመስረቱ ይታወቃል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Urgent🚨 በአማራ ክልል፣ በሰሜን ጎንደር ዞን ፣ ጠለምት ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የበርካታ ወገኖቻችን ህይወት አልፏል። በርካቶችም ችግር ላይ ወድቀዋል፤ ተፈናቅለዋል። ለተፈናቃዮቹ አስቸኳይ ድጋፍ ያስፈልጋል። ደጋግ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ወረዳው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርቧል። የወረዳው አስተዳደሪ አቶ ጋሻው እንግዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ቃል ፦ “…
#ጠለምት🚨

“ ናዳው ቀጥሏል፡፡  አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 25 ነው ” - ወረዳው

የመሬት መንሸራተት አደጋው መቀጠሉ የተነገረለት ሰሜን ጎንደር ዞን በተለይ ጠለምት ወረዳ የሟቾች ቁጥር መጨመሩን ወረዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች የተከተው ይሄው አደጋ የብዙዎችን ሕይወት መቀጠፉ የሚታወስ ሲሆን፣ በተለይ በጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ከመሬት መንሸራተቱ በተጨማሪ በሌሎች ቀበሌዎችም “ የህድሞ ” ቤት ናዳ አደጋ መከሰቱን ወረዳው ከሳምንት በፊት ገልጾልን ነበር፡፡

ይህ በእንዲህ እያለ፣ እስከ ነሐሴ 29 ቀን 2016 ዓ/ም ደግሞ የሟቾች ቁጥር በ15 መጨመሩን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ጋሻው እንግዳው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

“ ናዳው ቀጥሏል፡፡ በጠለምት ወረዳ የሟቾች ቁጠር 25 ደርሷል ” ነው ያሉት፡፡

አስተዳዳሪው በዝርዝር ምን አሉ ?

“ በወረዳው በሚገኙ ቀበሌዎች በናዳና የጎርፍ አደጋ ምክንያት በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው፡፡

ከነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ/ም እስከ ነሐሴ 29 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ብቻ አራት ወንዶች፣ 11 ሴቶች በአጠቃላይ 15 ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል፡፡

ሁለት ወንዶችና ሁለት ሴቶች በድምሩ አራት ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

አደጋው ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ነሐሴ 29 ቀን ድረስ በአጠቃላይ በወረዳው የሞቱ ሰዎች ብዛት 25 ደርሷል፡፡

የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ብዛት ደግሞ 10 ደርሷል፡፡ 456 ሰዎች የእርሻ መሬት ተጎድቶባቸዋል፡፡ 476.5 ሄክታር ሰብል ተጎድቷል፡፡

2911 እንስሳት ሞተዋል፡፡ 28 መኖሪያ ቤቶችና 236 የንብ ቀፎዎች ወድመዋል”
ብለዋል፡፡

የተለያዩ ተቋማት የተለያዩ ድጋፎችን እንዳደረጉ የገለጸው ወረዳው፣ አደጋውና መፈናቀሉ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመሆኑ የተጀመረው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል፡፡

አደጋው የተከሰተው በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ሲሆን፣ በተለይም ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ የተከሰተው የመሬት መንሸራተት መቆም እንዳልቻለ መገለጹ ይታወሳል፡፡

በዞኑ በሚገኙ ሌሎች ወረዳዎች አደጋው በምን ደረጃ እንደሚገኝ በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡

ፎቶ ፦ ፋይል

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰኞ ይፋ ይደረጋል። ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ/ም እንደሚገለጽ አሳውቋል። የዘንድሮው ብሔራዊ ፈተና በቅይጥ ማለትም በወረቀት እና በኦንላይን መሰጠቱ ይታወሳል። @tikvahethiopia
ዘንድሮስ ምን አይነት ውጤት ይመዘገባል ?

የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይገለጻል።

ትምህርት ሚኒስቴር በፈተናው ውጤት ዙሪያ ነገ ከሰዓት ማብራሪያ ይሰጣል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያውን ተከታትሎ ያቀርባል።

ከዚህ ቀደም የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መረጃ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡ 701,749 ተማሪዎች መካከል 684,205 ተማሪዎች ወይም 97.5 በመቶዎቹ ፈተናውን ወስደዋል።

ቀሪዎቹ በተለያዩ ምክንያቶችና ትምህርታቸውን ዘግይተው በመጀመራቸው ፈተናውን አልወሰዱም።

ከተፈታኞቹ ውስጥ 29,718 የሚሆኑ ተማሪዎች ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰጠው የኦንላይን ፈተና አማካኝነት ፈተናቸውን የወሰዱ ናቸው።

የብሔራዊ ፈተናው ውስጤት ነገ ሰኞ ጳጉሜን 4/2016 ዓ/ም ይገለጻል ተብሎ ይጠበቃል።

ባለፉት ዓመታት በተለይም ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (ዩኒቨርሲቲ) አስገብቶ ፈተና መስጠት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እጅግ ዝቅ ያለ ውጤት / በብዛት ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት የማያስመዘግቡበት መሆኑ ይታወቃል።

ለአብነት በ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑ 845,099 ተማሪዎች 50 በመቶና በላይ አምጥተው ማለፍ የቻሉት 27,267 / 3.2 በመቶ ብቻ ናቸው።

ከዛ በፊት በ2014ቱ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 896,520 ተማሪዎች ተፈትነው 50 በመቶና በላይ አምጥተው ያለፉት 30,034 / 3.3 በመቶ ብቻ ናቸው።

ትምህርት ሚኒስቴር በቀጥታ የሚያልፉ ተማሪዎች ዝቅተኛ መሆኑን ተከትሎ የሬሜዲያል ፕሮግራም በመስጠት ያን ያለፉ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ የማድረግ ስራ ሲሰራ ነበር።

ይህ ስራ " ለአንድ ጊዜ ብቻ " ተብሎ የነበረ ሲሆን በ2015 ቀጥታ ያለፉ ተፈታኞች ውስን በመሆናቸው የትምህርት ሚኒስትሩ ቃላቸውን ስላጠፉ በይፋ ይቅርታ ጠይቀው የሬሜዲያል ፕሮግራሙ እንዲቀጥል አድርገው ነበር።

° ዘንድሮውስ ምን አይነት ውጤት ይመዘገባል ?
° ምን ያህል ተማሪ የማለፊያ ነጥብ ያስመዘግባል ?


ሁሉንም አብረን የምናየው ይሆናል።

ነገ ከሰዓት የፈተናው ውጤት በትምህርት ሚኒስቴር ይገለጻል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጥታ ተከታትሎ ያደርሳችኋል።

#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪውን የ2017 አዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኝ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡

እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉ፡፡

ጥያቄው የሚካሄዳው ማክሰኞ ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ከቀኑ 8:00 ሰዓት ሲሆን ፤ ጥያቄውን ቀድመው ለመለሱ 5 ተሳታፊዎች በቅደም ተከተል ሊሸልም ዝግጅቱን ጨርሷል።

ከአንድ እስከ አምስት ለወጡ ተወዳዳሪዎች የተለያዩ ሽልማቶችን አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።

እርስዎም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!! ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
[Telegram] ( https://www.tg-me.com/LionBankSC )
[Facebook] ( https://www.facebook.com/LionBankSC )

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ
የስኬትዎ አጋር!
2024/09/30 22:13:35
Back to Top
HTML Embed Code: