Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ የአሜሪካንን ገመና ለዓለም ሁሉ ያጋለጠው ' ዊክሊክስ ' የተሰኘው ድረገጽ መሥራች ጁሊያን አሳንጅ ለዓመታት ከዘለቀው የፍርድ ቤት ሙግት በኋላ ከአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር በደረሰው ስምምነት ከእስር ተለቋል።

አሳንጅ ለአምስት ዓመታት ያህል በዩናይትድ ኪንግደም እስር ላይ የነበረ ሲሆን አሜሪካ ተላልፎ እንዲሰጣት ስትሞግት ነበር።

ከፍተኛ ምስጢራዊ ወታደራዊ መረጃዎችን ለዓለም ይፋ በማድረግ ክስ የቀረበበት አሳንጅ ጥፋተኝነቱን ማመኑን ተከትሎ ከዩኬ ከእስር ቤት በነጻ ተሰናብቷል።

ዩኬን ለቆም ወደ አውስትራሊያ ሄዷል።

ዊክሊክስ ከጦርነት ፣ ከስለላና ከሙስና ጋር የተያያዙ ምሥጢራዊ እንዲሁም መንግሥታዊ ሪፖርቶችን ጨምሮ ከአስር ሚሊዮን በላይ ሰነዶችን ለዓለም ይፋ አድርጓል።

#StellaAssange
#BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኬንያ ናይሮቢ፣ ሞምባሳን ጨምሮ በተለያዩ የኬንያ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች መደረግ ጀምረዋል። በወጣቶች መሪነት እየተካሄዱ ባሉት በነዚህ ሰልፎች ላይ መንግሥት ተጨማሪ ታክስ ለመጣል ያረቀቀውን የፋይናንስ ረቂቅ አዋጅ ሙሉ በሙሉ እንዲተወው እየተጠየቀበት ነው። መንግሥት በረቂቁ ላይ አንዳንድ ማሻሻያ አደረጋለሁ ቢልም ተቃዋሚዎች ግን " የምን አንዳንድ ነው ? ሙሉ ረቂቁን ተወው " የሚል አቋም እንደያዙ…
#Update

በኬንያ ተቃውሞ ሰዎች ተገደሉ።

የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥት ያረቀቀውን አዲስ የታክስ ሕግ የተቃወሙ ኬንያውያን የአገሪቱን ፓርላማ ቅጥር ጊቢ ጥሰው ገብተዋል።

ፖሊስ በከፍተኛ ቁጥር የወጡ ተቃዋሚ ወጣቶችን ለመበተን ጥይት እና አስቀሽ ጭስ ተኩሷል።

እስካሁን ድረስ ቢያንስ 5 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን ሁለቱ ሕይወታቸው አልፏል።

ከጥቂት ሰዓታት በፊት የአገሪቱ ም/ ቤት አባላት ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ገጥሞት የነበረውንና በተለያዩ ምርት እና አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ ታክስ የሚጥለውን ረቂቅ ሕግ አጽደቀዋል።

" አዲሱ የቀረጥ ሕግ ኑሯችንን ያስወድድብናል " ሲሉ የቆዩት ኬንያውያን ወጣቶች ከአገሪቱ ፓርላማ ፊት ለፊት የተቃውሞ ድምጻቸውን ለማሰማት በከፍተኛ ቁጥር ወጥተዋል።

ከፖሊስ ቁጥጥር አቅም በላይ የሆኑ አብዛኛዎቹ ወጣቶች የሆኑ ተቃዋሚዎች የፓርላማውን በር ጥሰው ገብተዋል።

በመቶዎች የሚቆጠሩ የፓርላማ አባላት ከምክር ቤቱ ምድር ቤት ለመደበቅ ሲሯሯጡም ተይተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ፥ ተቃዋሚዎች አንደኛውን የፓርላማውን ክፍል በእሳት ማያያዛቸውን ቢቢሲ እና የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በኬንያ ተቃውሞ ሰዎች ተገደሉ። የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥት ያረቀቀውን አዲስ የታክስ ሕግ የተቃወሙ ኬንያውያን የአገሪቱን ፓርላማ ቅጥር ጊቢ ጥሰው ገብተዋል። ፖሊስ በከፍተኛ ቁጥር የወጡ ተቃዋሚ ወጣቶችን ለመበተን ጥይት እና አስቀሽ ጭስ ተኩሷል። እስካሁን ድረስ ቢያንስ 5 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን ሁለቱ ሕይወታቸው አልፏል። ከጥቂት ሰዓታት በፊት የአገሪቱ ም/ ቤት አባላት…
ፎቶ ፦ በኬንያ ናይሮቢ የተቆጡ ተቃዋሚዎች የሀገሪቱን ፓርላማ ጥሰው በመግባታቸው በርካታ የምክር ቤቱ አባላት ምድር ቤት (ግራውንድ) ለመደበቅ ሲሯሯጡ ታይተዋል።

የተ/ምክር ቤት አባላቱ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞት የነበረውንና በተለያዩ ምርት እና አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ ታክስ የሚጥለውን ረቂቅ ሕግ አጽድቀው ነበር።

ተቃውሞ የቀሰቀሰው የፋይናንስ ሕግ በ195 የምክር ቤት አባላት ድጋፍ ፣ በ106 የም/ ቤት አባላት ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ ነው የጸደቀው።

በቀጣይ ወደ ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ይመራል።

#Kenya
#KenyaParliament

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ በኬንያ ናይሮቢ የተቆጡ ተቃዋሚዎች የሀገሪቱን ፓርላማ ጥሰው በመግባታቸው በርካታ የምክር ቤቱ አባላት ምድር ቤት (ግራውንድ) ለመደበቅ ሲሯሯጡ ታይተዋል። የተ/ምክር ቤት አባላቱ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞት የነበረውንና በተለያዩ ምርት እና አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ ታክስ የሚጥለውን ረቂቅ ሕግ አጽድቀው ነበር። ተቃውሞ የቀሰቀሰው የፋይናንስ ሕግ በ195 የምክር ቤት አባላት ድጋፍ…
ቪድዮ ፦ በኬንያ የተቆጡ ተቃዋሚ ወጣቶች ወደ ፓርላማው ህንጻ በኃይል ገብተው ሴኔት ቻምብርን ወረዋል።

ውስጥ ገብተውም ልብስ አውጥተው ለብሰው ሄደዋል።

የሀገሪቱ መንግሥት ትላንትና በሰጠው መግለጫ ሰላማዊ እስከሆነ ድረስ ሰልፍ እንደሚፈቀድ ነገር ግን ተቃዋሚዎች ወደ ቤተ መንግሥት ፣ ወደ ፓርላማ አካባቢ መሄድ እንዳይዳፈሩ አስጠንቅቆ ነበር።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ፎቶ ፦ የሀገሪቱን ፓርላማ በኃይል ጥሰው የገቡት መንግሥት ያረቀቀውን የፋይናንስ ሕግ የሚቃወሙ የኬንያ ወጣቶች በፓርላማው ካፍቴሪያ ምግብ ሲበሉ ታይተዋል።

ወጣቶቹ ዛሬ ጨምሮ ላለፉት ተከታታይ ቀናት " ታክስ ለመጨምር ያሰበው ረቂቅ ሕግ ኖሮ ያከብድብናል ፤ ተውት ይቅር ! አንደግፈውም " በማለት እየተቃወሙ ይገኛሉ።

በዛሬው ተቃውሞ የጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት የሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን ወጣቶቹ ግን የሀገሪቱን ፓርላማው ጥሰው ገብተዋል።

የተወሰነውን ክፍልም በእሳት አያይዘዋል።

#Kenya
#KenyaParliament

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 22 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://www.tg-me.com/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#ማያ ምርጥ ሀገርኛ የቪዲዮ ስትሪሚንግ!!!

📺#ማያ ያሻዎትን የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ፕሮግራሞች እንዲሁም የልጆች ፕሮግራሞችን ጨምሮ በርካታ የመዝናኛ እና የመረጃ አማራጮችን ይዞ ቀርቧል፡፡

📻 አገልግሎቱን በማያ መተግበሪያ https://onelink.to/7bv4u9 ወይም ወደ 863 Ok ብለው በመላክ ይመዝገቡ! በቀን 5 ብር ብቻ!

📦ዘወትር ማያን ብቻ የሚያስጠቅም #ነጻ 2 ጊ.ባ ዕለታዊ የዳታ ጥቅል ይበረከትልዎታል!

ለማንኛውም ጥያቄ፣ አስተያየት ወይም ቅሬታዎ በ https://www.tg-me.com/EthiotelecomChatBot ያግኙን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #SmartAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#Somaliland

" የአስገድዶ መድፈር ጉዳዮችን በባህላዊ መንገድ የመፍታት ዘዴ በአስገድዶ መድፈር ሰለባዎች ላይ ኢ-ፍትሃዊነትን ያሰፍናል " - ፕሬዜዳንቱ

የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሳ ቢሂ አብዲ፥ ማንኛውም የአስገድዶ መድፈር ጉዳይ በፍርድ ቤት እንዲታይ እና የፍትሕ ተቋማት እንዲከታተሉ ማዘዛቸው ተሰምቷል።

ፕሬዜዳንቱ ከካቢኔያቸው አባላት ጋር ምክክር ካደረጉ በኋላ የአስገድዶ መድፈር ጉዳዮችን የፍትህ አካላት እንዲከታተሉት / በፍርድ ቤት ብቻ እንዲዳኝ አዘዋል።

" አስገድዶ ደፋሪዎች ወደ ህግ ፊት መቅረብና በፍርድ ቤት መዳኘታቸው አስፈላጊ ነው " ብለዋል።

የፖሊስ ኮሚሽነር እና የጠቅላይ አቃቤ ህግ የአስገድዶ መድፈር ክስ ወደ ፍርድ ቤት መቅረቡን እንዲያረጋግጡ አሳስበዋል።

የአስገድዶ መድፈር ጉዳዮችን በባህላዊ በሆነ መንገድ የመፍታት ዘዴ በአስገድዶ መድፈር ሰለባዎች ላይ " ኢ-ፍትሃዊነትን የሚያሰፍን ነው " ብለዋል።

የፕሬዚዳንቱ ትዕዛዝ የጎሳ መሪዎች የአስገድዶ መድፈር ጉዳዮች ላይ ጣልቃ መግባትን የሚከለክል እንደሆነ ተጠቁሟል።

ይህን ትዕዛዝ ለማስተላለፍ የተገደዱት በሶማሌላንድ ውስጥ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች መበራከታቸውን ተከትሎ ነው።

@tikvahethiopia
#Amhara

" እስኪበቃን ተገዳድለናል ፤ እስኪበቃን ተዋጋን አሁን ይብቃን !! መፍትሔው ንግግር ነው፣ መነጋገር ነው፣ መከባበር ነው " - አቶ አገኘሁ ተሻገር

በአማራ ክልል ያለው የትጥቅ ግጭት በውይይት እና በድርድር እንዲቋጭ መንግስት በድጋሚ ጥሪ አቀረበ።

ጥሪውን ያቀረበው በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው የሰላም ኮንፈረንስ ነው።

የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር ምን አሉ ?

" ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ መሄድ ቅንጦት ሆኗል፣ ከአዲስ አበባ ባሕር ዳር መምጣት ቅንጦት ሆኗል ያላቸው በአውሮፕላን ነው የሚሄዱ፣ የእኔና የእናንተ ቤተሰቦች በአውሮፕላን መሄድ አይችሉም።

ተማሪዎች ትምህርታቸውን መማር አልቻሉም ፣ በርካታ ተማሪዎች ለክልላዊ እና ለአገራዊ ፈተናዎች መቀመጥ አልቻሉም ፣ እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች ተገቢ የሆነ ውጤት ለማምጣት እየተቸገሩ ነው፣ በርካታ ተማሪዎችም ትምህርታቸውን እያቋረጡ ነው።

መንግስት የልማት ስራዎችን መስራት አልቻልም።

በኢኮኖሚውም ዘርፍ የአማራ ክልል 35 ከመቶ እና ከዚያ በላይ የሚሆነውን የአገሪቱን የሰብል ምርት የሚሸፍን ሆኖ ሳለ ፣ ዛሬ ማምረት እንኳ አልቻለም ፣ ማዳበሪያ ማሰራጨት አልቻለም ፣ ምርጥ ዘር ማሰራጨት አልቻልም ፣ የአበዳሪ ተቋማት ብድር መሰብሰብ አልቻሉም ፣ ባንኮች አገልግሎት መስጠት አልቻሉም ፣ ነጋዴው ሰርቶ ፣ ነግዶ ራሱን ማሻሻል አልቻለም፡፡

ህዝባችን የከፋ ችግር ውስጥ ነው ያለው አይናገርም ቢናገር ችግር ይደርስበታል።

መገዳደሉና ፣ በጠላትነት መፈላለጉ ከበቂ በላይ ነው። ይሄን መገዳደል ካላስቆምን በስተቀር ክልላችን ወደፊት መራመድ / ፈቀቅ እንኳን ማለት አይችልም።

በቃ !! እስኪበቃን ተገዳድለናል፣ እስኪበቃን ተዋጋን ስለዚህ አሁን ይብቃን፣ መፍትሔው ንግግር ነው፣ መነጋገር ነው፣ መከባበር ነው።

ሌለው አካል ብቻ  ችግር ያለበት አድርጌ እኔ እራሴን ከችግር እያወጣው አይደለም፣ እኔ ችግር የለብኝም እያልሁም አይደለም፣ እኔም ሁላችንም የችግሩ አካል ነን፣ ስለዚህ ይብቃን፣ ህዝባችን ከችግር እናውጣው።

አሁንም መንግስታችን እና ፓርቲያችን የሰላም ጥሪ ያቀርባል፣ ለመነጋገር ፣ ለመወያየት ለመደራደር ፣ ለመመካከር የክልሉም ሆነ የፌደራሉ መንግስት ዝግጁ ነው። "

#Ethiopia
#AmharaRegion

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የሀገሪቱን ፓርላማ በኃይል ጥሰው የገቡት መንግሥት ያረቀቀውን የፋይናንስ ሕግ የሚቃወሙ የኬንያ ወጣቶች በፓርላማው ካፍቴሪያ ምግብ ሲበሉ ታይተዋል። ወጣቶቹ ዛሬ ጨምሮ ላለፉት ተከታታይ ቀናት " ታክስ ለመጨምር ያሰበው ረቂቅ ሕግ ኖሮ ያከብድብናል ፤ ተውት ይቅር ! አንደግፈውም " በማለት እየተቃወሙ ይገኛሉ። በዛሬው ተቃውሞ የጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት የሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን ወጣቶቹ ግን…
#Kenya

የኬንያ መከላከያ ሰራዊት ሰላምና የህግ ስርዓትን እንዲያስከብር ትዕዛዝ ተሰጠው።

የሀገሪቱ መንግሥት ለቀናት ከዘለቀው የፋይናንስ ህግ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ የኬንያ መከላከያ ሰራዊት የህዝቡን ደህንነት፣ ሰላምና የህግ ስርዓት እንዲያስከብር አሰማርቷል።

በሌላ በኩል ፤ የኬንያው ፕሬዜዳንት መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በመግለጫቸው የዛሬውን ታቃውሞ ፤" እንደ ሀገር ክህደት / ከሃዲነት " የሚቆጠር እንደሆነ ገልጸው ፤ የጸጥታ ኃይሎች የኬንያውያንን ደህንነት እንዲያስጠብቁ መመሪያ እንደሰጡ ተናግረዋል።

ተቃዋሚዎች የኬንያ ፓርላማን ሰብረው ስለገቡበት ክስተት ጉዳይም ምርመራ እንደሚደረግ አመልክተዋል።

የወንጀል ድርጊትና ወንጀለኞችን ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው የተቃውሞ ሰልፍ ከሚያደርጉት መለየት ይገባል ብለዋል።

ፕ/ት ሩቶ " አደገኛ ወንጀለኞች " ሲሉ የጠሯቸው አካላት ሊፈጸሙት የሚችልን ማንኛውም ሙከራ ከንቱ ሆኖ እንዲቀር የደህንነት አካላት እርምጃ እንዲወስዱ እንዳዘዙ ገልጸዋል።

ህዝቡንም " ዛሬ ማታ ተኙ ! የናተ፣ የቤተሰቦቻችሁ እና የንብረቶቻችሁ ደህንነት ከምንም በላይ ቅድሚያ ሰጥተን እንጠብቃለን " ብለዋል።

" የተቃውሞው የፋይናስ ምንጮች ላይም ምርመራ ይደረጋል " ሲሉ አክለዋል።

በኬንያ ዛሬ ማክሰኞ በነበረው ተቃውሞ እስካሁን በታወቀው ብቻ 10 ሰዎች ከጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተገድለዋል።

#Kenya
#FinanceBill2024

@tikvahethiopia
#eQUB_APP

በ20ሺህ ብር ብቻ ዕቁብ ገብታችሁ የቤት ዕቃዎችን የምታሟሉበት መተግበሪያ - eQUB APP! የሄ እድል እንዳያመልጥዎ!

Download the App Here👇
📱 Android - Google Play  | 📱 iPhone - App Store

Telegram Channel: @equbapp

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 0116671717 ወይም 0116670404 ይደውሉ።
#ዳሽን_ከፍታ: በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "ዳሽን ከፍታ" የሥራ ፈጠራ ውድድር ሶስተኛ ምዕራፍ ሊጀመር ነው፡፡

በዳሸን ከፍታ የመጀመሪያውና ሁለተኛው ዙር የስራ ፈጠራ ውድድሮች ተሳትፈው አሸናፊ የሆኑ ተወዳዳሪዎች ሸልማትና የፋይናስ ድጋፍ አግኝተው በተለያዩ የስራ ዘርፎች ስኬታማ እየሆኑ ነው፡፡ ለሌሎችም የስራ ዕድል መፍጠር ችለዋል፡፡

በዚህ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ ነዎት?

ዳሽን ከፍታ የሥራ ፈጠራ ውድድር በምዕራፍ ሶስት የቅድመ ውድድር ጅማሬ ስልጠና ለመስጠት በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች ይንቀሳቀሳል!

የስልጠና ቦታዎች ፡ አዲስ አበባ ፣ ባህርዳር ፣ አዳማ ፣ መቀሌ ፣ ድሬዳዋ ፣ ሀዋሳ ፣ ወላይታ ፣ ጅማ እና ደሴ

ምዝገባ እስከ #ሰኔ_22/2016 ዓ.ም. ድረስ በሁሉም የዳሸን ባንክ ቅርንጫፎች የሚካሄድ ይሆናል፡፡

ለበለጠ መረጃ ወደ 6333 ይደውሉ ወይም የባንኩን የማህበራዊ ትስስር ገጾች ይጎብኙ፡፡

ዳሸን ባንክ ሁልጊዜም አንድ እርምጃ ቀዳሚ!
" በየሶሻል ሚዲያ የሚፈጸም ስም ማጥፋት በህግ እንጅ በሶሻል ሚዲያ መልስ መስጠት አያስፈልግም " - የሰላምና ጸጥታ ቢሮ

የሀዋሳ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ፥ ያለ ማስረጃ በየተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የከተማዋን ስም እያጠፉ ያሉ አካላትን ጉዳይ በህግ እየተከታተልኩ ነው አለ።

ይህን ያለው ከሰሞኑን ' ቲክቶክ ' እና ' ዩትዩብ ' ላይ የከተማዋን ሁኔታ የሚገልጽ የወጣቶች ንግግር ከተሰራጨ በኃላ ነው።

ወጣቶቹ ከተማይቱ ለደህንነት የምታሰጋ ፣ እግታም የሚፈጸምባት እንደሆነ በመግለጽ ዜጎች ወደ ሀዋሳ እንዳይሄዱ ጥሪ ሲያቀርቡ ይደመጣል።

ይህንን ተከትሎ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሉን የሰጠው የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ፤ " ጉዳዩን በህግ አግባብ  እየተከታተልነዉ ነዉ " ብሏል።

" በየሶሻል ሚዲያ የሚፈጸም ስም ማጥፋት በህግ እንጅ በሶሻል ሚዲያ መልስ መስጠት አያስፈልግም " ሲል አመልክቷል።

" በእኛ በኩል እንዲህ ያለን የስም ማጥፋት አይተን ባናልፈውም ነዋሪው እና ሀዋሳን የጎበኙ እንግዶች ራሳቸዉ ምን አይነት አስተማማኝ ደህንነት እንዳለ ምላሽ ቢሰጡበት የተሻለ ነዉ " ሲል አክሏል።

ቢሮው ፥ " አሁን ላይ በኢትዮጵያ ካሉ ከተሞች ሀያ አራት ሰአት ሰዉ በነጻነት መንቀሳቀስ የሚችልባት ከተማ ሀዋሳ መሆኗን ላረጋግጥላችሁ እዉዳለሁ " ብሏል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየታችንን መስጠት እንፈልጋለን ያሉ ወጣቶች ደግሞ ተጎዳው የሚል ማንኛውም ዜጋ በማስረጃ ለፍትህ አካል ማመልከት ይቻላል ብለዋል።

" እኛ እስከምናውቀው ድረስ ከተማይቱ የምታስፈራ ከተማ አይደለችንም ፤ ሀገሪቱ ውስጥ ካሉ ከተሞች ደህንነት ያለባት ናት ፤ በዚህ ደረጃ ስም ማጥፋት እና መግለጽ ፍጹም ያልተገባ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update “ ከታገቱ ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም ሰባት ወራት ይሆናቸዋል። እንደቀላል ነገር በወጡበት ቀሩ ” - የታጋች ባለቤት ከ6 ወራት በፊት ወደ ባቱ (ዝዋይ) ለስራ ጉዳይ እየተጓዙ በታጣቂዎች ታገቱ ከተባሉ 6 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች መካከል 3ቱ ቢለቀቁም 3ቱ ግን እንዳልተለቀቁ ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የሚችለውን ሁሉ…
#Update

“ በታጣቂዎች ከታገቱ 9 ወራት አለፉ፤ ያሉበትን እንኳ አናውቅም። ወደ ማን እንጩህ ? ”- የታጋች ባለቤት

መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም በታጣቂዎች ታግተው የተወሰዱ 3 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ደብዛቸው እንደጠፋ መሆኑን የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

ወደባቱ ለስራ እየተጓዙ በነበረበት ወቅት በታጣቂዎቸ ታገቱ የተባሉት ሠራተኞቹ ያልተለቀቁት አጋቾቹ ገንዘብ ጠይቀው ከ2.8 ሚሊዮን ብር ከተላከ በኋላ እንደሆነ የታጋች ቤተሰቦች ከዚህ ቀደምም ገልጸው ነበር።

አሁንስ ምን አዲስ ነገር አለ ? 

- አቶ ልዑል አስፋወሰን
- አቶ ሰይፉ እንዳለ
- አቶ አብዩ ደገፋው የተባሉ ሠራተኞች በህይወት ይኑሩ አይኑሩ አይታወቅም።

ትላንት ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ 2 የታጋች ቤተሰቦች ስለ 3ቱም ታጋቾች ምንም የሰሙት ፍንጭ እንኳ እንደሌለ ገልጸዋል።

አንዷ የታጋች ባለቤት “ በታጣቂዎች ከታገቱ 9 ወራት አለፉ ፤ ያሉበትን እንኳ አናውቅም። ወደ ማን እንጩህ ? ” ሲሉ ሀዘን ያጀበው ጥያቄ አንስተዋል።

የሰው ልጅ ለ9 ወራት ያህል ያለበት እንኳን አለማወቅ ከባድ ሀዘን መሆኑን ፤ ኤሌክትሪክ ኃይልን በቅርቡ ቢጠይቁም ካቅሙ በላይ እንደሆነበት መግለጹን ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረበለት የኤሌክትሪክ ኃይል ጉዳዩ ከአቅሙ በላይ እንደሆነበት መግለጹ ይታወቃል።

#TikvahEthiopaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Reminder 🔔

የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት ምዝገባ ሊጠናቀቅ 11 ቀናት ቀርቶታል።

አከራይ እና ተከራዮች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም አስፈላጊ ሰነዶችን በመያዝ ምዝገባውን እንዲያከናውኑ ጥሪ ቀርቧል።

ከሰኔ 30 በኃላ የሚደረግ ማንኛውም ምዝገባ ቅጣት እንደሚኖረው ተገልጿል።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
" ' ሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል ' የሚል ግለሰብ ማስረጃ በማቅረብ ስልኩን መውሰድ ይችላል " - ፖሊስ

በአዲስ አበባ በሞተር ሳይክል እየተንቀሳቀሱ ከግለሰቦች ሞባይል በመንጠቅ ሱቅ ውስጥ ሲያከመቹ የነበሩ 4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

አቶ ሱራፌል ቢያብል የተባሉ የግል ተበዳይ በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14  ዋና ስራ አስፈፀሚ ሲሆኑ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም  በክፍለ ከተማው ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል አካባቢ እየተሰራ ያለውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ እያደረጉ ነበር።

በወቅት 2 ተጠርጣሪዎች በጥቁር ሞተር ሳይክል ኮድ 2 A19216 ደ.ሕ (ደቡብ ህዝብ) በሆነ 1ኛ ተጠርጣሪ እያሽከረከረ ፣ 2ኛ ተጠርጣሪ ሞተር ሳይክል ላይ ከኋላ በመሆን ከግለሰቡ  ሞባይል ስልክ ነጥቀው በፍጥነት እያሽከረከሩ ከአካባቢው ይሰወራሉ።

የግል ተበዳይ ወንጀሉ እንደተፈፀመባቸው በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለገርጂ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ያመለክታሉ።

ፖሊስም የግል ተበዳዩን አቤቱታ በመቀበል  ባደረገው ክትትል ከሁለቱ ተጠርጣሪዎች በተጨማሪ ከሌቦቹ የሚረከቡ 2 ተጠርጣሪዎች  በድምሩ  4 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል።

ህግን ተከትሎ ባደረገው ብርበራ ተጠርጣሪዎቹ ተከራይተው የሞባይል ጥገና የሚሰሩበት ሱቅ ውስጥ በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ ግለሰቦች ተቀምተው የተከማቹ 32 ስማርት ሞባይል ስልኮችን በኤግዚቢት ተይዘዋል።

" ሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል " የሚል ማንኛውም ግለሰብ በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያያ በአካል  በመቅረብና ትክክለኛ ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መውሰድ እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
2024/10/01 11:40:17
Back to Top
HTML Embed Code: