Telegram Web Link
ለሰው የምትነግረውን ሚስጥር በደንብ አስብበት!

የዛሬ የቅርብ ጎደኛህ የነገ ዋናው ጠላትህ ሊሆን ይችላል፡፡
@psychoet
#ይቻላል
JOIN TELEGRAM www.tg-me.com/psychoet

በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት ዕለት ተዕለት በሚኖራችሁ ህይወት ውስጥ ሁሉም ነገር አስጠልቷችሁ ፤ ምንም ለማድረግ ወኔና ፍላጎቱ ጠፍቷችሁ መነሳሳት ከእናንት ርቆ ያውቃል? እንግዲያውስ ህይወትን በኃይልና በመነሳሳት መንፈስ እንደገና ለመጀመር እነኚህን ነጥቦች ይተግብሯቸው፡፡

1. የህይወትን ዓላማ ማወቅ፡- እያንዳንዳችን ወደዚህች ምድር የመጣነው ያለ ዓላማና ምንክንያት ስላልሆነ ለእኛ በህይወት መኖር ለራስና ለሌሎች የሚያበረክተው ጥቅም ስላለው በህይወት የመኖራችንን ዓላማ ጠንቅቀን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡

2. ጊዜን በአግባቡ መጠቀም፡- ለሰው ልጅ በነፃ ከተሰጠው የተፈጥሮ ሃብት ውስጥ ጊዜ ነው፡፡ ማድረግ የምንፈልገውንና መሆን የምንመኘውን በጊዜ ቀመር ማስቀመጥ ወደ ምንፈልገው የዕድገት ደረጃ ይመራናል፡፡ ጊዜ ሰይፍ ነው ይቆርጣል ያቆስላል ፤ ጊዜ መድኃኒት ነው ከውድቀት ያነሳል፡፡ “ጊዜን ስሩበት እንጂ አይስራባችሁ!”

3. ተስፋ፡- ዛሬ በእጃችን መዳፍ ውስጥ ናት የስኬትንና የውድቀትን ካርድ ልንመዛባት እንችላለን፡፡ ዛሬ ባይሳካ ነገ ደግሞ ሌላ ቀን ነው ፤ ህይወት ሎተሪ ናትና ደጋግመን መሞከር ያስፈልጋል፡፡ የተሻለ ነገን ለማሰብ ተስፋ ትልቅ ስንቅ ነው፡፡

4. ውድቀትን አለመፍራት፡- ብዙዮች ጠንክረው ላመስራታቸውና ህይወትን በተሻለ መልኩ ላለመኖራቸው ትልቁ ምንክንያት ውድቀትን መፍራት ነው፡፡ ነገር ግን ሰዎች ወድቀው በተነሱ ቁጥር ጠንካራ መንፈስን እንደሚላበሱ ጥርጥር የለውም፡፡ ገና ለገና ባይሳካልኝና ብወድቅ እሳ ብሎ ከመጨነቅ ተፋልሞ ወድቆ መነሳት ይሻላል፡፡

5. በዕቅድ መመራት፡- ህይወት ዝብርቅር እንድትል ከሚያደርጉ ነገሮች ውስጥ አንዱ በዕቅድ አለመመራት ነው፡፡ በዕቅድ መመራታችን በህይወታችን ውስጥ ያሳካናቸውንና ያላሳካናቸውን ነገሮች እንድናውቅ ስለሚረዳን ምን ማድረግ እንዳለብን አቅጣጫ ያሳየናል፡፡

6. አወንታዊ አስተሳሰብ፡- በአሉታዊ አስተሳሰብ ጫና ውስጥ ያሉ ሰዎች የመስራትና የመነሳሳት ስሜታቸው ቀዝቃዛ ነው፡፡ ከብርሃን ይልቅ ጨለማው ቀድሞ ስለሚታያቸው ስልቹዎች ናቸው፡፡ መልካም ማሰብ ወደ መልካም ይመራል ድርጊት ከተጨመረበት፡፡

7. ፍላጎትን መቀነስ፡- መስራትና መሆን የምንፈልጋቸው ነገሮች በበዙ ቁጥር አንድ ነገር ላይ አእምሮአችንንና ጊዜአችንን አሳርፈን መስራት ስለማንችል በምኞት ብዛት ራዕይአችን፤ ጊዜአችንና ጉልበታቸን በከንቱ ይባክናል፡፡

8. ትዕግስት፡- የአንድን ነገር ውጤትና ለውጥ በቅጽበታዊ ጊዜ ውስጥ መፈለግ መነሳሳትን ይገድባል፡፡ በትዕግስት የሚጠባበቁና የሚጥሩ ከሆነ ቢዘገይ እንጂ መድረስ ያለባችሁ ቦታ ከመድረስ የሚያግዳችሁ የለም፡፡

9. ዛሬውኑ መጀመር፡- ስራዎቻችንንና ዕቅዶቻችንን ለማሳካት ከነገ ከመጀመር ይልቅ ከአሁኗ ደቂቃ መጀመር ትልቅ ጥቅም አለው፡፡ የነገን ለነገ በመተው የዛሬን በትንሽ በትንሹ መጀመር ወደ ትልቁ ደረጃ ይመራናል፡፡

10. ስራችንን በደስታ መጀመር፡- ውስጣዊ ስሜቶቻችንን ለስኬቶቻችን ትልቅ አስተዋጽኦ ስለሚኖራቸው የምንሰራውን ስራ መውደድ ይጠበቅብናል፡፡ የማንወደው ስራ ቢሆን እንኳን የምንወደውን ስራ እስክናገኝ የአሁኑን ስራችንን መውደድ አለብን፡፡

(በአንቶኒዮ ሙላቱ)
©ZePsychology

መልካም ቀን!
#Share_it
ከእለታት በአንዱ ቀን ሁለት በእድሜ የገፉ አዛውንት ባለትዳሮች አንድ ቀን ድብር ይላቸውና....

ባልየው <<የወጣትነት ጊዚያችንን ብንመልሰው ምን ይመስልሻል>> ይላታል ሚስትም በጣም ተደስታ <<እሺ>> ትላለች።
ከዛም ባል<< በቃ እኔ ታች ሱቁ ጋር ልውረድና ድንጋዩ ላይ ቁጭ ብዬ አንቺ በዛ በኩል እለፊና ይዤ ላዋራሽ>> ተስማሙና ባል ወደታች ወርዶ ድንጋዩ ላይ ቁጭ ብሎ መጠበቅ ጀመረ.....
ቢጠብቅ ቢጠብቅ ቢጠብቅ አትመጣም...4 ሰዐት ሙሉ ጠበቃት አልመጣችም። የሆነ ነገር አጋጥሟት ይሆናል ብሎ ወደቤት ሲመለስ ሚስት ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች ያገኛታል።
ባል ደንግጦ << ምነው የኔ ውድ ምን ሆንሽብኝ >>
ሚስት ማልቀሷን ሳታቆም
.
.
.
<< እናቴ ከቤት መውጣት ከልክላኝ ነው።>>

😂😂😂

©Nejat Ahmed
@psychoet
25 ጠቃሚ አባባሎች!!

1. አንተ ጠንክረህ በዝምታ ስትሰራ ፣ ስኬትህ ጮኾ ይናገራል፡፡
-ፍራንክ ኦሽን

2. በሕይወትህ ከዚህ በፊት ያልነበረህ አዲስ ነገር ለማግኘት ከፈለክ፣ አዲስ ሰርተኸው የማታውቀው ስራ ለመስራት መፍቀድ ይኖርብሀል፡፡
-ቶማስ ጄፈርሰን

3. ትክክለኛ ሕይወት የሚጀምረው የምቾት ቀጠና ሲያልቅ፡፡
-ዶናልድ

4. አንተን ሁለት ነገሮች ይገልፁሀል ፡፡ የመጀመሪያው ምንም የሌለህ ጊዜ የምታሳየው ትዕግስት ሲሆን ሁለተኛው ሁሉም ሲሟላልህ የምታሳየው ጠባይ ነው፡፡
-ኢማም አሊ

5. በምድር ላይ ትልቁ አስደሳች ነገር ሰዎች አትችልም ያሉህን ሰርተህ ማሳየትህ ነው፡፡
-ዋልተር ባግሆት

6. ወንዝ ድንጋይ ቦርቡሮ የሚገባው ሀይለኛ ስለሆነ ሳይሆን ያለማቋረጥ ስለሚፈስ ነው፡፡
-ጂም ዋትኪንስ

7. ህልምህን ለመፈፀም ብዙ ጊዜ በመውሰዱ ተስፋ አትቁረጥ ምክንያቱም ጊዜ ስለሚበር አርቀህ ያየኸው ህልም በፍጥነት መፈፀሙ አይቀርም፡፡
-አርል ኒተንጋል

8. ሰዎች በምታቅደው እቅድ ካልሳቁ ወይም ካልተገረሙ እቅድህ ትንሽ ነው ማለት ነው፡፡
-አዚም ፕሪሚጂ

9. ለመጀመር ትልቅ መሆን አይጠበቅብህም ነገር ግን ትልቅ ለመሆን መጀመር አለብህ፡፡
-ዚግ ዚግላር

10. ደስተኛ የሆነ ሕይወት ለመኖር ከፈለክ ከሁኔታና ከሰዎች ጋር ሳይሆን ከአላማና እቅድህ ጋር ተጣበቅ፡፡
-አልበርት አንስታይን

11. አንተ የምርጫህ ውጤት እንጂ በአንተ ላይ የሚደርሱት ነገሮች ውጤት አይደለህም፡፡
-ካርል ጉስታቭ

12. ባለትላልቅ አእምሮ ሰዎች በሃሳብ ላይ ይወያያሉ ፣ መካከለኞች በ ድርጊት / ሁኔታዎች ላይ ይወያያሉ ባለትናንሾች ቁጭ ብለው ሰው ያማሉ፡፡
-ሪያኖር ሮዝቪልት

13. እስካልቆምክ ድረስ በምንም ዝግታ ብትጓዝ መድረስህ አይቀርም ፡፡
-ኮንፊሺየስ

14. ችሎታ ያለው ሰው ምንም ስራ እስካልሰራ ድረስ ችሎታ በሌለው ጠንካራ ሰራተኛ ይበለጣል ፡፡
-ቲም ኖትኪ

15. ከውድቀት ይልቅ ጥርጣሬ የነገ ህልምን ይገላል፡፡
-ሱዚ ካስም

16. እውቀት ብቻ አይበቃም ተግባራዊ ካልተደረገ በስተቀር ፣ ፍቃደኛነት ብቻ አይበቃም ካልተሰራ በስተቀር፡፡
-ብሩስ ሊ

17. የዛሬ አመት በዚህ ሰአት ምናለ ምናለ ከአመት በፊት በጀመርኩ የምትላቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ፡፡
-ካረን ላንብ

18. ጀማሪዎቹ ለመስራት ከሞከሩት ጊዜ በላይ አለቃቸው ብዙ ጊዜ ወድቋል፡፡
-ስቴፈን ማክክሬን

19.ብዙ ጊዜ ላለመስራት የምትተዋቸው ስራዎች በውስጣቸው ብዙ እድልን የያዙ ናቸው፡፡
-ሮቢን ሻርማ

21. መተንፈስ እንደምትፈልግ ያህል ለስኬታማ ሕይወት ጥልቅ ፍላጎት ካለህ ይሳካልሀል፡፡
-ኤሪክ ቶማስ

22. ፊትህን ወደ ፀሀይ ስታዞር ጥላህ ከኀላህ ይወድቃል፡፡
-የማዎሪ አባባል

23. 99% የሚሆኑ ሰዎች ሀሳብህን ከተጠራጠሩህ ፣ እጅጉን ስተሀል አልያም ታሪክ ልትሰራ ነው፡፡
-ስኮት ቤልስካይ

24. ፈፅሞ አትድከም ምክንያቱም አሁን እጅግ ከባድ የሆነብህ ስራ ከጥቂት ጊዜያት በኀላ ለሌላ ስራ መሟሟቂያ ይሆናል፡፡
-ያልታወቀ ሰው

25. ሕይወት ልክ እንደ ካሜራ ነች ፡፡ የምትፈልገውና ጠቃሚ ነገር ላይ ስታተኩር ሌሎቹ የማያስፈልጉት እየደበዘዙ ይሄዳሉ፡፡

@Psychoet
መልካም ዜና ለኢትዮጵያዊያን ወጣቶች በሙሉ፡፡

በአይነቱ ልዩ የሆነ የስልጠናና የውድድር መድረክ ተዘጋጅቷላችኀል፡፡ አሸናፊው ወደ ካይሮ የሚሄድበትን ሽልማት የሚያገኝበት ትልቅ እድል!
ለኹሉም ሰልጣኞችና ተወዳዳሪዎች ደግሞ ሰርተፊኬትና ከወጣት መሪዎች ጋር በቅርበት የመወያየትና ልምድ የመቅሰም እድል ያገኛሉ::

The leadership conference and competition we have all been waiting for is here. Take part in this one of a kind event and get a prize.

Registration is open (በዚህ ሊንክ ይመዝገቡ)
https://bit.ly/leadershipconferenceregistration

Account no: 1000437297208 CBE

+251919367159
+251967304100

Detailed information is available via
https://bit.ly/3C7dD7l

[email protected]
ሜሎሪና መጽሐፍ ፭ኛ ዕትም በገበያ ላይ ውሏል

“ሜሎሪና” ታሪካዊ የሥነልቡና ልብወለድ የሰው ልጅ ሞትን ለማሸነፍ በሚያረገው ትግል ውስጥ የኢትዮጵያውያንን ቀደምት ጥበብ ሚና የሚተርክና የአስተሳሰብ ልዕልናን የሚያሳይ ልብወለድ መጽሐፍ ነው ፡፡ በአቀራረቡም #የሥነልቡና_ምክሮችንና ሀሳቦችን #ከታሪካዊ_ክስተቶች ጋር አጣምሮ ይዟል ፡፡

“ሜሎሪና” በኹለት ሀገራዊ ቋንቋዎች አማራጭ (በዐማርኛና በአፋን ኦሮሞ) ቀርቧል።

"ሜሎሪና"ን አንብባችሁ ስለወደዳችሁት እናመሠግናለን። ቅጽ ኹለት ከብዙ ተጨማሪ አጓጊ ታሪኮችና ትምህርቶች ጋር በቅርብ በእጃችሁ ይደርሳል፡፡ የመጀመሪያውን ክፍል ያላነበባችሁ ደግሞ በቀሩት ጥቂት ቀናት እንድታነቡ፣ ያነበባችሁና የተመቻችሁ ደግሞ ለሌሎችም እንዲያነቡ እንድትጋብዙ እንጠይቃለን፡፡🙏
ከ"ሜሎሪና" መጽሐፍ የተወሰዱ የሕይወት ምክሮችና እውነታዎች

📕‹‹ትልቁ የጦርነት ሥፍራ አእምሮ ነው፤ ትልቁ ድል ደሞ ራስን ማሸነፍ ነው››
“Dirreen lolaa inni guddaan sammuu namaati, Injifannoo guddaan of mo’uudha

📕ያለፍክበት የሕይወት መንገድ አስሮ ሊይዝህ አይገባም ፤ ነገህን መወሰን የራሳህ ምርጫ ነው፡፡

📕በምድር ላይ ምንም ፍጹም ነገር የለምና አንተም ፍጹም ለመሆን አትሞክር ሰዎችም ፍጹም እንዲሆኑ አትጠብቅ ነገር ግን ኹሉን በመልካምነትና በቅን ልቦና አከናውን ፡፡

📕ያለህን ችሎታ ፣ አቅም ፣ ዕውቀት አንተ ካላከበርከውና ካላወጣኸው ማንም መቶ ሊያከብርልህና ሊያወጣልህ አይችልም ፡፡ ስለዚህ ከተቀምጥክበት ተነሳና ከምኞት ወተህ ወደ ተግባር ተሻገር ፡፡

📕ዝምታ ፣ በውስጡ ትልቅ ጩኸት የያዘ የማይጠየቅ ጠያቂ ፣ የማይመረመር መርማሪ ነውና ከዙሪያህ ካለ የሰዎች ጫጫታ በላይ በላይ የውስጥ ዝምታህን አድምጥ ፡፡

📕በሕይወትህ ትልቅ መከራ ፣ ችግር ፣ ሀዘን ደርሶ ሊሆን ይችላል ፤ "ሰው እንዴት በዚህ ውስጥ ያልፋል?" ብለህ አዝነህ ፣ ተክዘህ ሊሆንም ይችላል ፡፡ ግን በሕይወት ዘመን መዘንጋት የሌለብህ ነገር "ተስፋ" የሚባል ነገር መኖሩን ነው ፡፡

📕‹‹... በምድር ላይ የሚወዱትን ሰው በሞት እንደመቀማትና ተስፋ ያደረጉትን እንደማጣት ትልቅ ህመም የለም፡፡ ሲደጋገም ደግሞ ሐዘን፣ ሥቃይ፣ ችግርና መከራ እንደመጫሚያና ልብስ አጥልቀዋቸው የሚዞሩ ያህል ይሰማል፡፡››

📕የሰው ልጅ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ መጠኑና ስፋቱ ቢለያይም፣ ራሱ በሠራው አሊያም ሌሎች ባጠሩለት እስር ቤት ይኖራል፡፡ እንደ ራሱ አሳብና አመለካከት ግን ትልቅ እስር ቤት የሚኾንበት አንዳች ነገር የለም፡፡ ለካስ እስር ቤት ቦታ ሳይኾን አስተሳሰብ ነው፡፡ በዚህች ምድር እጅግ ብዙ ሰው በአእምሮው እስር ቤት ውስጥ በአሉታዊ አስተሳሰብ ታስሮ፣ በከንቱና እንቶ ፈንቶ ፍርሀት ተይዞ ማንም እንዳይረዳው ኾኖ የእስር ቤት ቊልፉን ራሱ ደብቆ ይኖራል፡፡

መልዕክቱን ለሌሎችም ወዳጆቻችን እናጋራ ፔጁን ላይክ እናድርግ

"ሜሎሪና" በዚህ አመት ለወዳጅዎ የሚሰጡት ትልቅ ስጦታ ፡፡ ❤️❤️

በኹሉም መጽሐፍ መደብር ያገኙታል የአፋን ኦሮሞ ትርጉም በጃዕፈር መጻሕፍት እየተከፋፈለ ይገኛል።
ቴሌግራማ ቻናላችንን ይቀላቀሉ www.tg-me.com/psychoet
ጠንክር፣ በርታ ከህልምህ ማንም አያቁምህ፡፡

@Psychoet
ይሄንን ለዛሬ በደንብ አስቡበት
በጣም ቀላልና በጣም ከባድ ጥያቄ?
ከወደዳችሁት ለምን?
ከጠላቸሁት ምን?

መልካም ሳምንት ይኹንላችሁ
@psychoet
ማሸነፍ ይቻላል!!!
#ይሉኝታ
እጅግ ጠቃሚ ጽሑፍ ነዉ ። በደንብ ተነቦ ሼር ይደረግ ።

#ይሉኝታ_ምንድን_ነው?
የሰዎችን ደስታና ሃዘን መካፈል፤ ለሰዎች በችግራቸው ጊዜ ያአቅምን ማድረግ አብዛኞቻችን ያስደስተናል፤ እርካታም ይሰጣል፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንዴ ሰዎች በይሉኝታ ሲታሰሩና ከፍላጎታቸው እና ከአቅማቸው በላይ ጊዜያቸውን፤ ገንዘባቸውን፤ ሃሳባቸውን ለሌሎች ሰዎች ደስታ ሲያውሉ ይታያል፡፡ ይሉኝታ ሰዎች ምን ይሉኛል በሚል ሰበብ፤ የራስን ፍላጎት ገትቶ ሌሎችን ለማስደሰት መጣር፤ ሌሎችን ማስቀደም ማለት ነው፡፡ ይሉኝታ የሚያጠቃቸው ሰዎች ከሚጠበቅባቸው ኃላፊነት እና ግዴታ በላይ የሌሎችን ጉዳይ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ብዙ ርቀት ይጓዛሉ፡፡ ይሉኝታ የራሳቸንን ስራና አጀንዳ ወደ ጎን አድርገን ፤ ፍላጎታችንና እና ምርጫችን ተጭነን ሌሎችን ለማስደሰት የመፈለግ ውጤት፡፡


#ይሉኝታን_ለመቀነስ_የሚረዱ_መንገዶች

✿ለምናደርገው ነገር ከስሜት ይልቅ ምክንያታዊነትን ማስቀደም፡፡ ለምንድን ነው ይህን ጉዳይ የምፈጽመው? ሰው ምንይለኛል ብየ ስለፈራሁ? ወይስ ስለሚያስደስተኝ? ወይስ ኃላፊነት ስለሚሰማኝ? ብሎ መጠየቅ

✿በማድረጋችን፤ ወይም በመፈጸማችን ቆይተን የምንጸጸትበትን ጉዳይ ከማድረግ መቆጠብን መልመድ

✿አስፈላጊ ሲሆን “አይሆንም” ማለትን ወይም ደግሞ “ላስብበት” ማለትን መልመድ

✿የተበላሻ ነገር ስናይ ዝም በማለት ሳይኾን በግልጽ ፊት ለፊት በቅንነት መናገርና ለሰዎች መልካም በመሆንና በይሉኝታ መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት

✿በራስ መተማመንን ሊያዳብሩ የሚችሉ የህይወት ክህሎቶችን መለማመድ

✿ከሰዎች ጋር ባለን ግንኙነት ጤናማ ወሰን እንዲኖረን መጣር

✿ለራሳችን ክብር መስጠት፡- ሰዎች ስለኛ ምንም ቢያስቡ፤ በማንነታችን ላይ ሊያመጣው የሚችለው ተጽእኖ ብዙ እንዳልሆነ ለራሳችን መንገር

✿ያደግንባቸውንና ከማኅበረሰብ ያገኘናቸውን ልምዶች በህይወታችን ያመጡልን በጎና መጥፎ ጎን መከለስ፤ማስተዋል

©zepsychology

Join My Telegram Channel www.tg-me.com/Psychoet
🙏ሰላም ለእናንተ ይሁን እንዴት አመሻችሁ🙏

በጣም ልብ የሚነካ ታሪክ
😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍
ትንሿ ቆንጅዬ ልጅ ሁለት አፕል እንደያዘች እናቷ መጣች። እናትም "የኔ ጣፋጭ አንዱን ለኔ ለእናትሽ ትሰጪኛለሽ?" ስትል በትህትና ትጠይቃታለች፡፡ ልጅም ትኩር ብላ ከተመለከተቻት በኋላ አንዱን አፕል ግምጥ አደረገችው። ቀጠለችና ሁለተኛውንም ደገመችው። እናት በልጇ ሁኔታ ደንግጣ ፍዝዝ ብላ ቀረች። ስሜቷን በቁጣ ልታሳያት ብትሞክርም ድንጋጤው ከለከላት። 'እንዴት በኔ በእናቷ ትጨክናለች?' ብላ አሰበች።

በዚህ መሃል ልጅ የገመጠችውን አንዱን ለእናቷ እያቀበለቻት "እንኪ ማሚ ይበልጥ የሚጣፍጠው ይህኛው ነው።" አለቻት። እናት ያልጠበቀችውን ክስተት በማየቷ ልጇን አቅፋ ተንሰቅስቃ አለቀሰች።
😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍😍

ቢያንስ በእያንዳንዳችን ዙርያ እኛ ምንም ሳናውቅ የሚወዱን የሚያከብሩን የሚሳሱልን አንዳንዴም ከራሳቸው በላይ
የሚያፈቅሩን ሰዎች ይኖራሉ። እንደዚህ አይነት ሰዎችን አንዴ ካስቀየምናቸው መልሰን አናገኛቸውም። ታማኝና ከልቡ ወዳጅ ሰው በጠፋበት ዘመን እንደዚህ አይነት ሰዎችን ማጣት የእድሜ ልክ ፀፀት ማትረፍ ነውና ወዳጆቻችንን
ልክ እንደ ተሰባሪ እቃ በጥንቃቄ እንያዛቸው።

🙌መልካም ምሽት የነገ ሰው ይበለን

@Psychoet
📌🗓📕 ሲጠበቅ የነበረው የ2014 የሕይወት ክህሎት ስልጠና ምዝገባ ተጀምሯል

የሚሰጡ ስልጠናዎች
📝የሕይወትን አላማ ማወቅ
📝ለሕይወት እቅድና ግብ አዘገጃጀት
📝ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም
📝የስሜት ብልሀት
📝ተግባቦት፣ በራስ መተማመንና ፍርሀትን ማስወገድ

ስልጠው የሚሰጠው ለተከታታይ 5 ሳምንታት ሲሆን ያሉን ፈረቃዎች

📆📆➊ ቅዳሜ 3-5
➋ እሑድ 3-5
➌ እሑድ 8-10


#ስልጠናው ቅዳሜ ህዳር 4 እና እሑድ ህዳር 5 ይጀምራል
👉ጠቅላላ ክፍያ ምዝገባንና ሰርተፍኬትን ጨምሮ #600 ብር

🔔በአንድ ፈረቃ ጥቂት ሰው ብቻ ስለምናሰለጥን ከአራቱ በአንዱ በሚያመችዎት ፈረቃ ቀድመው ይመዝገቡ ፡፡

ስልጠናውን ቢወስዱ ይጠቀማሉ ለሚሏቸው ሌሎች ወዳጅዎ #Share ያድርጉ

ለመመዝገብ - 0912664084 በመደወል ወይም
በአካል በመምጣት መመዝገብ ይቻላል፡፡
🏢የስልጠና አድራሻ : 4ኪሎ ቱሪስት ሆቴል አጠገብ አዲስ ብርሃን ህንፃ ቢሮ ቁጥር 219 (Nova Training Center)

✿አላማችን የሰው ህይወት መለወጥ ነው፡፡ 📖
ለሰልጣኞቻችን በሕይወት ለውጥ ዙሪያ(በስራ፣ በትምህርት፣ በንግድ፣ በቤተሰብ፣ በግንኙነት) በግል የማማከሪያ ጊዜ እናመቻቻለን
@psychoet
📌🗓📕 የሕይወት ክህሎተት ስልጠናችን ነገ ቅዳሜ እነ እሁድ ይጀምራል

ሙሉ መረጃውን ከላይ ይገኛል

ያሉን ፈረቃዎች
📆📆➊ ቅዳሜ 3-5
➋ እሑድ 3-5
➌ እሑድ 8-10


በመደወል ወይም በአካል መጥታችሁ የተመዘገባችሁ ሰዎች በሰአቱ እንድትገኙ እናሳስባ ባሉን ቀሪ ቦታዎች ለመመዝገብ -
0912664084 በመደወል ወይም
በአካል በመምጣት መመዝገብ ይቻላል፡፡
🏢የስልጠና አድራሻ : 4ኪሎ ቱሪስት ሆቴል አጠገብ አዲስ ብርሃን ህንፃ ቢሮ ቁጥር 219 (Nova Training Center)

✿አላማችን የሰው ህይወት መለወጥ ነው፡፡ 📖
ለሰልጣኞቻችን በሕይወት ለውጥ ዙሪያ(በስራ፣ በትምህርት፣ በንግድ፣ በቤተሰብ፣ በግንኙነት) በግል የማማከሪያ ጊዜ እናመቻቻለን
@psychoet
# የአለም__እውነታወች
1. የሚከተልህ ሁሉ አድናቂህ አይደለም

2. ውሻ ጭራውን የሚቆላው ላንተ ሳይሆን
በእጅህ ላለው ዳቦ ነው፣ አስመሳይና
ተለማማጭ ሰውም እንዲሁ ነው።

3. ሕይወት ድልድይ ናት፣ አቋርጣት እንጂ
በላይዋ ላይ ቤት አትስራ።

4. ውሀ ቅርፁን ከመያዣው ጋር እንደሚስማማ
ሁሉ ብልህም ራሱን ከሁኔታው ጋር ይስማማል።

5. ምንም ያህል ርቀት በተሳሳተ መንገድ
ብትጓዝም ወደኋላ ተመለስ።

6. ዝቅ ብለህ ብትመለከት ምን ያክል ከፍ
እንዳልክ ታውቀዋለህ።

6. አንድ ሰው ስትተዋወቀው በልብሱ
ልትመዝነው ትችላለህ፣ ስትለየው ግን
በአስተሳሰቡ ትመዝነዋለህ።

7. ሠርግ እና ቀብር አንድ ናቸው። ልዩነቱ
የሠርግ አበባን ባለቤቱ ማሽተት መቻሉ ብቻ
ነው።

8. አምላክህን ደስታህን በቅንነት ብትጠይቀው
ይሰጠሀል። ብቻ በቤትህ በሀቀኝነት ኑር።

9. ማንክያ የሾርባን ጣዕም እንደማያውቅ ሁሉ
ለስሙ የተማረም የጥበብን ጣዕም አያውቅም።

10. ሀገር እንዳትጠፋ ትልቅ ነገርን አታጥፋ።
"ሰው ሆይ በትዕቢትና በንቀት መወጠርህን
አቁም። የውሸት መኖርህን፣ ሰዎችን መበደልህን፣
ፈጣሪህን ማሳዘንህን አቁምና መልካም ነገርን
አድርግ። ልብ በል ሺህ ጊዜ የውሸት ብትኖር
አንድ ጊዜ የእውነት መሞትህ አይቀርም።

ስንት ቁጥር ተመቻችሁ. ?
ፔጁን ሼር፣ ላይክ ያድርጉ
@psychoet
በእርቀት ለሚኖሩ ባለትዳሮችና ፍቅኞች የተዘጋጀ ምክር https://youtu.be/-rhsE0knCS8
14 ወርቃማ #አባባሎች!
------------------------ሼር
1) ምቀኞች መብዛታቸው በስኬት መንገድ ላይ የመሆንህ ምልክት ነው!

2) #ወንድ #ልጅ እናቱ በሕይወት እስካለች ድረስ #ሕፃን ነው..ለእናቱ!

3) በፈተና ላይ አለመታገስ ሌላ #ፈተና ነው!

4) #ፈገግታ ቃላት የሌለው መልካም ንግግር ነው!

5) ካንተ የባሰ አለና አመስግን ፈገግ በል!

6) ትንሽን ለመስጠት አትፈር ምንም አለመስጠት ከሱ የባሰ ነውና!

7) የተሸናፊዉ #ፈገግታ ያሸናፊውን #ደስታ ይቀንሳል!

8) የሁሉን #ሰው ውዴታ ማግኘት ሊደረስበት የማይቻል ግብ ነው!

9) #ነፍስ በኩራት ስትሞላ ጎደሎ የመሆኗ መገለጫ ነው!

10) ኩራተኛ ሰው ተራራ ጫፍ ላይ ሆኖ ሌሎችን ትንሽ አድርጎ እንደሚያይ ነው ነገርግን እሱንም ትንሽ አድርገው እንደሚያዩት አያውቅም!

11) ብዙ ጊዜ በጉጉት ከምንጠብቀው ይልቅ ድንገት የምናገኛቸው ነገሮች ውብ ናቸው እኛ ከለፋነው ጌታ የፃፈው መልካም ነውና!

12) ግኡዝ የሆኑት ውሃና አፈር ለእፅዋት አግልጋይ ናቸው ፤ እፅዋቶች ደግሞ ለእንስሳት ያገለግላሉ እንስሳት ፣እፅዋትና ግኡዛን ደግሞ የሰውን ልጅ ያገለግላሉ ... በተቃራኒው የሰው ልጅ ወደታች ወርዶ ለግኡዛን አገልጋይ (አምላኪ) መሆን ከጀመረ ያኔ ከነሱ የባሰ ይሆናል።

13) ብዙ ሰው ልጅ ለዘለዓለም እንደሚኖር ሆኖ ይለፋል አንድ ቀን ሳያልፍለት ይሞታል!

14) በሕይወት ትልቁ ስኬት የሕይወትን ትርጉም ማግኘትና አላማ ያለው ኑሮ መኖር ነው፡፡

@PSYCHOET
ውሸት
#ክፍል_1
ለምን እንዋሻለን ??? ውሸት ተናጋሪዎችን እንዴት እናውቃለን???

ከሜክሲኮ ወደ አራት ኪሎ ለመሄድ የታክሲ ሰልፍ  መጨረሻ ላይ ተሰልፌያለሁ፡፡ መቼም የስራ መውጫ ሰዓት ስለነበር የሰልፉን እርዝመት ልነግራችሁ አልችልም ደግነቱ የታክሲው ቶሎ ቶሎ መምጣት በጊዜ ወደ ቤት የመግባት ተስፋዬን አለምልሞታል፡፡ ከኋላዬ አንዲት ወጣት ሴት ልጅ መጥታ ተሰለፈች በስልኳ እያወራች ነበር  ልጅቷ የምታወራውን የጽሁፌ መነሻ ስለሆነ እነግራችኋለሁ በስልኩ በዛኛው ጫፍ ሆኖ የሚያወራውን ወዳጅዋን ደግሞ የሚመልሰውን መልስ ከእርሷ መልስ ጋር እያሰናሰልኩኝ በምናቤ እመልሳለሁ፡፡

ልጅቷ፡- በጣም ነው የደከመኝ ብታይ በጊዜ ነው ወደ ቤት የምገባው

ልጁ፡- ትንሽ አንቆይም ናፍቀሽኛል እኮ

ልጅቷ፡- Me too ግን ደክሞኛል እረፍት እፈልጋለሁ የት ነህ አሁን??

ልጁ፡- (የሆነ ቦታ ይላታል)

ልጅቷ፡- አሪፍ፣ እዛው ነሀ ከ 25 ደቂቃ በኋላ እደርሳለሁ

ስልኩ ይዘጋል የታክሲ ተራችንም ይደርስና ሶስተኛው ወንበር ላይ ጎን ለ ጎን ተቀምጠን ጉዞ ወደ አራት ኪሎ፡፡ እንቅስቃሴ የሚበዛበት ሰዓት ስለነበር መንገዱ በመጠኑም ቢሆን ተዘጋግቷል፡፡ ፓርላማ አካባቢ ስንደርስ ስልኳን አውጥታ መልሳ ደውላ ደርሼያለሁ ትለዋለች፡፡ እሱም ምን እንዳላት በእርግጠኝነት ባላውቅም ከመልሷ ግን መረዳት የቻልኩት ልጁ በቦታው አልነበረም፡፡ ቆይ ግን መዋሸት ምን አስፈለገህ ?? መቼ ነው ይሄን ውሸትህን የምታቆመው ?? ብላ ስልኩን ድርግም፡፡ ስልኳ በተደጋጋሚ ቢጠራም መልሳ አላነሳችም፡፡ መጨረሻቸው እንዳልሆነ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡የእነሱን ጉዳይ እንተውና እስኪ ስለ ውሸት ትንሽ እናውራ፡-

ውሸትን የተለያዩ ምሁራን ትርጓሜና እና ማብራሪያ ሰጥተውበታል በዚህም ነጋሪውን ለመጥቀም የታሰበ ሐሰታዊ የሆነ ግንኙነት የሚለው መጀመሪያው ሲሆን ይህም ብዙ ውዝግቦችን አስነስቶ ነበር፡፡ ምክንያቱም ነጋሪውን ብቻ ለመጥቀም  ውሸት አይነገርም የሚሉ፣ ውሸት ሆን ተብሎ የሚደረግ እውነትን የመደበቅ ስራ ነው ብለው መልስ የሰጡ ብዙ ወገኖች ነበሩ፡፡ በሁለተኛው የውሸት ማብራሪያ ወይም ፍቺ መሰረትም ሰዎች ሳያውቁት የተሳሳተ መረጃ ከተናገሩ እንደ ውሸት አይቆጠርም ማለት ነው፡፡ በርገን እና ቡለር የተባሉ ሁለት ምሁራን ደግሞ ውሸት ማለት መልዕክት ላኪው ለመልዕክት (መረጃ) ተቀባዩ ሆን ብሎ የተሳሳተ መረጃ በማቀበል መልዕክት ተቀባዩን መጉዳት ነው ይሉናል፡፡ እኛ ደግሞ የእራሳችን የሆነ የውሸት ትርጉም ወይም ፍቺ ይኖረናል፡፡

ውሸት ብዙ ጊዜ በቃላት ብቻ የሚገለጽ አይደለም በድርጊትም ጭምር እንጂ  ለምሳሌ ያልተጎዳ አትሌት እግሩን እንደተጎዳ አድርጎ እያነከሰ ከውድድር ወይም ከስልጠና ካቋረጠ ዋሽቷል ማለት ነው፡፡ መረጃን ሆን ብሎ መደበቅ ለምሳሌ የገቢን መጠን በመደበቅ ግብርን ለመቀነስ የሚደረግ ጥረትም ውሸት ነው፡፡ እኛ ሰዎች ውሸትን ለሌሎች ብቻ ሳይሆን ለእራሳችንም እንዋሻለን ለአብነትም ማሳካት የፈለግነውን ነገር በራሳችን በሆነ ምክንያት ካላሳካን ችግሩን በውጪ ኣካል በማሳበብ (Externalize) ለራሳችን ውሸት እንነግራለን፡፡ እንደ ዲፓውሎ እና ሌሎችም ምሁራን መሰረት ሶስት  የውሸት ዓይነቶች አሉ፡፡ የመጀመሪያው outright lie (falsification) ሲሆን በግርድፉ አማርኛ ፍጹም ውሸት የሚባለው ነው ይህም ውሸት ተናጋሪዎች ከእውነታው ፍጹም ተቃራኒ የሆነ መረጃን ወይም መልዕክት ይናገራሉ ወይም ያስተላልፋሉ፡፡ ሁለተኛው Exaggeration ወይም ማጋነን ሲሆን በዚህም ውሸት ተናጋሪዎች እውነታውን በማጋነን ያቀርባሉ ለምሳሌ ቀጠሮ ላይ አርፎዶ የሚመጣ ተቀጣሪ የመንገዱን መዘጋጋት ከዕውነታው በተጋነነ መልኩ ሊያቀርብ ይችላል፡፡ ሶስተኛው የውሸት ዓይነት subtle lie ሲሆን በዚህም የሚነገረው የውሸት ዓይነት ጥቂት ሆኖ ከብዙ እውነታዎች ጋር በማቅረብ ሰዎችን ለማማሳት የምንጠቀምበት ነው፡፡

ለምን እንዋሻለን ??

ይቀጥላል ......

#Share
በቁምላቸው ደርሶ
©Zepsychologist
@psychoet
2024/09/28 09:26:57
Back to Top
HTML Embed Code: