Telegram Web Link
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ 🤷‍♂
Photo
#ክፍል_6
(በናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ) #SHARE

ማስታወስ ! /Memory /

ብዙ ጊዜ ሁላችን በተለያዩ የሕይወት መስተጋብሮች "የመርሳት" ገጠመኝ አለን ፡፡ነገሮችን ማስታወስ አለመቻል በዙሪያችን ባሉ ሰዎች መካከል እንደግዴለሽ የመታየት ፣ በስራችን አመኔታ ማሳጣት ፣ በትምህርታችን ደግሞ ያጠናነውን ያለማስታወስ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ በእርግጥ ነገሮችን መርሳት ሲበዛ እንደ ህመም ይታያል ፡፡ ለዚህም ነው በተለምዶ "የመርሳት ህመም " የሚባለዉ ፡፡ ነገሮችን አለማስታወስ ብዙ ማህበራዊ ጉዳት ካስከተለ ታዲያ እንዳንረሳ ምን እናርግ የሚለው ትልቅ ሙያዊ መልስ ያሻዋል፡፡
__________________________________

እንዴት የማስታወስ ችሎታዬን እጨምራለሁ
መርሳትን እቀንሳለሁ የሚሉትን መፍትሔዎችን፡_______________________________________
ማስታወስ / ትዝታ በብዙ መንገዶች መጨመር እንችላለን በዋነኛነት የሚመጡት ግን እነዚህ ናቸው ፡፡

Pay attention (ለነገሮች ትኩረት መስጠት ) : ከዚህ ክፍል 4 እና 5 እንዳስተማርኩት አንድ መረጃ ወደ አዕምሮአችን ገብቶ ለረጅም ጊዜ የሚቀመጠው በስነስርአቱ መረጃው ሲገባ ነው ስለዚህ ነገሮችን ለማስታወስ መጀመሪያውንም ወደ ውስጥ ስናስገባው በጥንቃቄና በአትኩሮት መሆን አለበት ፡፡ በብዛት የሚረሱ ሰዎች መጀመሪያውኑም ለፈተና ከላይ የሚያጠኑ ፣ የምንላቸውን ከላይ ከላይ / በግዴለሽነት የሚሰሙ ናቸው ፡፡

Add meaning ፦የምንሰማውን ፣ የምናየውን ነገሮች እንዳንረሳ ከዚህ ቀድም ከምናውቃቸው ጋር ማቆራኘትና ከመሸምደድ ይልቅ ትርጉሙን መረዳት ፡፡

Take your time ፦ በአንድ ጊዜ ነገሮችን ለመያዝ / ለማገባት ከመሞከር ጊዜ ወስደን እያረፍን ወደ አዕምሮአችን እናስገባ ፡፡

over learn፦ አንድን ነገር እንደምናውቀው ብናውቅም ደጋግሞ ማንበብ ፣ መስማት ፣ ማየት ለብዙ ጊዜ እንዳንረሳው ይረዳል ፡፡

Monitor your learning ፦ ያወቅነውን እንዳንረሳ ደጋግሞ በቃል ማለት በጥያቄ መፈተሽ ፡፡ በተለይሞ ተማሪ የሆናችሁ አንድን ነገር ስላነበባችሁ ብቻ በቂ አይደለም ይልቁንስ ያነበባችሁትን ወረቀት ዘግቶ ማሰብ እንዲሁም እውቀታችንን / ትውስታችንን በተለያዩ መንገዶች መመዘን ፡፡ አርቲስቶችን ብንመለከት (በቲያትር / ሙዚቃ ሙያ ያሉ ሰዎች) አንድን ገፀ ባህሪ አንብበው ያወቁ ቢመስላቸውም ከመድረክ በፊት ግን ብዙ ጊዜ ደጋግመው ይሉታል ይለማመዱታል ፡፡ ይህን የሚያረጉት የሚናገሩት ከራሳቸው ጋር እንዲዋሀድ እና እንዳይረሱት ነው፡፡

___________________________________
እንዲሁም መርሳትን ለመቀነስ ባለፈው ትምህርት እንደተመለከትነው በተጨማሪ *
★የግል ምክር ነገሮችን እየረሳችሁ ላላችሁ !

በጣም ብዙ ሰዎች ሳማክር አንዱ የሚነግሩኝ ችግራቸው የመርሳት ጉዳይ ነው ፡፡ ምንም እንኳን ከእድሜ መግፋት ጋር ተያይዞ የሚመጣ የመርሳት (የአለማስታወስ) ችግር ቢኖርም በወጣቶች/ታዳጊዎች ላይም በተለያዩ ምክንያቶች መርሳት ያጋጥማል፡፡

ስለዚህ በመርሳት ለተቸገራችሁ ምክሬ እነሆ ፡- ነገሮችን መርሳት መጀመራችሁን ስትረዱ / የቅርብ ሰው ሲነግራችሁ መጀመሪያ ተረጋግታችሁ ለራሳችሁ ግዜ በመውሰድ እነዚህን አርጉ

1. በወቅቱ በብዙ ስራ / ተግባር ተወጥራችሁ ከሆነ ሀሳባችሁን በመሰብሰብ የምትሰሩትን ስራ ለመቀነስ ሞክሩ ከቻላችሁም ዋና መስራት ካለባችሁ 1/2 ስራ በስተቀር ሌሎቹን ተዋቸው ምክንያቱም መርሳት አንዱ ምክንያት በብዙ ስራ / ሃሳብ መወጠር ነው፡፡

2. ለጊዜው ለውጥ እስክታሳዩ ድረስ መስራት/ማድረግ ያለባችሁን ነገሮች በሙሉ አንድ በአንድ ወረቀት ላይ በመጻፍ ተከታተሉ ፡፡በሀገራችን "በቃል ያለ ይረሳል በፅሁፍ ያለ ይወረሳል" የሚባለውን እንደምሳሌ እንኳን ብንወስድ እንኳን ተማሪዎች የሆናችሁ ክፍል ውስጥ የምትማሩት አልቆ ስትወጡ የምታስታውሱት 50% ነው ከአንድ ቀን በኀላ ደግሞ ወደ 10% ይወርዳል ፡፡ይህም ማለት የምንማረውን ሳይቀር በአንድ ቀን 90% እንረሳለን ማለት ነው ስለዚህ ነገሮችን መጻፍ ለማስታወስ ዋነኛ መሳሪያ ነው ፡፡

3. በአንድ ጊዜ አንድ ብቻ ስራ ስሩ ይህም ማስተዋላችሁን (Concentration ) ስለሚጨምር የመርሳት ችግር ይቀንሳል ፡፡

4. (Quantity) በአንዴ ጥቂት ነገር ብቻ ይማሩ / ያጥኑ ፡ ብዙ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ለተከታታይ 5 ሰአት ከሚያጠና ሰው ይልቅ በቂ እረፍት በየመሀሉ እየወሰደ 3 ሰአት የሚያጠና ሰው የበለጠ የማስታወስ / ያለመርሳት አቅሙ ይጨምራል ፡፡

5. ለብቻችሁ በየቀኑ በቂ እረፍት ውሰዱ ፦ ይህ እረፍት ወደ አዕምሮአችን የሚገባውን መረጃ ፍሰት ለጊዜው ስለሚቀንሰው አዕምሮአችን እንዳይጨናነቅ ይረዳል፡፡

ሌላውና ዋነኛው ነገር #በጣም እየረሳችሁ ከተቸገራችሁ ከአዕምሮ ጤና ጋር ሊገናኝ ስለሚችል ወደ ህክምና ጣቢያ እንድትሄዱ እመክራለሁ ምክንያቱም የዚህ አይነች ችግር የሚታከመው በመድኃኒትም ጭምር ነው ፡፡

፠፠______________________________፠፠
፠፠______________________________፠፠

ምንጭ ፦ ካለኝ ዕውቀት ማለትም ከዚህ በፊት ከሰማኀቸው ፣ ከተማርኩት እንዲሁም ካነበብኩት ለአንባቢ እንዲቀር አድርጌ በአማረኛ የጻፍኩት ነው ።

ይህ ፅሁፍ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ሁላችንሞ ባለንበት የ Telegram / Facebookግሩፕ ውስጥ #ሼር እናርገው 💛

TELEGRAM 🚙 www.tg-me.com/Psychoet 👍
ሥነ ልቡና - Psychology

ዕውቀት ከአሉታዊ የአስተሳሰብ እስር ቤት ነፃ ያወጣል !
የማክሰኞ ሰው ይበለን!😘😄
ክፍል 4
የአሸናፊነት ሕይወት

በእርግጥ አሸናፊነት በዋነኛነት ከራሳችን ጋር የሚደረግ ውድድር ቢሆንም በሕይወት ዘመናችን ግን ብዙ ከሌሎች ሰዎች ጋር የሚደረጉ ውድድሮች ይኖሩናል ፡፡ ለምሳሌ ፦ በትራክ / በጎዳና የሚሮጡ እሯጮች የሚያሸንፋት ከሌሎች ተወዳድረው ቀድመው በመግባት እንጂ ከራሳቸው ጋር ተወዳድረው አይደለም ።
እግር ኳስ ተጫዎቾች አሸናፊ የሚባሉት ከሌሎች ተጋጥመው በሚያስቆጥሩት የበለጠ ጎል እንጂ ባላቸው የኮከብ ተጫዎች ብዛት አይሆንም ፡፡

በጦር ሜዳ ላይም የሚደረግ ፍልሚያ አሸናፊው ማን የበለጠ የጠላትን ድንበር / ወሰን ተቆጣጠረ / ብዙ ሰው ማረከ በሚል ነው ፡፡

በትምህርት ገበታችን 1 ኛ ወጣን የምንለው ከሌሎች በልጠን እንጂ 100 ስላመጣን አይደለም ፡፡

በንግድ ቦታ አሸናፊ የምንሆነው ከሌሎች ተመሳሳይ ነጋዴዎች የተሻለ ብዙ ደንበኛ ፣ ብዙ ሽያጭ ፣ ጥሩ ገቢ ስናገኝ ነው ፡፡

ስለዚህ አሸናፊነት ውድድርም መሆኑን መገንዘብ አለብን ስለዚህ በነዚህ ውድድር እንድናሸንፍ ማረግ ካለብን ዋነኛ ነገሮች ጥቂቱት እንመልከት

1. ራሳችንን እንወቅ፦

ይሄ ዋናውና መሰረታዊው ነገር ነው ፡፡ አብዛኞቻችን ራሳችንን ደካማና ጠንካራ ጎናችንን ምን መስራት ፣ የት መስራት እንዳለብን በደንብ ስለማናውቅ መወዳደር በሌለብን ዘርፍ ስንወዳደር እንገኛለን ፡፡ ከዛም ሁሌ የምንፈልገውን / ያሰብነውን ውጤት ሳናመጣ እንከርምና መጥፎ የተሸናፊነት ስሜት ይሰማናል ፡፡

ለምሳሌ ፦ ጥሩ እግር ኳስ ተጫዎች ሩጫ ቢወዳደር አይደለም ማሸነፍ ላይጨርሰው ይችላል ፡፡ ራሱንና ችሎታውን አውቆ እግሮ ኳስ ቢጫወት ጥሩ ውጤት ሊያመጣ ይችላል ፡፡

ራሳችንን ለማወቅ ማረግ ያለብን ነገሮች በጥቂቱ
ሀ.መጸሐፍቶችን ማንበብና ዕውቀትን ማሳደግ
ለ. በዚህ ጉዳይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን መውሰድ
ሐ. ተረጋግቶ ስለ እራስ ማሰብና ለራስ በቂ ግዜ መስጠት
መ. ሌላ በዘርፉ የተሻሉ ሰዎችን ማማከር ...


ከዚህ ቀጥሎ ያሉትን በቀጣዩ ክፍል አብራራቸዋለሁ _____________________________________
2. ተጋጣሚያችንን እንወቅ፦
3.ራሳችንን እናሻሽል
3. ካለንበት ምቹ የሚመስል የተለመደ ቀጠና እንውጣ፦
4. አሸናፊነት ያማልና ራሳችንን ለሕመም እናዘጋጅ፦
_____________________________________
መልካም እሑድ!
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ
T.me/psychoet


ከነገ ጀምሮ በአዲስ መልክ የተለያዩ የሳይኮሎጂ ጽሑፎችን መለጠፍ እጀምራለሁና ፔጁን በየቀኑ መጎብኘታችሁን ቀጥሉ !
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ 🤷‍♂
Photo
ለለውጥ መነሳሳት

በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት ዕለት ተዕለት በሚኖራችሁ ህይወት ውስጥ ሁሉም ነገር አስጠልቷችሁ ፤ ምንም ለማድረግ ወኔና ፍላጎቱ ጠፍቷችሁ መነሳሳት ከእናንት ርቆ ያውቃል? እንግዲያውስ ህይወትን በኃይልና በመነሳሳት መንፈስ እንደገና ለመጀመር እነኚህን ነጥቦች ይተግብሯቸው፡፡

1. የህይወትን ዓላማ ማወቅ፡- እያንዳንዳችን ወደዚህች ምድር የመጣነው ያለ ዓላማና ምንክንያት ስላልሆነ ለእኛ በህይወት መኖር ለራስና ለሌሎች የሚያበረክተው ጥቅም ስላለው በህይወት የመኖራችንን ዓላማ ጠንቅቀን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡

2. ጊዜን በአግባቡ መጠቀም፡- ለሰው ልጅ በነፃ ከተሰጠው የተፈጥሮ ሃብት ውስጥ ጊዜ ነው፡፡ ማድረግ የምንፈልገውንና መሆን የምንመኘውን በጊዜ ቀመር ማስቀመጥ ወደ ምንፈልገው የዕድገት ደረጃ ይመራናል፡፡ ጊዜ ሰይፍ ነው ይቆርጣል ያቆስላል ፤ ጊዜ መድኃኒት ነው ከውድቀት ያነሳል፡፡ “ጊዜን ስሩበት እንጂ አይስራባችሁ!”

3. ተስፋ፡- ዛሬ በእጃችን መዳፍ ውስጥ ናት የስኬትንና የውድቀትን ካርድ ልንመዛባት እንችላለን፡፡ ዛሬ ባይሳካ ነገ ደግሞ ሌላ ቀን ነው ፤ ህይወት ሎተሪ ናትና ደጋግመን መሞከር ያስፈልጋል፡፡ የተሻለ ነገን ለማሰብ ተስፋ ትልቅ ስንቅ ነው፡፡

4. ውድቀትን አለመፍራት፡- ብዙዮች ጠንክረው ላመስራታቸውና ህይወትን በተሻለ መልኩ ላለመኖራቸው ትልቁ ምንክንያት ውድቀትን መፍራት ነው፡፡ ነገር ግን ሰዎች ወድቀው በተነሱ ቁጥር ጠንካራ መንፈስን እንደሚላበሱ ጥርጥር የለውም፡፡ ገና ለገና ባይሳካልኝና ብወድቅ እሳ ብሎ ከመጨነቅ ተፋልሞ ወድቆ መነሳት ይሻላል፡፡

5. በዕቅድ መመራት፡- ህይወት ዝብርቅር እንድትል ከሚያደርጉ ነገሮች ውስጥ አንዱ በዕቅድ አለመመራት ነው፡፡ በዕቅድ መመራታችን በህይወታችን ውስጥ ያሳካናቸውንና ያላሳካናቸውን ነገሮች እንድናውቅ ስለሚረዳን ምን ማድረግ እንዳለብን አቅጣጫ ያሳየናል፡፡

6. አወንታዊ አስተሳሰብ፡- በአሉታዊ አስተሳሰብ ጫና ውስጥ ያሉ ሰዎች የመስራትና የመነሳሳት ስሜታቸው ቀዝቃዛ ነው፡፡ ከብርሃን ይልቅ ጨለማው ቀድሞ ስለሚታያቸው ስልቹዎች ናቸው፡፡ መልካም ማሰብ ወደ መልካም ይመራል ድርጊት ከተጨመረበት፡፡

7. ፍላጎትን መቀነስ፡- መስራትና መሆን የምንፈልጋቸው ነገሮች በበዙ ቁጥር አንድ ነገር ላይ አእምሮአችንንና ጊዜአችንን አሳርፈን መስራት ስለማንችል በምኞት ብዛት ራዕይአችን፤ ጊዜአችንና ጉልበታቸን በከንቱ ይባክናል፡፡

 8. ትዕግስት፡- የአንድን ነገር ውጤትና ለውጥ በቅጽበታዊ ጊዜ ውስጥ መፈለግ መነሳሳትን ይገድባል፡፡ በትዕግስት የሚጠባበቁና የሚጥሩ ከሆነ ቢዘገይ እንጂ መድረስ ያለባችሁ ቦታ ከመድረስ የሚያግዳችሁ የለም፡፡

9. ዛሬውኑ መጀመር፡- ስራዎቻችንንና ዕቅዶቻችንን ለማሳካት ከነገ ከመጀመር ይልቅ ከአሁኗ ደቂቃ መጀመር ትልቅ ጥቅም አለው፡፡ የነገን ለነገ በመተው የዛሬን በትንሽ በትንሹ መጀመር ወደ ትልቁ ደረጃ ይመራናል፡፡

 10. ስራችንን በደስታ መጀመር፡- ውስጣዊ ስሜቶቻችንን ለስኬቶቻችን ትልቅ አስተዋጽኦ ስለሚኖራቸው የምንሰራውን ስራ መውደድ ይጠበቅብናል፡፡ የማንወደው ስራ ቢሆን እንኳን የምንወደውን ስራ እስክናገኝ የአሁኑን ስራችንን መውደድ አለብን፡፡

#Share #Like
www.tg-me.com/psychoet

(በአንቶኒዮ ሙላቱ)
©Zepsychology
መልካም ዜና!
የሕይወት ክህሎት ስልጠና ሶስተኛ ዙር ምዝገባ !

ስልጠናው ለአንድ ወር የሚቆይ ሲሆን በመጪዉ ቅዳሜ የካቲት 14 ይጀምራል፡፡

ያሉት ፈረቃዎች
1. ቅዳሜ 3-5
2. ቅዳሜ 10- 12
3. እሑድ 2:30 - 4:30
4. እሑድ 10 - 12

ከአራቱ ጊዜዎች በሚመቻችሁ #በአንዱ_ብቻ ቀድማችሁ ተመዝግቡ ፡፡ በአንድ ክፍል ያለን ቦታ 25 ብቻ ነው ፡፡

አሰልጣኞች የአዲስ አበባ የሳይኮሎጂ አስተማሪ ፣ የማኔጅመንት ተመራቂዎች እንዲሁም አነቃቂ ተናጋሪዎች ሲሆኑ የስልጠናው ርዕሶች
*ሳይኮሎጂን መረዳት
*የሕይወት አላማን መረዳት
*ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀምና ሕይወትን በእቅድ መምራት
*ስለ አስተሳሰብና አመለካከት ለውጥ
*የስሜት ብልህነት እና ሌሎችም ....

" የስልጠናው ውጤት ምስክሮች ሰልጣኞቻችን ያየነው የሕይወት ስርአት ለውጥ ነው ፡፡ "


ቅድሞ ለመጣ ቅድሚያ እንሰጣለን ፡፡ በስራ ሰአት መጥቶ መመዝገብ የማይችል ከታች ባለውስልክ በመደወል ቦታ ማሲያዝ ይችላል
+251946333951

አጠቃላይ ክፍያ የምዝገባ ፣ የስልጠናና የሰርተፊኬት ጨምሮ
#500 ብር ብቻ ነው ፡፡

አድራሻ ካዛንቺስ ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ አጠገብ

T.ME/PSYCHOET

ስልጠና ለሚፈልጉ ጎደኞቻችሁም #SHARE አርጉዎቸው
በአዲስ መልክ ስራ ጀምረናል

ብዙውን ጊዜ ይህን ማስታወቂያ የምንመለከተው በምግብ ቤቶች ላይ ነው፡፡ ገበያቸው ሲቀዘቅዝ፤ ደንበኞቻቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ ሲመናመኑና መክሰር ወደሚባለው ደረጃ ላይ ሊደርሱ ሲሉ ለተወሰነ ቀናት ወይም ሳምንታት አገልግሎት መስጠት ያቋርጡና ቤቱን በማደስ አንዳንድ ጭማሪ ነገሮችን በማካተት የቀድሞና አዳዲስ ደንበኞችን ለመሰባብ ሲሉ በአዲስ መልክ ስራ መጀመራቸውን ባነር ወይም የሚታይ ማስታወቂያ ለጥፎ በማብሰር ስራቸውን ይጀምራሉ፡፡

ይህ የሚያመለክተው በህይወት ጉዞ ሁሌ ወደፊት ብቻ ሳይሆን አንዳንዴም ያሳለፍነውን ደስታ፤ መከራና ውጣ ውረድ ዞር ብሎ መመልከት ለዛሬ ማንነት አስተዋጽኦ እንዳለው ለማጠየቅ ነው፡፡

ትናንት ሞክረናቸው ያልሰመሩልን የህይወት ውጥኖችን ተስፋ ባለመቁረጥ በአዲስ ሞራልና ወኔ እንደገና እንሞክረው፡፡ በህይወታችን ውስጥ በአዲስ መልክ መጀመር ያለብን ነገሮች ምንድን ናቸው?

ትዳራችን እንዴት ነው?

አንቺ ትብሽ እኔ እብስ ተብሎ የተጀመረ ነገር ሁሉ በጊዜ እርጅና ይፈዛል አልፎ ትርፎም ቀለሙ ይወይባል፡፡ ትናንትና የነበረው ፍቅር፤ መረዳዳት፤ መከባበር፤ መደማመጥና ትዕግስት በጊዜ ሂደት ጠፍቶ ሊሆን ይችላል፡፡ በተጣማሪዎቹ መካከል አንደኛው ወይም ሁለቱም የመጠቃት ስሜት እየተሰማቸው ሊሆን ይችላል፡፡ እስቲ የቀደመውን ጊዜ ፍቅርና መልካምነት በማሰብ የዛሬ መጠቃትንና የመገፋት ስሜትን ለአንድ አፍታ በመተው ትዳራችሁን/ፍቅራችሁን እንደ ገና በአዲስ ምዕራፍ ለመጀመር ሞክሩት፡፡ በትዝታ ብቻ የቀረው ፍቅራችሁና የትዳራችሁ መልካምነት ወደ ቀደሞ ክብሩ ይመለሳል፡፡ ግድ የላችሁም ከቻላችሁ ሁለታችሁም ይህ የማይቻል ከሆነ አንዳችሁ በመጀመሪያ ኃላፊነት በመውሰድ ትዳራችሁን/ፍቅራችሁን እንደገና ስሩት፤ በውጤቱ ትደነቃላችሁ፡፡

ማኅበራዊ ህይወታችሁ?

ማኅበራዊ ህይወት መልካም እንደሆነ ሁሉ አንዳንዴ ባልተፈለገና ባልተጠበቀ አቅጣጫ ያመራና ከወዳችነት መንፈስ ወደ ጠላትነት የመሸጋገር ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ አንዱ በዳይ ሌላኛው ደግሞ ተበዳይ ሆኖ በአንጀት መቆሳሰል የግንኙነት ሰንሰለቱ ተበጣጥሶ ይሆናል፡፡ የተራራቃችሁትና የተቆራረጣችሁት ሰው ምንም እንኳን ቢያጠፋና ቢበድል በህይወታችሁ አስፈላጊ ነው ብላችሁ የምታምኑት ዓይነት ሰው ከሆነ እስቲ አንድ ዕድል ስጡትና ማኅበራዊ ህይወታችሁን በማደስ እንደገና ሞክሩት፡፡

ስራችሁስ?

በግልም ይሁን ተቀጥራችሁ በምትሰሩት ስራ ውጤታማና ተሸላሚ ለመሆን ብዙ ርቀት ተጉዛችሁ ፤ ለፍታችሁ፤ ወዛችሁን አሟጣችሁ በስተመጨረሻም የልፋታችሁ ውጤት ሲታይ ትርፍና ኪሳራው እንደማይታወቅ ነጋዴ ዓይነት ሆኖባችሁ ይሆናል፡፡ ዛሬ ላይ ቆም በሉና ሌሎቹ ሲሳካላቸው እኔ ያልተሳካልኝ ምክንያት ምንድን ነው ብላችሁ በመጠየቅ በአዲስ መንፈስና ወኔ ጀምሩት፡፡ እስቲ በትናንትናው ጅምርና ልምድ ሳይሆን በሌላ አተያይ ችግራችሁ ምን እንደነበር ለመፈልፈል ጥረት አድርጉ፡፡ ከዚያ በአዲስ መልክ ስራችሁን ጀምሩ በእርግጠኝነት ይሳካላችዋል፡፡

አመለካከታችሁ?

ለዘመናት ሰው ለምን ይጠላኛል ብላችሁ እራሳችሁን በሃዘን፤ በትካዜ እንዲሁም እራስን ከማኅበራዊ ህይወት እስከ ማግለል ደርሳችሁ በብቸኝነት ስሜት እየተገረፋችሁ ሊሆን ይችላል፡፡ ግድ የለም ሰው ለምን ይጠላኛል ሳይሆን የሚጠላብኝ ነገር ምንድን ነው ብላችሁ እራሳችሁን ፈትሹ፡፡ አንዳንዴም ሌላው ሰው ምንም ሳይለን እኛው እራሳችን በምንፈጥረው ምክንያት የለሽ አስተሳሰብ ሌሎች እንደሚጠሉን ልናስብ እንችላለን፡፡ አእምሮአችሁን በአወንታዊ አስተሳብ በመገንባት ስለእራሳችሁ ጥሩ ምልከታ ይኑራችሁ፡፡ ከዚያ ሁኔታዎችን እንደ አመጣጣቸው በአዲስ መልክ ለመመለስ ሞክሩ ፤ ደስታንም ታገኛላችሁ፡፡

ተስፋ መቁረጥ ይታይባችዋል?

ሁሉም ነገር በእናንተ ተቃራኒ የሚሄድ ከሆነ እናንተ እራሳችሁ የተሳሳታችሁት ነገር ሊኖር ስለሚችል ቆም ብላችሁ እራሳችሁን መርምሩ፡፡ ትናንት ብትወድቁና ባይሳካላችሁ ዛሬ ደግሞ ሌላ ቀን ነው እንደገና ሞክሩት፡፡ ከአይሳካልኝም፤ ይሳካልኛል፤ ከአልችልም እችላለሁ፤ ሁሉም ነገር ጨለማ ነው ብሎ ከማሰብ ከጨለማው በኋላ ጽልመቱ በብርሃን ጸዳል ይገፈፋል ብሎ ማሰብና አዲስ ተስፋ መሰነቅ፡፡ ህይወት ሎተሪ ናት ደጋግመህ ሞክራት ይባል የለ፤ ተስፋ ባለመቁረጥ ጉዞአችሁን አንድ በማለት እንደገና ጀምሩት፡፡

ሱሰኝነት?

አዲስ ዓመትና አዲስ ቀን በመጣ ቁጥር ከሱስ ለመገላገል ለእራስችሁ ቃል በመግባትና ምሎ በመገዘት ጥራችሁ ጥራችሁ ወደ ምትጠሉት ወጥመድ ትብታብ ውስጥ ወድቃችሁ ይሆናል፡፡ ትናንትና ሱስን ለመተው በመጀመሪያ አእምሮአችሁን ሳታሳምኑ ቀጥታ ድርጊቱን በመተው ጀምራችሁ ይሆናል፡፡ ዛሬ ግን መጀመሪያ እንደምትችሉ  አእምሮችሁን አሳምኑ ከዚያ ድርጊቱን በአንዴ ሳይሆን ቀስ በቀስ ለመተው በአዲስ አስተሳሰብና መንገድ ጀምሩት፡፡ በእርግጠኝነት መድረስ ወደ የምትፈልጉበት ቦታ ላይ እንዳትደርሱ እንቅፋት ሆኖ የሚይዛችሁ ነገር የለም፡፡ ከእናንተ የሚጠበቀው ቁርጠኛ መሆን ብቻ ነው፡፡

በአጠቃላይ በህይወት መንገድ ሁሌ ወደ ፊት ብቻ መሄድ ሳይሆን አንዳንድ ጊዜ ከተነሱበት የህይወት አቅጣጫ እራስን ዞር ብሎ በመመልከት እንደገና እንደ አዲስ የሚጀመሩ ምዕራፎች አሉ፡፡ ስለዚህ በህይወቴ ይህንና ያንን አጥቻለው ብላችሁ የምታምኑትንና እንደገና ለማግኘት የምትመኙት ነገር ካለ ያለማቅማማት ህይወትን በአዲስ መልክ ጀምሯት ይሳካላችዋል፡፡

(በአንቶኒዮ ሙላቱ)
©Zepsychology
3 ቀን ብቻ ቀረው

Life Improvement Training /LIT/
📅 የካቲት 14,2012
📍ካዛንቺስ ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ አጠገብ ሸገር ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201

3ኛ ዙር የአንድ ወር ተግባራዊ የህይወት መምሪያ ስልጠና ከሰርተፊኬት ጋር

-የህይወትን አላማ ማግኘት
-የስሜት ብልህነት
-ችግሮችን መፍታት
-ጭንቀትና ፍርሀትን ማስወገድ የንግግርና የተግባቦት ክህሎት ማሳደግ ...ሌሎችም ስልጠናዎችን ያካተተ ነው።

ልምድ ባላቸው ሳይኮሎጂስቶችና የህይወት ክህሎት አሰልጣኞች ይምጡ ይሰልጥኑ።

ለበለጠ መረጃ
0946333951 ይደውሉ።
@psychoet
Forwarded from Temesgen A.
መልካም ዜና ለሁላችሁም!

ለተማሪ ለሰራተኛ ለአዋቂ ለሕፃናት ለሁላችሁም የሚሆን 3ኛ ዙር የአንድ ወር ተግባራዊ የህይወት መምሪያ ስልጠና ከሰርተፊኬት ጋር

ከ70 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ላይ ለውጥ ያመጡበት ስልጠና።

-ሳይኮሎጂን መረዳት
-የህይወት አላማ /life purpose
-የስሜት ብልህነት
-ፍርሀት ድብርትና ጭንቀት
-ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም እና ሌሎችንም ያካተተ ስልጠና

የካቲት 14 ቅዳሜ ይጀምራል
የስልጠና ሰአቶች፡
ቅዳሜ 3-4:30 ወይም
ቅዳሜ 10-11:30 ወይም
እሁድ 10-11:30

500ብር ብቻ

አድራሻ፡ ቅዱስ ኡራኤል ቤ/ያን አጠገብ ሸገር ህንፃ 2ኛ ፎቅ #201

ለበለጠ መረጃ 0946333951

@Psychoet @temuabiy
ስልጠናውን እስካሁን ያልተመዘገባችሁ ዛሬ ቅዳሜ (9:30-10:00) እንዲሁም ነገ (9:30-10:00) ባለው ሰአት በቦታው ተመዝግባችሁ መጀመር ትችላላችሁ ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ 0946333951 ይደውሉ
ክፍል 5 (የመጨረሻ ክፍል)
የአሸናፊነት ሕይወት

ባለፈው ሳምንት ስለ አሸናፊነት ሕይወት ክፍል 4 ላይ ስለ እራስን ስለማወቅ ፅፌ ነበር ዛሬ ደግሞ የመጨረሻውን ክፍል አቀርባለሁ ፡፡ ማሸነፍ የማይፈልግ ሰዎ የለምና እነዚህን መንገዶች ተተገብሩ ዘንድ እመክራለሁ ፡፡

2. ተጋጣሚያችንን እንወቅ፦

ይህ ለማሸነፍ አንዱ ወሳኝ ነገር ነው ፡፡ ከዚህ በፊት እንዳፃፍኩት ለማሸነፍ ውድድር ያስፈልጋል ውድድራችን ደግሞ ከራሳችን ጋር ብቻ ሳይሆን በዙሪያችን ካሉ ተመሳሳይ ሙያ ፣ ዘርፍ ላይ ከተሰማሩ አካሎች ጋርም ጭምር ነው ፡፡ ስለዚህ የማሸነፊያ ሌላው ሚስጥር ስለ ተጋጣሚያችን / ተወዳዳሪያችን ጥሩ ግንዛቤና እውቀት ይዘን ወደ ውድድር መግባት ነው ፡፡ ይሄ ጥበብ አንድም እንዴት ነገሮችን መሰልጠን እንዳለብን ያሳስበናል ሌላው ደግሞ በውድድሩ መስክ ላይ ደግሞ ተጋጣሚያችንን እንዴት ማሸነፍ እንዳለብን እንረዳለን ፡፡

ለምሳሌ ፦ በጦርነት ወቅት ሰላዮች የሚላኩት የተቃራኒው ጦር ስላለው ድክመት እና ጥንካሬ ለመሰለል እንዲሁም ይህን ተጠቅሞ ተቃራኒን ሀይል በቶሎ ለማሸነፍ ነው ፡፡ በንግድም ዘርፍ የሚፎካከረን ነጋዴን ዋጋ በተለያዩ መንገዶች ካወቅን በኀላ በምን መንገድ ገበያውን እንደምንይዝ እናስባለን ፡፡


3.ራሳችንን እናሻሽል

ሌላው ምንም አይነት የችሎታ ፣ የአቅም ሁኔታ ቢኖረን ሁሌ ለመማር ፣ ለመለወጥ ፍላጎትና ተነሳሽነት ይኑረን ፡፡ ብዙ ሰው ለመለወጥ ዝግጁ ስላልሆነ ሁልጊዜ በአንድ መንገድ ሲሰራ ሕይወቱ እየተሻሻለሳይሆን እየደከመ ይሄዳል ፡፡ ስለዚህ ማሸነፍ ከፈለግን ራሳችንን በስልጠናዎች ፣ በትምህርቶች እንለውጥ ፡፡ Software ራሱ ቀየጊዜው Update ይደረጋል ብዙ ሰዎች ግን አንዴ የሆነ መንገድ ከጀመርን Update መሆን ስለማንፈልግ አሸናፊ መሆን ቀርቶ አሸናፊ ከሆንበት መድረክ ተሸንፈን እንወርዳለን ፡፡
★★★★★
ከስልጠና ጋር በተያያዘ በየሳምንቱ በምሰጠው ስልጠና ላይ ብትገኙ እጅግ ስለሚጠቅማችሁ ጊዜያችሁን አመቻችታችሁ እንድትጀምሩ እመክራለሁ ፡፡ ★★★★★

3. ካለንበት ምቹ የሚመስል የተለመደ ቀጠና እንውጣ፦

4. አሸናፊነት ያማልና ራሳችንን ለሕመም እናዘጋጅ፦
አሸናፊነት ቁጭ ብሎ አልጋ በአልጋ ስለማይመጣ ሁላችንም ምንም ቢከብድ ፣ ቢያስቸግር ጠንክረን እንስራ ሯጮች አንድን ሩጫ ለማሸነፍ ስንት ጉዳት ደርሶባቸው ፣ ስንቴ ወድቀዉ ተሰብረው ስንቴ ተስፋ ቆርጠው ፣ እኛ ለሊት አልጋ ላይ ስንፈላሰስ እነሱ በብርድና በዝናብ በለሊት ሲሮጡ ብዙ ህመም አይተው ነው ለአሸናፊነት የሚደርሱት፡፡ ስለዚህ ተቀምጦ በምኞት ብቻ አሸናፊነት የለም ተነስታችሁ ለአሸናፊነት ጠንክራችሁ ስሩ ፡፡
_________________________________
ባለፈው አንድ የፔጄ ተከታይ ለምን ተከታታይጠየሆኑ ክፍሎችን በPDF አድርገህ በቴሌግራም አትልክልንም ባለኝ መሰረት ከዚህ በፊት ያሉትን የ5ሳምንት የአሸናፊዎች መገጫ ሚስጥሮችን በቴሌግራም ማክሰኞ ማታ እለጥፋለሁ ፡፡
_________________________________
መልካም እሑድ!
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ
T.me/psychoet
መልካም ሳምንት!
ለማንኛውም ሰው የሚሆን የሕይወት ክህሎት ስልጠና !
ባሳለፍነው ቅዳሜ እና እሑድ በነበሩት የስልጠና ፕሮግራሞች እጅግ በጣም አስደሳች ስለ ስልጠናው ገለፃ ጊዜ ነበረን ፡፡ አሁንም ጥቂት ቦታዎች ስለሚቀሩን በሚመቻችሁ ፈረቃ እየደወላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ ፡፡

ቅዳሜ 3-4:30
ቅዳሜ 10-11:30
እሑድ 10-11:30

በቀሩት ቦታዎች ይደውሉና ይመዝገቡ 0946333951
አድራሻ ፦ ካዛንቺስ ቅ /ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ሸገር ሕንፃ ቢሮ 201
2024/10/01 09:36:16
Back to Top
HTML Embed Code: