Telegram Web Link
በ 2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ እና በመንግስት ተቋማት ገብታችሁ መማር የምትፈልጉ ተማሪዎች የተቋም ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ የካቲት 02/2015 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ:-

በ 2015 የትምህርት ዘመን በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የምትፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን አውቃችሁ መርጣችሁ መመደብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ የምትሹ (ተመሳሳይ ጾታ ያላችሁ መንትያዎች፣ እመጫቶች(በቅርቡ የወለዳችሁ እናቶች) ፣ ነፍሰጡር ተማሪዎች፣ በመንግስት ሆስፒታሎች ህክምና ቦርድ የተረጋገጠ ልዩ ክትትል የሚሻ ህመም ታማሚዎች … ወዘተ) ተማሪዎች ማመልከቻችሁን እና ደጋፊ ሰነዶቻችሁን በቀጣዩ ሊንክ

https://student.ethernet.edu.et

በኩል ብቻ እንድትልኩ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።

ትምህርት ሚኒስቴር!
Greeting message from Mekelle University.
መቐለ ዩኒቨርሲቲን ወደ ቀድሞ ልኽቀቱ ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ገለጸ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከወራት በኋላ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ባወጣው መልዕክት፤ የተቋሙን ልኽቀት ለመመለስ የሁሉንም የትብብር ድጋፍ ጠይቋል፡፡

ባለፉት ሁለት አስቸጋሪ ዓመታት በሀሳብ እና ድጋፍ ከዩኒቨርሲቲው ጋር አብረው ለነበሩ ዓለም አቀፍ አጋሮች፣ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አስተዳደሩ ምስጋና አቅርቧል፡፡
በትግራይ ክልል ዩኒቨርሲቲዎችን ዳግም ስራ ለማስጀመር አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ነው ተባለ::

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችን ዳግም ስራ ለማስጀመር አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አመለወርቅ ሕዝቅኤል እንደገለጹት፥ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በትግራይ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ዳግም ስራ ለማስጀመር በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡

 በዚህም መሰረት መጀመሪያ የባለሙያዎችና ቀጥሎም አምስት አባላት ያሉት የአመራር ቡድን በክልሉ በሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በቦታው በመሄድ የጉዳት ዳሰሳ ጥናት ማድረጉን አንስተዋል፡፡

ልዑካኑ ከመቀሌ፣ አክሱም፣ አዲግራትና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች አመራሮች ጋር በፍጥነት ስራ ማስጀመር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከሩን ጠቁመዋል፡፡

 የመቀሌ፣ አክሱም፣ አዲግራትና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉበትን አጠቃላይ ሁኔታ የሚገልጽ የዳሰሳ ጥናት በዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች እና አባላት ቀርቦ ውይይት መደረጉንም ተናግረዋል፡፡

 በተቋሙ የተቋቋመው ዓብይ ኮሚቴ ዩኒቨርሲቲዎቹ ወደነበሩበት እስከሚመለሱ የማያቋርጥ ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግ አቅጣጫ መቀመጡንም ስራ አስፈጻሚዋ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

 ዩኒቨርሲቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በማቀድ በቀጣይ ወደ ስራ በሚገቡበት ሁኔታ ላይ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውንም አረጋግጠዋል፡፡

Source-FBC
#ማስታወቂያ የዩኒቨርስቲ ምደባን በሚመለከት

በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከየካቲት 05/2015 እኩለ ሌሊት ጀምሮ ይፋ ይደረጋል።

ስለሆነም ተማሪዎች ከታች በተገለጹት አማራጮች የተመደባችሁበትን ተቋም ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ከየካቲት 15/2015 ዓ.ም ድረስ ተገቢዉን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርሃ ግብር የሚያሳዉቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትቆዩ እናሳስባለን፡፡

የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች

Website: https://result.ethernet.edu.et

SMS: 9444

Telegram bot: @moestudentbot

ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችሁ ማንኛውም ጥያቄ

result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Complaint

የሚለውን በመጫን ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ምንም አይነት ጥያቄም ሆነ ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።

በዚሁ አጋጣሚ ተማሪዎች የትምህርት ጥራትን ለማረጋጋጥ የጀመርናቸውን የሪፎርም ሥራዎች እንዲሳኩ የበኩላችሁን እንድትወጡ እያልን በዩኒቨርስቲ ቆይታችሁ ህልማችሁ እንዲሳካና በቀጣይ ጠንካራ አገር ለመገንባት እንደ ህዝብ ለጀመርነው ተግባር ተገቢውን እውቀትና አስተውሎት የምትይዙበት ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር
Cut Point for Remedial Program
#Grade-12
(Remedial )ፕሮግራም ና ዩኒቨርሲቲ ምርጫን በተመለከተ

በ 2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ የካቲት 10/2015 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ:- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ና የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች በዚህ ፕሮግራም የማይካተቱ መሆኑን እንገልጻለን።

ትምህርት ሚኒስቴር!
Prof. Domenico pioneered a visit to Mekelle University after an over two years communication blackout in Tigrai.
Prof. Domenico Patassini from lUAV University of Venice,Italy has visited Mekelle University to reinitiate the
partnership between the two universities. In his staying from Jan 23rd to Feb1st 2023, he held a series of discussions with the president of our university Dr. Fana Hagos, the Scientific Director of ElIT-M
Dr. Haddush Goitom and dean of the School of Architecture and Urban Planning Mr. Tuumay Allene. He also undertook a collective and individual consultive meeting with his PhD students from the school. In her discussion with Prof. Domenic, Dr. Fana Hagos extended her appriciation to him and the university of IUAV for their pioneer initiation to reinistate the partnership.
The president moreover underscored that Mekelle University is also undertaking necessary preparations to resume networking with all our partners.

Source- Mekelle University official
FB page
#AKSUM UNIVERSITY

Aksum University is loading for resumption!

In fact, it was hard to stay being disconnected from the
connected world for a couple of years. But now, we are on board in the digital world, and we will continue to be dedicated to find new ways to enact its mission of teaching, research and community service engagements.

Join @MUSUofficalchannell
✍️To hear News about
Tigrai Universities
#Axum University
Vacancy
Join @MUSUofficalchannell
#ማስታወቂያ

የRemedial ፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆኗል።

በ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባችሁን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑንና በተመደባችሁበት የትምህርት ተቋሞች በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን እንድትከታተሉ እንገልፃለን ።

ማሳሰቢያ :-
የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን።

የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች

Website:

https://placement.ethernet.edu.et
SMS: 9444

ትምህርት ሚኒስቴር
Hello every body how is every thing on going
#AKSUM UNIVERSITY
call for Financial and Material Support
# ለ አክሱም ዩኒቨርሲቲ
የገንዘብ ና የማተርያል ድጋፍ ጥሪ
#AxumUniversity

አክሱም ዩኒቨርስቲ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሳቢያ የደረሰበት ጉዳት 15 ቢሊዮን ብር እንደሚገመት ማስታወቁን " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

ላለፉት 19 ወራት ትምህርት መስጠት አቁሞ የቆየው ዩኒቨርስቲው፤  ሊያከናውነው ላቀደው ዳግም ግንባታ የድጋፍ ጥሪ አቅርቧል።

የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረእየሱስ ብርሃነ የሰጡት ቃል ፦

- ዩኒቨርስቲው በጦርነቱ ሳቢያ በደረሰበት #ውድመት እና #ዘረፋ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የሚያስችሉት ቁሳቁሶች እና መሳሪያዎች አጥቷል።

- ሙሉ ለሙሉ የተዘረፉ እና ከወደሙ የዩኒቨርስቲው ንብረቶች ውስጥ ኮምፒውተሮች፣ የላብራቶሪ መሳሪያዎች፣ ሰርቨሮች እና የቢሮ በሮች ይገኙበታል።

- ዩኒቨርስቲው ከጦርነቱ በፊት የነበሩት 60 ገደማ ተሽከርካሪዎች ተዘርፈው እና ተቃጥለው አሁን በስራ ላይ የሚገኘው #አንድ_መኪና ብቻ ነው።

- በጥር ወር ላይ በተደረገ ዳሰሳ የደረሰው ውድመት 15 ቢሊዮን ብር ይደርሳል።

- ጉዳት የደረሰባቸውን ንብረቶች በተወሰነ መልኩ በመተካት ወደ ስራ ለመግባት ታቅዷል።

- ለሚያከናውነው ዳግም ግንባታ እና ጥገና ስራ የገንዘብ እና የማቴሪያል ድጋፍ እንዲደረግልን  ጠይቀናል። የድጋፍ ጥሪው ለዓለም አቀፍ እና ለሀገር በቀል አጋር ድርጅቶች፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ነው።

- ዩኒቨርስቲው የሚያገኘውን ድጋፍ በፌደራል መንግስት ከሚመደበለት በጀት ጋር በማጣመር በአጭር ጊዜ ውስጥ የመማር ማስተማር አገልግሎቱን ለመስጠት ታቅዷል። 

- ቁሳቁሶችን በተወሰነ መልክ ቅድሚያ እየሰጠን ካስገባን፤ የግዢ ሂደቱ ፈጣን ከሆነ፤ ተማሪዎችን #በሶስት_ወር ውስጥ ማስገባት እንችላለን። በትግራይ ክልል የሚኖሩ እና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት ያቋረጡ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን ትምህርት ማስጨረስ ላይ ትኩረት ይደረጋል።

አክሱም ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ከፌደራል መንግስት በጀት ባይለቀቅለትም፤ በስሩ ለሚገኘው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 43 መምህራንን ለመቅጠር ከ2 ሳምንት በፊት ማስታወቂያ አውጥቷል።

የቅጥር ሂደቱ የሚፈጸመው በትምህርት ሚኒስቴር ተፈቅዶ፣ በጀት ሲለቀቅ መሆኑ ተገልጿል።

ከፌደራል መንግስት የሚለቀቀው በጀት፤ ለዩኒቨርስቲው ሰራተኞች ደመወዝ ለመክፈል እና ትምህርት ለማስጀመር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

#አራት_ሺህ ገደማ የሚሆኑት የዩኒቨርስቲው መምህራን እና ሰራተኞች ከሐምሌ 2013  ዓ.ም. ወር ጀምሮ #ደመወዝ_አለማግኘታቸውን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።

Credit : www.ethiopianInsider.com

Via - @tikvahethiopia
#Aksum University
Subiect: Disclosing Bank Account Number
Recently, we have invited all concerned bodies to support Aksum University in cash and/or in kind for the reconstruction and rehabilitation endeavor of the University. At the moment, our supporters are requesting for bank account number of Aksum University to support
in cash. Hence, we are kindly disclosing that Aksum University bank account number is 1000022445956 (Commercial Bank of Ethiopia,Aksum Branch).

We respectfully inform you that we will issue a receipt and certificate of appreciation for the support to be given to the University in kind and/or cash. We thank you so much in advance for your financial and material support.


Aksum University

For additional information, use the following address.

Mobile no. +251910593109
+251962212100

Email: [email protected]
2024/09/22 21:28:03
Back to Top
HTML Embed Code: