Telegram Web Link
💚 #ሀቢቡና_ሙሀመድ

    አሚር ሰይድ

ኢብኑ ኢስሀቅ እንደዘገቡት ሐሊመንት ቢንት አል ሀሪስ ስለ ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ አስተዳደግ እንዲህ ሰትል አስተላለፈች


    «ድርቅ በሆነበት ዓመት ከሌሎች የበኒ ሰዕድ እንስቶች ጋር ሆኜ የማደጎ ልጅ ፍለጋ ወደ መካ መጣን፡፡ ከደከመች ነጭ አሀያ ላይ ሁኜ ነበር የመጣሁት። ልጄ እና አንዲት ያረጆች ግመል አብራን ነበረች። ምንም ወተት አትታለብም ነበር። ልጃችን ሲርበው ስለሚያለቅስ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ የለንም። ጡቴ ምንም ነገር የለውም፡፡ ግመሌም ጋቷ ደርቋል" አላህ ከዚህ ጭንቅ እንደሚገላግለን ተስፋ እናደርግ ነበር።

መካ ደረስን። የአላህ መልዕክተኛ ﷺበማደጎ ልጅነት ቀርበውላት አልወስደውም ያላለች ሴት አላውቅም። የቲም ነው ሲባሉ ሴቶች ሁሉ ይተዉታል። «እናቱ ምን ታደርግልኛለች?» በማለት። ምክንያቱም የማደጎ ልጅ የምንወስደውም ከአባቱ አንዳች በጎ ነገር ፍለጋ ነው፡፡

ሁሉም ባልንጀሮቼ የማደጎ ልጅ አገኙ። እኔ ብቻ ቀረሁ። ከነቢዩ ውጭ ሌላ አጣን። ባዶ እጃችንን ልንመለስ ስንል ባሌን ሁሉም ባልንጀሮቼ የማደጎ ልጅ አግኝተው እኔ ባዶ እጄን አልመለስም» አልኩት፡፡ እናም ይህን የቲም ልጅ ለመውሰድ መወሰኔን ነገርኩት።

«ጥሩ አስበሻል። ምናልባትም አላህ በርሱ ስበብ በረከትን ይስጠን ይሆናል» አለ። ሄድኩና ያዝኩት። ሌላ ልጅ ስላጣሁ ብቻ ነው ይህን የቲም ለመውሰድ የተገደድኩት። ይዤው ወደ መኖሪያዬ ስሄድ ጡቴ ወተት ቋጠረ። ይህ ልጅ እስኪጠግብ ጠጣ። ወንድሙም እንዲሁ ጠጣ። ባለቤቴ ወደ ግመሏ ሄደ። ጋቷ ሞልቶ አገኘው፡፡ አለባትና ለኔም ለርሱም ጠጣን።

ጥሩ ሌሊት አሳለፍን። ሲነጋ “ሐሊማ ሆይ! የተባረከ ልጅ ያገኘሽ ይመስለኛል። እርሱን ካገኘን በኋላ እንዴት ዓይነት ደግና በረከታማ ሌሊት እንዳሳለፍን አላየሽምን?» አለኝ።

አላህ በረከቱን ያክልልን ጀመር። ወደ አገራችን ስንመለስ አህያዬ ጉልበት ጨመረች። ፈጥና ትገሰግስም ገባች። ባልንጀሮቼL «ይቺ የመጣሽባት አህያ አይደለችምን?» ይሉኝ ነበር። እርሷው መሆኗን ስነግራቸው አንዳች ነገር እንዳገኛት ይነግሩኛል። በዚህ ሁኔታ ከበኒ ሰዕድ ምድር ደረስን አገራችንን ገባን"

በአላህ እምላለሁ በዚሀች ምድር ላይ እንደቀያችን ደረቅ ወይም ምድራ በዳ የሆነ ምድር ያለ አይመስለኝም። ይህም ሆኖ ግን ፍየሎቼ ውለው ሲገቡ ጠግበውና ወተታቸው ሞልቶ ነው፡፡ በዙሪያችን ያሉ ሰዎች የፍየሎቻቸው ጋቶች ደርቀው ጠብታ ወተት እንኳ በማይሰጡበትና በሚራቡት ሁኔታ የኔ ፍየሎች ይጠግባሉ፡ ይታለባሉ፡፡ ከኔ ፍየሎች ጋር እንዲያሰማሩ ይመክሯቸው ነበር"

እረኞችም ፍየሎቻቸውን ከኔ ፍየሎች አጠገብ ያሰማራሉ። ግን የነርሱ ተርበው ይመለሳሉ" ጠብታ ወተት እንኳ አይሰጡም። የኔዎቹ ግን ጋቶቻቸው ሞልተውና ጠግበው ይመለሳሉ፡፡አላህ የተለያዩ በረከቶችን እያሳየን ይህ ልጅ አደገ"


አስተዳደግ ከሌሎች ልጆች የተለየ ነው። ሁለት ዓመት ሲሞላው ምግብ መመገብ የሚችል ሆነ። ጡት መጥባቱን አቆመ። ልጁን ባየንበት በረከት የተነሳ በጣም ብንፈልገውም ለእናቱ መመለስ ስለነበረብን ይዘነው ሄድን።
.... እናቱ ስታየው ሌላ አንድ ዓመት ከኛ ጋር ይቆይ ዘንድ ፍቀጅልን! የመካ ወረርሽኝ እንዳያገኘው እንሰጋለታለን» አልናት። በአላህ እምላለሁ! ደጋግመን ጠየቅናት። በመጨረሻ ፈቃደኛ ሆነች። መልሼ ወሰድኩት። ሦስት ወራት ያህል ቆየን።



      አንድ ቀን ከቤታችን ጀርባ ከልጅ ጋር በመጫወት ላይ እያለ ልጁ በድንጋጤ ተዉጦ መጣ...ሙሐመድን ሁለት ነጭ ልብስ የለበሱ ሰዎች መጥተው ካስተኙት በኋላ ሆዱን ቀደዱት» አለ።
....እኔና ባሌ ደንግጠን ወደርሱ በረርን። ቆሞ አግኘነው። ገፅታው ተለውጧል።ባሌ አቀፈውና ምን አገኘህ?» ሲል ጠየቀው፡ ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች መጡና

አስተኝተውኝ ሆዴን በመቅደድ አንዳች ነገር አውጥተው ጣሉት። ከዚያ በኋላ እንደነበር መለሱለት» አለን። ወደቤት መለስነው።
....ባሌም ሐሊማ ሆይ! ልጁ አንዳች ነገር አግኝቶት እንዳይሆን እሰጋለሁ» አለኝ። የምንፈራው ነገር ከመከሰቱ በፊት ለቤተሰቦቹ ልንመልሰው ተስማማን። ተሸከመን ወሰድነው፡፡ ከእናቱ ዘንድ ስንደርስ፣ ምን ሆናችሁ አመጣችሁት? ከናንተ ጋር እንዲቆይ ጓጉታችሁ አልነበረምን?» አለችን።

«አዎ፣ በእርግጥ ብለን ነበር። አላህ ፍላጎታችንን ሞልቶልናል። አንዳቸ ክፉ ነገር ሳያገኘው በፊት ወደናንተ እንመልሰው ብለን ነው» አልን።
«ምን ሆናችሁ ነው? እውነቱን ንገሩኝ?» አለች። እንድንነግራት አጥብቃ ጠየቀችን። የሆነውን ነገርናት። «ሰይጣን ሰግታችሁለት ነውን? ይህን ልጅ ሰይጣን አያገኘውም። የተለየ ተሰጥኦ ያለው ልጅ ነው.

በማለት በእርግዝናዋ ወቅት ያጋጠማትን አጫወተችን «እርግዝናዬ በጣም ቀላል ነበር። አንድ ቀን በሕልሜ አንዳች ብርሃን ከኔ ዘንድ ወጣ። የሻምን ሕንፃዎች ሲያበራ አየሁ፡፡ አወላለዱም ከሌሎች ልጆች የተለየ ነው፡፡ እጆቹን ተመርኩዞና ራሱን ወደሰማይ አቅንቶ ነበር» አለችን።»

ሀቢቡና ሙሀመድ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም

ይህ ሐዲስ በበርካታ የሐዲስ መስመሮች ተላልፏል። እጅግ ሰፊ ተቀባይነት ካላቸው ሐዲሶች መካከል አንዱ ነው፡፡



join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#አላህን_የት_ትወነጅለዋለህ??
አሚር ሰይድ


ከዕለታት አንድ ቀን እንድ ሰው ወደ ኢብራሃም ኢብኑ አድሀም( አላህ ይዘንላቸውና) በመምጣት ለመፈፀም የሚፈልገውን የኃጢአት ዓይነት ጠቀሰላቸው፡፡
....እሳቸውም “አላህን ለመወንጀል ከፈለግክ እሱ በፈጠራት ምድር ላይ እንዳትኖር፤ እሱ በፈጠራት ሰማይ ሥርም አትቁም' አሉት፡፡

ሰውየውም በመገረም “አላህ ከፈጠራት ምድር ሌላ ምድር አለን? እንዲሁም ከፈጠራት ሰማይ ሌላ ሰማይ አለን?" ሲል ጠየቃቸው፡፡ እሳቸውም “ታዲያ ይህን ካወቅክ በእሱ መሬት ላይ እየኖርክ በርሱ ሰማይም ስር እየተጠለልክ ልትወነጅለው ይቻልሃልን?!' አሉ፡፡ ሰውየውም ፈፅሞ አይቻለኝም በማለት በሁለተኛ ደረጃ የሚሰጡትን ምክሮ አዲለግሱት ጠየቀ፡፡


እሳቸውም “አላሁን ለመወንጀል ከፈለግክ ከሲሳዩ አንዳች ነገር አትመገብ አሉት፡፡ ሰውየው እንደገና በመልሳቸው በጣም በመገረም “ለአላህ ጥራት ይገባው! ከአላህ ሲሳይ ውጭ ሌላ ሲሳይ ይገኛልን?” ሲል ጠየቃቸው፡፡
.....እሳቸውም በምድሩ ላይ እየኖርክ፤ በሰማዩም እየተጠለልክ፤ ከሲሳዩም እየተመገብክ ልትወነጅለው ይቻልሃልን?!' አሉት::


ሌላ ምክር ይጨምሩልኝ አላቸው፡፡
....እሳቸውም ምክራቸውን ቀጥለው "አላህን (ሱ.ወ) ለመወንጀል ከፈለግክ መለከል መዉት ወደ አንተ ሲመጣ ንስሀ እስከማደርግ ድረስ ትንሽ ጊዜያት ጠብቀኝ" በለው ወይም ከርሱ አምልጥ" አሉት።

ሰውየውም  በጣም  የሚገርም ነው! የሰው ልጅ የሕይወት ፍፃሜ ሊዘገይ ይችላል?! ፍፁም የማይመስል ነገር ነው:። ምክንያቱም አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ብሏል አይደለምን?

فَإِذَا جَاۤءَ أَجَلُهُمۡ لَا یَسۡتَـٔۡخِرُونَ سَاعَةࣰ وَلَا یَسۡتَقۡدِمُونَ

"ጊዜያቸውም በመጣ ወቅት ጊዜ አንዲትን ሰዓት ‎ አይቆዩም አይቀድሙም(አን ነህል 61)

“አራተኛውን ምክርዎትን ይጨምሩልኝ" አላቸው፡፡ እሳቸውም "በአላህ (ሱ.ወ) ምድር ላይ እየኖርክ በሰማዩም እየተጠለልክ ሲሳዩንም እየተመገብክ እሱን ልትወነጅል ይቻልሃልን!? ካሉት በኋላ "አላህን (ሱ.ወ) ለመወንጀል ከፈለግክ የጀሀነም ዘበኞች ወደ ጀሀነም እሳት ይዘውህ ሊሄዱ ሲሉ ከነርሱ አምልጥ ወይም ወደ ጀነት ሽሽ አሉት፡፡ ሰውየውም “ለአላህ ጥራት ይገባው! እነሱ እኮ


عَلَیۡهَا مَلَـٰۤىِٕكَةٌ غِلَاظࣱ شِدَادࣱ لَّا یَعۡصُونَ ٱللَّهَ مَاۤ أَمَرَهُمۡ وَیَفۡعَلُونَ مَا یُؤۡمَرُونَ
በእርሷ ላይ ጨካኞች፣ ሀይለኞች የሆኑ መላእክት አሉ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምፁም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ(አት ተህሪም6)

የተባሉት መላእክት ናቸው" አላቸው፡፡ እሳቸውም “በርሱ ምድር ላይ እየኖርክ፣ በሰማዩ እየተጠለልክ፤ የመሞቻ ቀን እየተቃረበ መሆኑን እያወቅክ፤ ከጀሀነም ዘበኞች ማምለጥ እንደማትችል እየተረዳህ አላህን (ሱ.ወ) ልትወነጅል ይቻልሃልን?" አሉት፡፡ ሰውየውም “ፍፁም አይቻለኝም ካላቸዉ ቡሀላ በዚህ የኢብራሂም ኢብኑ አድሀም ምክር ወደ አላህ(ሱ.ወ)ተዉባህ አድርጎ አላህ(ሱወ)በመታዘዝ ላይ በርትቶ ብዙ አመታት ከቆየ ቡሀላ ሞተ፡፡


⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️

#አላህን_ምህረት_ጠይቅ

አንድ ሰው ወደ ሐሰነ-ል-በስሪይ (ረ.ዐ) መጥቶ የዝናብ መቋረጥን በምሬት ነገራቸው እሳቸውም “አላህን ምሕረት ጠይቅ" አሉት፡፡
....ሌላ ሰው መጣና የውሀ ማነስን በምሬት ነገራቸው፡፡ ለእሱም “አላህን ምሕረት ጠይቅ” አሉት፡፡
......ሶስተኛ ሰው መጣና የልጆቹ ቁጥር ማነስ በምሬት ነገራቸው፡፡ ለእሱም እንደሌሎቹ "አላህን ምሕረት ጠይቅ" አሉት፡፡
.....አራተኛ ሰው መጣና “ምድሪቱ ምርት ከመስጠት ደርቃለች" በማለት በምሬት ነገራቸው፡፡ እሱንም ለአንደኛው ለሁለተኛውና ለሶስተኛው ሰው እንዳሉት “አላህን ምሕረት ጠይቅ" አሉት፡፡



ሰዎቹ ከሄዱ በኋላ አብረዋቸው የነበሩት “ሐሰነል-በስሪይ ሆይ! የሚጠይቅዎት ስው በመጣ ቁጥር “አላህን ምሕረት ጠይቅ" ይላሉን?" በማለት በግርምት ጠየቋቸው፡፡ እሳቸውም ይህ የአላህ ቃል አልገባችሁምን? ብለው የሚከተለውን የቁርአን አንቀጽ ለሰዎቹ አነበቡላቸው፡፡


{ فَقُلۡتُ ٱسۡتَغۡفِرُوا۟ رَبَّكُمۡ إِنَّهُۥ كَانَ غَفَّارࣰا }{ یُرۡسِلِ ٱلسَّمَاۤءَ عَلَیۡكُم مِّدۡرَارࣰا
{ وَیُمۡدِدۡكُم بِأَمۡوَ ٰ⁠لࣲ وَبَنِینَ وَیَجۡعَل لَّكُمۡ جَنَّـٰتࣲ وَیَجۡعَل لَّكُمۡ أَنۡهَـٰرࣰا }


አልኳቸውም፡- ጌታችሁን ምሕረትን ለምኑት፡፡ እርሱ በጣም መሐሪ ነውና፡፡በእናንተ ላይ ዝናምን ተከታታይ አድርጎ ይልካል፡፡በገንዘቦችና በልጆችም ይለግሰላችኋል፡፡ ለእናንተም አትክልቶችን ያደርግላችኋል፡፡ ለእናንተም ወንዞችን ያደርግላችኋል፡፡»(ኑህ10-12)


ወንድሜ እህቴ ሆይ አላህን ምህረት መጠየቅ እናብዛ


join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#ዲናሩል_ከዕቢይ
አሚር ሰይድ

ዲናሩል-ከዕቢይ (አላህ ይዘንላቸውና) በኃጢአትና በወንጀል ላይ የተዘፈቁ ሰው ነበሩ፡፡ ከልጅነታቸው አንስቶ የምትመክራቸው እናት የነበራቸው ቢሆንም የእናታቸውን ምክር ፈፅሞ አይቀበሉም ነበር፡፡

    ከዕለታት አንድ ቀን ብዙ የአስክሬን አጥንቶች ባሉበት የቀብር ስፍራ  በኩል ሲያልፉ አንዱን አጥንት አንስተው ካደቀቋት በኋላ " #አንቺ_ነፍሴ_ሆይ! ወየውልሽ!" አሉ፡፡ ለትንሽ ጊዜያትም ፍፃሜያቸውንና መመለሻቸውን በምናባቸው አስታወሱ፡፡


ለራሳቸውም “ #ነፍሴ_ሆይ! እስከ አሁንም ድረስ በስሜት ላይ ነሽን?'' ካሉ በኋላ "ጌታዬ ሆይ! በራሴ ላይ የፀፀትኩ ሆኜ አግኝቻለሁ፡፡ የሕይወቴን ቁልፎች ላንተ አስረክቤያለሁና ተቀበለኝ፤ ሸሽገኝም፤ አንተ ከአዛኞች በላይ እጅግ አዛኝ የሆንክ ጌታ ሆይ!" ብለው መፀፀታቸውን ለአላህ (ሰ.ወ) ተናገሩ፡፡ ተውባህ አድርገው ጠባያቸውን አርመው ለሊትን በሰላት የሚያሳልፉ ሆነው፣ ሰውነታቸው እስኪደክም ድረስ አላህን (ሱ.ወ) በመገዛት ወደ እናታቸው ተመለሱ፡፡

ዘወትር " #ዲናር_ሆይ! የጀሀነም እሳትን የምትሸከምበት ኃይል አላህን?! እንደለለህ ካወቅክ እንዴት ራስህን ለአላህ ቁጣ አጋለጥክ?" በማለት ራሱን እየጠየቀ ተንሰቅስቆ ያለቅስ ነበር፡፡

     በዚህ ሁኔታ ለብዙ ጊዜ ከቆየ በኋላ አንድ ቀን እናታቸው “ለራስህ ትንሽ እዘን አሏቸው፡፡ እሳቸው ግን
" #እናቴ_ሆይ! ትንሽ እንድደክም ተይኝ ምናልባት ለረዥም ጊዜያት ላርፍ እችላለሁና፡፡

እናቴ ሆይ! አላህ (ሱ.ወ) ፊት እቆማለሁ፣ የሚያስጠልል ጥላ አገኝ ወይም አላግኝ አላውቅም፡፡ እረፍት የሌለበት ችግር እንዳያጋጥመኝ እፈራለሁ" አሏቸው፡፡

....እናታቸውም “ #ልጄ_ሆይ! እጅጉን በጣም ራስህን አድክመሀል” በድጋሚ አሏቸው፡፡ እሳቸውም “እናቴ ሆይ! እረፍት እፈልግ ነበር.
.. እናቴ ሆይ! ምናለ እኔን ከመውለድ መኻን በሆንሽ ኖሮ! ለልጅሽ ረዥም ጊዜያት የሚፈጅ እስር ቀብር ውስጥ ተዘጋጅቶለታል፡፡ ከዚያም አላህ ፊት ለረዥም ጊዜ የመቆም ኃላፊነት አለበት” አሏቸው፡፡ ዲናር አብዛኛውን ጊዜ ሶላት ውስጥ

{ فَوَرَبِّكَ لَنَسۡـَٔلَنَّهُمۡ أَجۡمَعِین
{عَمَّا كَانُوا۟ یَعۡمَلُونَ
በጌታህ እንምላለን!ሁላቸዉንም እንጠይቃቸዋለን፡ይሰሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ(አል-ሐጀር 92-93)

የሚለዉን የቁርአን አንቀፅ እያነበቡ ራሳቸዉን ስተዉ ይወድቁ ነበር፡፡


#Share
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሏሁ አክበር 10 ጊዜ
አልሀምዱሊላህ 10ጊዜ
ሱብሀን አሏህ 10ጊዜ ካልክ ቡሀላ ዱአህን ጀምር
አላህ ዱአህን ይቀበልሀል!!


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#አሳፋሪ_ጥያቄና_አጥጋቢ_መልስ
      አሚር ሰይድ


    ከዕለታት አንድ ቀን ሮማዊው _ ቄሳር _ ለሙዓዊያህ (ረ.ዐ) የሚከተለውን የደብዳቤ መልዕክት ላከለት፡፡ “አቅጣጫ፣ አባት የሌለዉ፣ ወላጅ ስሌለው፥ ቀብሩ ውስጥ ደስተኛ ስለሆነው በማህፀን ውስጥ ስላልተፈጠሩ ሶስት ነገሮች ሙሉ፣ ግማሽና ባዶ ስለሆነ ነገሮች ንገረኝ። የማናቸውንም ነገሮች መፈጠሪያ ዘር የሆነችውንም በብልቃጥ አድርገህ ላክልኝ።''

ሙዓዊያህ (ረ.ዐ) የደብዳቤውን መልዕክት ካነበበ በኋላ መልስ ይሰጡበት ዘንድ መልዕክቱን ለዑብደላህ ኢብነ ዐብባስ (ረ.ዐ) ላከው፡፡



    ዐብደላህ ኢብነ- ዕብባስ (ረ.ዐ) የደብዳቤውን መልዕክት አንብበው የሚከተለውን ምላሽ ለሮማዊው ቄሳር ፃፉለት፡፡
☞“አቅጣጫ የሌለው ነገር የተከበረው ከዕባህ ነው፡፡
☞ አባት የሌለው ዒሳ(ዐሰ) (ኢየሱስ)ናቸው፡፡
☞ወላጅ የሌለው አደም (ዐ.ሰ) ናቸው፡፡
☞በቀብሩ ውስጥ ደስተኛ የሆነው ዩኑስ (ዐ.ሰ) ናቸው።
☞ በማህፀን ውስጥ ያልተፈጠሩት ሦስት ነገሮች
➊ የነብዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) በግ
➋የነብዩላህ ሷሊሕ ሴት ግመልና
➌የነብዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ) ዘንዶ ናቸው።
☞ሙሉ የሆነው ነገር አእምሮ ኖሮት በዚህ አእምሮው የሚጠቀም ሰው ሲሆን፥ ግማሹ ነገር አእምሮ የሌለው ግን አእምሮ ባላቸው ሰዎች የሚሠራ ሰው ነው፡፡
☞ ባዶ ነገር ደግሞ አእምሮ የሌለውና አእምሮ በሌላቸው ሰዎች አእምሮ የሚሠራ ነው፡፡

ከዚያ በአንዲት ብልቃጥ ውስጥ ውሀ ከሞሉ በኋላ “ይህች የማናቸውም ነገሮች መፈጠሪያ ዘር ነች በማለት ከፃፉለት በኋላ መልዕክቱን ወደ ቄሳር ላኩት።

ቄሳሩ ዐብደላህ ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) በሰጡት ምላሽ በጣም ተደነቀ።


join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#የሱን_እሬሳ_ምድር_አትቀበለዉም
          

ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺከኢስላም ያፈነገጠውን ሰው ሬሳ ምድር እንደማትቀበል መናገራቸው
የነብዩﷺ ተአምር ጭምር ነዉ፡፡

      ኢማም አህመድ እንደዘገቡት አነስ ኢብኑ ማሊክ የሚከተለውን አስተላልፈዋል

    የበኒ ነጃር ጎሣ አባል የሆነ አንድ ሰው   ከመካከላችን ነበር። አል. በቀራህንና አል ዒምራንን ምዕራፎችን አጠና (ቀራ)፡፡ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ፀሐፊ ነበር። ከሙስሊሞች ሸሽቶ ሄደና ከክርስቲያኖች ጋር ተቀላቀለ"

ክርስቲያኖቹም የሙሐመድ ራዕይ ፀሐፊ ነበር» በማለት የክብር ቦታ ሰጡት፡ብዙም ሳይቆይ ሞተ። ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት። ምድር ግን አልተቀበለችውም ተፋችው። እንደገና ቀበሩት አሁንም ተፋችው። ከዚያ በኋላ ግን ሳይበብሩ ተውት።


     ይህ የሆነበትን ምክንያት ዐብባስ ሲናገሩ፡ ይህ ሰው በቀራንና አል ዒምራንን ያጠና (የቀራ) በመሆኑ እኛም ለርሱ ልዩ ክብር ነበረን። የአላሀ መልዕክተኛ ﷺ «መሐሪና አዛኝ» የሚል ቃል እንዲፅፍ ሲያዙት «መሐሪና ጥበበኛ» እያለ ይፅፋል። ወዋቂና ጥበበኛ» ብሎ እንዲጽፍ ሲያዙት፡ «ሰሚና ተመልካች» ብዬ ልፃፍ ይላቸዋል...

«ይህ ሰው ከኢስላም አፈነገጠና ከጣዖታውያን ወገነ። «ስለ ሙሐመድ ልንገራችሁ። ራዕይ ፀሐፊው ነበርኩ። የፈለግኩትን ነበር የምጽፈው» በማለት የነቢዩን ስም ማጥፋት! የሐሰት ጥላሸት መቀባት ጀመረ።

ይህ ሰዉ ሲሞት ነብዩ ﷺ ምድር አትቀበለዉም በማለት ተናገሩ።

አነስ እንዳሉት አቡ ጦልሐ ሰውየው ወደሞተበት ሀገር መሄዱን ነግሮኛል። ሜዳ ላይ ተጥሎም አገኘው። «የዚህ ሰዉ ነገር ምንድን ነው?» ሲል ጠየቀ። «ደጋግመን ብንቀብረውም ምድር ልትቀበለው አልፈቀደችም። መልሳ እየተፋች አስቸገረችን» አሉት



ቡኻሪ አነስን በመጥቀስ እንደዘገቡት፡ ሰውየው ክርስቲያን ነበር ሰለመ። በቀራንና አል ዒምራንም አጠና። የነቢዩ ፀሐፊም ሆነ። ተመልሶም ወደ ክርስትና ገባ። ሙሐመድ እኔ የፃፍኩለትን ብቻ እንጅ ሌላ ነገር አያውቅም» ይል ነበር። አላህ ይህን ሰው ገደለው፡፡ ቀበሩት። ምድርም ተፍታው አደረች።

«ይህ የሙሐመድና የባልንጀሮቹ ድርጊት ነው። ከነርሱ ስለሽሽ ከመቃብሩ አውጥተውት ነው» አሉ፡፡ ይበልጥ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍረውም ቀበሩት። ምድር በድጋሜ ተፍታው አደረች። «ይሀ የሙሐመድ እና የባልንጀሮቹ ድርጊት ነው። ከነርሱ ስለሽሽ ሬሳውን አውጥተው ጣሉት» አሉ። ይበልጥ ጥልቅ የሆነ ጉድጓድ ቆፈሩና ቀበሩት። ምድር ለሶስተኛ ጊዜ ተፋችው" በዚህ ጊዜ የሰው ድርጊት እንዳልሆነ አወቁና ሬሳውን ወረወሩት፡፡


ሱበሀነሏህ!!!


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መላኢካዉ አላህን ጀነትን አሳየኝ ያለበት ታሪክ

Join👇👇

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#ቤት_እንግዳ_የመዉሰድ_ጥቅም


   ሚስት ባሏ እንግዳ ይዞ እየመጣ ስልችት ብሏት ስሞታ ለማቅረብ ወደ ረሱል ﷺ መጣች ችግሯን ዘርዘር አድርጋ  ነገረቻቸው፡፡ ነብዩ ﷺ ዝም ብለው ሰምተዋት ምንም አልመለሱላትም

ሴትዮዋ ከሄደች በኋላ ለባሏ አስጠርተው ዛሬ አንተ ቤት እንግዳ ነኝ አሉት ....ባል በጣም ተደስቶ ለሚስት ነገራት ሚስትም በጣም ተደሰተች ራሕመተል ዓለም እቤቷ ሊገቡ ነዋ ቤት  ያፈራው ነገር በደስታ አዘጋጀች

ነብዩ ﷺ ገብተው ከተስተናገዱ በኋላ ለባልየው ስወጣ ሚስትህ እኔ በምወጣበት በር ወደዛ እንድትመለከት ንገራት አሉት
    ረሱል ﷺ ሲወጡ ሚስት ትመለከታለች ከኋላቸው ጊንጥ እንሽላሊት ሌላም ጎጂ ነፍሳቶች ተከትሏቸው ሲወጡ አየች ሚስት ደንግጣ ዞረባት
....ከዚያም ነብዩ ﷺ እንዲህ አሉ:- "አንድ እንግዳ ከተጠራበት ቤት ሲወጣ ልክ እንደዚህ ከዛ ቤት ችግር በላ እና ጎጂ ነፍሳቶች ተከትለዉት ይወጣሉ"
  እንግዳ የሚበዛበት ቤት አላህ የሚወደው ቤት ነው አሉ

በሌላ ዘጋባ ረሱል ﷺ እንዲህ ይላሉ
አላህ ኸይር የፈለገለት ሰው ስጦታ ይልክለታል ሲሉ
... ያስጦታ ምንድን ነው???ተብለው ሲጠየቁ እንግዳ ብለዉ መለሱ

በሌላ ሀዲስ
☞ "እንግዳ የማይገባበት ቤት መላኢካ አይገባበትም"
☞"እንግዳ ወደ ጀነት አመላካች ነው"
☞"በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ እንግዳውን ያክብር" ብለዋል ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ

 ⚡️⚡️⚡️ እንግዳ መጋበዝ አለብኝ ብለን የግድ ከአቅማችን በላይ መጣጣር የለብንም ቤት ባፈራው ሊላህ ብለን ብቻ እንግዳውን ቀልቡ ለማስደሰት በኢኽላስ ከሆነ እንግዳው የሚያስደስተው የምግቡ አይነት ሳይሆን እሱን አክብረን መጥራታችን ነው!



አላህ እንግዳን የምናከብርበት ተውፊቅ አላህ ይስጠን


Join👇👇

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዱአ ስታደርግ በአሏህ በተቀደሰ ስሙ ጠርተህ ዱአ አድርግ
Join👇👇

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#ቁርአን_በዚና_ጉዳይ_ለምን_ሴቶችን_ተጠንቀቁ_ብሎ_አስቀደመ??
            አሚር ሰይድ
         

#ምንጭ☞በዝሙት አንዘምን መፅሀፍ

     
     የሰው ልጆች ወደ ዚና አብዝተው የሚሳቡባቸው ሁለት አበይት ምክንያቶች አሉ፡፡

#አንድኛዉ የሴቶች ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስ ነው፡፡
#ሁለተኛዉ ሰይጣን የሰው ልጆችን ከምንም በላይ ጸያፍ ድርጊቶችን እንዲሠሩ ይገፋፋቸዋል፡፡ ከፀያፍ ድርጊቶች መካከል ግንባር ቀደሞቹ ደግሞ ዝሙትና ግብረ ሰዶማዊነት ናቸው፡፡

ዋናዉ የዝሙት መንደርደሪያ ሁለት ናቸዉ

1⃣ የሴቶች አለባበስ
በተፈጥሮ ለወንዶች ሲበዛ ከተሸላለሙለት ነገሮች መካከል ቀዳሚዎቹ ሴቶች ናቸው፡፡ ወንዶችን በማሳሳትና በማማለል እነርሱን ይበልጥ የሚፈታተናቸው ነገር ደግሞ የሴቶች ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስ ነው፡፡ እናም ዛሬ ዛሬ አብዛኞቹ ሴቶች አለበበሳቸው  መረኑን የለቀቀና አሳሳች በመሆኑ ወንዶች ሲበዛ በሴቶች እየተፈተኑና ወደዝሙትም እየተሳቡ ይገኛሉ፡፡

ማረስረሻው ሒጃብ ስለተነሳ ሒጃብም ሲለበስ አላህ ያዘዘዉን ሒጃብ ባለመሆኑ የዝሙት ዛሩ በየቦታው ተስፋፍቷል፡፡ ዝሙትም በየሜዳው እየተሰበከ ነው፡፡

ዛሬ ዛሬ የሴቶች አለባበስ እጅግ አሳሳችና ወሲብ ቀስቃሽ ከመሆኑ የተነሳ በርካቶች በቀላሉ ዝሙት ላይ እየወደቁ ይገኛሉ፡፡ የሴቶች አለባበስ ወሲብ ቀስቃሽ ሆነ ማለት እነርሱ በቀላሉ ይከፋፈታሉ፤ ጥብቆችና ንፅሕቶች አይደሉም፤ ጨዋዎችና ታማኞች አይደሉም፤ ገላቸው ለአላፊ አግዳሚው አምሮት መውጪያ ቅምሻ የቀረበ ነው፤ ወዘተ የሚል መልዕክትን ያስተላልፋል፡፡

የሴት ልጅ አለባበስ ወሲብ ቀስቃሽ ከሆነ ወንዱ በገላቸው ፍቅር ይሰከራል፤ ምክንያቱም የወንድ ልጅ ወሲባዊ ፍላጎት የሚነሳሳው በዕይታው ነውና፡፡  በዚህን ጊዜ
☞ ለሴት ልጅ ተገቢውን አክብሮት ከመስጠት ይልቅ እነርሱን እንደ ወሲባዊ ዕቃ አድርጎ መመልከት ይጀምራል፡፡
☞ለሴቶቹ ሰብአዊ ማንነት ግን ምንም ክብር አይሰጥም:: ሴቶችን ያራከስና ገላቸውን ለመደሰቻነት ይጠቀማል፡፡
☞እነርሱን እራቁቶ በገላቸው መዝናናትን ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ሴቶች ተሳስተው ላለማሳሳት፣ ጠፍተው ላለመጥፋትና ነድደው ላለማቃጠል ከወሲብ ቀስቃሽ አለባበስ መራቅ አለባቸው፡፡


2⃣/ ሰይጣን የሰውን ልጆች ከምንም በላይ እንዲሠሩት የሚገፋፋቸው ወንጀል ቢኖር ዝሙትን ነው፡፡ ይህንኑ አስመልክቶም አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦
«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሰይጣንን እርምጃዎች እትከተሉ፡፡ የሰይጣንንም እርምጃዎች የሚከተል ሰው (ሀጢአትን ተሸከመ)፡፡ እርሱ በመጥፎና በሚጠላ ነገር ያዛልና (አን-ኑር24:21)



🔰🔰#ሴቶች_በዚና_ሳቢያ_እንዴት_ከወንዱ_የበለጠ_እንደሚጎዱ_የሚከተሉትን_ነጥብ_እንመልከት



✏️✏️ ዚና ላላገባች ሴት ለድንግልናዋ መገርሰስ ዋናው መንስኤ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህም የተነሳ ሴቷ በዚና ድንግልናዋን ስታጣ ከወንዱ የበለጠ ተጎጂ ትሆናለች፡፡ ይኸው ጠባሳም ዕድሜ ልኳን አይሽርላትም፡፡

በተለምዶም ሴቶችና ዝሆኖች ጠባሳቸውን ፈፅሞ አይረሱም” ይባላል፡፡ ለጋብቻ ላትመረጥ ትችላለች። ስታገባም ለባሏ የምታበረከተው ትልቁ ወሲባዊ ስጦታዋ (ከብረ ንፅህናዋ) አብሯት አይኖርም፡፡ እናም በዚህ ሳቢያ መላው የጋብቻ ሕይወቷ ይጎዳል፡፡

⚡️⚡️ ዝሙተኛይቱ ያገባች ሴት ከሆነች ደግሞ ለባሏ ትልቅና ቀጣይነት ላለው ውርደት መንስኤ ትሆነዋለች፡፡ በተለምዶም “አንድ እውነተኛ ባል የሚስቱን ምንዝርነት ከሚሰማ ተገድላ መርዶውን ቢሰማ ይሻለዋል» ይባላል፡፡

✏️✏️ ያገባች ሴት ከዚና አርግዛ ልጅን ብትወልድ የባል ቤተሰብ የዘር ሐረግ ንፅህናቸው ይበላሻል፡፡ ያላገባች ከሆነች ደግሞ በቤተሰቧ ላይ ታላቅ ሀፍረትንና ውርደትን ታስከትላለች፡፡ ይህም ቤተሰቦቿን ለበቀልና ለአፀፋዊ እርምጃዎች ያነሳሳቸዋል፡፡ አንዱ ቤተሰቡ ከሌላው ጋር ለመፋጀትም ይበቃል፡፡

⚡️⚡️ በሴት ልጅ ወሲባዊ ሕይወት ውስጥ ትልቅ ስህተት ተፈፀመ የሚባለው እርሷ ዜናን ለመሥራት ውሳኔዋን ባሳለፈች ቀን ነው፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የሴት ልጅ ወሲባዊ ሕይወቷ የመበላሸት ዕድሉ ሰፊ ነው:: ዝሙተኛ ሴት ለወደፊቱ የሕይወት አጋሯ እራሷን ጠብቃ ማቆየት አትችልም፡፡ ትዳር ወደተባለው ተቋም ስትገባ ዋናው የመግቢያ መስፈርት (ድንግልናው) አብሯት የለም፡፡

✏️✏️ በተለምዶ ሴቶች አራት ዓይነት ናቸው ይባላል፡- ➊ድንግል፤
➋ ዝሙተኛ፡
➌ፈት እና
➍ ፈትም የልጆች እናትም የሆነች፡፡ ድንግሏን ካገበሀት ያንተ ብቻ ናት፡፡ ፍቺም አይኖርም፤ ደባል ባልም አያሰጋህም፡፡ ዝሙተኛዋ ያንተ ልትሆንም ላትሆን ትችላለች፡፡ ሌላው ቢቀር ደባል ባል ይዛብህ ልትመጣ ትላለች:: ዝሙተኛ ሴቶች በቁርኣን አገላለጽ «አል-ኸቢሣት›› (መጥፎዎቹ ሴቶች፣ቆሻሾቹ) ተበለዋል።

ፈት ሴት ያንተ መሆን ብትችልም፣ ግና የቀድሞ ባሏን አትረሳውም፡፡ ፈትም የልጆች እናትም የሆነች ደግሞ ያንተ ብትሆንም ልጆቿንም የቀድሞ ባሏንም አትረሳቸውም፡፡

አሁንም ሴቶችን በአለባበስ ረገድ ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስን የሚከተሉና ሒጃባቸውን በወጉ የሚለብሱ ብለን ለሁለት መከፈል እንችላለን። ታዲያ የዚህ ኡማ ወንዶች ትልቁ ፈተናም እነዚህ ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስን የሚከተሉ ሴቶች (ቀበጥ ሒጃቢስቶች) መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል፡፡

⚡️⚡️ ዝሙተኛይቱ ከዚና አርግዛ ለውርጃ ልትዳረግ ትችላለች፡፡ ይህም በወንጀል ላይ ወንጀልን ያሸከማታል፡፡ ከዚና ከወለደችም ልጁን ለማሳደግ በርካታ ፈተናዎች ታያለች፡፡ በልጁ አስተዳደግና እነፃ ላይ ትልቅ ከፍተት ይፈጠራል፡፡ ይህም በተራው አሳዳጊ የበደለው ልጅ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀል ያደርጋል።

✏️✏️ ሴት በዚና ሳቢያ ከወንዱ የበለጠ ለአባላዘር በሽታዎችና ለኤድስ የመጋለጥ ዕድሏ ሰፊ ነው፡፡ ወንዱ ኮንዶምን እንዲጠቀምና ጥንቃቄ የተሞላበት ወሲብን እንዲያደርግ የማስገደድ አቅሟም አነስተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ዚናው የሚካሄደዉ ከሞላጎደል በርሱ ፍላጎት መሠረት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ማሕፀኗ ሊጎዳና የማሕፀን ግድግዳዋ ሊደማ ይችላል፡፡ ለፊስቱላ በሺታም ልትጋለጥ ተላለች፡፡

⚡️⚡️ ሴት በዚና ሳቢያ ከማንኛውም የወሲብ መንገደኛ ጋር አስሬ በአፍጢሟ ስትድፉ ከብሯ ሁሉ ይቀንሳል፡፡ ዝሙተኛውም ፈፅሞ እንደሰው እይቆጥራትም።

✏️✏️ ሴት በዚና ሳቢያ ለተለያዩ ወሲባዊ አብደቶች ልትጋዝጥ ትችላለች በዝሙተኛውና በዝሙተኛይቱ መካከል ፍቅርና ውዴታ ስለሚይኖር እርነሱ ፈፅሞ አይራራላትም፡፡ ከዚህም የተነሳ የፊንጢጣ ወሲብን ሊሠራባት ይችላል፡፡ የአፍ ወሲብንም ሊሠራባት ይችላል፡፡ የነዚህ ወሲባዊ እብደቶች ጉዳት ደግሞ እጅግ የከፋ ነው፡፡ መላውን ወሲባዊ ሕይወቷን ሊያበላሽ ይችላል፡፡

⚡️⚡️ በተለይ የዘመናችን ዝሙተኞች የተለያዩ የወሲብ ማነቃቂያ ነገሮችን በመውሰድ ሴቶችን እንደሚያሰቃዩ እሙን ነው፡፡ ለምሳሌ ሱስ አስያዥ ዕፅን የወሰደ ወንድ ሴቷን በአንድ የወሲብ ዙር ብቻ እስከ 40 ደቂቃዎች ሊያሰቃያት ይችላል፡፡ ከዚህም የተነሳ ሴቷ በቀላሉ ትዳከማለች፡፡ አካሏም ሆነ መንፈሷ ሲበዛ ይጎዳሉ፡፡ ይህም በርሷ ምርታማነት ላይ ትልቅ ተጽዕኖ አለው፡፡👇👇👇
✏️✏️ ሴት ልጅ በተለይ አሁን ቴከኖሎጂው በብዛት ለመጥፎ ነገር ማስፋፈያነት በሚውልበት አግባብ ውስጥ በለየለት እኩይ ወንድ እጅ ከገባች እርሱም ዚናውን እየፈጸመባት በተጓደኝነትም ያንን ትዕይንት ቀርፆት ያስቀምጠዋል፡፡ ወንዱ ይህንን ካደረገ ደግሞ ከዚህ በኋላ የርሷ ነገር በርሱ እጅ ውስጥ ገባ ማለት ነው፡፡ እንደፈለገ ይጫወትባታል፡፡ ያስፈራራታል፤ ያስለቅሳታል፡፡ ከዚህም የተነሳ ሴቷ ለብላክሜይሊንግ (ማስፈራሪያ) ትጋለጣለች፡፡ ይህም ነገር በተውበት ወደ አላህ (ሱ.ወ) እንዳትለመስ ሁሉ ደንቃራ ይሆንባታል፡፡ በዚያ ቪዲዮ ሳቢያም ሴቷ ወደ ጌታዋ ሁሉ መሸሽ የማትችልበት ሁኔታ ያጋጥማታል፡፡

⚡️⚡️ ዝሙተኛ ሴት ለአስከፊው የሴተኛ አዳሪነትና ለወሲብ ንግድ የመጋለጥ ዕድሏ ሰፊ ነው፡፡ በተለይ ጉንተላ የሚበዛባት ከሆነ በቀላሉ ወደዚህ ሥራ ልትገባ ትችላለች፡፡ የሴተኛ አዳሪነት ሥራ ጭንቅላት፣ ተያዥ፣ የሕከምና ማስረጃ፣ የሥራ ፈቃድና የመነሻ ካፒታል ስለማይጠይቅም የዝሙት ሱስ ያለባቸውን ሴቶች የመሳብ ችሎታው ከፍ ያለ ነው፡፡

በአጠቃላይ ሴት ልጅ በዝሙተኛ ወንድ እጅ ገባች ማለት የትዳር አጋሯ ባልሆነ፣ በማይወዳት፣ በማያፈቅራት፣ በማይጠነቀቅላትና በማያዝንላት ሰው እጅ ገባች ማለት ነው፡፡ ይህ የወሲብ መንገደኛም ለራሱ ስሜት እንጂ ለርሷ ደህንነት አንዳችም ነገር አይጨነቅላትም፡፡ ለሚመጣው መዘዝም ኃላፊነቱን አይወስድም፡፡ ጉዳት ሲደርስባትም አብሮነቱን አያሳያትም፡፡ ከዚህም የተነሳ በወሲብ መንገደኛ እጅ የገባች ሴት ለአውሬያዊ አያያዝ ትዳረጋለች፡፡ ይህም ሴቶችን በሁሉም መልኩ ይጎዳቸዋል፡: ዚና ሴቶችን የወሲብ ሕይወታቸውን ብቻ ሳይሆን ሁለንተናዊ ማንነታቸውን ጭምር ያራክሳል፡፡ ከብራቸውን ዝቅ ያደርጋል፡፡በገላቸዉ እንጂ በጭንቅላታቸው እንዳያስቡ ያደርጋቸዋል፡፡ እራሳቸውን እንዲያሻቅጡና አስከፊውን የሴተኛ አዳሪነት ሕይወትን እንዲቀላቀሉ ምከንያት ይሆናቸዋል፡፡ ይህም በመሆኑ ሴቶች በዚና ሳቢያ ከወንዶች በላይ ተጠቂዎችና ተጎጂዎች ሆነው ይገኛሉ፡፡ ለዚህም ሲባል ነው ቁርኣን በዚና ጉዳይ ሴቶችን ያስቀደማቸው፡፡


⚠️⚠️በዚና መስመር ላይ ያለን፡በመንደር ደር ላይ ያለን ከአላህ ጋር እየተጣላን እርዚቃችንን ደስታችንን ከማሸሽ ከዚህ ከዚና አስከፊ በሽታ ሞት ሳይቀድመን ቶብተን እንጠብቀዉ

መታወቅ ያለበት የሴቶች አለባበስ ለራሱ የዚና መንደርደሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡


👌የዚና ጉዳይ ሲነሳ ተፈራርቶ አይሆንም ለሌሎች ሼር ያርጉ አይታወቅም አንድ ሰዉ ወደ ቀልቡ ተመልሶ ከዚና ቢቶብት ሼር ባደረግንበት ከአጅሩ ተጠቃሚ ሆን ማለት ነዉ

ስለዚና ያተኮሩ ርዕሶች ኢንሻ አላህ ይዘጋጃሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
ሉቅማን አል-ሐኪም ልጁን እንዲህ ሲል መክሮታል፡፡

>> “ልጄ ሆይ ከሰው ልጅ ጀርባ ያለውን ነገር ሳታውቅ ፈገግታው እንዳያታልልህ !! ምክንያቱም የሰው ልጆች የማንነት መቃብር ልቦናቸው ውስጥ ሲሆን የሚያስጐመዥ ፍሬያቸው ደግሞ ፊታቸው ላይ ይገኛል፡፡

ስለዚህ እሮሮህና አቤቱታ ዘውትር ይህን ዘመን ወደ ፈጠረው አላህ (ሱ.ወ) ይሁን፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ጥሩውንም ሆነ መጥፎውን ነገር ባንተ ላይ ከሻተ ሰዎች ወደዱም ጠሉም አንተ ላይ ከመከሰት ወደኋላ እንደማይል ጠንቅቀህ እወቅ፡፡"

@አሚር ሰይድ


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#በሰባት_ጣዖታውያን_ላይ_ያደረጉት_ዱዓ

ቡኻሪና ሙስሊም ኢብኑ መስዑድን በመጥቀስ እንደዘገቡት፡

«ነቢዩ ﷺ ከዕባ ውስጥ ይሰግዱ ነበር። አቡ ጀሀልና ባልደረቦቹ ተቀምጠዋል። «ሙሐመድ ሱጁድ ሲያደርግ ፈርስ የሚያፈስበት ማን ነው?» ተባባሉ። ከመካከላቸው ይበልጥ ተንኮለኛው ፈርስ ይዞ መጣ። ሱጁድ እስኪያደርጉ ጠበቀና ከጀርባቸው ላይ አፈሰስባቸው፡፡ እኔ ሁኔታውን እከታተል ነበር። ምንም ላደርግ አልቻልኩም። ጉልበት ቢኖረኝ ኖሮ ይህ ነገር በነቢዩ ላይ እንዳይደርስ በተከላከልኩ ነበር።

ሰዎቹ ይሳላቁ ጀመር። አንተ ነህ አንተ ነህ እየተባባሉም ይቀልዱ ጀመር። የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ሱጁድ እንዳደረጉ ናቸው" ራሳቸውን ከሱጁድ አላቀኑም። ልጃቸዉ ፋጡማ(ረ.ዐ) መጣችና ቆሻሻውን ከጀርባቸው አስወገደችላቸው። ራሳቸውን ቀና አደረጉና፡ «አላህ ሆይ! ቁረይሾችን ተበቀልልኝ» በማለት ሦስት ጊዜ በመደጋገም ዱዓ አደረጉ።

እርግማኑን ሲስሙ ሰዎች ተጨነቁ። በዚያ ሀገር ውስጥ የሚደረግ ዱዓ ተቀባይነት እንዳለው ያምኑ ነበር። ነቢዩ በመቀጠልምሰዎችን በስም ጠርተው ዱዓ አደረጉባቸው፡፡ እንዲህ አሉ  «አላህ ሆይ!
>አቡ ጀህልን ተበቀልልኝ።
> ዑትበት ኢብኑ ረቢዓህን'
>ሸይበት ኢብኑ ረቢዓህን፡
>ወሊድ ኢብኑ ዑትባህን
>ኡመያ ኢብኑ ኸለፍንና
> ዑቅበት ኢብኑ አቢ ሙዒጥን ተበቀልልኝ»
አንድ ሰውም ጨምረው ጠሩ። ስሙን አላስታወስኩትም።

ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ፣ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ስማቸውን ጠቅሰው የረገሟቸው እነዚህ ሰዎች በድር ላይ ተገደሉ። ገደል ውስጥም ተጣሉ።


ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ያአሏህ😢

አረ በዱአ አንዘንጋቸዉ ልብ ይሰብራል😔

ይቺ ህፃን ልጅህ(ልጅሽ) ወይም እህትህ(እህትሽ)ብትሆን የስቃይ ስሜታችን መቆጣጠር እንችል ይሆን😔
⚠️#ኢስላምን_በዉርስ_ያገኘነዉ_ሀይማኖት_ስለሆነ_ዝሙትን_ተዳፈርን
     አሚር ሰይድ

«በአሜሪካ ያሉ ሰለምቴ ሙስሊሞች ከምንም በላይ ከሁለት ወንጀሎች በግልፅ እንደራቁ አስረግጦ መናገር ይቻላል፡፡ አዎን! ማንኛውም ሰለምቴ አሜሪካዊ ሙስሊም ከሪባ የራቀ ነው፡፡ እንዲሁም ማንኛውም ሰለምቴ አሜሪካዊ ሙስሊም ከዝሙት የራቀ ነው፡፡» (ኑእማን አሊ ካን - አሜሪካዊ ዳዒይና የቁርኣን ተንታኝ)


         እንደሚታወቀው አብዛኛው የሀገራችን ሙስሊም ኢስላምን የሚወርሰው ከቤተሰብ ነው፡፡ ቤተሰቡ ሙስሊም የሆነ ልጅ እርሱም ሙስሊም ይሆናል፡፡ ከዚህም የተነሳ ኢስላምም በውርስ የሚያገኝ ሃይማኖት ይሆናል፡፡ ኢስላምን በውርስ የሚያገኝ ልጅ ደግሞ ስለእምነቱ ይህንን ያህል የበዛ ትኩረት ሰጥቶት ላያጠናው ይችላል፡፡

ነገር ግን አሜሪካዉያን ሙስሊሞችን በምሳሌነት ብንወስድ እነርሱ ዘንድ አብዛኞቹ ኢስላምን የተቀበሉት አንብበው፣ አጥንተው፣ ተመራምረው፣ አነፃፅረውና እዉነቱን አንጥረው ካወቁ በኋላ ነው፡፡ ከዚያም በዚህች ምድር ላይ ብቸኛው እውነት ብቸኛው መለኮታዊ ሀይማኖትና ታላቁ ፀጋ ኢስላም መሆኑን ስለሚረዱ ወደ ኢስላም ሲመጡ ዲኑን በሚገባ ለመተግበር ነው፤ በሙሉ ልባቸው፡፡

በተለይም ምዕራባዉያን ዜጎች ሙስሊም ከሆኑ በኋላ አንዳች ሲሠሩት የነበረው ነገር በኢስላም የተከለከለ መሆኑን ካወቁ ወዲያው ያንን ነገር ይተውታል፡፡

⚡️⚡️አሜሪካዊው ታላቁ ዳዒይና በቁርኣን ተፍሲር ትልቅ ዕውቅናን ያገኘው ኑእማን አሊ ካህን በበኩሉ በምዕራቡ ዓለም እጅጉን የተንሰራፉ ነገሮች በተለይ ወለድና ዝሙትን የመሳሰሉ ኃጢአቶች እነሱ ዘንድ ከሞላ ጎደል እንደማይታወቁ ይናገራል፡፡ በተለይም ከጥቂት ዓመታት በፊት የደረሰውን የምዕራቡን ዓለም የገንዘብ ቀውስን አስመልክቶ ቀውሱ ሙስሊሞችን እምብዛም እንዳላጠቃቸው በመጥቀስ አሜሪካዊው ሙስሊም ከወለድ የራቀ መሆኑን እንደማሳያ ያነሳል፡፡

#ቀጥሎም ዝሙትን አስመልከቶ አሜሪካዉያን ሙስሊሞች ከዚህ መራቃቸውን እንደ ማሳያ የሚያነሳው ነገር ቢኖር የመስሊም ሴቶችን ታላቅ ግብረገብነትና የሒጃብ አለባበሳቸውን በመጥቀስ ነው::

በዚህች ሀገር የሴቶች ትልቁ መከበሪያቸው ሒጃብ ነው:: የራስ መተማመናቸውና ለኢስላም ያላቸው ፍቅር ያስደንቅሃል፡፡ ሴቶቹ እንዴ ከሰለሙ በኋላ ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስን ሊከተሉ ቀርቶ ከቶውኑ አያስቡትም፡፡ ቀድሞውኑ ኢስላምን አጥንተውትና መርጠው ስለሚመጡ ሰዉ ምን ይለኛል የሚለውን ነገር ከመጤፍ አይቆጥሩትም፡፡ ወንዶቹም ቢሆኑ አብዛኞቹ ያገቡ ስለሆኑ ስለዝሙት አይነሳባቸውም፡፡

እንደውም በአንድ አጋጣሚ የተከሰተውን ነገር ለምን አልነግራችሁም? በአንድ ወቅት አንዲት ደምቃና የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ ተሸሞንሙና የወጣች እንስት ከአንድ ወጣት ሙስሊም ጋር በባቡር ላይ ይገናኛሉ፡፡ ሰዉ ሁሉ አተኩሮ ያያታል፡፡ እርሷም እየተገማሸረች የምትወጣው ለዚህ ነው፡፡ ወንዱ ሁሉ በአድናቆትና በምኞት ይመነጥራል፡፡ ይህ ወጣት ግን አንዳችም ትኩረት ላይሰጣት ቀረ፡፡ እርሷ ግን አልፎ አልፎ ትገረምመዋለች፡፡ እርሱ ወይ ፍንክች አላለም፡፡ ታዲያ ተሳፋሪው ቀስ በቀስ እየወረደ ሲቀንስ እርሷ አውቃ የወጣቱ ዓይን ውስጥ ለመግባት ተጠጋችው፡፡ እርሱ ግን አሁንም ከምንም አልቆጠራትም፡፡ ወዲያ ወዲህ ብትቀበጥም አላተኮረባትም፡፡
..... በመጨረሻም በኃይለኛው ተቆጥታ ለመሆኑ አንተ ወደኔ አንዴም የሚታየው እኔ ይህን ያህል ቀፋፊ ነኝ እንዴ? ቆይ እንዲህ ከሆነ እኔ ለማነው ተጋጊጬ የምወጣውን ስትል አቧረቀችበት፡፡

እርሱ ግን በተረጋጋና የራስ መተማመን መንፈስ በተሞላበት ሁኔታ ይህንን ለምን እንደማያደርግ አስረዳት፡፡ አየሽ! እኛ ሙስሊሞች ዕይታችንን እንድንቆጣጠር ታዘናል፡፡ ስለዚህ ወደ ባዳ ሴት ሆነ ብሎ መመልከት የተከለከለ ነው፡፡ ለዚህ ስል ብቻ ነው እኔ ወደ አንቺ የማላየው፡፡ ከዚህ ውጭ በግል ምንም ያደረግሸኝ ነገር የለም፡፡ የእምነት ጉዳይ ሆኖብኝ ነው ወዳንቺ የማልመለከተው አላት፡፡ ልጅቷ በሰማችሁ ነገር ተገረመች፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰውና እምነት እንደዚያ ሰይጣንን አብዝታ በምታበረታታው ሀገረ አሜሪካ መኖሩ አስደነቃት፡፡ እምነት ሰውን ከብልግና ሲታደግ አስተዋለች፡፡ እናም ለመሆኑ ያንተ እምነት ምንድነው? ስትል ወጣቱን ጠየቀችው፡፡ እርሱም እምነቱ ኢስላም መሆኑን ነገራት፡፡ ስለኢስላምም አንዳንድ ነገሮችን ነገራት፡፡ ከዚያም ስልክ ተለዋወጡና በዚሁ ተለያዩ፡፡

ልጅቷ በሰማቸውና ልጁ ላይ ባየችው እፁብ ድንቅ ምግባር እጅጉን ተደምማለች፡፡ እንዲህ ዓይነት ወጣት ገጥሟት ስለማያውቅ ስለርሱ እምነት ልታጠና ጓግታለች፡፡ ወዲያው በነጋታው ደውላ የቁርአንን ኮፒ እንዲሰጣት ጠየቀቸው:: እርሱም የቁርአን ኮፒ ሰጣት ልጅቷም ቁርአንና ሌሎችንም ኢስላማዊ መጻሕፍት ለስድስት ወራት አከታትላ አጠናችው፡፡ ስድስት ወሩ እንዳለቀም ለልጁ ደወለችና ኢስላምን መቀበል እንደምትፈልግ አበሰረችው፡፡ እሱም ወደመስጊድ ወሰዳትና ሰለመችም፡፡ የአላህን አንድነትና ብቸኛ አምላክነቱን መሰከረች፡፡ገና ልትሰልም ስትመጣ እራሱ ሒጃቧን በወጉ ለብሳ ነበር፡፡ እናም አሁን በኛ ማዕከል ውስጥመደበኛ ሴት ዳዒይ ስትሆን በርሷ ሰበብም በርካታ ሴቶች ወደ ኢስላም መጥተዋል፡፡
(ምንጭ፡- ቮይስ ኦፍ ኢስላም - አሜሪካ)

በመጨረሻም ኑእማን አሊ ካን አያይዞም እንዲህ ይላል፡-
«በአሜሪካ ፊትናው ከባድ ነው:: ግና የሰለምቴው ንቃተ ሕሊና ከፍተኛ ነው::

ሙስሊሙ ሐራምና ሐላልን በሚገባ ለይቶ ያውቃል፡፡ እዚህ በአላህ (ሱ.ወ) ሕግ ማቻቻል የሚባል ነገር የለም፡፡ አንዳች ነገር ሐራም መሆኑን ካወቁ ከቤተሰብ ጋር የሚያለያይ እንኳን ቢሆን ለኢስላም ሲሉ ያደርጉታል፡፡,, (ምንጭ፡- ቮይስ ኦፍ ኢስላም - አሜሪካ)

✏️አላዋቂነት ለሁሉም ኃጢአት አብይ ምክንያት ነው፡፡ በተለይ ዝሙት ላይ የድንቁርና አሻራ እጅጉን ይጎላል፡፡ የሰው ልጅ ዓይን ስላለው በጭለማ ውስጥ እንደማያይ ሁሉ ጭንቅላት ስላለው ብቻ ዕውቀት አለው ማለት አይቻልም፡፡ ዕውቀት ከሌለው ደግሞ ድንቁርና መጥቶ እንደ ወቃቢ ይሰፍርበታል፡፡ በርግጥም ከድንቁርና የበለጠ ክፉ ውቃቢ የለም፡፡ ታዲያ የድንቁርና ውቃቢ ያለበት ሰው ቢያንስ በአራት መንገዶች ዝሙት ላይ የወድቃል በአይኑ በምላሱ በእጁ...

🙄እኛ ኢትዮጲያን የነጃሺ ሀገር በአለም ሁለተኛ ሙስሊም የተቀበልን የኢትዮ ግማሽ ፐርንሰት በላይ ሙስሊም ነን ..ዲነኛ ነን ኪታብ ቀርተናል ..መስጊድ ተነካ..ኢስላም ተደፈረ ..ወዘተ በምላስ እንላለን በጎን ዚና እንሰራለን🤔

☞ክርስቲያኖች ኢትዮ የሙሴ ፅላት አለ ..አርባ አራት ታቦት አለ ..ኢትዮ ገማደ መስቀሉ አለ ይሄን ያህል ገዳም አለን ኢትዮ የኛ ናት በጎን ዚና እንሰራለን🤔

ለወደፊት የማዘጋጀዉ ፁሁፍ አዲስ አበባ ከአፍሪካ አንደኛ ከአለም አራተኛ የዝሙት ሀገር መሆኗን በአለም ተረጋግጧል በዚህ ሰፋ ያለ ፁሁፍ ጊዜ ሳገኝ አዘጋጃለሁ፡፡

ግን ኢትዮጲያ አዲስ አበባ ያለዉ ሀይማኖተኛ ሀይማኖት ያለዉ ነዉ ግን ከአፍሪካ 1ኛ የዝሙት ሀገር ነዉ...ኢንሻ አሏህ ስለ አዲስ አበባ  የማይታመኑ 100% እዉተኛ ነገሮች በፁሁፍ ይቀርባሉ፡፡ሀይማኖት በልብም በተግባር ነዉ

ፈጣሪ የምላስ ሀይማኖተኛ አስመሳይ ከመሆን ይጠብቀን፡፡
ከዝሙት እንጠንቀቅ ..በዝሙት መስመር ያለን እንቶብት!!!

#ምንጭ ☞በዝሙት አንዘምን መፅሀፍ



ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
2024/10/01 17:31:01
Back to Top
HTML Embed Code: