Telegram Web Link
.የትምህርት ቤት ጓደኝቼ ነዋል ለምን አታገቢም?? ቆንጆ ነሽ ደግሞም ብዙ የትዳር ጥያቄ መጥቶልሻል ይሉኛል
....የአሁን ወንድ አምኜ ከማገባ እንደ መብራት ፓል ቁሜ ብቀር ይሻለኛል ሆነ የዘወትር መልሴ

ማንኛቸዉም እኔን የሚቀርቡኝ የሴት ጓደኞቼ ነዋል ላገባ ነበር ብላ ካማከረችኝ...አረ ወንድ አትመኝ ..ዛሬ አገባሽ ነገ አብረሽ እንደምትኖሪ እንደማትፋቺ እንዴት እርግጠኛ ሆንሽ ???የአሁን ወንድ እወድሻለሁ አፈቅርሻለሁ ቢልሽ ከአፉ ነዉ ከልቡ አይደለም አትመኝ እያልኩ ክፉ መካሪ ሆንኩ ፡፡ በሰፈር እና በሬፍት ቫሊ ኮሌጅ ተሰሚነት ተቀባይነት ስላለኝ አምነዉኝ ብዙ ጓደኞቼ ትዳር መልሰዋል፡፡ አላህ ይቅር ይበለኝ

እኔ ትዳር የሚባለዉ ጠላሁኝ በጭራሽ ስለትዳርም ማሰብ አልፈልግም..እኔ ለትዳር ያለኝ አመለካከት በጣም የወረደ ሆነ፡፡ደግሞ ትዳር አርአያ ያስፈልገዋል እኔ ሳድግ ከቤተሰቦቼ ያየሁት ሲጨቃጨቁ ሲጣሉ ነዉ እንጂ የቤተሰብ ፍቅር አላየሁም አሁን ድረስ የሚገርመኝ እናት እና አባቴ የመጨረሻዋን እህቴን ከወለዱ ቡሀላ አብረዉ እንኳ ሲተኙ አይቻቸዉ አላቅም፡፡የየራሳቸዉ ክፍል አላቸዉ፡፡
እናትና አባቴ ከመቀያየማቸዉ የተነሳ መኖሪያ ቤት ሲገቡ አሰላሙ አለይኩም ማለት ጎጂ ባህል ነዉ የተባሉ ይመስል አባቴ ሳሎን ከተቀመጠ እናቴ ሌላ ክላስ ነዉ የምትሆነዉ ...ዋ ሳትጣሉ ታድሩና የተባሉ ይመስል በተለያዩ ምክንያት ለምን ዉሀ ቀጠነ በሚል ስበብ ቤቱን በአንድ እግር ያቆሙታል ...
ይወደኛል ያለአንቺ መኖር አልችልም ሲለኝ ከዛም አልፎ እኔን ሊያገባ ሽማግሌ የላከዉም ሚፍታህ እስከ ነመፈጠሬም ረስቶኛል ፡፡ የተማረ ይግደለኝ በሚለዉ የዋህ ህዝብ ባህል አድጌ እንደ ዶክተር ሷሊህ ያለም ሙሁር እሱም ሊያገባኝ ሽማግሌ ልኮ ግን አላማዉ ሌላ ሁኖ እንደዉም የብስ ስለትዳር ተስፋ አስቆረጠኝ ፡፡ ታዳ ስለትዳር ማንን ጥሩ አርአያ ላድርግ??

በኔ በደረሰብኝ በደል ታማኝ ወንድ የለም...ይሄን ስታነቡ ሁሉም ሊያጉመተምት ይችላል እደግመዋለሁ ታማኝ ወንድ የለም ....ወንድ ልጅ ሴትን ህልም እንደሌላት የወንድ ልጅ መጠቀሚያ ብቻ አድርጎ ያስባል፡፡ ሴት ልጅ ስትፈጠር ጀምራ በእሾህ የተከበበች ናት እኛ ሴቶች ግዴታችን እሾሁን እየነቀልን መሄድ ነዉ ..ግን የሚያሳዝነዉ በሴት ዙሪያ የተሰከሰከዉ እሾህ ከሴት ማህፀን የወጣዉ ለሴት ልጅ እዝነት ክብር የሌለዉ አላማዉን የዘነጋ ወንድ ልጅ ነዉ፡፡ ሴት ልጅ በሒወቷ ብዙ ፈተና ችግር መሰናክል ብታሳልፍም ብዙ መስዋአትነት ለሱ ከፍላ አንድ ጎዶሎ ካገኘባት ምን ሁነሽ ነዉ?? በምን ምክንያት ይሆን የተሳሳትሽዉ?? ብሎ ሳይጠይቅ በራሱ አስተሳሰብ ብቻ የሚጓዝ ከሴት በላይ ነኝ ምን ታመጣለች ብሎ የሚያስብ ነዉ፡፡ ከዛም የፈለገዉን ካረገ ቡሀላ ወይም መወደዱን ካረጋገጠ በሴት ልጅ ንፁህ የዋህ ልብ ሞት አፋፍ እንደቀረበች ቁንጫ በእጁ እያፍተለተለ መጨዋት ይፈልጋል..ታዳ እኔ ንፁህ ልቤን ሰጥቼ ተጎዳሁ አይበቃኝም??

በቃ አላገባም ምን እሆናለሁ?? ባላገባ ምን የሚቀርብኝ አለ ?? ከስሜትና ከዘር ማስቀጠል ዉጭ ትዳር ለኔ ምን ይጠቅመኛል ??አግብቼ ማንነቴን የማይቀበል ወንድ ለኔ ምን ይጠቅመኛል??? የሰዉ ልጅ ለስሜት ብቻ ነዉ እንዴ የተፈጠረዉ??? እስኪ ንገሩኝ፡፡ አላማ አለኝ ተምሬ እመረቃለሁ Coc አልፌ ስኮላርሽፕ እማራለሁ ከዛም ...ትልቅ ሰዉ ስሆን ከጎን አንድ ልጅ ያስፈልገኛል.....ልጅ መዉለድ እንኳ ቢያምረኝ ከህፃናት ማሳደጊያ ጉድፈቻ አንዲት ሴት ልጅ ወስጄ አሳድጋለሁ ብየ እራሴን አሳመንኩኝ ይሄ የራሴ አስተሳሰብ ብቻ ነዉ ..ለኔ የምኖረዉ እኔ ነኝ ከዚህም ዉጭ ብዙ ማሰብ እችላለሁ

     ለወንድ ልጅ የተጣመመ የተወላገደ አስተሳሰብ እያለኝ ከካሊድ ጋር በጣም መደዋወል ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ ተቀራርበን ማዉራት ተያይዘነዋል፡፡ ካሊድ ባጃጅ አለዉ ቀን በቀን ትምህርት ቤት በር ላይ እየጠበቀ ከትምህርት ስወጣ ባጃጁን ይዞ መጥቶ እቤቴ ድረስ ይሸኘኛል..

ካሊድን የማደንቀዉ ባህሪ አለ ስራዉን አክባሪ በጣም ጎበዝ ነዉ ሁለት ባጃጅ አሉት አንዱን እራሱ እየሰራ አንዱን ለሹፌር ሰጥቷል.....በጊዜ ብዛት በእነዚህ ባጃጆች ስራየን ሰርቼ ሀይሮፍ መኪና ገዛሁ ሲለኝ በጣምምምም ገረመኝ ፡፡
ስራ አክባሪዋን ታከብራለች ይባላል እዉነት ነዉ ደግሞ ሲኖር ከሰዉ በታች ሁኖ ነዉ እንጂ አለሁ አለሁ ልታይ ልታይ አይልም..ጉረኛም በጭራሽ አይደለም

ካሊድ በተፈጥሮዉ እንከን የሌለዉ ሰዉ ነዉ....መጥፎ አይናገር ሰዉ ጋር አይጣላ በስራ ቦታ ስለ እሱ ሁሉም በጥሩነቱ እንጂ በመጥፎ ማንም የሚያነሳዉ የሌለ ሁሉም ሰዉ ጋር ተግባቢ ነዉ፡፡
....ካሊድ ለኔ 1% እንኳ ባያስቀይመኝም ባያስከፋኝም እኔ ጥሩነቱን ልቤ መቀበል አልቻለም ምክንያቱም ወንድ ማመን ስልችቶኛል ..በተለያዩ ወንዶች የተወጋዉ ልቤ ቆስሏል ገና አላገገምኩም ....በተለይ ደግሞ አፍቅሮ ማጣት እንዴት እንደሚጎዳ ስሜቱን ስለማቀዉ ከካሊድ ለመራቅ ወሰንኩኝ

....ካሊድ ጋር የመጣያ መንገድ ማፈላለግ ጀመርኩ ..እሱ የሚሰራበት አካባቢ የባጃጅ ፌርማታ የሚቆምበት ቦታ እየሄድኩ..መቼም የባጃጅ ሹፌር ስራቸዉ ሴት ጋር መጃጃል ሶስት እግር ሲይዙ ከእነሱ በላይ ሰዉ ያለ አይመስላቸዉም ..ብዙዎቹ ከትርፉ ላይፉ እያሉ ነዉ ባጃጅ ገዝተዉ ስራ የሚጀምሩት፡፡ ታዳ የአሁን ዘመን ሴቶች ሁለት ወይ ሶስት ብር ትራንስፓርት ሸኘሁሽ አልቀበልሽም ሲላት በአዉሮፕላን በሌላ ሀገር የሸኛት ይመስል ተደስታ በዚህ ሶስት ብር ዉለታህን አረሳም ብላ ዉለታዋን ለባጃጅ ሹፌር የፈለገዉን ክብሯን አሳልፋ ስትሰጥ እያየን ነዉ..አይ ሴትነት በሁለት በሶስት ብር ብለሽ ሹፌር ያዝናናል ነጋዴ ጊዜ የለዉም እያልሽ በረከሱ ሹፌሮች ማንነትሽን አታርክሺ....እኔም ካሊድ እንደነዚህ አይነት የባጃጅ ሹፌሮች ቢሆን ብየ ለመጣላት ስለሚያመች የተለያዩ ሰዎችን ስለእሱ ባህሪ በተለያዩ ዘዴ ለማዉጣጣት ብሞክር የእሱን መጥፎ ጎን የሚነግረኝ አንድ ሰዉ እንኳን አጣሁ፡፡

ካሊድ መጥፎ ባህሪ አለበት ሴት ጋር ይሄዳል የሴት ጓደኛ አለዉ ወይ ጫት ይቅማል ወይ ሲጋራ ያጨሳል የሚል አጣሁ...በምን ምክንያት ልጣላዉ ???
ካሊድ ሲደዉልልኝም አዉቄ እንዲናገረኝ ተናግሬዉ እንዳስቀይመዉ እያልኩ መጥፎ ቃላቶች ስናገረዉ እሱ በኸይር ነዉ የሚመልስልኝ....ብዙ ከካሊድ መራራቂያ ዘዴ በተለያየ ምክንያት ከዉሸቱም ከእዉነቱም እየደባለኩ ብናገረዉ ካሊድ በጭራሽ ሊርቀኝ አልቻለም...እኔም እሱን የምጣላበት ምክንያት አጣሁኝ.... ወላሂ ሱመወላሂ ካሊድን አንድ ጥፋት እንከን ባገኝበት ልርቀዉ 100% ወስኛለሁ ግን በጭራሽ እንዴት ጥፋት ላግኝበት?? አልቻልኩም

ካሊድ በስልክ ደዉሎ እንደዚህ አለኝ
...ነዋል ከቤተሰቦቼ ወጥቼ #ቤት_ተከራይቼ_ብቻየን_መኖር_ጀመርኩኝ አለኝ



#ክፍል 2⃣1⃣

ይ........ቀ.........ጥ
...........ላ.........................ል


          `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሀያ አንድ 2⃣1⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




..ነዋል ከቤተሰቦቼ ወጥቼ #ቤት_ተከራይቼ_ብቻየን_መኖር_ጀመርኩኝ አለኝ


በሌላ ቀን ሲደዉልልኝ ለቤቱ የገዛዉን ይነግረኛል .አንድ ቀን ቡፌ ገዛሁ ሌላቀን ቴሌቪዢን አረ ብዙ ነገር እያሟላ እንደሆነ ይነግረኛል፡፡ እኔንም በተለያዩ ቅኔዎች እንደሚወደኝ ይነግረኛል..ለምሳሌ አንቺን የመሰለ ልጅ ፈልጊልኝ ይሄ ቤት ብርድ ብርድ አለኝ ሀላሌ ናፈቀችኝ...ወይም እቃዉ ቤቱ ተሟሏ ምሳ
ቁርስ አዘጋጅታ እንብላ የምትል ጠፋች....ቤቱ ሙድ እየያዘብኝ ተቸገርኩ ብቻየን ሊወረኝ ነዉ...አንዳንዴም የገዛሇቸዉ የቤት እቃዎች ሳልጠቀምባቸዉ ሸረሪት ድር አደራበት እኮ ማን ይስራበት...እያለ በተለያየ ዘዴ እንደሚወደኝ እና በዘዴ እኔን ማግባት እንደሚፈልግ እየነገረኝ ይመስለኛል ባልሳሳት...ግን እንጃ ደግሞ የወንድ ፍቅር ከአፍ መች ያልፋል

ዘንድሮ መመረቂያ አይደል አፓረንት መዉጣት ግድ ነበር ከጂማ የሶስት ሰአታት መንገድ የሚሆን ሰካ የምትባል ገጠራማ ቦታ ጤና ጣቢያ ለሶስት ወር ጊዜ ወጣሁኝ እዛዉ ለ3ወር ቤት ጓደኞቼ እኔ መፍቱሀ እና ብሩክ ታይት ጋር አንድ ላይ ቤት ተከራይተን መኖር ጀመርን ፡፡ ላለመደዉ ሰዉ በጣም ይከብዳል በግድ አገሩን ተላመድኩት፡፡አይ ዱንያ
★★★ነብዩላህ ኑህ (ዐ.ሰ) ሊሞቱ በተቃረቡበት ጊዜ የሚከተለዉ ጥያቄ ቀርቦላቸዉ ነበር፡-እረጅም እድሜ የታደሉት ነብይ ሆይ!!!!ይህን አለም እንዴት ተመለከቷት??
ኑህ (ዐ.ሰ)ለዚህ ጥያቄ መልስ ሲመልሱ ""ሁለት በሮች እንዳሉት ቤትና በአንዱ በር ገብቼ በሌላዉ በር የወጣሁ ያክል ሆና ነዉ ያገኘሆት .የሚል ምላሽ ሰጥተዋል
★★★ነብዩላህ ኑህ (ዐ.ሰ)ለራሳቸዉ በቀርቀሀ አነስተኛ ጎጆ ቀልሰዉ ነበር የሚኖሩት
ከዚህ የተሻለ ጠንካራ ቤት መስራት እየቻሉ..ለምን በዚህ ደካማ ጎጆ ዉስጥ ይኖራሉ ? ተብለዉ ሲጠየቁ
ነገ በሞት ይችን አለም ለሚለቅ ሰዉ ይህ ራሱ ሲበዛበት ነዉ ብለዋል፡፡
ዱንያ የዚህን ያህል ጭንቀት ደስታ ይፈራረቅብናል እንጂ የዚህን ያህል የሚጓጓላት ለሚኖር የሚናፈቅባት አይደለችም.. አላህ ልቦና ይስጠን!!!!!


አፓረንት ላይ ሁኜ ከካሊድ ጋር እናወራለን
...ሆስፒታሉ አንድ ቀን አዳር አንድ ቀን ደግም በቀን ነበር ተመድቤ የምሰራዉ፡፡
እዛ ስንሰራ አዳር እንቅልፍ እንዳይዘኝ ካሊድ ይደዉልልኛል አኩለ ለሊት እስኪያልፍ ስናወራ እናመሻለን ...ጉድ ነዉ ካርዱ ተገዝቶ መሆኑን እረስተን ከምንጭ ተጠልቆ የተሞላ ይመስል ትዝ አይለንም ፡፡


ካሊድ በሶስት ቀን ልዩነት ከጂማ ምግብና የሚጠጡ የተለያዩ ነገሮች ይዞልኝ ይመጣ እና በሩቁ ሰላም ናችሁ አብሽሩ ብሎን ይመለሳል፡፡ ካሊድ በስልክ ነዉ እንጂ ዘና ብሎ የማያወራኝ በአካል ስንገናኝ እንደተደገመት ሰዉ አፉ ይያያዛል ቶሎ ለመሄድ ነዉ የሚቸኩለዉ . ነዋል አብሽሪ አትፍሪኝ የምፈልጊዉ ከጂማ የሚመጣ ነገር ካለ ንገሪኝ ..እኔም እየመጣሁ አያችሇለሁ በሉ ቻዉ ብሎን ይሄዳል፡፡

ካሊድ እነዚህን ሶስት ወራት እየመጣ ገጠር ድረስ አይቶኝ አንዳንድ ነገር ይዞልኝ ይመጣል...በስልክም ማታ እንቅልፌ እንዳይመጣ እዛዉ ጤና ጣቢያ ሁኜ አሱ ጋር እያወራን እኩለ ለሊት ያልፋል፡፡፡

በዚህ ሶሰት ወራት አዲስ ነገር ተፈጥሯል ጓደኛችን ብሩክ ታይት በመፍቱሀ ምክር ደአዋ በፊትም ልቧ ወደ ኢስላም ያዘነበለ ነበር እስልምናን ተቀበለች በጣም ደስ አለን፡፡ እሷም ሙስሊም መሆኔን ለቤተሰቦቼ ሳልዉል ሳላድር ማሳወቅ አለብኝ አለችን..
ቆይ ተረጋጊ በሒደት ትነግሪያቸዋለሽ አሁን እስልምናን በደንብ እወቂ ብንላት
..ብሩክታይት ልንገራቸዉ እና ይለይልኝ ቤተሰቦቼ ከኢስላም ሀይማኖት አይበልጡብኝም ብላ እኛ ተረጋጊ ብንላት ልትሰማን አልቻለችም ... ለእናት እና ለአባቷ ስትደዉል...የገጠማት የማይታመን ነበር ሙስሊም ከሆንሽ እቤት እንዳትመጪ ብለዉ የወለደ አንጀታቸዉ ቆራጥ አመራር ገጠማት.እኛም ጭንቅ ጥብብ አለን ፡፡መፍቱሀም አትሰቢ እኔ ጋር ትኖሪያለሽ አብሽሪ አለቻት



አፓረንታችንን 3ወር ያህል ጨርሼ ተወልጄ ወደ አደኩበት አባጅፋር ሀገር ጂማ ከተማ ተመለስኩኝ ፡፡ ብሩክታይትም መፍቱሀ ቤተሰቦች ጋር አብራ መኖር ጀመረች
ከተመለስኩ ጀምሬ ካሊድ ጋር በስልክ እያወራን ነዉ....ሀሙስ ቀን እንደዚህ አለኝ

ነዋል ነገ ከጓደኛሽ መፍቱሀ ጋር አብራችሁ መጥታችሁ ችብስ ትወጅ የለ እንዴ ልጋብዛችሁ አለኝ
...እንደዚህ ሲለኝ የዶክተር ሷሊህ ትዝታ አእምሮየ ላይ ብልጭ አለብኝ
እሺ መልሼ እደዉልልሀለሁ ብየ ስልኩን ዘጋሁት..

ካሊድ ችብስ ልጋብዝሽ ያለኝ ችብስ በጣም እንደምወድ ስለሚያቅ ነዉ፡፡ አፓረንት ገጠር በወጣንበት ጊዜ ለራሱ ሲመጣ ይዞልኝ ይመጣ ነበር
..... .....ደዉየ መፍቱሀን ሳማክራት ምን ችግር አለዉ የምንሄደዉ አብረን ነዉ  እንሄዳለን አለችኝ

መፍቱሀ ሁሌም ቢሆን ካሊድ ጋር እንድቀራረብ ጥረት ታደርጋለች...ለኔ ጥሩ ነገር ነዉ የምታስብልኝ ..ሁሌም ቢሆን ሚፍታህ ጋር በምናወራ ጊዜ መፍቱሀ እንዲህ ትለኛለች....#ሚፍታህ_የጀመረሽ_ትዳር_ፈልጎ_ሳይሆን_ጓደኛዉ_አንቺን_ዳረኝ_ስላለዉ_አንቺን_ለማግባት_እልክ_ይዞት_ነዉ፡፡ ብላኝ ነበር ፡፡ መፍቱሀ እዉነቷን ነዉ...ብዙ ጊዜ ሚፍታህ ጋር የነበረንን ግንኙነት አልወደደችዉም ግን በፍቅር መሀል ጣልቃ አልገባም ብላ ትታን ነዉ፡፡ በፊት ጀምራ ታያለሽ አንቺ የካሊድ ነሽ እሱ ነዉ ባልሽ  ፡፡ አንቺን የሚወድሽን የሚጠቅምሽን እኔ ነኝ የማቀዉ ትለኛለች.... እኔ ግን ካሊድ ጋር ትዳር የማይታሰብ ነዉ ፡፡ ግን ለኔ በዚህ ጭንቀቴ መፍቱሀን የመሰለች ጓደኛ ፈጣሪ ባይሰጠኝ ምን ይዉጠኝ ነበር??? ፡
  ካሊድ ደዉሎ ግብዣየን ተቀበልሽኝ ወይስ አልተቀበልሽኝም?? አለኝ
.....እኔም እሺ ተቀብያለሁ አልኩት
.....ካሊድ በጣም ደስ አለዉ

የማይደርስ የለም የሀሙስ ለሊት ለጁምአ ቀን አስረከበች ከዛም ከኡስር ቡሀላ ካሊድ መኪናዉን ይዞ እኔ እና መፍቱሀን ይዞን ሊጋብዘን ጉዞ ጀመርን....እየሄድን ማንም የሌለበት ሰዉ የማይበዛበት ቦታ ዉስጄ ልጋብዛችሁ አለኝ
.....እኛም እሺ አልነዉ

ከዛም እልም ያለ ገጠር ዉስጥ ዛፍ አዋፋት የበዛበት ማንም ሰዉ የሌለበት ቦታ ወሰደን፡፡ ከመኪናዉ ወረድን ተቀመጥን ....ያለነዉ ሶስታችን ነን ወሬ ማዉራቱን ተያያዝነዉ...

በወሬያችን መሀል ካሊድ  እንደዚህ አለን......መፍቱሀ...እኔን ነዋል ብዙ ነገር በድላኛለች ..እሷ የበደለችኝን ነገር እሷ ባለችበት ለአንቺ ልንገርሽ እና ቅጣት እንድትቀጣልኝ እፈልጋለሁ አለ..
መፍቱሀም እሺ ተናገር አለችዉ
.....እኔም ካሊድ አንተን በድየህ አስቀይሜህ አቃለሁ እንዴ ???አልኩት
....አዎ ብዙ በድለሽኛል ነዋል አለኝ
....ምን ምን በድየሀለሁ ?? አልኩት

እሱም እንደዚህ አለኝ>>>>>>በሒወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ለትዳር ስጠይቅሽ አልፈልግህም አንተን ማግባት አልፈልግም ስትይኝ ለሁለት ወር ያህል አሞኝ ስራ መስራት አልቻልኩም ነበር አለኝ<<<<<
.....እኔም መታመምህን   በምን አቃለሁ??? አልኩት👇👇👇
ካሊድም ቀጠለ ....እሺ ሌላኛዉ ደግሞ ስደዉል ብዙ ጊዜ ስልክ አታነሺም፡፡ አንስተሽም ቡሀላ እደዉላለሁ ነበር የምትይኝ ..ስፈልጊ ስልኬን block ታረጊኝ ነበር..text ስልክልሽ አመልሽም ... መንገድ ላይም ፊት ትነሺኝ ነበር ...እያለ በደሉን በአንዴ ዘረገፈዉ ኮሌጅ መማር ከጀመርኩ  ጀምሮ የሶስቱንም አመቱን ብሶቱን አንድ ባንድ ነገረኝ ...
ከዛም አንቺስ ይሄን አድርገህኛል ይሄ ጥፋት አለብህ የምትይኝ አለ ?<?<? ንገሪኝ አለኝ
.....,እኔም የምለዉ የምመልሰዉ ሳጣ ምንም አላረከኝም ላለማለት አንድ ቀን callme back ልኬልህ እንድደዉልልኝ ፈልጌ አልመለስክልኝም አልኩት
......እሱም ሳቀ

መፍቱሀም ጥፋተኛ እሷ ናት ምን እንድትቀጣ ነዉ የምፈልገዉ ??? አለችዉ
ካሊድም >>>እኔ ልቤን ሰጥቻት ልቤን ጣለችብኝ ልቤን ከጣለችበት አንስታ ትስጠኝ<<<አለ

በጣምምም ደነገጥኩ ካሊድ እንደዚህ ይላል ብየ አስቤም ትዝም ብሎኝ አያዉቅም
.....እኔም እንዳልገባኝ ለማስመሰል ምን ለማለት ፈልገህ ነዉ ??አልኩት
...መፍቱሀ ሰምተሻል በአንቺ ቤት ማደናቆርሽ ነዉ??.. ልቤን ሰጥቻት ጥለዋለች ብሏል ከጣልሽበት ሂደሽ ፈልገሽ አምጪ አለችኝ

....እኔም ወደ ካሊድ ዙሬ ምን ለማለት ፈልገህ ነዉ?? ንገረኝ ዙሪያ ጥምጥም አትሂድ እያልኩ ፍጥጥ አርጌ ያዝኩት
.....ካሊድም ነዋል ዛሬ ተረጂኝ እባክሽ ከልቤ እወድሻለሁ አፈቅርሻለሁ ፍቃደኛ ከሆንሽ ላገባሽ እፈልጋለሁ  ልትመረቂ ሁለት ወር ነዉ የቀረሽ...,ታስታዉሽ እንደሇነ ገና ኮሌጅ ሳትመዘገቢ ላግባሸ ስልሽ አሁን መማር እፈልጋለሁ ነዉ ያልሽኝ...አሁን ትምህርት ጨሬሰሻል የቀረሽ የምረቃን proces ብቻ ነዉ
.....ስለዚህ ላገባሽ እፈልጋለሁ እና ፍቅሬን ተቀበይኝ ...በዚህ ሁለት ወር ዉስጥ እንግባባ ስለ እኔ ማጣራት የምፈልገዉ ነገር ካለ ከማንኛዉም ሰዉ ማጣራት ትችያለሽ ..,እኔ ግን ስለአንቺ ምንም የማጣራዉ የምጠይቀዉም የለም ዛሬም ነገም ብትይኝ አንቺን ለማግባት ዝግጁ ነኝ..,አለኝ

....እኔም ከአነጋገሩ እምቢ የምልበት ድፍረት አጣሁኝ.... አስቤበት ይሁን በድንጋጤ አላወኩትም ከአፌ ግን እሺ የምትል ሁለት ቃላት ተነፈስኩኝ

ካሊድ በጣም ደስ አለዉ የዛን ጊዜ የተደሰተዉ ደስታ በቃላት መግለፅ አልችልም ቁጭ ብድግ ነዉ እያለ የሚያወራዉ ጠፍቶታል፡፡ የሚያወራዉ ሲያጣ በቃ የዛሬ ሳምንት ጁምአ ምሳ ሰአት እንገናኛለን አለኝ
.....እኔም ኢንሻ አላህ አልኩት
ወደ ጂማ ከተማዉ ሳይመሽ ተመለስን...እቤቴ ድረስ በመኪና ሸኝቶኝ ተመለሰ፡፡



     እቤቴ ከገባሁ ቡሀላ እንደገና የረሳሁትን ማሰብ የማልፈልገዉ የአእምሮ ጥያቄ እየመጣ ያቃጭልብኝ ይዟል... መጨነቅ መጠበብ ሆነ ካሊድ ድንግል ነሽ ወይስ አይደለሽም ?? ብሎ ቢጠይቀኝ ምንድን ነዉ መልሴ??...እንዴትስ ነዉ የማስረዳዉ ???እያልኩ ስጨናነቅ እንቅልፍ በአይኔ ሳላይ አደርኩኝ.....

የማይነጋ ለሊት የለም ጨለማ ለፀሀይ ቦታዋን አስረከበች ወደ ትምህርት ቤት ሄድኩ ዘንድሮ ተመራቂ ስለሆንኩ coc እንዳልወድቅ ዝግጅት እያረኩ ነዉ.... ግን ካሊድ ይደዉልልኛል፡፡ በነዚህ ቀናት ዉስጥ በቀን ዉሰጥ በትንሹ ደወለ ከተባለ ቢያንስ 5 ጊዜ ሳይደዉል ቀርቶ አያቅም ፡፡
......እኔ ካሊድ ጋር ስናወራ ከበፊቱ ጀምሬ የምፈራዉ በማንነቴ ነዉ ..ሁሌም ሀሳቤ በዚህ ማንነቴ መጣላታችን አይቀርም እያልኩ አስባለሁ ፡፡ እንዴት እኔን ሊረዳኝ ይችላል??

ካሊድን እሺ ካልኩ ቡሀላ እንደ በፊቱ መጨናነቅ ይዣለሁ ...ካሊድን እንዴት ልራቅ??? ማንነቴን ላይቀበለኝ ይችላል እያልኩ ሳስብ ጨጓራ አለብኝ በጣም አመመኝ በሁለት ቀን ልዩነት ሀኪም ቤት እስከ መሄድ ደርሻለሁ.... ካሊድም ምን ሁነሽ ነዉ ያመመሽ ??ተሻለሽ ወይ ??እያለ በየሰአቱ ነበር የሚደዉለዉ....መልስ የሌለዉ ጥያቄ እንዴት ልመልስ በሆዴ ታምቆ ተቀምጧል...ካሊድ ቀላል ህመም ነዉ ይሻለኛል ብየ እመልስለታለሁ ......
ለዉጥ ሲኖረኝ ወደ ክላስ ሂጄ ለCoc ዝግጅት አደርጋለሁ፡፡

እንደዚህ እያለ ሳምንቱ አልፎ ጁምአ ደረሰ ... ካሊድ የጠራኝን ምሳ እረስቸዋለሁ ትምህርት አልገባሁም.. ጁምአ ለመስገድ ቀደም ብየ አጅፕ መስጊድ ገብቼ ቁርአን  ቀራሁ....ከዛም ጁምአ ተሰግዶ እንደጨረስን ....መፍቱሀ እኔም በተጨማሪ ሌሎች ሶስት ጓደኞቼ ጁምአ ጁምአ ምሳ የምንበላዉ አንድ ላይ ነዉ፡፡ በየተራ ሁላችንም እቤት እያዘጋጀን ዛሬ አንዷ ቤት ሳምንት ሌላ የጓደኛችን ቤት የእኔ ተራ ሲሆን እኛ ቤት እያልን ጁምአን ምሳ እንደዚህ ነዉ የምናሳልፈዉ...

ከዛም እኔ የካሊድን ቀጥሮ ረስቼ  መፍቱሀ ቤት ሆድኩ ፡፡ የሄድኩበትም ምክንያት የጁምአ ምሳ ተረኛ የሆነችዉ ጓደኛችን ቤት አብረን ለመሄድ ነዉ፡፡
መፍቱሀ ቤት እንደ ደረስኩ ...እሷ የምልብሰዉ በጣም የሚያምር ጅልባብ አምጥታ ይሄን ልበሽ አለችኝ
....እኔም ሰርግ ነዉ እንዴ የምንሄደዉ?? አልኳት...
ብዙ ጊዜ ብዙ ሰዉ ይሄን ጅልባብ ስለብሺ ያምርብሻል ይሉኛል እኔም ሰርግ ሲኖረኝ የመፍቱሀን ጅልባብ ነዉ የምለብሰዉ
.....እሷም ጅልባቡን ልበሽ ከሰርግ በላይ ነዉ አለችኝ

ባጃጅ ገብተን እየሄድን...ካሊድ ደወለልኝ
..... የኔ ፍቅር እየመጣችሁ ነዉ ??? አለኝ
.........የት ነዉ የምንመጣዉ ?? አልኩት
....እሱም እኔ መኖሪያ ቤት አለኝ
ከዛም ተናድጄ ጆሮዉ ላይ ስልኩን ዘጋሁት


ከዛም መፍቱሀን እወንድ ቤት ነዉ እንዴ የምወስጂኝ ?? የሷሊህን ገጠመኝ ነግሬሽ እንዴት ትወስጂኛለሽ ??መፍቱሀ አሳልፈሽ ልሰጪኝ ነዉ እንዴ?? እያልኩ ባጃጅ ዉስጥ ሁኜ አለቀስኩኝ

መፍቱሀም ነዋል ተረጋጊ ምንም አትሆኝም ድብቅ ሚስጥር የለዉም ...እህቶቹ ምሳ አዘጋጅተዉ እየጠበቁን ከእነሱ ጋር ሊያስተዋውቅሽ ነዉ እንጂ ለሌላ አይደለም አለችኝ

ካሊድ የመጨረሻ ልጅ ነዉ ፡፡ ያገቡ ልጅ ያላቸዉ ታላቅ እህቶች አሉት ...ብዙ ጊዜ ስለእህቶቹ ስለነገረኝ እሺ ብየ ተረጋጋሁ እና እንባየን ጠረኩኝ ፡፡


ካሊድ መኖሪያ ቤት እንደደረስኩ ያየሁትን ማመን አቃተኝ ሰርፕራይዝ ነዉ የሆነብኝ ፡፡ የሒወቴ የመጀመሪያ የደስታ ጊዜ ይቺ ቀን ናት ብየ መናገር እችላለሁ የዚህን ቀን ደስታ ወላሂ መናገር አልችልም...አባቴ እኔን የተለያዩ ቦታ ወስዶ አዝናንቶኛል ...ግን የዚህን ቀን ደስታ እሩብ እንኳ አያክልም ...

ገና እቤቱ በር ላይ ስደርስ መፍቱሀ አይኔን አሰረችኝ
....እኔም ደነገጥኩኝ ምንድን ነዉ መፍቱሀ እየተፈጠረ ያለዉ ነገር አልገባኝም?? አልኳት
....መፍቱሀም በሂደት ይገባሻል አለችኝ...የካሊድ አንዱ እህቱ Video እየቀረፀችኝ ነዉ፡፡

መፍቱሀ እጄን ይዛኝ ፤ አይኔ እንደተጨፈነ ወደ ዉስጥ ገባሁኝ ...የቤቱ ሳሎኑ  በጣም ሰፊ ነዉ

ካሊድ እንዲህ አላት:- መፍቱሀ አሁን አይኗን ግለጫት አላት
-------መፍቱሀም አይኔን ገለጠችኝ .....ያየሁትን ማመን አቃተኝ እንደዚህ አይነት ሰርፕራይዝ በፊልም ለራሱ አይቼዉ አላቅም እንኳን በኔ ሒወት ከፊልም በላይ ነዉ የሆነብኝ
#ክፍል 2⃣2⃣
ይ ...........ቀ........
.......,ጥ...........ላ..............ል


JOIN
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሀያ ሁለት 2⃣2⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ



------መፍቱሀም አይኔን ገለጠችኝ .....ያየሁትን ማመን አቃተኝ እንደዚህ አይነት ሰርፕራይዝ በፊልም ለራሱ አይቼዉ አላቅም እንኳን በኔ ሒወት ከፊልም በላይ ነዉ የሆነብኝ

ቤቱ በዲምላይት እና በዲኩሬሽን አሸብርቋል በየመሀሉም ILOVE YOU NEWAL የሚል ወረቀቶች ተለጥፈዋል፡፡ ኬኩ ላይ ለራሱ ነዋል ሁሌም እወድሻለሁ ልታገቢኝ ፍቃደኛ ነሽ ወይ?? የሚል አፅፎበታል...ቸኮሌቱ ፍራፍሬዉ ተሰናድቷል ...በየቦታዉ ሻማ ተደርጓል  ከምነግራችሁ በላይ ቤቱ አሸብርቋል

ቤቱ ዉስጥ ከገባሁ ቡሀላ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ቁሜ ቤቱ ማሸብረቁ ድባቡ ለአይኔ አዲስ ሁኖበት ገርሞኝ እንደቆምኩኝ አየዉ ይዣለሁ ...ወላሂ ህልም ህልም ነዉ የመሰለኝ አይኔን ብገልጠዉ ብጨፍነዉ ነገሮች ሊቀየሩ አልቻሉም እዉነት ነዉ ብየ ከመቀበል ዉጭ.... ይሄ ሁሉ ለኔ ዝግጅት በጭራሽ ሊዋጥልኝ አልቻለም በጣም አጀበኝ እንዴት ቤቱ አምሯል በአላህ .....

ቁሜ እየተገረምኩኝ እየተአጀብኩኝ ካሊድ መጥቶ በጉልበቱ ተንበርክኮ
.....ነዋል የኔ ፍቅር በጣም እወድሻለሁ ግዙፍ  ሶስት አመት ያህል ታግሼ ጠብቄሻለሁ ...ወላሂ ብየ ነዉ የምነግርሽ ሶስት አመት ያህል ለሊት እየተሳሁ እየሰገድኩ ነዋልን ለኔ አድርጋት እያልኩ አልቅሻለሁ ከአሁን ቡሀላ አመታትን እንኳ ይቅር አንድ ሳምንት አንቺን አጥቼ መኖር አልፈልግም  .....ልታገቢኝ ፍቃደኛ ነሽ ወይ ???? አለኝ

......ካሊድ ተንበርክኮ እንደዚህ ሲለኝ ማመን አቃተኝ ተገረምኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ተንበርክኮ አግቢኝ ሲለኝ ____አረ ሌሎችም ወንዶች ብዙ የትዳር ጥያቄ ሲመጣ ማንም ተንበርክኮ ጠይቆኝም አያቅም የካሊድ ግን ገረመኝ

እኔ በጣም ደስ አለኝ እንደዚህ ያለ ፍቅር ወላሂ ምኞቴ ነዉ ግን በማንነቴ እፈራለሁ.....ምን እኔ ብቻ ብዙ ሴቶች እንደዚህ አይነት ምኞታቸዉ ነዉ ይሄን በህልማቸዉ የሚያዩትን የፍቅር ምኞታቸዉን ለማሳካት በሀራም መንገድ በር ሲከፍቱ ይስተዋላላሉ ....ካሊድ ተንበርክኮ ሲጠይቀኝ እምባየ ቀደመኝ

እምባየ በቆምኩበት ጭንቅ ጥብብ እያለኝ እየተወዛገብኩ በጉንጮቼ በሁለት ረድፍ ኮለል እያሉ እየወረዱ ነዉ ጭንቀቴም እኔን እስከማንነቴ ይቀበለኛል ወይ ??? ይሄን ሁሉ ሰርፕራይዝ ይሄ ሁሉ ፍቅር ለኔ እየገለፀልኝ እኔም እሺ ብል ቡሀላ ስነግረዉ ካሊድ ከነማንነቴ ባይቀበለኝስ ?? ግራ ተጋባሁ ...አሁን ዉሳኔዉ ለዛሬዉ ደስታ ሳይሆን የወደፊት ደስታየን አያደፈርስም ወይ ??ነዉ......
ማንነቴን ይቀበለኛል ወይስ አይቀበለኝም ??"

በሀሳብ ዉስጥ ሁኜ ለካሊድ ...እንዲህ አልኩት...

#ግን_እኔን_ከልብህ_ትወደኛለህ ??? አልኩት
.......ካሊድም:- ነዋል ወላሂ ከልቤ እወድሻለሁ በፊት እንደዛ ፊት ስትነሽኝ ስታስቀይሚኝ ለራሱ አልጠላሁሽም ..እንኳን ልጠላሽ ፍቅርሽ ጨመረብኝ እንኳን ዛሬ ከፊለፊቴ ሁነሽ አለኝ...

እኔም የምመልሰዉ የማወራዉ ግራ ገባኝ ከዝምታ ዉጭ መልስ አጣሁ
....ካሊድም ዝም ብለሽ ቆየሽ እኮ ዉሳኔዉን ንገሪኝ??? እምቢ ልትይ ነዉ እንዴ??? አረ ተንፍሺ በሀሳብ ጨረሽኝ እያለ ሲያወራ እምባ ተናንቆታል፡፡

.......እኔም እሺ ፍቃደኛ ነኝ እንጋባለን አልኩት፡፡
ካሊድ በጣም ደስ አለዉ እህቶቹም እልልታዉን አቀለጡት ፡፡ ቀለበት ገዝቶ ይዞታል ...አንድ ቀን እንኳ ከካሊድ ጋር እጅ ለእጅ ተነካክተን አናቅም  ..ካሊድ ጋር ቀጥ ብሎ አይን ለአይን ተያየን ፡፡ ለመፍቱሀ እንኪ ቀለበቱን አድርጊላት ብሎ ሰጣት....መፍቱሀም ቀለበቱን አደረገችልኝ እህቶቹ በእልልታ ቤቱን አደመቁት

ከዛም ካሊድ ቆይ መቼ ጨረስን ...ነዋል ለኔ ቀለበት አታረግልኝም እንዴ ??? አለ
......እኔም ደንግጬ ካሊድ እኔ እኮ ምንም አልገዛሁም እዚህ ስመጣ ይሄ ይሆናል ብየ አልገመትኩም አልኩት
.....ካሊድም እየሳቀ ችግር የለዉም እኔ ገዝቻለሁ ብሎ ሰጠኝ....ከዛም ቀለበቱን እጁ ላይ ሳንነካካ አስቀመኩለት እሱም ጣቱ ላይ አደረገ

እኔ እና ካሊድ አንድ አይነት ቀለበት አደረግን፡፡ እህቶቹ በየተራ እየመጡ በደስታ ተጠመጠሙብን እንደ ህፃን ልጅ ሳሙን፡፡ ምሳ ዝግጅት በየአይነት ምግብ ተዘጋጅቶ ነበር እህቶቹ እያጎረሱኝ እየተሳሳቅን እየተጨዋወትን ምሳ በላን

ከዛም ኬኩን እኔዉ ቆርሼ በላን.... ከጁምአ ሶላት ቡሀላ የጀመርን እስከ መቅሪብ ሊደርስ አካባቢ ድረስ እህቶቹ ጋር ሁላችንም ሰንጨዋወት ደስ የሚል ጊዜ አሳለፍን፡፡


ከካሊድ ቤት ወደ መኖሪያ ቤቴ ተመለስኩኝ.... እቤት ስመለስ ይሄዉ በሽታየ ጀመረኝ ብቻየን መጨናነቅ ለካሊድ እንዴት ነዉ በልጅነት መደፈሬን የምነግረዉ ??? እያልኩ ብቻየን ሳስብ ሳስብ የማልገፋዉን የተራራ ቁልል ሀሳብ ብቻየን በአእምሮየ ሳመላልሰዉ አደርኩ

ጭንቀት ሳበዛ ጨጓራየን ያመኛል ምግብም አልወስድም ሲያስታዉከኝ አደረ.....

የሚገርማችሁ ነገር እኔ ካሊድን እወደዋለሁ ግን ልቤ ሰፍ አይልለትም....በጣም እንደሚወደኝ እንደሚያፈቅረኝ አዉቃለሁ .....እኔ ደግሞ ይናፍቀኛል እወደዋለሁ ከእሱ የሆነ ነገር እጠብቃለሁ ግን አላፈቅረዉም ፡፡ እንዴት እንደምገልፀዉ ግራ ይገባኛል አንዳንድ ሴቶች ይሄን ልጅ ሳየዉ ልቤ ሰፍ ይላል ልቤ ይርገበገባል ይላሉ ..እኔ ደግሞ ለካሊድ እንደዚሁ ነኝ ሁሌም እወደዋለሁ ግን ለእሱ  ልቤ ሰፍ አይልም፡፡ እኔ ይሄን ፍቅር ስተረጉመዉ ካሊድን የወደድኩት በአእምሮየ ነዉ እንጂ በልቤ አይደለም ይመስለኛል፡፡እናንተ እንደዚሀ አይነት ፍቅር ገጥሟችሁ ያቃል ??? የገጠመዉ የሚያቀዉ ሊረዳኝ ይችላል

  ሁሌ ጁምአ ከአሱር ቡሀላ እዛ እገጠሩ ቦታ ሰዉ የሌለበት እየሄድን እናወራለን ይሄ ፕሮግራማችን ሆነ  ፡፡ እንደ ዘንድሮ ፍቅር ጎን ለጎን ሁኖ እወድሻለሁ አበድኩልሽ..ልሳምሽ ልንካሽ በጭራሽ የለም፡፡
 ቁም ነገር ነዉ የምናወራዉ ካሊድ ደስታዉ እኔን ማየቱ ብቻ ነዉ

    ቀለበት ካረገልኝ ቡሀላ ካሊድ ፍቅሩ ከበፊቱ ባሰበት፡፡ ጠዋት ማታ መደወል ስለትዳር ማዉራት ሁኗል ወሬዉ እስከምንገባ በጣም ቸኮለ
..እኔ ደግሞ ማንነቴ አስጨነቀኝ በጣም በስቃይ በለቅሶ በዱአ ላይ ነኝ ...ካሊድ ሲደዉል እስቃለሁ ደህና ነኝ እላለሁ ..ግን ስልኩን ሲዘጋዉ የማይጠፋ እሳት ሆዴ ዉሴጥ ተለኩሶ በእንባየ የሚጠፋ ይመስል አለቅስ ይዣለሁ፡፡ ደግሞ ትምህርት ቤት እና በየመንገዱ ደስተኛ ነኝ ፊቴ ዘና ብሎ ጥርሴ መሳቅ አመሉ ነዉ....አይ ጥርሴ የልቤን ብታየዉ እንኳን መሳቅ ከነጭነት ወደ ጥቁርነት በተቀየርኩ ባልከኝ እንኳን እኔን ከፍቶኝ አይኔ ሲያለቅስ ጥርሴ ግን በልቤና በእምባየ እየቀለደ ይመስል ፈገግ ይለዋል፡፡

  ወላሂ ብየ ነዉ የምነግራችሁ ሰዉ ሁላ ዘመድ ጎረቤት ጓደኞቼ ቀለበቴን ሲያዩት በደስታ ፣ መቼ ነዉ ሰርግሽ ??? የማይለኝ የለም ፡፡ ታዋቂ መሆን አንዳንዴም አስቸጋሪ ነዉ....በየመንገዱ ያገኘኝ ሁሉ መቼ ነዉ ንገሪኝ የማይለኝ የለም....

የለበስኩትን ቀለበት ብቻ አይተዉ ነዋል ልታገባ ነዉ የሚል ወሬ በእኛ ሰፈርና በኮሌጅ ሳይቀር በአንዴ ተናፈሰ...


#ክፍል 2⃣3⃣
ይ..........ቀ...............,
.......ጥ.........ላ..............ል


     Join     `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሀያ ሶስት 2⃣3⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ

የለበስኩትን ቀለበት ብቻ አይተዉ ነዋል ልታገባ ነዉ የሚል ወሬ በእኛ ሰፈርና በኮሌጅ ሳይቀር በአንዴ ተናፈሰ...

በመንገድ ያገኘኝ ሰዉ ነዋል ልታገቢ ነዉ እንዴ?? ብሎ ሲጠይቁኝ.... አብሽሩ መቼም ሰርጉ ሲደርስ እናንተን ጥየ ያገባሁት ሰርግ... ሰርግ ሳይሆን ሀዘን ነዉ ዱአ አድርጉልኝ ኢንሻ አላህ በቅርብ ቀን አይቀርም እያልኩ ለሰዎች እመልስላቸዋለሁ፡፡

  ሁሌም ከካሊድ ጋር በሳምነት ጁምአ ከአሱር ቡሀላ ስንገናኝ ልንገረዉ አልንገረዉ እያልኩ ብቻየን አስባለሁ ..ግን ከምኑ እጀምራለሁ??አፍ አዉጥቶ ለመንገር አንደበቴን ይሳናል .....


አላህ ይርዳሽ በሉኝ ለሚመጣዉ ሳምንት ካሊድ በሚመቸዉ ቀን ቀጠሮ ይዤ ሁሉንም አፍረጥርጬ ልነግረዉ ወሰንኩኝ...

   ሰኞ ጠዋት ለካሊድ ደዉየ በጣም እፈልግሀለሁ የማወራህ አስቸኳይ ጉዳይ አለ  አልኩት
.....እሱም ስራ ላይ ነኝ ዛሬ አይመቸኝም ምን አልባት እሮብ እና ሀሙስ ልቀር እችላለሁ ...ለምን ጁምአ በሳምንት የምንገናኝበት ቀን ነዉ ጁምአ አነግሪኝም ወይ ?? አለኝ
.....,እኔም ጁምአ እኮ የደስታችን ቀን ነዉ አሁን የምነግርህ የተደበቀ ሚስጥር ለጁምአ የሚነገርበት ቀን አይደለም አልኩት
......የምነግሪኝ የሀዘን ነዉ ማለት ነዉ???? ...አታስጨንቂኝ አሁን ንገሪኝ አለኝ
.........እኔም ዝም አልኩት፡፡
....እሱም ሀሙስ ከሰአት ስራ አልገባም እንገናኛለን ትነግሪኛለሽ አለኝ.....
...እኔም ኢንሻ አላህ ብየ የስልክ ወሬያችንን ጨረስን

ከካሊድ የምወድለት ሶስት ባህሪዎች አሉት የመጀመሪያዉ ምንም ነገር ቢፈጠር በስራ ቀልድ አያቅም ስራ ስራ ነዉ የሚለዉ ደግሞም ስራ አይመርጥም ሁለተኛዉ በጭራሽ አይዋሽም ሶስተኛ አይደብቅም ለምሳሌ አንዳንድ ሰዉ ስታጠፋ መስመር ስታልፍ የሚደብቅልህ አለ እሱ ግን ሀቅ ከሆነ ከፈለገ ቅር ይበልህ እንጂ እሱ ነዉርን ካየ ፊለፊት ነዉ የሚናገረዉ ይሄ ባህሪዉ ይመቸኛል ፡፡

  ስልክ አዉርተን ብንጨርስም ካሊድ እየደወለ በጣም አስቸገረኝ ምንድን ነዉ የምነግሪኝ??? ነዋል እባክሽ ንገሪኝ በሀሳብ ልሞት ነዉ?? ስራ መስራት አልቻልኩም እያለ በየሰአቱ እየደወለ ነዉ፡፡ እኔም ተጨኔቄ እሱንም አስጨነኩት
....እኔም ይሄንን ሀሳብ ተረጋግቼ ማሰብ ስላለብኝ እሱም እየደወለ ሲያስቸግረኝ ...ካሊድ እኔም ለራሴ ሀሳብ ላይ ነኝ በአላህ አንድ ነገር ተባበረኝ???አልኩት
.....እሱም ምን ልተባበርሽ ??? አለኝ.....
....,እኔም ሀሙስ እስከሚደርስ በተደጋጋሚ አትደዉል በቀን አንዴ ከደወልክ ይበቃል በዚህ ተባበረኝ አልኩት
......እሱም ጭራሽ የማይሆን ነዉ እኔም ተጨንቂያለሁ..,የኔ በተደጋጋሚ አለመደወል አሁን ለአንቺ ሰላም የሚያረግሽ ከሆነ እሺ ሳልወድ በግዴ የተናገርሽዉን አከብራለሁ አለኝ
....በዚህ ሀሳብ ተስማማ

እኔ ይሄን ያልኩበት ምክንያት ካሊድ በኔ ፍቅር በጣም እየተጎዳ ስለሄደ ...በቀን አንዴ ከደወለ ይበቃል ..እኔ ስነግረዉ እንደማይቀበለኝ አቃለሁ በዚህ የተነሳ እኔን እየረሳኝ ይሄዳል ብየ አሰብኩኝ ፡፡ካሊድ በቃሉ መሰረት በቀን አንዴ መደወል ጀመረ

   እኔም መደወል ሲያቆም ትንሽ ጊዜ አገኘሁ ወላሂ ቢላሂ ቀን ማታ ማልቀስ ሆነ ስራየ ፡፡ ለሊት እየተነሳሁ ሶላት እየሰገድኩ ወላሂ ዱአ እያረኩ አለቅሳለሁ፡፡ ሶላተል ሀጃ ሶለተል ኢስቲሀራ አየሰገድኩ በቂያምም በሩኩኡም በሱጁድም እያለቅሱ አላህን እጠይቀዉ እለምነዉ ይዣለሁ አላህ እርዳኝ ካሊድ ማንነቴን እንዲቀበለኝ እርዳኝ .... ሁሌ ደካማ አታርገኝ አሁንስ ደከመኝ ማን ማንነቴን ይረዳኝ ??ጌታየ እኔንም በማንነቴ ካሊድንም በፍቅር አታሰቃየን ፡፡ እያልኩ ዱአ ማድረግ ተያይዠዋለሁ...እናንተም በዱአችሁ አትርሱኝ

★★★ ዱአ
ዱአ በሀይማኖታችን ዉስጥ ትልቅ ጠቀሜታ ያለዉ ሲሆን እኛን የሰዉ ልጆች ደካማነትና ረዳት የለሽነት በመለኮታዊ ችሎታ ፊት የማቅረቢያ መንገድ ነዉ።

አንድ ባሪያ ጉዳዮቹን ይፈፅምለት ዘንድ ወደ ሀያሉ አላህ ፊት ይዞ ሲቀርብ ከቃላት ማነብነብ ባለፈ ልባዊ በመሆንና ፊትን ወደ አላህ በማዞር መሆን አለበት። ይህም ሲሆን ሁል ጊዜም ቢሆን አላህን በመፍራትና ምህረቱንም ተስፋ በማድረግ መካከል መሆን ግድ ነዉ። ለምሳሌ አንድ አማኝ አላህ ሀጥያቱን እንዲምረዉ ከፈለገ በዱአዉ ዉስጥ ሙሉ ትኩረት ማድረግና ጉዳዩን በሙሉ ልቡ ለፈጣሪዉ ማቅረቡን ማረጋገጥ ይኖርበታል። በፀፀት በተቃጠለ ልብና እንባ የሚያወርዱ አይኖች የፈጣሪን ትኩረት የማግኘት እድላቸዉ ሰፊ ነዉና።

በሁሉም አጋጣሚዎችና ሁኔታዎች አንድ አማኝ የአላህ ባሪያ መሆኑን ከሚያረጋግጥባቸዉ መስፈርቶች አንዱ ሁል ጊዜም እርሱን መለመን መቻሉ ነዉ። ባሪያ የመሆን ሚስጥሩና የእዉነተኛ አምልኮት አስኳል የሚገኘዉም አላህን በተከታታይና በዘዉታሪነት በመለመን ነዉ። ምክንያቱም ሶላትና ዱአ ወደ አላህ የሚወስድ ወሳኝ መንፈሳዊ መንገዶች ናቸዉና።

አላህ በተከበረ ቃሉ በቁርአን እንዲህ ብሏል
ባሮቼ ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ(እንዲህ በላቸዉ)""እኔ ቅርብ ነኝ የአማኝን ፀሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ።ስለዚህ በእኔ ይታዘዙ በእኔም ይመኑ እርሱ ሊመሩ ይከጂላልና""(አል በቀራህ186)

ተወዳጁ የአላህ መልክተኛ ሀቢቡና ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ከሰላታቸዉ በተጨማሪ እንባቸዉን እያፈሰሱና በመቆም ተረከዛቸዉ እስከሚያብጥ ድረስ አላህን በፅኑ ይማፀኑና ይለምኑ ነበር። አጭርና ልባዊ የሆነን ዱአ የመዉደዳቸዉን ያህል ከልብ ያልሆነን ማነብነብ ይጠሉ ነበር። ተከታዮቻቸዉም እንደሚከተለዉ በማለት ይመክራሉ።
""ባሪያዉ ወደ ጌታዉ ይበልጥ ቅርብ የሚሆነዉ ሱጁድ ላይ ሲሆን ነዉ። ስለዚህ ሱጁድ ባደረጋቹህበት ጊዜ ብዙ የምትፈልጉትን ነገር አላህ ያሳካላቹህ ዘንድ ለምኑት"" ብለዉናል፡፡

አንድ አማኝ ሁል ጊዜም በዱአ አላህን በመለመን መትጋት የሚገባዉ መሆኑ እንደተጠበቀ ሁኖ በእምነት ወንድሙ የሆነ ሰዉም ዱአ እንዲያደርግለት መጠየቅ ይኖርበታል። ይህ ሰዉ ምናልባትም ድሀ፤ደካማ፤ችግረኛ...ቢሆን እንኳን አላህ የእርሱን ልመና ሊሰማዉ ይችላል። ምክንያቱም የአላህ መልክተኛ(ሰ.ሰ.ወ) እንዲህ ብለዋል።
"" አንድ ሙስሊም ለሌላዉ ወንድሙ በሌለበት ከሚያደርግለት የበለጠ በፍጥነት ተቀባይነትን የሚያገኝ ዱአ የለም።(ቲርሚዝ) እናንተም በዱአ አግዙኝ
ከሰኞ ጀምሬ ሀሙስ ድረስ ትምህርት ሳልሄድ እቤቴ እየዋልኩ ከሶላት በፊትም ቡሀላም ዱአ ላይ ነኝ ፡፡ ወላሂ እነዚህ ቀናቶችን ዳግመኛ በሒወቴ ላይ ማሰብ አልፈልግም በጥላቴም ላይ በጭራሽ አልመኛቸዉም .ጠዋት ጀምሬ እስከ ማታ ይሄም አልበቃኝ ብሎ አዳሬን ማልቀስ😰😰 ሆነ የኔ ነገር፡፡ እንቅልፍ አስተካክየ መተኛት እንኳን አልቻልኩም አይኔ አለመፍረጡም የጉድ ነዉ፡፡


የሚገርማችሁ እያለቀስኩ ዱአ ሳደርግ ምን ብየ ዱአ እንደማደርግ ታቃላችሁ?? ከሁሉም ሰዉ የተለየ ዱአ ነበር የማደርገዉ👇👇👇
ዱአየም......
>>>>>>>>> የፈጠርከኝ ጌታየ አላህ ሆይ!!!! እባክህ እርዳኝ ደካማህ ባሪያህ ነኝ ;ካሊድ ከሁሉም ወንድ የተሻለ ነዉ ለኔም የተሻለ ሰጥተህኛል አቃለሁ ...ማንም ከሚወደኝ በላይ ይወደኛል ..ማንም ሳያከብረኝ እሱ ግን አክብሮኛል ....የእኔ እና እሱን የመጨረሻዉን በሰላም አርገህ አሳየኝ...ማንነቴን ነግሬዉ ከተቀበለ አልሀምዱሊላህ እሰየዉ .ነገር ግን ማንነቴን የማይቀበለኝ ከሆነ በዱንያ መሬት መኖር አልፈልግም ;እኔም ታንቄ መርዝም ጠጥቼ መሞት አልፈልግም አንተዉ እንደፈጠርከኝ ግደለኝ ... ጌታየ ሆይ ወድጄ አይደለም...ከዚህ በላይ መታገስ አልችልም፡፡ ስቃየ በዛ እኔም ተሳቅቄ በማንነቴ ተሸማቅቆ መኖር በቅቶኛል ፡፡ ሞትን የመረኩት ምክንያት አለኝ ------ ማንነቴን የሚቀበለኝ ከሌለ በዱንያ ላይ ወንድን አልፈልግም #አንተዉ_በጀነት_ላይ_አንተን_ሲገዛ_የኖረ_አንተ_ከምወደዉ_ባሪያህ_መርጠህ_ታጋባኛለህ ..የማገባዉ ጀነት ዉስጥ ብቻ እንዲሆን ነዉ የምፈልገዉ ...መቼም ይሄንን ሁላ ግፍ አሳልፌ ከልጅነቴ ጀምሬ ሳለቅስ ኑሬ ስጨናነቅ ኑሬ በዱንያ የሀሳብ እና በእንባ ጎርፍ በአንተዉ ዉሳኔ ተቀጥቼ....እራሴን አጥፍቼ አንተ ጋር ብመጣ  ይሄንን ሁላ ግፍ ለቅሶ አሳልፌ በአንተ ራህመተህ እዝነትህ የጀሀነም እንደማታደርገኝ እርግጠኛ ነኝ..... ለነገሩ ምን እርግጠኝነት አለ??? አንተዉ ፈጥረሀኝ ወደ አንተዉ ተመላሽ ነኝ ምን ዋስትና አለኝ??? የሰዉ ልጅ ለመሞት አንድ ስንዝር ስትቀረዉ በአላህ ሲያምፅ ኑሮ የጀነት ስራ ሰርቶ ጀነት የሚገባ እና በተዘዋዋሪ የጀነት የሚያስገባ ስራ ሰርቶ ለመሞት አንድ ስንዝር ስቀረዉ የጀሀነም የሚያስገባ ስራ ሰርቶ ጀሀነም የሚገባ አለ ....እራሱን ያጠፋም ጀነት እርም እንደሆነ አቃለሁ ብቻ አንተዉ ጠብቀኝ እኔም ግራ ገባኝ፡፡ #አላህዋ ካሊድ የኔን ማንነት የማይቀበል ከሆነ እዚሁ ሱጁድ ላይ እንዳለሁ ግደለኝ ..ሂወት በቃኝ ግደለኝኝኝኝ  መኖር አልፈልግም ይበቃኛል፡፡  እስከ አሁን ደስተኛ ሁኜ የኖርኩበት ቀን የለኝም...የኔ ደስታ አንተ ያዘጋጀህልኝ ጀነት ነዉ ጌታየ አንተዉ ሽማግሌ ሁነህኝ ደስታየን በጀነት ወንድ አርግልኝ ....,እየደጋገምኩ እየደጋገምኩ ካሊድ ማንነቴን የማይቀበለኝ ከሆነ ግደለኝ መኖር አልፈልግምምም እያልኩ ስጁድ ላይ እማባየን አፈስ😢😢 ይዣለሁ
 
ካሊድ በቀን አንዴ እየደወለ አረ አስጨነቅሽኝ ምን ሁነሽ ነዉ??? ንገሪኝ እያለ ይጠይቀኛል
.....እኔም ሀሙስ ተባብለናል ሀሙስ ሲደርስ እነግርሀለሁ እለዋለሁ፡፡


የማይደርስ የለም የፈራሁት ዱአ ያረኩበት ልነግረዉ የወሰንኩት ቀን ሀሙስ ደረሰ ..
....ካሊድ ጋር ተገናኘን ወሬዉን ለመስማት ቸኩሏል፡፡ሰንገናኝ የምንዝናናበት ቦታ እንሂድ እንዴ??? አለኝ
......እኔም አንተ መኖሪያ ቤት ይሻላል አልኩት..,ምክንያቱም በመንገድ ስመጣ ወይም እዛ ማልቀሴ የማይቀር ነዉ ሰዉ እይታ እንዳልገባ በማሰብ ነዉ መኖሪያ ቤቱን የመረጥኩት
....እሱም እስከዛሬ ወንድ ቤት አልሄድም ብየ ስላስቸገርኩት . ..እርግጠኛ ነሽ እኔ ቤት እንሂድ??? አለኝ
......እኔም አዎ አንተ ቤት ነዉ የምነግርህ አልኩት
..............እሺ መርሀባ ብሎኝ ወደ እሱ ቤት ጉዞ ጀመርኩኝ ፡፡ ግን ምን ሁነሽ ነዉ?? ንገሪኝ በጣም ተጨነኩኝ እቤት እስከምደርስ አላስቻለኝም አለኝ
.......እኔም ምንም አልሆንኩም ቤት ስንድረስ ብነግርህ ይሻላል አልኩት .
ከዛም በመኪናዉ መኖሪ ቤቱ ወሰደኝ
..... እቤት እንደገባሁ ብዙም የተካበደ ሳይሆን የወንደ ላጤ ግብዣ ጋበዘኝ እና...የኔ ፍቅር ምንሁነሽ ነዉ ???ንገሪኝ እኔም በጭንቀት አለኩኝ እኮ ስራ መስራት አልቻልኩም አለኝ

....እኔም ለመናገር ምራቄን ዋጥ አርጌ ምላሴ ለመንገር እየፈራ እየተንቀጠቀጠ መንገሬን ጀመርኩ....ካሊድ አንንተተ ምን ያህል እንደምወደኝ እንደ እንደደደ ምታፈቅረኝ  አቃለሁ ፡፡ አፈቅርሀለሁ ብየ ባልዋሽህም እወድሀለሁ አንተተተን ማማማጣት አልፈልግም ....አንድ ስለ እእእእኔ ማንነት የምነግርህ አለ ይሆናልልልል ብለህ የማጠብቀዉ ነዉ፡፡
  
ለካሊድ ባለፈዉ ያረገልኝን ቀለበት አዉጥቼ ሰጠሁት ፡፡አሁን የምነግርህን የማትቀበለኝ ከሆነ ቀለበቱን እንደያዝከዉ ለኔ አታድርግልኝ ዝም ብለኝ ...ምንም አስተያየት ጥያቄ አንዳታነሳብኝ ..እንዴት ለምን ሆነ ??እያልክ ታሪኩን  እንድጠይቀኝ አልፈልግም...ከቤት ዉጪ በለኝ ከቤት እወጣለሁ ደግሜ በሒወትህ በጭራሽ አልገባም ከአሁን ቡሀላ በጭራሽ አንገናኝም ..ብሞት ለራሱ ነዋል አላህ ይርሀማት ብለህ ለመቅበር እንዳትመጣ
....እሱም አረ ምንድን ነዉ ነገሩ?" አስጨነቅሽኝ አለኝ
.......,እኔም እስከማንነቴ ለመቀበል ለመወሰን ጊዜ እሰጥሀለሁ ይሄ ነገር ቀልድ አይደለም፡፡ አንድ ቀን ፈጣሪ ካለ አንድ ላይ ሁነን ትዝ ብሎህ ወይም ከተጋባን ቡሀላ ይሄ ነገር እንዴት እንደዚህ ሆነ ??ብለህም እንድትጠይቀኝ አልፈልግም...በጠቅላላ ዛሬ ከነገርኩህ ቡሀላ፡ዳግመኛ ይሄን ወሬ ማዉራት አልፈልግም አልኩት፡፡
ይሄን ወሬ ለመስማማት ወይም ለመተዉ 24ሰአት እሰጥሀለሁ ..አሁን 8:00ነዉ አይደል ??? አልኩት
.....እሱም አዎ አለኝ
.....እኔም ነገ ጁምአ 8:00 ላይ ደዉለህ ዉሳነኔህን ታሳዉቀኛለህ ፡፡ ከስምንት ሰአት አንድ ደቂቃ ካለፈ ሀሳብህ አልፈልግሽም ስለሆነ እንዳትደዉል መቼም ይቅር ልልህ አልችልም አልኩት
....እሱም ደነገጠ አረ ምን ሁነሽ ነዉ???ይለኛል
......በቃ ልነግረዉ ነዉ......የስንት አመት የታፈነዉን የሆድ ዉስጥ ፉም እሳቱን ልነግረዉ ማልቀስ ሆነ ስራየ... ልረጋጋ አልቻልኩም እምባየ እንደወራጅ ወንዝ ይጓዛል😢...ካሊድ አላስቻለዉም አብሮኝ ያለቅሳል አረ ንገሪኝ የአንቺን ሀዘን ማየት አልችልም እያለ መላቀስ ይዘናል

እኔም መናገር አቃተኝ እንዴት ብየ ቃላት አዉጥቼ ልንገረዉ ?? ሁለታችንም እየተያየን መላቀስ ሆነ ፡፡ አፌ ተያያዘ ልጅ ሁኜ ተደፍሬ ነበር ብየ እንዴት ብየ ልንገረዉ ???.ከዛም አንድ ሀሳብ መጣልኝ ስልክህን ያዝ text አሁን እልክልለሁ አንተ የምትለኝ እዉነትሽን ነዉ ...ብቻ በለኝ ጥያቄ እንዳታበዛብኝ  አልኩት
....እሱም እሺ አለኝ
.........እኔም ሳይበዛ በmessage በአራት አመቴ በጎረቤት ልጅ ተደፍሬ ነበር የነገረችኝ የቤት ሰራተኛችን ናት..አባቴ የጎረቤታችን ልጅ በልጅነትሽ የተደፈርሽዉ ብላኝ አባቴ በሽጉጥ ሊገላት ነበር ብየ በአጭሩ ፃፍኩለት
....ካሊድ እየደጋገመ የላኩለትን Message አነበበዉ አነበበዉ ...በአንዴ ፊቱ ተቀያየረ 😡መናደዱ ፊቱ ላይ ያስታዉቃል ከንፈሩን በፊት ጥርሱ ነክሶ ፍጥጥ ብሎ ያየኝ ጀመረ.... ..እንም የካሊድን ለኔ ያለዉን አመለካከት ስመለከት በጣም ደነገጥኩ፡፡ ከመደንጠጤ የተነሳ ልቤ ከቦታዉ ተነቅላ የሄደች ነዉ የመሰለኝ .... ምን ይደረጋል የፈራሁት ስጨነቅበት የነበረዉ ነገር ደረሰ😔


#ክፍል 2⃣4⃣
ይ.........ቀ........
.......ጥ .........ላ...........ል


    Join     `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሀያ አራት 2⃣4⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




ካሊድ የላኩለትን message እየደጋገመ አነበበዉ አነበበዉ ፊቱ ተቀያየረ መናደዱ ፊቱ ላይ ያስታዉቃል ...የፈራሁት ስጨነቅበት የነበረዉ ደረሰ ብየ አሰብኩኝ
......... ካሊድ አብሽር አትደንግጥ አልፈልግሽም ማለትህ አይደል? በቃ ልነሳ እና ልሂድ አንተን ማስጨነቅ አልፈልግም ብየ ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ
......እሱም ነይ ተቀመጭ ምንድን ነዉ የምትይዉ?? አሁን ከአፌ ምን ሲወጣ ሰማሽ?? ብሎ ሲቆጣኝ መልሼ ተቀመጥኩኝ
......እሱም አንድ ጥያቄ ብቻ ልጠይቅሽ message በደንብ አልገባኝም እስኪ አብራሪልኝ የአራት አመት ልጅ ሁኜ ነዉ ያልሽዉ ወይስ ከአራት አመት በፊት ነዉ ??? ብለሽ የፃፍሽዉ?? አለኝ
.....የአራት አመት ልጅ ሁኜ ነዉ አልኩት
......ካሊድም ዝም ብሎ ቆየና... ያላሰብኩት ይለኛል ብየ ያልገመትኩት መልስ ሰጠኝ >>>>> #እንዴት_ሰዉ_የአራት_አመት_ልጅ_ጋር_ስሜቱ_ይታዘዝዋል ???<<<<<<< ግን የምርሽን ነዉ የኔ ፍቅር መቼም አፕሪል ዘፉል እያልሽ ሰዎቹ እንደሚጃጃሉት እየተጃጃልሽ አይደለም አይደል ?? አለኝ
.....እኔም አዎ እዉነቴን ነዉ አልኩት
........እኔን ለመፈተን አይደለም ???እንደዚህ ስለዉ ከተወኝ ልተወዉ ከተቀበለኝ ደግሞ የወደፊት የትዳር ምርጫየ ነዉ ብለሽ አስበሽ እኔን ለመፈተን..የአንቺ የፈተና መሰናክሉን ማለፍ አለማለፌን ለማረጋገጥ ብለሽ  አይደለም ??? አለኝ
.....አዎ አይደለም እዉነተኛ ነዉ የነገርኩህ አልኩት
..........እሱም ወላሂ በይ ??? አለኝ
..............ወላሂ ቢላሂ ብየ ማልኩለት
......እሱም እንዴት ሰዉ ገና ለጋ በሆነች የአራት አመት ልጅ ጋር ስሜቱ ይታዘዝዋል ???ምን አይነት ጨካኝ ቢሆን ነዉ ??? የኔ ፍቅር አለኝ
....እኔም ጥያቄ እያበዛህ አታጨናንቀኝ .....አልኩት
.......አንድ ነገር ልጠይቅሽ ፍቃደኛ ከሆንሽ ??አለኝ
.... እሺ ምን ነበር ጥያቄዉ??? አልኩት
.......እዚሁ ቁጭ እንዳልሽ የማስብበት ሀያ ደቂቃ ብቻ ስጭኝ አለኝ
......እሺ ቅድም እንዳልኩህ እንኳን ሀያ ደቂቃ አንድ ቀን እሰጥሀለሁ አልኩት
   
ካሊድ ለ20 ደቂቃ ያህል እየደጋገመ ቴክስቱን እያነበበዉ ነዉ ...የካሊድ ሁኔታ በጣም አስጨነቀኝ ወላሂ እምባዉ እያነበበ ዱብ ዱብ እያለ ይወርዳል ....

ከዛም ከ20ደቂቃ ቡሀላ እንደዚህ አለኝ ...ነዋል እኔ የምወደዉ አንቺን ነዉ ሁሌም ቢሆን እወድሻለሁ፡፡ ፍቅር ማለት ከነማንነት መቀበል ነዉ፡፡ እኔ የምፈልገዉ አንቺን ነዉ ...እኔ ምኞቴ አንቺ የኔ ስትሆኝ ዱአየ ደርሶ ማየቴ ነዉ ፡፡ እኔ አንቺን ምን ያህል እንደማፈቅርሽ አታዉቂም ማለት ነዉ ??? ፍቅር ማለት እንደ አሁን ዘመን ሰዎች ተገናኝተዉ ስሜታቸዉን ማብረድ ..መንገድ ለመንገድ ተገናኝተዉ መጋተት መገባበዝ ብቻ መሰለሽ እንዴ ???አለኝ
.......እኔም ካሊዶ አታስጨንቀኝ ነገሮችን አታወሳስብብኝ ግልፁን ንገረኝ አልኩት

....ነዋል አንቺ ምንም ሁኚ ምንም የምፈልገዉ ነዋል የኔ እንድትሆኝ ብቻ ነዉ ..አንቺን አግብቼ አቅፌሽ እንድተኛ...ከአንቺ ጋር ደስተኛ ሁኜ ልጅ መዉለድ ....ልብሽ ከልቤ ጋር እየመታ እንዲኖር ነዉ የምፈልገዉ ..ለኔ ሌላዉ ትርፍ ነዉ ምንም አልፈልግም ...ይሄ እኮ ቀላል ነገር ነዉ እኔ የተማርኩ ሰዉ ነኝ ብዙ ነገር አዉቃለሁ ..የግድ ድንግል አይደለሽም ብየ ሀገር የምበጠብጥ በረዶ ይቆላልኝ እያልኩ የምለፈልፍ መስሎሽ ነበር እንዴ ??? ድንግልና እኮ ለትዳር መስፈርት አይሆንም ...እንዴት ፍቅርን በዚህ ተራ መስፈርት የምተዉ መስሎሽ ነበር እንዴ??? ብሎ እንደመቆጣት አለኝ
.......እኔም ካሊድ የሚያወራዉ እዉነት እዉነት አልመሰለኝም... ከምርህ ነዉ ??? አልኩት
...........እሱም የሰዉ ልጅ ከወደደ እንኳን አንቺ በማታቂዉ በልጅነትሽ ክብርሽን የአጣሽዉን.....አንዴት ሴት አግብታ ልጅ ወልዳ ተፋታ ከአንዴም በላይ አራት የተለያዩ ባሎች ጋር ኑሮዉን አይታ መፋታት የምታበዛ ፀባይ የሌላት ጨቅጫቃ...... በዛም ላይ  ልጅ ኑሯት ይችን ሴት በፍቅር አምነዉ ወድቀዉ ተዋደዉ ....እያገቡ አይደል እንዴ ???  አለኝ
......እኔም ምን ለማለት ፈልገህ ነዉ ??ካሊድ አንድ ቃል ብቻ ንገረኝ ..ማንነቴን ተቀብልሀል አልተቀበልክም??? አልኩት
......የሰጠሁትን ቀለበት መልሶ እጄን ይዞ አስተካክሎ  በጣቴ አረገልኝ ፡፡ ስሜታዊ ስለሆነ አጂ ነብይ የሚለዉን ዘንግተንዋል
......እኔም በኔ ማንነት ተስማምተሀል ማለት ነዉ ???አልኩት..ጭራሽ የሚሆነዉን ነገር ማመን አልቻልኩም
............እሱም ምን ለማለት ፈልገሽ ነዉ ??ይሄ እኮ ቀላል ነገር ነዉ ቀለል አርገሽ እይዉ....የኔ ፍቅር እስከዛሬ ለዚህ ቀላል ነገር እንደዚህ ተጨንቀሽ ነበር ማለት ነዉ ?? አንቺስ ተጨንቀሽ እኔንም ያስጨነቅሽኝ ለዚህ ተራ ነገር ነዉ ??? ወላሂ እኔም ተጨንቄ ቀን ስራ መስራት ማታ መተኛት አልቻልኩም ነበር ..አለኝ
........እኔም ተቀብለህኛል ማለት ነዉ ??? አልኩት
እሱም አዎ ተቀብያለሁ ይሄ ተራ ነገር ነዉ ..ለወደፊት ስለዚህ ጉዳይ ማዉራትም አያስፈልግም ..በዚሁ እርሺዉ አለኝ
.....ግን አስበህበታል ??? ሁለት  ቀን ልስጥህ እና እሰብበት ቡሀላ እንዳይቆጭህ አልኩት
.....ሁለት ቀን አያስፈልገኝም አሁኑኑ ወስኛለሁ ብቻ አሁንም ለወደፊትም አንቺቺቺቺቺቺቺቺቺቺቺቺ የኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔኔ ብቻቻቻቻቻቻቻቻ  ሁኝልኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝኝ አለኝ፡፡

ከዛም ይሄን ያህል አመት ከልጅነትሽ ጀምሮ እንደዚህ ስታለቅሺ የኖርሽበት ገና በአራት አመትሽ ስሜቱ ታዞት ይሄንን በደል ፈፅሞብሽ ስታለቅሺ እንድቶኖሪ የፈረደብሽን ልጅ አሳየኝ  እገለዋለሁ አለኝ
......እኔ እሱን ለአላህ ብየ ትቸዋለሁ በቀል ጥቅም የለዉም ይቅርታ ያሸንፋል...ግን ፈጣሪ የስራዉን ወይ በዱንያ ወይ በአኼራ ይሰጠዋል አልኩት
....እሱም ማሻ አላህ.. እኔ ብሆን ለእምባየ ምክንያት የሆነዉን በአገኘሁት አጋጣሚ እበቀለዉ ነበር...አንቺ ይቅር የሚል ጥሩ ልብ አለሽ አለኝ ፡፡


ከዛም ካሊድ አሁን ሳይመሽ ወደ ቤትሽ ልዉሰድሽ ብሎኝ ከቤት ወጣን...መኪናዉ ወስጥ ሁነን ነዋል እንዴት ቅልል እንዳለኝ ልነግርሽ አልችልም ..ተረጋጋሁ በጣም እየተቀጨነኩ ነበር ምን ሁነሽ ይሆን እያልኩኝ ለወደፊት በእንደዚህ ያሉ የሒወት አጋጣሚዎች ተስፋ መቁረጥ የለብሽም ብሎ የተለያዩ ምክሮች መከረኝ...

እኔም ይሄ የተጨነኩበት ቀን እንደዚህ እኔ ባልጠበኩት ሁኔታ አለፈ....አልሀምዱሊላሂ ረቢል አለሚን አልቅሸም አልቀረሁም አላህ ዱአየን ተቀበለኝ፡፡
ወንድ ልጅን ሳስብ ትዳር ሲመጣ ድንግልና ብቻ ነዉ መስፈርታቸዉ ብየ አስቢያለሁ..ባስብም አይፈረድብኝም ከአንድ ሁለቴም ደርሶብኛልና ..ደግሞ በተዘዋዋሪ እንደ ካሊድ ያሉ አስተዋይ ለሴት ልጅ የሚያዝኑ ቅንጣት ሰዎች አሉ

★★★ ግን አሁን ድረስ ወንዱ ድንግልናን ደም ጋር ያያዙታል..ግን ደም ብቻ ነዉ የድንግልናዉ መገለጫዉ???
#ድንግልና_ወይም_ክብረ_ንፅህና_የምንለው_ምንድንነው?
አንዳንድ ወንዶች ግድ ደም ካላየን ድንግል አይደለችም እያሉ ያዙኝ ልቀቁኝ እያሉ ሲያቅራሩ ይስተወላሉ፡፡ ነገር ግን ስንት ጥብቅ አላህን ፈሪ የሆኑ ሴቶች ጌታቸዉን ትዕዛዝ ተቀብለዉ ከዚህ አስከፊ ዘመን ሙሲባዉ ሹብሀዉ በበዛበት ጊዜ👇👇👇
ከወንጀል ተከልክለዉ ኑረዉ... ትዳር ላይ ሲገቡ ምሽት ላይ በማታየዉ ምልክት አጅሬዉ ነብር ይመስል ደም ካላየ አንቺ ድንግል አይደለሽም እየተባለች ባልሰራቸዉ ስራ ባልሰራቸዉ ዚና በባሎች ተጠርጥራ በግራ አይን እንድትታይ .... ነገሩም ከከፋ እስከ መፋታት ድረስ የሚደርሱ ብዙ ትዳሮች እያየን ነዉ፡፡ ዉድ እንቁ እህቶች በዚህ ምክንያት ፈጣሪ በሰጣቸዉ ፀጋ ለምን ደም አላየንም አንቺ ዉሸታም ድንግል ነኝ ብለሽ ዋሸሽኝ እየተባለች በባሎች ማሸማቀቅ ምነዉ አግብቼ ባልነበር እያሉ ሲያለቅሱ የሚኖሩ ብዙ እህቶች እንዳሉ ቤት ይቁጠረዉ ፡፡ ወንድሜ ሆይ!!!!! ደም መድማት ብቻ ነዉ እንዴ የድንግልና መገለጫ ??? አትሳሳት ከአእምሮህ ላይ ደም ብቻ ነዉ የሚለዉን ፍቀህ አዉጣዉ....ደም ማየት ብቻ የድንግልና ማረጋገጫ አይደለም፡፡

መጀመሪያ ስለድንግልና ትርጉም እወቅ.. ድንግልና ለሴት ልጅ ብቻ አይደለም ለወንድም አለ...ነገር ግን ምን ይደረግ የወንድ በሴት ልጅ መታወቅ አይችልም..አንተ አወኩኝ ብለህ የምታሸማቅቅ ከሆነ ...የአንተን ማንነት የሚያቅ ፈጣሪ እንዳለ አደራ አንዳትዘነጋ ፡፡ #ድንግልና ማለት የወንዶችም ሆነ የሴቶችን የአካል መቆጠብ ለመግለፅ የምንጠቀምበት ቃል ሲሆን ይሄም ማለት ከግብረ ስጋ ግንኙነት (ከሩካቤ ስጋ) መቆጠብን ይመሰክራል ፡፡ ይህ የመቆጠብና የመጠበቅ ሒደትም ለሰውነት ክብር መስጠት ነውና የሰውነትን ንፅህና ለመግለፅ ስንጠቀምበት ክብረ ንፅህና(የንፅህና ክብር) ወይም ድንግልና ይባላል፡፡

‼️ #ድንግልና_በምን_ይገለፃል?
በእርግጥ ሁለቱም ፆታዎች መታቀብን ተከትሎ ቢያገለግልም በወንዶች ላይ መታቀቡንና መፅናቱን ተከትሎ የሚታይ የአካል ለውጥ የለም፡፡ በሴቶች በኩል ግን የተራክቦ አካላት ከሆኑት መሀል በብልት አካባቢ ይህን የድንግልና መገለጫ ምልክት ይሆን ዘንድ ተፈጥሮ አስቀምጦት ይገኛል።
ድንግልና በሴቶች ብልት በራፍ ላይ የተቀመጠ አነስተኛ መጠን ያለው በደም ስሮች የተሞላ ስስና ሴንሴቲቭ የሆነ የሰውነት ክፍል ነው።

ይሄ በጣም ስስ የሰዉነት ክፍል(አካል) በቀላሉ ሴት ልጅ ልታጣው ትችላለች፡፡ ለምሳሌ፡- ሳይክል በመንዳት ፣ ፈረስ በመጋለብ ፣ ጅምናስቲክ የመሳሰሉ እስፖርቶችን በመስራት...በሀይድ መደራረብ...በከባድ ህመም ወዘተ ያለምንም ፆታዊ ተራክቦ ታጣዋለች።

#የድንግልና_አይነቶች_ስንትናቸው?
አምስት አይነት የድንግልና አይነቶች አሉ። እነርሱም #አንደኛዉ ➊ ☞ ሙሉ የብልት አካል በራፍ ላይ እንደ መጋረጃ የዘጋው ሲሆን የእጃችን ቀዳዳ ምታክል ክፍተት አለው ለወር አበባ መፍሰሺያ ሆኖ የተፈጠረ ድንግልና አለ። ይሄ ቀዳዳ ሙሉ የድንግልናውን ቦታ አይሸፍንም የድንግልናውን መጋረጃ ሩብ ምታክለዋ ቀዳዳ ናት።

#ሁለተኛ ➋☞ ብዙ ጊዜ ባይሆንም አንዳንድ ሴቶች ላይ የወንፊት መልክ በተያዘ በርካታ የተበሳሱ ቀዳዳዎች የተሞላ ሆኖ የተፈጠረ ድንግልና አለ።

#ሶስተኛ ➌☞ በተፈጥሮዋ ምንም የተጋረደ ነገር የለዉም ፡፡ በመጀመሪያው ግንኙነትዋ ጊዜ የሚፈስ ደም የሌላት ሴት አለች ድንግል እንደሆነች የምታውቀው እርስዋ ብቻ ናት ምንም ድንግል እንደሆነች ምልክት አታሳይም ደም አይፈሳትም።

#አራተኛ ➍☞ ድንግልናው በተፈጥሮ የጠነከረና በወንዱ ብልት ሊበጠስ የማይችል ነው ፡፡ይሄ አይነት ድንግልና ያላቸው ሴቶች ድንግልናቸውን ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ በሰርጀሪ ወይም በቀዶ ጥገና ወቶላቸው ነው ግንኙነት የሚፈፅሙት።

#አምስተኛ ➎☞ ሴትዋ ምንም አይነት የድንግልና መጋረጃ ሳይኖራት በብልትዋ ግርግዳ በኩል ብቻ ትናንሽ ሄመኖች ሲገኙ እነሱም የሚወገዱት በወንዱ ብልት ፍትጊያ ነው።
የሴቶች ድንግልና እላይ በጠቀስኳቸዉ አምስቱ ምክንያት ከፈጣሪ የሚሰጣቸው የተፈጥሮ ፀጋ ነው፡፡
.ይህ ፀጋ ደሞ የሚገኘው በመወለድ አንድ ጊዜ ነዉ፡፡ እድል ነውና በህይወታቸው ውስጥ ሴቶች የማይረሳ አሻራን ጥሎ ሚያልፍ ነው። ብዙዎቻቹ የመጀመሪያ ግንኙነታቹን አይረሱትም ለዛ ነዉ ወንዱ ድንግል ምርጫዉ ያደረገዉ፡፡ እናም ወንድሞቼ ደም ካላየሁ ድንግል አይደለችም ብለህ ንፁህ እህትህን ሚስትህን ለተናግሮ ተናጋሪ እንዳትሰጥ በተጨማሪ ከእኔ በፊት ከሌላ ጋር ባልጋለች ብለህ እቺን ንፁህ እንስት እንዳታረክስ ፡፡ የለቅሶዋ ምክንያት እንዳትሆን፡፡


ከዛም ጁምአ ደረሰ እና ብቻችንን ሂደን የምናወራበት፡ቦታ በመኪናዉ ሄድን ... ከአሁን ቡሀላ ጊዜ አንፍጅ አንቺም እቤት አሳዉቂ እኔም አሳዉቃለሁ በቅርብ ቀን ሽማግሌ ልልክ አስቢያለሁ ..አንቺ ምን ሀሳብ አለሽ ?? አለኝ
.......ግን ካሊድ ቤተሰቦችህ ድንግል ናት ወይ ብለዉ ቢጠይቁህ ምን ትላቸዋለህ ?? ብየ ጠየኩት
.....ካሊድም እንዲህ አለኝ_

#ክፍል 2⃣5⃣

ይ.............ቀ.................
........ጥ............ላ...................ል

join👇👇👇👇

        . www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሀያ አምስት 2⃣5⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




.......ግን ካሊድ ቤተሰቦችህ ድንግል ናት ወይ ብለዉ ቢጠይቁህ ምን ትላቸዋለህ ?? አልኩት
......ካሊድም ቤተሰቦቼ በሌላዉ ሒወቴ እንጂ ጣልቃ የሚገቡት በዚህ የትዳር ሒወት የምወስነዉ እራሴ ነኝ ...ደግሞም ቤተሰቦቼ ስለፀባይ ስለዲን ነዉ የሚጠይቁኝ እንጂ አንቺ ስለምትይዉ በጭራሽ ትዝም አይላቸዉ አለኝ

  እኛ ሀገር አንድ ባህል አለ ..ሁለት ጥንዶች እንደተጋቡ ...አዳሩ ላይ በሩ ላይ ሁነዉ ዘመዶች ያዳምጣሉ የሴቷ የጩኸት የማቃሰት ድምፅ ካልሰሙ አይተኙም ...ከአዳራቸዉ ቡሀላ ጠዋት ላይ የወንዱ ዘመዶች በር ላይ ሁነዉ ይጠብቃሉ... አዲሱ ሙሽራ በቀይ ደም የተበከለዉን አንሶላ ካላሳያቸዉ ድንግል ናት ብለዉ አያምኑትም፡፡ ማታ የወንዱ ቤተሰብች ገብተዉ አንሶላዉን ያነጥፋሉ ጠዋት ደግሞ አንሶላዉን ማሳየት አለበት ፡፡ ሙሽራዉ ድንግል ናት ብሎ ሲናገር..የወንዱ ቤተሰቦች ደስታ በደስታ ነዉ የሚሆነት እልልታዉ ጭፈራዉ #ሰበታ_መቀነት ይባላል... ከሰርጉ ያልተናነሰ ጭፈራ ይጨፈራል የወንድ ቤተሰብ ቤት ይደምቃል ፡፡ ከዛም ሴቷ ቤተሰብ ቤት ተሂዶ ልጃችሁ ስነስርአት ያላት አደበኛ ጨዋ የሽማግሌ ልጅ ናት ተብሎ ስጦታ ይሰጣል ......

እኔም ይሄን ባህል ስለማቀዉ ካሊድ ለቤተሰቦችህ እንዴት ልታደርግ ነዉ አንተ ??? አልኩት
.....እሱም አብረን የምናድረዉ እኔ እና አንቺ ነን እነሱ ምን አገባቸዉ መቼም መኝታ ክፍላችን ገብተዉ አፍጥጠዉ አያድሩ ...እኔ እራሴ የምላቸዉን አቃለሁ ....ለምን እንደዚህ አይነት ሀሳብ ታስቢያለሽ ???  ብሎ እኔ በተናገርኩት እሱ ይናደዳል ...
ነዋል እኔ ብቸኛ አንድ መሆኔ ሰልችቶኛል ..ከአንድ ይልቅ ሁለት መሆን ስቃይ ደስታን ለመጋራት ይመቻል...እኔ የናፈቀኝ ሀሳብ የሆነብኝ መቼ ይሆን እኔ እና አንቺ እኔም የአንቺ አንቺም የኔ የምትሆኝዉ ነዉ ሀሳቤ ጭንቀቴ....እናም ትዳር ነዉ የናፈቀኝ አለኝ..

ትዳር ሐላል አክሲዮን ነው፡፡ አክሲዮኑ በሁለት ተፈቃቃጅ በሆኑ ወንድ እና ሴት መካከል የሚመሰረት ግንኙነት ነዉና እንደዋዛ መታየት የለበትም፡፡ እንደዋዛ ከታየ እንደዋዛ ይፈርሳል፡፡

ትዳር ከሐራም ኑሮ ወደ ሐላል ግቢ ሽሽት ነው፡፡ ከጉድለት ሕይወት ወደ ሙሉነት ቤት ሩጫ ነው፡፡ ጠፍቶ የቆየን ግራ ጎን ማሟያ ፍለጋ ፅድቅ ስደት ነው፡፡

ትዳር የንፅህና ሻወር ነው፡፡ ሲንከራተት ለኖረ ዐይን ማረፊያ ነው፡፡ ሲባዝን ለኖረ ልብ ማስከኛ ነው፡፡ ፍላጎትን ሐላል እና ነፍስ በምትወደው መልኩ ለማሳካት ምክንያት ነው፡፡

ትዳር ባልና ሚስት ተፈጥሯዊ ስሜታቸዉን ሐላል እና አላህ በፈቀደው መልኩ የሚያረኩበት ጥምረት ነው፡፡ ለዚህ ጥምረት ዘላቂነትና ስኬት ከወዲሁ ሀሳብን ማስተካከል ግድ ይላል፡፡ “ከሞቀኝ እቀጥላለሁ ከበረደኝ እወጣለሁ” በሚል ስሜት የተገባበት ቤት የመፍረስ ዕድሉ ከፍ ያለ ነው፡፡ ከሙቀቱ ይልቅ ብርዱ ሊበዛ ይችላልና፡፡ ሀብት ንብረት ለመካፈል ብለው የሚገቡበት ጥምረት ዕድሜው አጭር ነው፡፡ ሀብት ንብረቱ አልገኝ ሲል ያነጫንጫልና፡፡ “አለው” ብለው የተቀበሉት ኪዳን አይዘልቅም፡፡ ያጡ ቀን ባህሪን ያባላሻልና፡፡

ትዳር በሕይወት በምድር ላይ እስካሉ ድረስ ባልና ሚስት የሚኖሩበት ህንፃ ነው፡፡ በዚህ ህንፃ ግንባታ ላይ የአላህ እጅ እንዲኖርበት መፍቀድ ብልህነት ነው፡፡ ብቻችንን የምንሰራው ቤት.. ቤት አይሆንም፡፡ አላህ (ሱ.ወ.) የሌለበት ቤት መሰረቱ ደካማ ነው፤ ጣሪያውም ያፈሳል፣ ግድግዳው በቀላሉ ይዘማል፣ ምሰሶው ያረገርጋል፣ ሁለመናው ስጢጥ ስጢጥ ይላል፡፡
ትዳርን ስናስብ ቁሳዊም ሆነ መንፈሳዊ ሰበቡን እናሟላ፡፡ አላህን በቤታችን ስናኖረው ያኔ የቤታችን መሰረት ፅኑ ይሆናል፣ ምሰሶው መሬት ይይዛል፣ ግድግዳው ቀጥ ይላል፡፡
ለአላህ ብለው ያሰቡት ነገር የሱ ጥበቃ አለበት፡፡ አላህ የሰራው ቤት አይፈርስም፣ እሱ ያነጸው ህንፃ አይዘምም፡፡ አላህን ከፊታችን እናድርገው፡፡ ትዳር ወሳኝ ነገር ነዉና ቤታችንን በበረከትና በፍቅር ይሞላልን ዘንድ እሱን እናስቀድመው፡፡ ዋናዉና መቅደም ያለበት እሱ ነዉና የሚቀድመውን በማስቀደም የሚከተለውን እናስከትል፡፡ ለባለትዳሩም የትዳር እድሜ ይስጣችሁ ..ላላገባንም አላህ ፈላጊ ከፈላጊ ያገናኝ አሚን...

           ካሊድ ለኔ ያንን ሁሉ የሒወት ዉጣ ዉረድ አልፌ ለዚህ በቃሁኝ ....ደስተኛ ለመሆን መሞከር ረጅም ለመሆን የሞመከር ያህል ለኔ በጣም ከባድ ነበር የሆነብኝ
ዛሬ የምወደዉ የሚወደኝ ፍቅር ምን እንደሆነ በዱንያ ምድር ካሊድ አሳየኝ፡፡ ፍቅር ማለት ይሄ ነዉ ..ፍቅር ከሆነ ግድ መተማመን አለ .. ካሊድ ቢወደኝ ቢያመነኝ ነዉ ሒወቴን ያረጋጋዉ...ደግሞ ባለፈዉ ታሪኬ እንደ ዶክተር ሷሊህ ያለ ተስፋ እንድቆርጥ የስነልቦና ጫና አድሬሶብኝ...ወንድ እና ቁንጫ በልቶ እሩጫ ብየ ከትዳር አለም ተስፋ ቆርጬ ነበር........የብዙ አመት ጠባሳየ ሲያመኝ ሳለቅስ ከሰዉ በታች ነኝ ብየ ሁሌ እራሴን እንደ አሰብኩ እንደ ካሊድ አይነት ጥሩ አስተሳሰብ ያለዉ ሒወቴን ልቤን ማንነቴ ሳይቀር በእሱ መለሰልኝ ..እኔ ሁሌ ድንግል ነኝ ብየ እንዳስብ አረገኝ...አዎ ሁሌም እኔ ድንግል ነኝ... ለምን አስቤበት አምኜበት ስሜቴን መቆጣጠር አቅቶኝ አሳልፌ የሰጠሁት አይደለም... ገና በልጅነቴ እህሉን ከአፈር በማለይበት ጊዜ ተገድጄ የተቀበልኩት ነዉ፡፡

በሳምንቱ ጁምአ ደርሶ በተለመደዉ ሰአት ተገናኝተን...... ካሊዶ ጋር እያወራን ሁሌም ድንግል ባለመሆኔ ስቆጭ
.....እንደዚህ አለኝ ... ነዋል አትሰቢ አትጨናነቂ ይሄ ተራነገር ነዉ እኮ...አንቺ ግድ መሆን አለብኝ ብለሽ ካሰብሽ የአላህ ነገር አይታወቅም ተስፋ መቁረጥ አንችልም ..... ድንግልም ልትሆኝም ትችያለሽ እኮ.......ለምን ብትይኝ ገና በልጅነትሽ በ4 አመትሽ ነዉ ይሄ በደል የደረሰብሽ ..እና በዛ እድሜ ደግሞ ልጅ ስለሆንሽ የሚጠብቅሽ መላኢካ ነዉ ..እናም ሙሉ በሙሉ ተስፋ አትቁረጭ በአላህ ፍቃድ አንቺ የለኝም ብለሽ የምታስቢዉ ነገር ሊኖር ይችላል አለኝ......


.....,እኔም የHealth ተማሪ እንደመሆኔ መጠን አንዴ ድንግልና ከሄደ እንደማይመለስ አቃለሁ ..ካሊድ በጭራሽ መሆን አልችልም አልኩት
..... ምነዉ ነዋል ከአላህ እኮ ተስፋ አይቆረጥም አለኝ፡፡ ካሊዶ እንደዚህ ሲለኝ እዉነቱን ነዉ ከአላህ ተስፋ አልቆርጥም ብየ እንደገና ሞራል ሰጠኝ፡፡

    አንድ ቀን የሞባይሌ ባትሪ ተበላሽቶ ለመግዛት ጂማ መርካቶ ሰፈር አካባቢ አንድ ኤሌክትሮኒክስ ሱቅ ስገባ..ያየሁትነ ማመን አቃተኝ ...በጣም ደነገጥኩኝ፡፡ ሚፍታህ ጋር ተገናኘን
....እሱም ድንጋጦ ነዋል አሰላሙ አለይኩም አለኝ
.......እኔም ወአለይኩም ሰላም ሰላም ነዉ አልኩት
....እሱም እንዴት ነሽ ሁሉ ሰላም ቤተሰብ ሰላም ናቸዉ?? አንቺስ እንዴት ነሽ ??አለኝ👇👇👇
....እኔም አልሀምዱሊላህ ደህና ነኝ አልኩት
.......እሱም ቀለበቴን እያየ ነዋል ልታገቢ ነዉ እንዴ ??? አለኝ
....እኔም...አዎ ኢንሻ አላህ በቅርብ ቀን አስቢያለሁ አልኩት
ሚፍታህም :- ሽማግሌ ተልኳል ወይስ አልተላከም??? አለኝ
....እኔም ገና አልተላከም በቅርብ ቀን ይልካል አልኩት
....... ነዋል ወላሂ ብየ ነዉ የምነግርሽ በጣም ነዉ የምወድሽ ..አንቺ የሌላ ስትሆኝ ማየት አልችልም... ወላሂ ሁሌም ህልሜ አንቺ ጋር ተጋብቶ መኖር ነዉ፡፡

አንድ ነገር እንድታቂልኝ እፈልጋለሁ ... አንቺ የሌላ ሰዉ ሁነሽ ..ትዳር ከሌላ ሰዉ ጋር ብትመሰርች ፀቤ ከአንቺ ወይም ከአገባሽ ሰዉ አይደለም..ፀቤ ከፈጣሪ ከአላህ ጋር ነዉ..... ለምን ብትይ ሀጅ ባደረኩበት ጊዜ አላህን ከሁሉም ሀጃየ አስበልጬ ስጠይቀዉ ስለምነዉ የነበረዉ....አንቺ የኔ እኔድትሆኝ ነበር... አላህን ስለምነዉ የነበረዉ ከአንቺ ልጅ መዉለድ እስከ እለተ ሞቴ አንቺ ጋር አብሮ መኖር ነዉ አለኝ
....ይሄን ሲለኝ አብረዉ ጓደኞቹ ነበሩ... ይሄን እየተናገረ ሚፍታህ እምባ ነዉ የቀረዉ፡፡
ቁርጤን ንገሪኝ ቁርጤን ንገሪኝ ..የሌላ ስትሆኝ ማየት አልፈልግም የኔ ብቻ ሁኜ እባክሽ እያለ ይለምነኛል
........እኔም በጣም ተወዛገብኩ ግራ ገባኝ...ሚፍታህ ዉሳኔየን በስልክ ደዉየ አሳዉቅሀለሁ አልኩት

ከሱቁ ወጥቼ ወደ ቤቴ እየተመለስኩ ነዉ... ልቤ ተሸበረ ...ዉሳኔ መወሰን አልቻልኩም ...የማልክደዉ እዉነት ቢኖረዉ ሚፍታህ በጣም እወደዉ ነበር ለመጋባት ድረስ ደርሰን ቤተሰብ ለቤተሰብ ተጠይቆ እሺ ተብሎ ጨርሰን እንደነበር በአለፈዉ ታሪክ ላይ ታስታዉሳላችሁ...ሚፍታህ አንቺን ማግባት ነዉ የምፈልገዉ ሲለኝ የማላቀዉ ስሜት ከየት መጣ የማልለዉ ወረረኝ ...እሱ ጋር ያሳለፍኳቸዉ የፍቅር ገጠመኞች ጊዚያቶች ፊቴ ላይ እንደመስተዋት መልሶ ያሳየኛል

  ከዛ እንደዚህ እየተጨናነኩ የምወስነዉ ግራ ገብቶኝ ሁለት ልብ ሁኜ ለካሊድ ደወልኩለት፡፡
  ሰላምታ ከተለዋወጥን ----- ካሊድ እኔን ብታጣኝ የሌላ ብሆን ምን ይፈጠራል ብለህ ታስባለህ ? እኔን አጥተህ ብትኖር ምን ይሰማሀል ??? ብየ ጠየኩት
......ካሊዶ ለካ እንደሌሎቹ ወንዶች አይደለም የመለሰልኝ መልስ አስገራሚ ነበር እንደዚህ አለኝ ... #አንቺን_ማጣት_ምን_እንደሆነ_ነዋል_የኔ_ባትሆን_የሚለዉን_በጭራሽ_ማሰብም_መገመትም_አልፈልግም ፡፡ አንቺ የሌላ ስትሆኝ እንዲህ እሆናለሁ ብየ ምሳሌ እንኳ መስጠት አልፈልግም ... ነዋል እኔን ለመቀለድ ብለሽ እንኳን እንደዚህ አይነት ጥያቄ ዳግመኛ እንዳትጠይቂኝ...አለኝ

ወላሂ ጥፋቱ የኔ ነዉ.... ሶስት አመት በትዕግስት ጠብቆ ከነማንነቴ ተቀብሎኝ...ገና ሚፍታህ አንቺን ነዉ ማግባት የምፈልገዉ ሲለኝ ልቤ ወላዉሎ ካሊድን ይሄን ጥያቄ መጠየቄ ከደወልኩ ቡሀላ ብቻየን አፈርኩኝ..

ዉየ ሳላድር ወዳዉኑ ለሚፍታህ Text ላኩለት ...እንደዚህ አልኩት>>>>> ሚፍታህ ከአሁን ቡሀላ ወደ ሆላ መመለስ አንችልም ትናንት ከትናንትናዉ ጋር አብሮ አልፏል ..በርግጥ የማልዋሸህ በፊት እወድህ ነበር ያደግሞ በጊዜዉ አልፏል ...፡፡ አሁን ላይ መጉዳት የማልፈልገዉ የምወደዉ የሚወደኝ እሱን አጥቼ እሱም እኔን አጥቶ መኖር የማይችል እኔም እሱን አጥቼ መኖር አልችል ሁኜ ልቤ ዉስጥ ያስቀመኩት እሱም ያስቀመጠኝ ሰዉ አለ ብየ ላኩለት......
 

  ሚፍታህ ጋር በዚሁ message አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተለያየን...አንድ የወንድ ልጅ ድክመት አለች እየወደዱ ማግባት እየፈለጉ የተሻለ አገኛለሁ ብሎ ከኔ ዉጭ አታገባም ትጠብቀኛለች ብለዉ እያሰቡ ነገር ግን እሷን የሚወዳት አግኝታ ልታገባ ስትል ትጠብቀኛለች ብሎ ያሰበዉ እንደ አዲስ ከእንቅልፉ ሲባንን ይስተዋላል፡፡ ታዳ ሚፍታህም አገባሻለሁ ብሎ ሽማግሌ ልኮ አጭቶኝ ጥፋቴን ሳላቀዉ አመታት ያህል ረስቶኝ ነገር ግን ላገባ ነዉ ስለዉ እንደገና በቅናት ተንገብግቦ አንቺን ነዉ የማገባዉ ማለቱ አግባብ አይደለም..ሴትነት የእናት ነት የእህትነት ደረጃ እንጂ የምርጫ የቅርጫ ለትዳር መወዳደሪያ አይደለችምና፡፡



ካሊድ ከ 15 ቀን ቡሀላ ቅዳሜ ሽማግሌ እልካለሁ አለኝ
....እኔም መርሀባ ብየ ተስማማሁኝ፡፡


እነዚህ አስራምስት ቀናት ለሁለታችንም እርቃልብናለች ቀን በቀን በተደዋወልን ቁጥር ይሄ ቀን ቀረን እያልን ሲቀርብ ሲቀርብ ..ሶስትም አልፎ ሁለት ቀናት ቀረን ፡ ነገ ቅዳሜ ሁኖ ዛሬ ጁምአ ላይ ደርሰናል  
......ከዛም ጁምአ ቀን የኔ ፈተና መቼም አይለቅ ...ያልተሳበ ይሆናል ብየ ያልገመትኩት በራልኝ ስል የጨለመብኝ የሒወት አዙሪት በባሰ መልኩ አይኑን አፍጥጦ መጣብኝ...እኔ ስፈጠር እንዳትደሰቺ የተባልኩ ይመስል....ያላሰብኩት ነገር ተፈጠረ የሸይጧን መሰናክል ሁሌም ቢሆን አይጠፋም.....



#ክፍል 2⃣6⃣

ይ...............ቀ.............
..........ጥ...........ላ...............ል

Join👇👇👇
💐_⭐️💐⭐️___💐
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሀያ ስድስት 2⃣6⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ

ከዛም ጁምአ ቀን ያልተሳበ ይሆናል ብየ በራልኝ ስል የጨለመብኝ የሒወት አዙሪት በባሰ መልኩ አይኑን አፍጥጦ መጣብኝ...እኔ ስፈጠር እንዳትደሰቺ የተባልኩ ይመስል...ያላሰብኩት ነገር ተፈጠረ የሸይጧን መሰናክል ሁሌም ቢሆን አይጠፋም ፡፡
 
     ቅዳሜ ካሊድ ሽማግሌ ሊልክ ጁምአ እናቴ ከአባቴ ጋር ተጣልታ ዘመዶቿ ጋር ሄደች ፡፡ በእኛ ሰፈር የሚገኙ ሽማግሌ ተሰብስበዉ ሁለቱም እንዲታረቁ ቢለመኑ ..አንታረቅም የኛ መጨረሻዉ ፍች ብቻ ነዉ መፍትሄዉ ብለዉ በጭራሽ ሊስማማሙ አልቻሉም፡፡
...እኔም ለካሊድ ደዉየ ቤተሰቦቼ እንደተጣሉ እና ሽማግሌዎቹን እንዳይልክ ነገርኩት

ጊዜያቶች እየነገዱ ነዉ....አባቴ ሌላ ሴት ለማግባት እየፈለገ ነዉ...እናቴም ፍርድ ቤት ከሳ ንበረቱን ተካፍላ ከቤት ይዉጣልኝ እያለች ነዉ፡፡ ነገሩ በጣም ሲጠና ...አባቴ ለልጆቼ ብየ እታረቃለሁ ቢልም ..እናቴ ግን በጭራሽ አልታረቅም ብላ አሻፈረኝ አለች.... የሰፈር ታዋቂ ሸሆች... የመስጊድ ኢማማችን ሳይቀር ቢለምኗት እምቢ አለች፡፡


እኔ እና ካሊድ ለመጋባት 100% ጨርሰናል ሁለታችንም ለትዳር ልባችን ቢንጠለጠልም ግን እናት እና አባቴ ተለያይተዉ በሚኖሩበት ቤት በተበታተነ ቤተሰብ ለማን ሽምግልና ይላካል??? ዱአ ከማድረግ ዉጭ ምንም አማራጭ የለም...

   ደግሞ አዲስ ነገር የማይፈጠር የለም ...ሚፍታህ ደወለልኝ እና ...ነዋል አንቺን ማግባት ነዉ የምፈልገዉ ነዋል ከልቤ ነዉ እወድሻለሁ ሽማግሌ ልልክ ነዉ አለኝ
......እኔም ሚፍታህ አሁን መቼም ቢሆን የአንተ መሆን አልችልም ለሁሉም ጊዜ አለዉ አንተም በጊዜህ እኔን ትተህኛል...አሁን እኔም ልቤ የሌላ ነዉ ...ተስፋ ቁረጥ እንደፈለክ የምከፍተዉ የምዘጋዉ የቤትህ በር አይደለሁም አልኩት ቆጣ ብየ
 

አይጠቅምም ብለዉ የጣሉት እቃ ሌላ ሰዉ አንስቶ ሲጠቀምበት ምነዉ ባልጣልኩት ብለዉ ይቆጩ የለ... ..ሚፍታህ እኔን ትቶኝ ላገባ ፕሮሰስ ላይ መሆኔን ሲያቅ ..እንደገና ካላገባሁ ሙቼ እገኛለሁ..ሽማግሌ ልልክ ነዉ እያለ አሁንም ተስፋ ያልቆረኩ ይመስለዋል..ሴት ልጅ ስወድ ወደደች ነዉ ከጠላች ደግሞ በእሷ መስፈርት ሁሉንም አሟልተህ ብትገኝ ከጠላችህ መቼም በልቧ መግባት እንደማችል እንደነ ሚፍታህ ያሉ ወንዶች ዘንግተዉታል... መቼም ካሊድን በማንም የማልቀይረዉ እዉነተኛ የትዳር አጋሬ ነዉ፡፡

✿✿✿ ምርጥ ጓደኛየ መፍቱሀም ተመርቃ የግል ሆስፒታል ዉስጥ ገብታ እየሰራች ነዉ..

✿✿✿ብሩክታይትም ቢላል የሚባል የወንዶች የጀመአ አባል ብሩክታይት ዲነል ኢስላምን አስተምራለሁ ቁርአን አቀራታለሁ ብሎ መፍቱሀን እና እኔን አማከረን ...እኛም ብሩክታይትን አማከርናት ... ቢላልን ታቀዋለች በትዳር ጥያቄዉ ተስማማች .. ስሟንም በራሷ ፍቃድ ብሩክ ታይት ሳይሆን ራዉዳ ነኝ ብላ ከቢላል ጋር እህል እና ዉሀቸዉ ገጥሞ በትዳር አለም አብረዉ መኖር ጀምረዋል፡፡

✿✿✿ ካስታወሳችሁ በአለፉት ክፍል ናርዶስ(በአጎቷ እና በአባቷ ጓደኛ በልጅነቷ የተደፈረችዉ) በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ ተምራ ተመርቃለች

✿✿✿ የሱፍ (ለሚፍታህ ነዋልን ዳረኝ ብሎ ስልኩን የሰጠዉ) እሱ ደግሞ ሚፍታህ ጋር አንዴ ተጣልተዉ...ነገሩ ከብዶ ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሂደዉ ነበር በሽምግልና ታረቁ ቢባል የሱፍ በጭራሽ አልታረቅም እበቀለዋለሁ እንዳለ ቂም እንደያዘ .. በመጨረሻም የሱፍም ቤተሰቦች እነሱዉ አምጥተዉ እሱም ጎጆ ቀልሶ እየኖረ ነዉ፡፡

✿✿ ሚፍታህም በንዴት ይሁን አስቦበት አላቅም እኔ ላገባ ነዉ ከአሁን ቡሀላ አንተ እና እኔ አንድ ላይ መሆን አንችልም ካልኩት ቡሀላ ...ብዙም ሳይቆይ አንድ ወር ባልመላ ቀናት ዉስጥ እኔን አናዳታለሁ ብሎ አስቦ ይሁን ..ትዳሩን አምኖበት ይሆን...ነዋልን ልቀደማት ብል አስቦም ይሆን አላቅም እሱም የትዳር ጎጆዉን ቀልሷል

✿✿✿ ካሊድም የቤት እቃ እያማሏ ነዉ ፡፡ እኔም ነገሮች እስከሚስተካከሉ ብየ ጅማ የሚገኝ የመንግስት ሆስፒታል በተመረኩበት ፊልድ ማገልገል ጀመርኩኝ...አልሀምዱሊላህ አባቴ ያሰበዉ ደረጃ ደረስኩኝ ..

ሆስፒታል መቼም የብዙ ሰዉ ብሶት መቀበያ አይደል....እንደ እኔ በልጅነታቸዉ የተደፈሩ ሴቶች በጣም ብዙ ገጥመዉኛል ..ልጆችን በማፅናናት ከጎናቸዉ በመሆን እነሱን ማገዝ የአእምሮ ጭንቀት እንዳይዛቸዉ የስነልቦና አገልግሎት መስጠት የዘወትር ስራየ ነዉ. .በተጨማሪም በፍቅር ለተጎዱ ሴቶች ...እንደ እኔ በቤተሰብ ፍቅር ዉጭ ለአደጉ ልጆች..በተለያዩ ጉዳዮች ዲፕሬሽን(በአእምሮው ጭንቀት) የተጎዱ የዱንያ የአኼራ እህቶቼን ከጎናቸዉ በመሆን እነሱን መንከባከብ በሀሳባቸዉ ተረድቼ መፍትሄ ስሰጥ ለኔ የዉስጥ ደስታ ሰላም ይሰጠኛል፡፡ የሰዉ ልጅ ደስታዉ ብቻዉን መቀየሩ ደስታን ማግኘቱ ሳይሆን በእሱ የተነሳ ስንት ሰዉ መቀየሩ መደሰቱ ታላቅ ደስታ ነዉ..

የሚገርማችሁ እዛዉ ጤና ጣቢያ በሴት ልጆች ላይ የሚደርሰዉ በደል ሳይ የኔ ምን አለበት አልሀምዱሊላህ ያልኩባቸዉ ብዙ ቀናቶች አሉ..
እኔ ከገጠመኝ በታላቅ ወንድሞቻቸዉ የተደፈሩ ልጆች ገጥሞኛል..በተዘዋዋሪ ጭካኔ የበዛበት ዘመን መሆኑ ያሳዝናል ብዙ ህፃናት በአባቶቻቸዉ ተደፍረዉ የሚመጡ ብዙ ልጆች ገጥመዉኛል፡፡እኔ አንድ ሴት ነኝ ከጎኔ ማን አለ?? ሁሉም ከጎኔ ባይሆኔም ግን እንደ እኔ ተብድለዉ በሆዳቸዉ አፍነዉ የሚኖሩ ቤት ይቁጠረዉ,..... መቼ ድረስ ነዉ የሴት ልጅ እምባ መዉረድ የሚያቆመዉ ??? ሁሌም በልቤ ቁጭት አለ ታዳ ምን ያደርጋል አንድ ሰዉ አስቦ አንድ በሬ ስቦ አይሆንም...እኔ የራሴን ታሪክ በፁሁፍ ዘረገፍኩት እንጂ ብዙ ሴቶች አሁን ድረስ ዛሬ ከነገ ይሻላል ቢሉም ግን የብስ እየጨለመ የሚሰቃዩ ለቁጥር አይገባም. ... እንደ እኔ እንቅልፍ አጥተዉ የሚኖሩ ሴቶች አይናገሩ ሰሚ የለ ....ለማን ይነገር?? በእንባ ጎርፍ ለፈጣሪ አቤት ከማለት በቀር ፡፡ ስለሆነም ወንዶች እባካችሁ ለሴት ልጆች እዘኑ ይሄ ሁሉ ለቅሶየ ስቃየ በኔ በራሴ የመጣ አይደለም በጨካኝ ስሜቱን መቆጣጠር በአቃተዉ ወንድ የተፈጠረብኝ በልጅነት መደፈር ነዉ ፈጣሪ ሁላችንንም ልቦና ይስጠን

ቢያንስ ከ5 ወራት ቡሀላ በስንት ሽምግልና አልሀምዱሊላህ እናት እና አባቴ ተስማምተዉ መልሰዉ አብረዉ መኖር ጀመሩ ..

እናት እና አባቴ ታርቀዉ ብዙም ቀን ሳይቆዩ በቤተሰብ የትዳር ጥያቄ መጣ ...
ማታ ላይ ሳሎን ቁጭ ብለን አባቴም፡- ነዋል ይሄ መታለፍ መመለስ የሌለበት ትዳር ነዉ..እኛ እንተማመንበታለን ጥሩ ሰዉ አላህን ፈሪ ነዉ ፡፡ነዋል እኔ አባትሽ ለምወድሽ ልጄ መጥፎ ምርጫ እንደማልመርጥ ታቂያለሽ .. አሁን የመጣዉን ትዳር እንድታገቢ ምርጫየ ነዉ እሺ በይኝ አለኝ
....... አባቴ አንተ የተናገርከዉ ልክ ነህ ...ነገር ግን እኔ ትልቅ ልጅ ነኝ የሚጠቅመኝን የሚጎዳኝን ለይቻለሁ ..እኔን በደስታ ሊያኖረኝ የሚችል የኔ የራሴ የምለዉ አንድ ሰዉ አለኝ አልኩት
.....አባቴም ማን ነዉ ልጁ እኔ አቀዋለሁ??አለኝ
....እኔም አዎ ታቀዋለህ ካሊድ ነዉ ብየ ... እሱን እንዲያቁት በምልክት ሰፈሩን ቤተሰቡን ስነግራቸዉ እናቴም አባቴም አወቁት👇👇👇
......እናቴም፡- በጭራሽ ካሊድ ጋር እንድትጋቡ አልፈቅድልሽም ... ለምን ብትይ ሹፌር አይታመንም ሴቶችን ሲያጀዝቡ አይደል እንዴ የሚዉሉት ??..እኔ በካሊድ አልስማማም አይኔ እያየ ለካሊድ አልድርሽም አለችኝ
...እናቴ ጋር በዚሁ ምሽት ዉርክብ ብጥብጥ ተፈጠረ በጭራሽ መግባባት አልቻልንም ... አባቴም በኔ ምርጫ ጣልቃ ላለመግባት ፈልጎ...ነዋል ትዳር ቀልድ አይደለም ተረጋግተሽ እሰቢበት አለኝ..እናቴ ደግሞ ሹፌር መቼም ቢሆን አታገቢም እያለች እየደነፋች ነዉ፡፡

ለነገሩ በእናቴም አልፈርድም አሁን ዘመን ላይ ያሉ ሹፌሮች አላማቸዉን የረሱ ከትርፉ ላይፉ እያሉ ራሳቸዉን እና ሞኝ ተላላ ሴቶችን የሚታልሉ ብዙ ፡ናቸዉ ...ደግሞ በተዘዋዋሪ ሹፌሮችን የሚያስቸግሩ ሴቶችንም እያስተዋልን ነዉ...

ጃፓን መኪናዉን ስትሰራዉ መሪዉ ላይ ሹፌር ሹፌር የሚያስብል የቀበረችበት ያለ ነዉ የሚመስለዉ...ግን ከሁሉ የሚያናደኝ በነዚህ ጋጠወጥ ሹፌሮች እንደ ካሊድ ያሉ ምርጥ ለሴት ልጆች የሚያስቡ ሹፌሮች አብረዉ መወቀሳቸዉ እና መሰደባቸዉ አሳዛኝ ነዉ

★★★ አንዲት አበባል አለች ጭልፊት የወደቀ ስጋን እንጂ በቁሙ ያልተገፈፈ በግን እንደማይነካ የታወቀ ነዉ፡፡
እህቴ ሆይ ሒወትሽ እንደ በግ ነጋዴ በግ ተራ እንደወሰደዉ በግ እጣ ፈንታ አትወስኝ...አንድ በግ ሊሸጥ ሲል በጣም ብዙ ገዥ አገላብጦ ሽንጡን እየያየዘ ስጋ አለዉ የለዉም እያለ ያየዋል..ከተቻለ ዛሬ አለዛም ነገ ቀይም ከነገ ወዳ ሲገላበጥ ቢቆይም ይሸጣል.. አንቺም እንደዚህ እንደሚሸጥ በግ አላማቸዉን ከዘነጉ ተኩላ ወንዶች እያገላበጡ እየታየሽ አለፈች ወደቀች እየተባልሽ በየመንገዱ ስትሄጅ ግምገማ አትቀረቢ...መስሪያ ቤት ግምገማዉ በወር ወይ በአመት ነዉ...አንቺ ግን ኮስሞቲክስ እየተጠቀምሽ ቀን በቀን የወንዶች መሳለቂያ አትሁኝ...ሒወትሽ ሊሸጥ ገበያ የሄደ በግ አይነት እንዲሆን በራስሽ ጊዜ አትፍቀጅ...
ብዙዎች ሴቶች በመጥፎ ጓደኛ ግፊት እንየሚበላሹ የማይካድ ሀቅ ነዉ
ግን እህቴ ሴት ልጅ ብዙ ነገሮችን ተቋቁማ ወደ ትዳር አለም ትገባለች ያንን እንዴት ነዉ ፈተናዉን ማለፍ ያለብሽ?? ..ሴቶች ተማሪዎች አብረሽ መደበኛ ትምህርት ስትማሪ ሁሉንም ትምህርት ሂሳብ እንግሊዝ አማረኛ civics ወ.ዘ.ተ ዉጤትሽ ጥሩ ሊሆን ይችላል ግን ከትምህርት ዉጤትሽ በላይ የአንቺ የሂወት ዉጤትሽ ጓደኞችሽ ሲሆኑ  የጓደኞችሽ ግፊት አንቺን ወደ ማፈልጊዉ ወደ ማታቂዉ አለም ትገቢያለሽ ...ስምንት ማትሪክ ስትፈተኝ ጥሩ ዉጤት አመጣሽ ወደ ዘጠኝ አለፍሽ ከዛስ አስርም አለ ማትሪክን ስትወስጅ ከዘጠኝ እና ከአስረኛ ክፍል ከበፊቱ ምን ለዉጥ አለኝ?? ቂርአት ላይ ጥሩ ነኝ ወይስ መጥፎ የሴት ጓደኞች አሉኝ ወይስ በሀራም ከወንድ ጋር ሀራም የሆነ የማይጨረስ ፍቅር ጀምሪያለሁ ወይ?? ወ.ዘ.ተ የሚለዉን አንቺ እራስሽ ለራስሽ ጥያቄዉን አቅርበሽ መመለስ አለብሽ
ከዛስ ማትሪክ ተፈተንኩ ትምህርቴን ካለፍኩኝ 11 ክፍል ስገባ አላማየ ምን መሆን አለበት ከ10 ብወድቅስ ? ብለሽ እሰቢ

እህቶቼ አራት አመት ፈተናዉን ማለፍ መታገስ ከቻላችሁ የወደፊት የእናንተ ከአላህ ጋር የአርባ አመት ፕላናችሁ መስተካከል ይችላል ፡፡ ግን አራት አመት ላይ ግን የምትሸወዱ ከሆነ በሀራም ከአጂ ነቢ ጋር ግንኙነት ከጀመራችሁ ለአንድቀን ለዛዉም 20 ደቂቃ ለማይሞላ ስሜት የ40 አመታት ፕላናችሁን ታበላሻላችሁ ማለት ነዉ፡፡ እነዚህ አራት አመታት እነማን ናቸዉ ካልን ከዘጠነኛ ክፍል እስከ 12 ክፍል ያሉትን አመታት ፋየር ኤጅ ሁሉም አለሁ አለሁ ከሰዉ በላይ ነኝ የሚባልበት እድሜ ነዉ ስለሆነም እነዚህ የትምህርት አመታት የወደፊት ሂወታችሁ ወሳኝ ናቸዉ፡፡ University በምገቡበት ጊዜ እናንተ የአራት አመቱ ምርት ዉጤት ናችሁ አራት አመቱን በመጃጃል ያሳለፍሽ ከሆነ university ከቤተሰብ ቁጥጥር ዉጭ ነሽ ለቤተሰብም ለሀገርም ለአንቺም አጠቅሚ ትበላሻለሽ ..


...በዚህ ሁኔታ እኔ ካሊድን አገባለሁ እናቴም በጭራሽ አታገቢም እያለች ቀን በቀን ስንጨቃጨቅ የአላህ ነገር ይሄ covid 19 መጥቶ ከችክችክ ከንዝንዝ አረፍኩኝ...የሰዉ ወሬ ስለዚሁ በሽታ ሲሆን እናቴም ጋር ስለትዳሩ ሁኔታ ማዉራት አቆምን

..የእኔ እናት አላማዋ እኔን ከሀብታም ጋር በትልቅ ድግስ በሰፊ ሰርግ እኔን ለመዳር ነበር ....የነብዩ ሰ.ዐ.ወ የሰርግ ስነ-ስርአት እና ሱና ነገሮች ለመተግበር የመጣ ይመስላል ኮረና ደሀም ሀብታምም ሰርጉ ልዩነት የለዉም ሁሉም በኒካህ ኢስራፍ ከሆነ ከሰርግ ወጭ ገላግሏል፡፡

ቤተሰቦቼም በአባቴ ጥረት ብዙ ነገሮችን ከጠየቀኝ ቡሀላ አባቴ ተስማምቶ እናቴም ባይዋጥላትም በግድ ካሊድን እንዳገባ ፈቀደችልኝ .. ከካሊድ የ 2012 ረመዷን ሊደርስ የተወሰኑ ቀናት ሲቀረዉ በትንሹ ሰርግ ተደግሶ ...እኔም ጂልባቤን ለብሼ መፍቱሀ እና ሩቅያም ሌሎች የዓሊይ መስጂድ የጀመአ ጓደኞቼም በጅልባባቸዉ አምረዉ ድምቅ ብለዉ ከጎኔ ሁነዋል...አልሀምዲሊላህ እኔም ከምወደዉ ከሚወደኝ ካሊድ ጋር የሰርጌ ቀን ደረሰ...

ካሊድም የተወሰኑ ጓደኞቹን ይዞ መጥቶ ኒካህ ታስሮ ያሁሉ ጉፍ መከራ ለቅሶ አልፎ የሚስትነት ማዕረጉን ይዤ ከእናት አባቶቼ ተለይቼ  ካሊድ ጋር የትዳርን ህይወት አሀዱ ብለን ልንጀምር እሱ ጋር የሰርጌ ምሽት ሄድኩ ፡፡ ሁለታችንንም የናፈቀንን የሀላል ጨዋታ ምሽት ላይ ጀምረናል፡፡ ሰርግ ላይ ሲጨፈር የምሰማት ግጥም ትዝ አለችኝ እስኪ ልበላት
ካሊድ ምሽት 3:45 ታላቅ ፍልሚያ አለዉ
እኛም አላገዝነዉ አላህ ይሁነዉ
የሚሏት ግጥም እዉነትም ከፕሪሚየርሊግ የበለጠ ፍልሚያ ነዉ ...

ከዚህ ፍልሚያ ቡሀላ ያልተጠበቀ ይሆናል ብላችሁ የማጠብቁት ነገር እኔም ማመን ያልቻልኩት ነገር ተፈጠረ ...

#የመጨረሻዉ_ክፍል

ይ.......ቀ.........ጥ............ላ................ል

          `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል#የመጨረሻዉ_ክፍል

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ


ከዚህ ፍልሚያ ቡሀላ ያልተጠበቀ ይሆናል ብላችሁ የማጠብቁት ነገር ተፈጠረ

እኔም ካሊድም ገረመን አላህ ምን ይሳነዋል..
ይገርማል አረ በጣም ይገርማል ገርሞም ይገርማል የሚገርም ነዉ... #ድንግል ነበርኩኝ ፡፡ በአራት አመቴ ተደፍሪያለሁ እያልኩ ሳለቅስ ኑሬ ...በትምህርት ቤት በሰፈር በልጅነትሽ የተደፈርሽዉ እያሉ ሲያስለቅሱኝ ሲያገሉኝ ያለፉት የኖርኩባቸዉ አመት አላህ እኔን እየፈተነኝ እንደሆነ ተረዳሁኝ
...ካሊድም እየተገረመ ነዋል ታስታዉሻለሽ በምታለቅሽበት ጊዜ የአላህ ነገር አይታወቅም ድንግልም ልትሆኝ ትችያለሽ ስልሽ አላምንም ብለሽ ነበር ከአላህ ምንም ተስፋ መቁረጥ አያስፈልግም አለኝ

#የጫጉላየ_ምሽት

ፊቴ አብርቶ ጥርሴ ይስቃል
ከጀርባ ያለዉ ሀዘን ከቶ ማን ያዉቃል
እንዲህ ደምቄ ፈክቼ ላየኝ ሰዉ
በሆዴ ፍም እሳት ያለም አይመስለዉ

ዛሬ ላይ ሁኜ የትናንቱን ግፍ አስታዉሳለሁ
በትዝታ መስኮት እያንዳንዱን ህመም እመለከታለሁ

በጨቅላ እድሜየ ክፉን ከደጉ ባለየሁበት
ጫማ ለመልበስ ግራዉን ከቀኙ ባላወኩበት
ስጋና አጥንቴ ከደሜ ጋራ ሳይዋሀዱ
ሁለቱ እግሮቼ እንኳን እርቀዉ ሳይራመዱ
ሲመሩኝ ምመራ ኩልትፍትፍ የምል
ዉብ ፅጌሬዳ ሲያዩኝ ደስ የምል

እንኳን ጭካኔ ለኔ ሊገባኝ
ለቁንጥጫ እንኳን የማሳሳ ነኝ
ምን ዋጋ አለዉ የሰዉ አዉሬ ጨከነብኝ
ለማይረባ ለደቂቃ ስሜቱ ተጫወተብኝ
ከሰዉ በታች አድርጎ እንዳልነሳ ቀበረኝ
አንገቴን ላይነሳ እንድደፋ አደረገኝ

ያ! ሰው መሳይ ሰው ያልሆነው
ህልሜን በአንድ ቀን አጠልሽቶ በላዉ
ቅስሜን ሰብሮ ልቤን አደማዉ
ያ የሰዉ አዉሬ ደስታየን ነጥቆ ሀዘን አሸከመኝ
ሚስጥሩን ያወቀም ከጎኔ እንዲሸሽ አረገኝ


ሂወትን በጠላሁ ሰው ባጣሁ ሰአት
ሞቴን ስናፍቃት ቀብሬን ስመኛት
ትዝ አለኝ አንድ ቃል የመጠጊያዬ
ለምኑኝ ሰጣለው ያለውን ጌታዬ

ያኔ በጥዋት በማታ በቀን በለሊት
እንባየ ሲፈስ ለብዙ አመታት
አብሽሪ የሚለኝ ሀዘኔን አይቶ
እንባየን አባሽ አንድ ሰዉ ጠፍቶ
ተደፍረሻል ብለዉ ሰዎች ሲሸሹኝ
እጆቼን ዘርግቼ ያረቢ አልኩኝ

እኔም ሁሉንም ትቼ ወደሱ ሸሸሁ
እንደመርየም ንፁህ መሆንን ተመኘሁ
ማንነቴን የሚቀበለኝ ደግ ባሪያህን ስጠኝ ብየ አንገቴን ሱጁድ ላይ ደፋሁ
ሌት ተቀን እየሰገድኩ አምርሬ አነባሁ
ያረብ አልኩት አላህም ዱአየን ሰምቶኝ
ማንነቴን ተቀብሎ የወደድኩት የወደደኝ
ደጉን ባሪያዉን የዱአሽ ዉጤት ብሎ ሰጠኝ
ሀዘንሽ ሀዘኔ ደስታሽም ደስታየ ብሎ ተቀበለኝ

የበደለኛ እንባ መች ይቀራል ፈሶ
ትአምር አየሁ ዱአየ ደርሶ
ልክ እንደመርየም እንደጠየኩት
ቢክራ አደረገኝ በሰርጌ ምሽት
በደቂቃዎች ሁኔታዎችን የሚቀያይር
ለኛም አሳየን የማይታመን ትልቅ ታአምር

ነብዩ ዪኑስን
ከአሳ ነባሪ ፈልቅቆ አወጣዉ

ነብዩ ሙሳን
ከሚያሰምጥ ዉሀ ነፃ አወጣዉ
ነቢዩ እስማኤልን
በአንገታቸዉ ላይ ያንን ቢላዋ አቅም አሳጣዉ

ለነቢ ኢሳ
የሞተዉን ሰዉ ህያዉ እንዲያደርግ ችሎታ ሰጠዉ

ነቢ ኢብራሂምን
ከዛ ከነበልባሉ ከአስፈሪዉ እሳት ነፃ አወጣዉ

የሰዉ ዘርን
ከአፈር ከጭቃ በታላቅ ጥበብ አቡክቶ ሰራዉ

ከመርየም ገላ ክብርዋ ሳይነካ ልጅ ፈጠረው

ታድያ...!

ይሄን ያረገ ታላቁ ያመውላ
ድንግል ማድረግ የነዋልን ገላ
እንዴታ ይሳነው እሱ እኮ ጌታ ነው
ሁሉ ሚታዘዘው ሁን ሲል የሚሆን ነው

ዛሬ ያሁሉ ሀዘንና ስቃይ ተወግዶ
በደስታ ተተካ የሀዘን ተራራዉ ተንዶ
አልሀምዱሊላህ ከማለት ዉጭ ምን ይባላል
በርግጥም ሁኔታዉ አጃኢብ ያስብላል
እልፍ ምስጋና ጥራት ይገባዉ
ለአንዱ ጌታችን ወደር ለሌለዉ

ይሄዉ ከአራት አመቴ ጀምሮ ሳለቅስ የኖርኩትን በአንድ ቀን ወደ ደስታ ቀየረዉ...በጣም ደስተኛ ነኝ ያለፉትን ጊዜያት ሀዘኔ  ከአሁኑ ደስታ ሳወዳድረዉ የሰማይና የምድር ልዩነት አለዉ ሌላ ምን ይባላል አልሀምዱላህ


ልብ በይ እህቴ!!!! በሴቶች ላይ የሚገኘዉ ገቢ በዓመት ከ7ቢሊየን ዶላር እንደደረሰና..ይህም ገቢ ከመሳሪያ ሽያጭና ከአደንዛዥ እፅ ቀጥሎ በሶስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥናቶች ይገልፃሉ

እህቴ ሆይ የሴቶች እኩልነት ብለዉ ምዕራባዉያን ለአንቺ የሰጡሽ መብት ምን አንቺን ለማጃጃል እንደሆነ ምን ያህል ታቂያለሽ? ለምሳሌ ስፔን እንዉሰድ የሴቶች መብት ተብሎ መስሪያ ቤት ገብተዉ እየሰሩ ነዉ ..በስፔን በተደረገዉ ጥናት ከአንድ ሚሊየን በላይ ሴቶች በየመስሪያ ቤቱ የመደፈር ሙከራ ተደርጎባቸዋል፡፡ በስፔን ዋና ከተማ ማድሪድ ብቻ በተደረገዉ ጥናት 13100 ሴቶች በአለቃዎቻቸዉና በስራ ባልደቦቻቸዉ የመደፈር ሙከራ ተደርጎባቸዋል..በአጠቃላይ 15% የሚሆኑት የስፔን ሴት ሰራተኞች በጠቅላላ 8ሚሊየን 425 ሺ ሴት ሰራተኞች ለመደፈር አደጋ እንደተጋለጡ ጥናት ያሳያል፡፡ደፈራ የተደረገባቸዉ ሴቶች ስማቸዉን ለመጠበቅ እና ከሀፍረታቸዉ የተነሳ ለሚመለከተዉ አካል ክስ አይመሰርቱም ..ክስ ለመመስረት ሙከራ ያደረጉት 25% ብቻ ናቸዉ..56% ተደብቀዉ ይገኛሉ..8% የሚሆኑት ክስ በመመስረታቸዉ ከአለቆቻቸዉ ከሚሰሩት ድርጅት ከስራ እንዲሰናበቱ ተደርገዋል..45% የሚሆኑት ከስራቸዉ እንዳይባረሩ የመደፈርን ችግር ተቀብለዉ ጊዚያቸዉን ያሳልፋሉ፡፡ በዚህ የተነሳ ሴቶች ለጭንቀት ለመረበሽ ሰላምና እንቅልፍ አልባ ለመሆን አደጋ ስለተጋለጡ የማስታገሻና የማረጋጋት መድሀኒት ለመዉሰድ ተገደዋል፡፡ ሴቶች በእኩልነት ወደ መስሪያ ቤት በመግባት ባስከተለባቸዉ የጭንቀት በሽታ በአሜሪካ 61% በኢማራት 38% የጭንቀት ማስታገሻ መድሀኒት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ እናም እህቶቼ መብቴ ነዉ እያልሽ በዚህ አዘቅት ዉስጥ እንዳትገቢ አንቺም ተጠንቀቂ ሰዉ ሲሸወድ ሲዘነጋ በአንድ ቀን አይለይም በሒደት በጊዜ ብዛት እየተንሸራተተ ነዉ የሚሄደዉ የአቋም መዋዠቅ ሲገጥምሽ ጠርጥሪ

★ የሴት ልጅ ጥቃት መቼ ነዉ የሚያበቃዉ? አንተም እሱም እነሱም እነዛም ዘር ብሔር ሀይማኖት ሳይለያየን ከጎናችን ቁሙሉን ..ሴት እናትህ ነች እህትህ ነች ለቅሷዋ ሊያስለቅስህ ሊያስዝነን ይገባል፡፡ ለሴት ልጅ ክብር የሚጨነቅ ሴትን ልጅ ለስሜት ብቻ ማሰብ ትተን በሆዷ ዉስጥ አፍና የምትዞረዉን የፉም እሳት ለመረዳት ሞክሩ .ሴት ልጅ ሀዘን በዉስጧ እያለ በጥርሷ ደስተኛ ተጨዋች መስላ መኖር የምትችል ፍጥረት ነች .ማንኛዉም ሴት ስለሳቀች ስለተደሰተች ደስተኛ አይደሉም ብዙዎቹ ለሊት ላይ ሲጨነቁ ሲጠበቡ ሲያለቅሱ የሚያድሩ በብዙ የሀሳብ ማዕበል እና ሆዳቸዉ ዉስጥ ተናገረዉ የማይወጣ የሚቀጣጠል ጥፋ ቢሉት የማይጠፋ እንደዉም እየተፏፏመ የሚሄድ የእሳት ማዕበል ተሸክመዉ የሚሄዱ ናቸዉ ..እናም አንተ ወንድ ነህ በእሳት ላይ እሳት ከመጨመር በሆዷ ያለዉን እሳት አንተዉ ተረድተህ በስሜት መነዳቱን ትተህ ሸክማን በሀሳብህ ተቀብለህ እሳቱን በብልሀት አጥፋላት..የዛን ጊዜ አንተ ለሷ የደስታ ምንጭ እና የህሊና እረፍት ታገኛህ
ታሪኬ ከሞላ ጎደል ይሄን ይመስላል፡፡
አሁን ላይ የአንድ ልጅ እናት ነኝ...ወንድ ልጅ አላህ ሰጥቶኛል አድጎ ለዲነል ኢስላም የሚጠቅም ልጅ እንዲሆን ዱአ አድርጉልኝ፡፡👇👇👇
2024/09/21 20:17:34
Back to Top
HTML Embed Code: