Telegram Web Link
🟢🟡🔴
ጳጒሜን 3 |
የመላእክት አለቃ የከበረ
#ቅዱስ_ሩፋኤል በዓሉ ነው።

እርሱም ከመላእክት አለቆች ሦስተኛ የሆነ ነው።
ደግሞም ከእስክንድርያ ውጭ በደሴት የታነፀች ቤተ ክርስቲያኑ በከበረ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የተገለጸባት የከበረችበት ነው።

ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው። ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔርም በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮኹ።

ያን ጊዜ ይህ የከበረ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ እንዲህ አለው፦ እግዚአብሔር አዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጽ ጸጥ ብለህ ቁም። አንበሪውም ጸጥ ብሎ ቆመ አልታወከም። በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለሕሙማንም ፈውስ ሆነ።

🍀 ለእግዚአብሔር ልጅ ምሳሌው የሆነ #የመልከጼዴቅ መታሰቢያው ነው።

አብርሃምም ከጦርነት ነገሥታትን ድል አድርጎ በተመለሰ ጊዜ ኅብስትንና ወይንን አቀረበለት። አብርሃምም ከገንዘቡ ሁሉ ከዐሥር አንድ ሰጠው እርሱ ካህንም ንጉሥም ሁኖ ተሹሟልና።

🍀 መልካም ስም አጠራር ያላቸው #ዓፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ ዐረፉ።

ተአምረ ማርያምን ጨምሮ ከ11 ያላነሱ መጻሕፍትን በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ደርሰዋል። ብዙ መጻሕፍትን ከውጪ አስመጥተው አስተርጉመዋል፡፡ ሰው ሁሉ ለእመ ብርሃንና ለቅዱስ መስቀሉ ፍቅር እንዲገዛ ጥረት አድርገዋል፡፡

እመቤታችንን በፍጹም ልባቸው ከመውደዳቸው የተነሣ ዛሬም ድረስ በሃገራችን ድንግል ማርያም "የዘርዓ ያዕቆብ እመቤት" እየተባለች ትጠራለች፡፡

🍀 #ቅዱስ_ሰራጵዮን ዐረፈ።
ይህም ቅዱስ ራሱን ባርያ አድርጎ እየሸጠ አሕዛብን ወደ ክርስቶስ የሚመልስ ነው።


🍀 ባለ ስድስት ክንፉ፣ በቃልኪዳናቸው መልአከ ሞትን የማያሳዩት #አቡነ_ቀፀላ_ጊዮርጊስ ዐረፉ።

T.me/Ewnet1Nat
Audio
መልክአ ቅዱስ ሩፋኤል
Audio
የቅዱስ ሩፋኤል ክብር እና ሥልጣን
በመሬት መንሸራተት የ3 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ትናንት ጷጉሜ 2/2016 ዓ.ም በቄለም ወለጋ ዞን ጅማ ሆሮ ወረዳ በሶስት ቀበሌዎች ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት በንብረት ላይ እና የሶስት ሰዎች ህይወት አልፏል። ተጨማሪ በ10 የአርሶ አደር ቤቶች ላይ አደጋው ጉዳት ሲያደርስ፣ በ15 ቤተሰብ እና 150 ሰዎች ተፈናቅሏል።
🟢🟡🔴
ጳጕሜን 4 | #ቅዱስ_አባ_ባይሞን ዕረፍቱ ነው።

ይህም አባት ባይሞን በአስቄጥስ ገዳም ለሽማግሌዎችም ለጎልማሶችም አረጋጊ ወደብ የሆነ ነው። ከጠላት ሰይጣን ፈተና የሃይማኖት ጥርጥር ወይም ደዌ ያገኘው ሁሉ ወደርሱ ይመጣል ወዲያውኑ ያረጋጋዋል፤ ከደዌውም ይፈውሰዋል።

ከአፉ በሚወጡ ጥዑም ምክሮቹ የታወቀ ነው። ጥቂቶቹ፦

፩. "ባልንጀራህ በወደቀ ጊዜ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥበት። ይልቅስ አንቃው፣ አበረታታው፣ ሸክሙንም አቅልለት እንጂ"

፪. "ለጥሩ ባልንጀራህ የምታደርገውን ደግነት ለክፉው በእጥፍ አድርግለት። መድኃኒትን የሚሻ የታመመ ነውና። አልያ ግን ለበጎው ያደረከው ከንቱ ነው።"

፫. "ባልንጀራህ በበደለ ጊዜ አትናቀው። ያንተ ተራ በደረሰ ጊዜ ጌታህ ይንቅሃልና።"

፬. "የማንንም ኃጢአት አትግለጥ (አታውራ)። ካላረፍክ ጌታ ያንተኑ ይገልጥብሃልና።"

፭. "አንደበትህ የተናገረውን ሁሉ ለመሥራት ታገል። አልያ ውሸታም ትሆናለህ።"

🍀
T.me/Ewnet1Nat
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🌻🌼 ✞የደናግል መመኪያ✞

የአዋጅ ነጋሪ ቃል በበረሃ አየለ 
የእግዚአብሔርን መንገድ አስተካክሉ እያለ 
ምስክርነቱን ዮሐንስ ካስረዳን 
ልባችን ለጌታ መልካም መንገድ ይሁን 

     የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም 
     አውደ ዓመቱን ባርኪልን ድንግል   ማርያም


ተራራው ዝቅ ይበል ጠማማውም ይቅና 
ካልተስተካከሉ መንገድ የለምና 
የእግዚአብሔርን መንገድ እንመስርት ሁላችን 
ማለፊያ እንዲሆነን ለሰማይ ቤታችን
       አዝ= = = = =
ክፋትና ተንኮል ከልባችን ይጥፋ 
ፍቅርና ርኅራኄ በእኛ ላይ ይስፋፋ 
ሥጋና ደምህን በክብር አግኝተናል 
ሕይወት እንዲሆነን አምላክ ተማጽነናል 
አዝ= = = = =
ሁለት ልብሶች ያሉት ከማብዛት ልብስን 
ለሌለው ያድለው ሁለተኛውን 
ከበደላችንም አንጻን አደራህ 
በክፉ እንዳንጠፋ እኛ ባሮችህ
     መዝሙር - መሪጌታ ፀሐይ ብርሃኑ
             
"የአዋጅ ነጋሪ ቃል የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ..."

                ኢሳ ፵፥፩-፰
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   www.tg-me.com/Ewnet1Nat
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
❗️At least 40 people were killed and 60 injured in an Israeli air strike on a neighborhood in Khan Yunis in the Gaza Strip, Al Jazeera reports
🟢🟡🔴
መስከረም 1 | ርእሰ ዐውደ ዓመት

#ርእሰ_ዐውደ_ዓመት

በግእዝ ዐውደ ዓመት ይባላል - ርእሰ ዐውደ ዓመት - የበዓላት ሁሉ የበላይ፣ ራስ ማለት ነው፡፡ በዓመቱ ውስጥ የሚውሉት በዓላትና አጽዋማት የሚወጡት መስከረም አንድን መነሻ አድርጎ ስለሆነ ርዕሰ ዐውደ ዓመት ተባለ።

[🌼] በዚህች ቀን ከ9ኙ ሊቃነ መላእክት አንዱ የከበረ መልአክ ራጉኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው።

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል መስከረም 1 ቀን ከሊቃነ መላእክት በብርሃናት ላይ የተሾመበት ዕለት ነው።

ግንቦት 1 ቀን ለታላቁ አባት ለሄኖክ ምሥጢራትን የገለጸበት በዓሉ ነው፡፡

በብርሃናት ሁሉ ላይ የሰለጠነ መልአክ ነው። ነቢዩ ሔኖክ "ከቅዱሳን መላእክት አንዱ የሆነ ጸላዒ ዲያብሎስን የሚበቀለው ራጉኤል በብርሃናት ላይ የሰለጠነ ነው" ሲል ስለ እርሱ ተናግሯል፡፡

እግዚአብሔር ዓለምን ይቆጣጠር ዘንድ የሾመው ታላቅና ቅዱስ መልአክ ነው።

የመልአኩ ልዩ ቃልኪዳን
"የራጉኤል አምላክ ይቅር በለኝ በማለት አንዲት ቃልስ እንኳን ቢናገር እንደ ወዳጄ እንደ አብርሃም፣ እንደ ባለሟሌም እንደ ይስሐቅ፣ እንደ አከበርኩትም እንደ ያዕቆብ ክብርን ባለሟልነትን እሰጠዋለሁ። በራሱ ላይም አክሊል አቀዳጀዋለሁ። ረጅም ዘመናት ሰፊ፣ ወራትም እሰጠዋለሁ" ሲል ቃሉን ሰጥቶታል፡፡

[🌼] ዳግመኛም በዚህች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ሐዋርያ #ቅዱስ_በርተሎሜዎስ በአሸዋ ከረጢት ውስጥ ተከቶ ወደ ባሕር በመጣል ምስክር ሆኖ ዐረፈ።

[🌼] በዚችም ዕለት #ጻድቁ_ኢዮብ በፈሳሽ ውኃ ታጥቦ ከደዌው ሁሉ ተፈወሰ።

[🌼] ይህች ቀን የታላቁ የቊልዝም ሰው የሆነ ፍጹም ጻድቅ፣ ሰይጣንን አስሮ ዐሥራ አራት ሰው ሊይዙት የማችሉትን ደንጊያ ያሸከመው #የአባ_ሚልኪ የዕረፍት በዓሉ ነው።

#እንኳን_አደረሳችሁ
T.me/Ewnet1Nat
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2024/09/23 10:34:01
Back to Top
HTML Embed Code: