Telegram Web Link
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ www.tg-me.com/kyrieelesion)
''ነገር ግን ይህች የሞት መርዶአችሁን የያዘችው ደብዳቤ ታሪክን ልታሳያችሁ እነሆ መጣችባችሁ። አንድ ጊዜ ለከፋ ጥፋት ተፅፋችኋልና እንኳን በደብዳቤ ከደጃችሁ ነጋሪት ቢጎሰም እንቢልታ ቢነፋ አትሰሙም።

ዛሬም የማይሆን መስሏችሁ በትእቢታችሁ እንደምትዘልቁ ምንም አያጠራጥርም። ተረት ነው እንደምትሉም ሁሌም ይህንኑ ቃል እንደምትናገሩት የተረጋገጠ ነው። ግን ልታውቁት ይገባል የእግዚአብሔርም የሕዝቡም የእውነትም ጠላቶች ናችሁና! ተረት የምትሆኑት እናንተ ናችሁ።''


📌 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ ገጽ- 4
ተፃፈ ጥር 7 ቀን 2012ዓ.ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አሸንዳ - አሸንድዬ - ሶለል - ሻደይ
🌹🌱🌹🌱🌹

ይሄ በዓል (ኧኸ) የማነው በዓል?
የአባታችን (ኧኸ) የሙሴ በዓል
ሙሴ ነቢያት(×፬)

ወገባችን (ኧኸ) ያሠርነው ቅጠል፥
በምን በምን (ኧኸ) በምን ይመሰል፥

ሙሴ ነቢያት(×፬)
አሸንዳችን (ኧኸ) ቅጠሉ ማለት፥
የሙሴ ነው (ኧኸ) የተጣለበት፥

ሙሴ ነቢያት(×፬)...

ሶለላዬ (ኧኸ)
በገነት የወጣው አባቷ ዳዊት፥
ሶለል በዪ

ሶለላዬ (ኧኸ)
ወደ ላይ ስታርግ የአምላክ እናት፥
ሶለል በዪ


🌹🌱🌹🌱🌹
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🍀🌼🌺
«ዐሥር ሰዎች ሞተው ተቀበሩ ዛሬ፤
ድጓ ጾመ ድጓ፥
ብሉይና ሐዲስ፥
ቅኔና አቋቋም፥ መጻሕፍተ ሊቃውንት
እንዲሁም ቅዳሴ፥ መዋሥዕት ዝማሬ።»


[ባሕታዊ አምኃ ኢየሱስ ገብረ ዮሐንስ ስለ አለቃ አያሌው ታምሩ ዕረፍት የተናገሩት]

"ቤተ ክርስቲያን በሯን ዘግታባቸው የአለቃ አያሌው ታምሩ ቀብር ተፈጸመ"
፨ነሐሴ 17 | 1999 ዓ.ም፨

#ዝክረ_አለቃ_አያሌው
▮በረከታቸው ይደርብን።
▯www.tg-me.com/AlphaOmega930
ኦርቶዶክሳዊውን እምነት፣ እውነቱን መስክር፣ የኢትዮጵያ ፍቅር፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ክብር፣ የአምላኳን ገናናነት፣ ኃያልነት፣ ቸርነት ተናገር! ተናገር! ዝም አትበል እያለች ትቀሰቅሰኛለች። ይህ ደግሞ የግቢውንም የውጪውንም ጋኔን ያስጮኸዋል። ያስለፈልፈዋል። እኔ ግን ደንታ የለኝም ። ወንጌልን በማስተማር አላፍርበትም። ለሆዴ ብዬም ክብሬን፣ ኦርቶዶክሳዊ፣ ኢትዮጵያዊ መብቴንም አላስረግጥም ። ይህንንም ሀብቴን ፈቃደኛ ለሆነ ሁሉ ለመንፈሳዊውም ለሥጋዊ ልጆቼም አወርሳለሁ ። ይህ ነው እውነተኛው መንገድ ።

📌 ክቡር አለቃ አያሌው ታምሩ
ከ“ምልጃ፣ ዕርቅና ሰላም” መጽሐፋቸው የተወሰደ
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
«ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት ለ15 ዓመታት በአጠገብህ ሲፈሱ መች ሰማሃቸው ፡፡ በየፌስቡኩ በቴሌግራሙ በዩቲዩቡ ጧት ማታ ተጥደህ የምትውል ትውልድ ፤ በቢሊዮኖች የምትቆጠረው መልእክታቶቹ ሁሉ በፊትህ አልነበሩም እንዴ ስቀህና ንቀህ እያፌዝክ አልተውካቸውም ፡፤ በታላላቅ ቋንቋዎች በሙሉ ተጽፈው በድምፅም ተዘጋጅተው ደርሰውሃል ። ለምነውሃል ያለመታከት ጮኸዋል ስለዚህ ዛሬ በፍርድ ስትያዝ ማን ያስጥልሃል ማንም አያስጥልህም የተጣላኸው ከሥላሴ ነውና፡፡»

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት 9ኛ መልዕክት ገጽ 36 * ተጻፈ ታኅሣሥ 21/2013 ዓ.ም !
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🍀 እግዚአብሔር አንድ ኃይል ያስነሣል!

“እኔ ተስፋ አልቆርጥም።
#ኢትዮጵያ እንደገና ትነሣለች።
#ኢትዮጵያ ትታደሳለች።
#ኢትዮጵያ ትመለሳለች።
እንደነበረም ትሆናለች
።”

#_ዝክረ_አለቃ_አያሌው_ታምሩ
            
#የአለቃ_ሳምንት

💚 አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ
💛
www.tg-me.com/AlphaOmega930
❤️
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA)
"በፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የምትመራው ቤተክርስትያናችን፤ ሲኖዶስ፤ የዋናውም የየክልሉም የጠቅላይ ቤተክህነቱ መዋቅር ከፓትርያርኩ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ያሉ አገልጋዮች፤ ካህናት ዲያቆናት ጳጳሳት ሰባኪዎች መምህራን ዘማሪዎች ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች አስተማሪዎች ወዘተ በተመዘናችሁበት መሰረት የተወሰነላችሁን እጣችሁን ታገኛላችሁ። ይህ ደብዳቤ እናንተ ጋ ከደረሰ ጀምሮ በተከታታይ እርምጃው ይቀጥላል። መድኃኔዓለም አባታችን መድኃኒታችን ከእናታችን ከእናቱ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ጋር ጎብኝተዋችኋል። ሥራችሁም መዝነው በጣት ከሚቆጠሩ በስተቀር ቀላችኋል። ፍርዳችሁን የታዘዘውን ሁሉ ለመተግበር ሊቀ-መላእክት ቅዱስ ሚካኤል፤ ሊቀ-መላእክት ቅዱስ ገብርኤል፤ ሊቀ-መላእክት ቅዱስ እሩፋኤል፤ ሊቀ-መላእክት ፋኑኤል በማይቆጠረው ሃይላቸውና ክብራቸው ውሳኔውን ለመተግበር ተነቃንቀዋል። ራሳችሁን አዘጋጁ የሚሰጥ ምንም ጊዜ የለም።"

ኢትዮጵያ የአለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ ገጽ 5*
📌ተፃፈ ጥር7/2012ዓ.ም
    «ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይኾንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።»
  የዮሐንስ ወንጌል ፰ ፥ ፲፪

  «እናንተ የዓለም ብርሃን ናችኹ።»
   የማቴዎስ ወንጌል ፭ ፥ ፲፬
ሰሜን ጎንደር : በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ
የ10 ሰዎች ሕይዎት አልፏል!

ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ በሰው ሕይዎት ላይ ጉዳት ደርሷል።

በአደጋው የ10 ሰዎች ሕይዎት አልፏል ያሉት የጠለምት ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ተስፋየ ወርቅነህ ናቸው።

ኀላፊው ከአሚኮ ጋር በስልክ በነበራቸው ቆይታ የአራት ሰዎች አስከሬን በፍለጋ ተገኝቷል ብለዋል። የቀሪ ስድስት ሰዎች አስከሬን ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሊገኝ አልቻለም ነው ያሉት።

በጉዳቱ በስምንት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል ያሉት ኀላፊው በደጃች ሜዳ ጤና ጣቢያ የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው ብለዋል።

በመሬት መንሸራተት አደጋው ከ35 በላይ የቤት እንሰሳት ሞተዋል። ከ30 ሄክታር በላይ በሰብል የተሸፈነ መሬት ጉዳት ደርሷል ተብሏል።

እንደ አቶ ተስፋየ መረጃ በደረሰው አደጋ 480 አባውራዎች እና 2 ሺህ 400 የቤተሰብ አባላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል። በቀበሌው ማዕከል ወደሚገኙ ማኅበራዊ ተቋማት በጊዜያዊ እንዲጠለሉ መደረጉንም ኀላፊው ጠቁመዋል።

ኀላፊው አያይዘውም በቀጣይም የመሬት መንሸራተት አደጋ ሊከሰትባቸው ይችላሉ በተባሉ የኖላ፣ ላጌ፣ ውፋ፣ ኩዳድ እና ጅብ ዋሻ አካባቢዎች የሚኖሩ ወገኖች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።

አሁን ካለው ከባድ የዝናብ ስርጭት አንጻር ማኅበረሰቡ ከጎርፍ እና መሰል አደጋዎች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ያሳሰቡት ኀላፊው ለተፈናቃዮች አፋጣኝ የሰብዓዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ነው ያሉት።
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA)
« ከዘረኛ በላይ ክፉና ወንድሙን እጅግ የሚጠላ የዲያብሎስ ፈረስ የለም ። ዘረኛ በነገሰበት በየትኛውም የአገራችንም ሆነ የዓለም ሥፍራ ፍቅር ሰላም የተዋህዶ እምነት ምልክታቸውም አይኖርም ።»

🇨🇬 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን፥ ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ መልእክት 8 ገጽ 45 — ተጻፈ ታኅሣሥ 21/2011ዓ.ም
2024/09/23 18:33:03
Back to Top
HTML Embed Code: