Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዘመኑ የፍርድ፤የመቅሰፍት ነውና ባንድ በኩል በድርቅ ምክንያት ርሃብ ሲሆን ባንድ በኩል ደግሞ እህል እንዲህ እየተቃጠለ ይታያል።
እንግዲህ ዘመኑ የፍርድ ነውና
ሁሉን ነገር ለፈራጁና ለአስፈጻሚው አሜን ብሎ መተው ነው።
የግል ዝግጅት ያላደረጋችሁ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች የሚያስፈልጋችሁን በተቻለ ፍጥነት ብታደርጉ መልካም ነው ስንል በልዑል እግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።
🟢 🟡 🔴
የካቲት 21 | ሊቃውንት አበው እንዳስተማሩን (በዚህች ዕለት) እንዲህ ብለን እንጸልያለን፦

"ረስዪ ፍና ትሕትና አእጋርየ ይሑሩ፥
ትዕቢትሰ ለአምላክ ጸሩ"


{ትርጉም}
እመቤቴ ሆይ፥
አስኪጂልኝ እግሮቼን #በትሕትና ጎዳና፥
ልጅሽ አምላካችን #ትዕቢትን ይጠላልና።

▰ ▰ ▰
🌹 ትሕትናዋን ምሳሌ አድርገን ከልጇ ሞገስን፣ ይቅርታን እንድናገኝ ኃይል ትሁነን።

🌹 የወርቅ ጫማዋን አውልቃ ውኃን ለውሻ ያጠጣች እመ ብርሃን፥ ያደረቀንን የኃጢአት ንዳድ ዘለዓለማዊ የሕይወት ውኃ በሆነው በልጇን ታርቅልን። ከነፍስ የጥም ሞት ታድነን።

ልመናዋ ክብሯ ለዘለዓለሙ በዕውነት በሁላችን በተዋሕዶ ልጆች ላይ አድሮብን ይኑር፨

#_ያለ_ድንግል_ማርያም_አማላጅነት_ዓለም_አይድንም

www.tg-me.com/Ewnet1Nat 🇨🇬
http://www.tg-me.com/AlphaOmega930 🇨🇬
- ✤ - ✤ - ✤ -
ምሕረት #የአምላክ
የድኅነት ኪዳን #የእመ_አምላክ ነው!

የእመቤታችን ቃልኪዳን ለፍጥረቱ #የመዳን_ምክንያት እንዲሆን ከአምላክ የተሠጡ መሆናቸውን ቤተክርስቲያን በተቀደሰው ትውፊቷ ትመሰክራለችን። ይልቁንም ይህን መናቅ ማቃለልና አለማመን ነገረ ሥጋዌን እንዳለማመን ከቤተክርስቲያን ኅብረት የሚያስለይ ስለመሆኑ ተነግሯል።

«ወእመሰ ያሰትቱ መጽሐፈ ተአምሪሃ ወኪዳና ለእግዝእትነ ማርያም ውጹዓን እሙንቱ እምአሚነ ትስብእተ ወልደ እግዚአብሔር ➟ የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ተአምሯን የሚንቁ ግን የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ከማመን የወጡ ናቸው»

ይህን ሥርዓተ አበው ትውፊተ ቤተክርስቲያን ማሰብና መጠበቅ ያስመሰግናል፤ ቅዱስ ጳውሎስ ስለሚያስቡትና የተሠጣቸውን ወግ (ትውፊት) የሚጠብቁትን እንዳወደሰ “ወንድሞች ሆይ፥ በሁሉ ስለምታስቡኝና አሳልፌ እንደ ሰጠኋችሁ ወግን ፈጽማችሁ ስለ ያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ።”【፩ኛ ቆሮ ፲፩፥፪】

🌹 የእመቤታችን አምስቱ ቃልኪዳናት 🌹

❶ በስደቷ ወቅት በጣና ቂርቆስ በደሴተ ጻና የተቀበለችው #ቃልኪዳን

" ስምዒ ኦ ማርያም እምየ ዘንተ ኵሎ ወሀብኩኪ አድባራተ ኢትዮጵያ ዓሥራተ ይኩኑኪ ➟እናቴ ማርያም ሆይ፥ ስሚኝ። የኢትዮጵያን አውራጃዎች ሁሉ ዓሥራት ይሆኑሽ ዘንድ ሰጥቼሻለሁ" ብሎ በዚያም እስከ ዓለም ፍጻሜ ስሟ እንደሚመሰገንበት ቃልኪዳን ሰጥቷታል።

በመጽሐፈ ጤፉትም (ቁ.፸፰) እመቤታችን ራሷ ስትናገር "እስመ ዛቲ ሀገር ዐባይ ይእቲ ወወሀበኒ ወልድየ ሶበ ሖርኩ ኢትዮጵያ ጊዜ ስደትየ ትኩነኒ ርስተ ለትውልደ ትውልድ ወይሰባሕ ስምየ ውስቴታ እስከ ለዓለም" {ይህችም ሀገር በስደቴ ወደ ኢትዮጵያ በሔድኩ ጊዜ ልጄ ርስት ትሆነኝ ዘንድ የሰጠኝ፣ እስከ ዘለዓለም ስሜ በትውልዶቿ የሚመሰገንባት ታላቅ ሀገር ነች}

❷ በሰኔ ፳፩ ቀን በጎልጎታ የተቀበለችው #ቃልኪዳን
የሰኔ ጎልጎታ በመባል በስፋት የሚታወቀውና ከየካቲት ፲፮ቱ ቃልኪዳን (ኪዳነ ምሕረት) ቀድሞ የተገባላት ቃል ኪዳን መሆኑ የሚነገርበት ዕለት ነው።

"አመ ዕሥራ ወአሚሩ ለሰኔ ሖረት እግዝእትነ ቅድስት ድንግል በክልኤ ማርያም ኀበ ደብረ ጎልጎታ ዘውእቱ መቃብረ እግዚእነ በወበኅየ ጸለየት ወመጽኡ መላእክት ወአእረግዋ ካዕበ ➟ ሰኔ ፳፩ ቀን በሁለት ወገን ድንግል የሆነች እመቤታችን ማርያም የልጇ መቃብር ወዳለበት ወደ ጎልጎታ ተራራ የሔደችበትና በዚያም የጸለየችበት (ቃልኪዳንን የተቀበለችበት) መላእክትም መጥተው ሁለተኛ ወደ ሰማይ ያሳረጉበት ቀን ነው"

❸ የካቲት ፲፮ ቀን የተሠጣት #ቃልኪዳን
"አመ ዓሡሩ ወሰዱሱ ለየካቲት ሖረት ካዕበ መካነ ቀራንዮ ዘውእቱ ጎልጎታ ወቆመት በከመ ታለምድ ጸለየት ወሰአለት ➟ በየካቲት ፲፮ ቀን የጌታ መቃብር ወደሚገኝበት ቀራንዮ ወይም ጎልጎታ ዳግመኛ ሄዳ እንደልማዷ ቆማ ጸለየች"

መታሰቢያዋን ለሚያደርግ ፣ በስሟ ቤተክርስቲያን ለሚሠራ ፣ በስሟ የታረዘ የሚያለብስ፣ የተራበ የሚያበላ፣ የተጠማ የሚያጠጣ፣ ያዘነ የሚያረጋጋ፣ የተከዘ ደስ የሚያሰኝ፣ ምስጋናዋን የጻፈውን፣ ልጁን በስሟ የጠራ፣ በክብረ በዓሏ ቀን ምስጋና ያመሰገነውን እንዲምርላት፣ #ወደ_ሲኦል_ከመውረድ_ነፃ_የወጣ_እንዲሆን ተማጽና የለመነችውን ሁሉ ሊያደርግላት የፈቀደችውን ሁሉ ሊፈጽምላት ቃልኪዳን ገብቶላታል።

❹ በእንተ ኀምስቱ ኀዘናት የተቀበለችው #ቃልኪዳን

ታላቆቹን አምስቱን ኀዘኖች፦
፩. ስምዖን ስለሞቱ በተነበየ ጊዜ
፪. ለሦስት ቀን በቤተ መቅደስ ፈልጋ ስታጣው
፫. እጅ እግሩን አሥረው በጲላጦስ አደባባይ መገረፉን ስታስብ
፬. ዕለተ ዓርብ ዕርቃኑን በሁለት ወንበዴዎች መኻል ቸንክረው እንደሰቀሉት ስታስብ
፭. ወደ ሐዲስ መቃብር እንዳወረዱት ስታስብ

➻ እነዚህን ኀዘናትና መከራዎችን አቡነ ዘበሰማያትና በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል እየደገመ ያሰበውን "ኃጢአቱን አስተሠርይለታለሁ፤ መንግሥተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ፤ ከሞቱ አስቀድሞ ከሦስት ቀን በፊት ካንቺ ጋር መጥቼ እገለጽለታለሁ" ሲል ቃል ኪዳን ገባላት።

❺ ነሐሴ ፲፮ ለዕርገቷ መታሰቢያ (ተዝካረ ዕርገታ) የተገባው #ቃልኪዳን

በዕለተ ዕርገተ ሥጋኪ ውስተ ሰማይ (ሥጋሽ ወደ ሰማይ ባረገበት ቀን) ብሎ የሠጣትን ቃልኪዳን የተአምሯ ክፍል እንዲህ ይነግረናል፦

"ለዕርገትሽ መታሰቢያ… ተዝካርሽን ላደረገ ኃጢአቱን ሁሉ እኔ አጠፋለታለሁ፤ እሳትንም ፈጽሞ አያያትም ሰውን ሁሉ ቸርነቴ ትጠብቀዋለች፤ በዚች ቀን ሥጋዬን ደሜን የተቀበለውን በክብር እቀበለዋለሁ"

እኛም ከላይ ለእናቱ የተገለጠውን ቃልኪዳን ሁሉ በማሰብ "ምሕረት የአምላክ፥ ኪዳን የእመ አምላክ" ነውና ከቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ጋር እንዲህ እያልን ልጇን ደጅ እንጠናዋለን፦

«ወካዕበ ተማኅፀነ በማርያም እምከ እንተ ይእቲ እግዝእትነ ወትምክሕተ ዘመድነ በወሊዶተ ዚአከ እስመ አንተ ትቤላ ዘገብረ ተዝካሪኪ ወዘጸውዐ ስመኪ ሕይወተ ዘለዓለም የሐዩ ➟ ዳግመኛም በእናትህ በማርያም ተማፅነናል። ይህችውም አንተን በመውለድ እመቤታችንና የባሕርያችን መመኪያ ናት። አንተ መታሰቢያሽን ያደረገ፣ ስምሽንም የጠራ የዘለዓለም ደኅንነትን ይድናል ብለሃታልና»

ይህን የቅድስት ቤተክርስቲያን ትውፊት ለሚቃልሉ ለብዎ ማስተዋሉን ያድልልን። ለቤተክርስቲያን ልጆች ግን ሐዋርያው እንዲህ ይመክራል፦

“ወንድሞች ሆይ፥ ከእኛ እንደ ተቀበለው ወግ ሳይሆን ያለ ሥርዓት ከሚሄድ ወንድም ሁሉ ትለዩ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን።”【፪ተሰ ፫፥፮】

#ያለ_ድንግል_ማርያም_አማላጅነት_ዓለም_አይድንም

ከቴዎድሮስ በለጠ የተወሰደ፡ ሰኔ ፳፩ / ፳፻፲፬ ዓ.ም.
T.me/Ewnet1Nat
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
ቅድስት ቤተክርስቲያንን እናንተ የዘመኑ ጉደኛ "ጳጳሳት ነን" ባዮች ነገሣችሁባትና ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አደረጋችኋት ! የቤተክርስቲያን አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር ዋጋችሁን ይሰጣችኋል !! እጅግ በቅርቡ #አትጠራጠሩ

በጀርመን ዶላር እየተዝናናህ መኖር አልበቃህ ሲል በምሥራቅ ጎጃም አገረ ስብከት ደግሞ የሞግዚት ሊቀ ጳጳስ ተብለህ በሁለት አህጉር ተቀጥረህ እንጀራ የምትበላ ኧረ ምን እንበልህ!?!?

🛑
#ለታሪክ_ትቀመጥ !
የካቲት 21/2016 ዓ.ም
ርሃብ በተለያየ መንገድ በኃይል እየመጣ መሆኑን ልብ ያለው ልብ ይላል ከዚያም የተመከረውን ፤የታዘዘውን በፍጥነት ተግባራዊ ያደርጋል።

ብዙዎቻችን ሰው እንዴት እህል እየበላ በእህል ቆሞ እየሄደ እንዴት እህል ያቃጥላል ልንል እንችል ይሆናል?
መልሱ ግን አንድና አንድ ነው እሱም
ጊዜው የፍርድ ስለ ሆነ ነው።
🛑 ''ዛሬ የኛው ፈርኦኖች መንግስታቸው ተቆረጠ። ተፈጠመ። አራተኛ የኢሕአዲግ ጭንብል አጥልቆ ብቅ ማለት የለም። ውህድ ነኝ፤ ድምር ነኝ፤ ምርጥ ዲሞክራሲ ነኝ፤ የአሜሪካው የእንግሊዙ ዘመናዊ ዲሞክራሲ ነኝ። የለም አይሰራም። ከሁሉም ምንነታችሁ ጋር ተሰናብታችኋል። አብቅታችኋል። እግዚአብሔር ብርሃናዊ መንግስት እንደ ንጋት ፀሐይ ብቅ ይላል። ሲጨንቃችሁ የሽግግር መንግሥት ትሉ ይሆናል። ዲያብሎስና ምድርን የሸፈኑ ቅራቅንቦዎች መንግሥታት ተብዬዎች ደግፎ ከያዛቸው ስርአት ጋር ተደምድመዋል። ከእንግዲህ የኛ የምትሉት ዘመን የለም። እቅድ የለ ፤ በጀት መበጀት የለ ፤ የመጪው ዓመትን ማየት የለ።  ሩቅ አሳቢዎች አዳራችሁ ቅርብ ነው በቃ!!''

📌 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ ገጽ-4 ተጻፈ ጥር 7/2012 ዓ.ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በዓለም ላይ እጅግ አሰቃቂ የተፈጥሮ አደጋዎች 2024 በካሜራ ተይዘው የቀሩ
2024/09/28 01:25:19
Back to Top
HTML Embed Code: