Telegram Web Link
ጀማይካ.pdf
12.1 MB
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ
ለ ጃማይካ መንግሥት

7/5/2016 ዓ.ም
ጉያና.pdf
11.9 MB
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ
ለ ጉያና መንግሥት

7/5/2016 ዓ.ም
ፍልስጤም.pdf
19.3 MB
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ
ለ ፍልስጤም መንግሥት

7/5/2016 ዓ.ም
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ➯ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን)
🇨🇬"አማራና ክርስቲያን አንድ ሁነህ
በተጠንቀቅ እንድትጠብቅ

በአራተኛው መልእክቴ በሰፊው እስክመጣ ድረስ ለአሁኑ ግን ለመላዋ አዲስ አበባ ከተማና በመላው ኦሮሚያ ክልል ተብየው የምትኖሩ አማራዎችና ክርስቲያን የሆናችሁ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በአንድነት ሁናችሁ በሀገር በቀል ጠላት ከሚሰነዘርባችሁ ጥቃት ትድኑ ዘንድ በተጠንቀቅና በጥንቃቄ ራሳችሁን እንድትጠብቁ ንቁ ንቁ ንቁ እላችኋለሁ። መልእክቴን ሁሉ ከልብ ብታዳምጡና ብትቀበሉ ይበጃችኋል። እያንዳንድህ በእኔ ላይ ሳይሆን በራስህ ሕይወት ላይ አትቀልድ። ተው ልብ ግዛ። ለመጣብህ ነገር ሁሉ ገላጋይ የለህምና። ሐምሌ ፲፯ ፪ሺ፲፩ ዓ.ም ዕለተ ረቡዕ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል ላይ የመጣልኝ መልእክት ነበር። እኔ ግን በሁለተኛውም ሆነ በአሁኑ መልእክቴ ሳላስተላልፈው ቀረሁ። አሁንም የማልናገረው መልእክት ነው። ምክንያቱም የሚመጣው መልእክት ሁሉ አስጨናቂ ስለሆነብኝ ነው ቶሎ ቶሎ የማልለቀው። አሁን ግን ይችን ብቻ እንድለቅ ተገደድኩ። "ጃርቱ ጃዋር እሾሁን በቅርብ ጊዜ ይረጨዋል"። ይኸውም የእሱ የሆኑ አበጋዞቹ አጋንንቶች ያጥለቀልቁታል። በተረፈ ግን ወያኔ ከሽፍትነት መንግስትነቱ ወድቋል ፥ ዓብይ አህመድ መንግሥትና መንግሥታችን ነው ፥ ሀገርንና ሕዝብን የሚጠብቁ መንግሥትንና ታጣቂውን የሚገሥጹ የሃይማኖት መሪ የሆኑ አባቶች አሉን ፥ የሚጠብቀን የመንግሥት ታጣቂ ጦር አለን ፥ ፍትሕ የሚሰጥ ዳኛ አለን ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ክርስትያንና አማራ ካለ የሚያስብበትና የሚያገናዝብበት አዕምሮና ልቦና የተነሣው ጅል ነው።

እናቴ ኢትዮጵያ ክፉ ቀን መጣብሽ፣
አካልሽን በሙሉ ጨለማ ሊውጥሽ፣
ወያኔና ኦነግ ክፉ መከሩብሽ፣
ጃዋርና ቄሮ አብደው ተነሱብሽ፣
ከውጮቹ ቀድመው እነሱ ሊያፈርሱሽ።
እነዚያም አይቀሩ ፈጥነው ይመጣሉ፣
ባልታሰበ ሌሊት ድንገት ይገባሉ፣
በውስጥሽ ያለውን ሁሉን ያወድማሉ።
ይህን እየሰሙ ልጆችሽ በሙሉ፣
በክፋት አንድ ሆነው ሊጠፉ ያብዳሉ፣
ተው ስንላቸው እኛን ይሰድባሉ፣
ነገ ዋይ ዋይ ሊሉ፣
ገብተው ከገደሉ።"
➩ አባታችን አባ አምኃ ኢየሱስ ገብረ ዮሐንስ በመስከረም 27/2012ዓ.ም ካስተላለፉት ትምህርት አዘል አገራዊ መልእክት ቁጥር ፫ የተወሰደ!
💚 www.tg-me.com/christian930
💛 www.tg-me.com/EthioBirhan
❤️ www.tg-me.com/AlphaOmega930
አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ
◦24/02/2012ዓ.ም
◦ከሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ የድንግል ማርያም ርስት የዓለሙ ሁሉ ብርሃንና ገዢ ምድር ኢትዮጵያ
🟢🟡🔴
የካቲት 14 | #ቅዱስ_ሳዊሮስ የዓለም ሁሉ መምህር ዐረፈ፨

ቅዱስ ሳዊሮስ በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሶርያ አንጾኪያ የተነሳ አባት ነው።

ወቅቱ መለካውያን (ሁለት ባሕርይ ባዮች) የሰለጠኑበት እንደ መሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ያነሱበትና የሚሰደዱበት ጊዜ ነበር። በዚህ ጊዜ ነበር ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስ በሥላሴ ፈቃድ ለቤተ ክርስቲያን የተነሳው። ሊቃውንት አንበሳ ሲሉ ይጠሩታል።

ቅዱሱ ለተዋሕዶ ሃይማኖት ብዙ ሆኖላታል። የመናፍቃን ጸር በመሆኑ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል። ንጉሡን ዮስጢያኖስን (Justinian) ሳይቀር በይፋ ይገስጸው ነበርና ንጉሡ ሊገድለው ቆረጠ።

ሃይማኖቷ የቀና ንግሥቲቱ ታኦድራ ግን ይህንን ስትሰማ በሌሊት ወደ ሊቁ ሒዳ "እባክህን ሽሽ።" አለችው። እርሱ ግን "ሞት ለእኔ ክብር ነውና አልሔድም።" ሲል መለሰላት። አባቶችን ሰብስባ "ስለ ቤተ ክርስቲያን ስትል" ብለው ለምነው ወደ ግብጽ ሸኙት።

እርሱ እየሔደ ገዳዮቹ ያሳድዱት ገቡ። መንገድ ላይ ቢደርሱበትም ተሰወረባቸው። ለብዙ ቀናትም አብሯቸው ተጓዘ። እነርሱ ተስፋ ቆርጠው ሲመለሱ እርሱ ግን ምድረ ግብጽ ደረሰ።

በምድረ ግብጽም የጵጵስና ልብሱን ትቶ የመነኮሳትን አሮጌ ልብስ ለብሶ ሕዝቡንና መነኮሳቱን አስተማረ፤ አጸና። በየቦታውም ብዙ ተአምራትን ሠራ።

አባቶች መነኮሳትም ማንነቱን ባወቁ ጊዜ ሰገዱለት። ዶርታኦስ (ዱራታኦስ) በሚባል አንድ ደግ ሰው ቤትም በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ የካቲት ፲፬ ቀን ዐርፏል።

T.me/Ewnet1Nat
🟢 🟡 🔴
የካቲት 16 | የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም በዓልን ያደርጋሉ።

በዚህች ቀን መታሰቢያዋን ለሚያደርግ ስሟን ለሚጠራ፣ ለድኆችና ለችግረኞች እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጥ፣ የክብር ባለቤት ከሆነ ከተወደደ ልጅዋ ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳንን ተቀብላለችና።

ይህችም የከበረች እመቤታችን ልጅዋ ንጹሕ ሥጋዋን ተዋሕዶ ከብቻዋ ኃጢአት በቀር የሰውነትን ሥራ ፈጽሞ በክብሩ ካረገ በኋላ እመቤታችን ማርያም ትጸልይ ዘንድ ያለ ማቋረጥ ወደ ልጅዋ መቃብር ሁልጊዜ ስትሔድ ኖረች ይኸውም ጎልጎታ ነው።

ከዚህም በኋላ መላእክት ወደ ሰማይ አሳረጓትና የጻድቃንን ማደሪያዎች አሳዩዋት። አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብም ወዳሉበት አደረሱዋት።

ከአዳም ጀምሮ እስከዚያ ዕለት በአካለ ነፍስ ያሉ አባቶች ሁሉ፦

"አንቺን ከሥጋችን ሥጋን ከዐፅማችን ዐፅምን ለፈጠረልን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። የአምላክ ልጅ ከአንቺ ሰው በመሆኑ በአንቺ ድኅነት አግኝተናል። ከጥፋትም የሕይወት ወደብ ሆነሽልናልና" እያሉ ሰገዱላት።


ዳግመኛም የሥቃይን ቦታ ያሳዩዋት ዘንድ መላእክት ከዚያ ወሰዷት። ለሰይጣንና ለሠራዊቱ በእርሱ ጎዳና ለሚጓዙ ሁሉ ወደተዘጋጀ ወደጨለማው ዳርቻ አደረሷት። እመቤታችን ማርያምም ወዮልኝ ወደዚያ እንዳይመጡ ለሰው ልጆች ማን በነገራቸው አለች።

ከዚያንም ጊዜ ጀምራ እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለ ኋጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች። እንደ ዛሬይቱም #የካቲት_16 ቀን በጎልጎታ ቦታ ቁማ ወደ ልጇ ለመነች።

❝ ልጄ ወዳጄ ሆይ ጌታዬና ፈጣሪዬ አለኝታዬና መጠጊያዬ በእናቴ ማኅፀንም ሳለሁ ባንተ ጸናሁ። አንተም ጠበቅኸኝ። ሁልጊዜም ስም አጠራሬ አንተ ነህ።

አሁንም ጸሎቴንና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ እኔም አገልጋይህ የምለምንህ ይህ ነው፦

መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ፣ በስሜ አቢያተ ክርስቲያን ለሚሠሩ ወይም የተራቆተውን ለሚያለብሱ፣ የተራበውን ለሚያጠግቡ፣ የተጠማውንም ለሚያጠጡ፣ የታመመውን ለሚጎበኙ፣ ያዘነውን ለሚያረጋጉ፣ የተከዘውንም ደስ ለሚያሰኙ ወይም ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ ዐይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰውም ልቡና ያልታሰበውን በጎ ዋጋ ስጣቸው።

በአማላጅነቴም የሚታመነውን ሁሉ ከሲኦል ነጻ አድርገው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረኃቡንና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ
❞ አለችው።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽም ቃል ኪዳን እንዳይታበል በራሴ ማልኩልሽ አላት።

ውድ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች እንኳን 👉 ለኪዳናት ሁሉ ማኅተም ኪዳነ ምሕረት በዓል በቸርነቱ አደረሳችሁ።
T.me/Ewnet1Nat
◦✞◦ እመቤቴ ሆይ፥ በቃል ኪዳንሽ ኃጢአቴን አስተሥርዪልኝ። #ያለ_ቃል_ኪዳንሽና #አዳኝ_ከሚሆን_ከክርስቶስ_መስቀል በስተቀር ከሲዖል የሚድን ሰው ከቶ አይኖርምና። ◦✞◦
      [መልክዐ ኪዳነ ምሕረት ቁ. 16]
                      🌼🌼🌼
               #እንኳን_አደረሳችሁ
            ◦ T.me/Ewnet1Nat
ንስሓ ምንድን ነው?

የንስሓ ነገር ሲነገር ከሥሩ
ብዙ ታሪክ አለው ብዙ ነው ምሥጢሩ፡፡

የንስሓ ምሥጢር ሲነገር በቅኔ
ዘላለም መራቅ ነው ከክፉ ኩነኔ፡፡

ንስሓ ምንድን ነው ? ካላችሁ በቃል
መጸጸት ነው በቃ በሰሩት በደል፡፡

ከልብ ተጸጽቶ ባለፈው ኀጢአት
በጾም ጸሎት ስግደት እንዲሁም ምጽዋት
መልካም እየሰሩ እስከ እለተ ሞት
ሁሌም እግዚአብሔርን ከልብ በመፍራት
መኖር ነው በደስታ እስካሉ በህይወት፡፡

የጠባቧ መንገድ አስጎብኚና መሪው
የንስሓን ነገር እስኪ እንመርምረው፡፡

ንስሓ እምነት ነው ንስሓ ተስፋ ነው
ንስሓ ፍቅር ነው ንስሓ ለውጥ ነው
ክፉ የሆነውን ለይቶ ማወቅ ነው
እሱን ላለመስራት ሁሌም መወሰን ነው፡፡

ባለፈው ኀጢአቱ ያልተማረ ፍጡር
ምንም አልገባውም የንስሓ ምሥጢር ፡፡

በመቶ ብርና በመቶ ስግደት
በሦስት ቀን ጾምና በሦስት ቀን ጸሎት
አይቆምም ንስሓ ገናም ወደፊት፡፡
መልካም እየሰሩ መኖር ነው ንስሓ
በሳምንት አያልቅም በትንሽ አምኀ፡፡

የነነዌ ሰዎች ንስሓ ገቡና
ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በአንድ ላይ ጾሙና
የታዘዘው መቅሰፍት ወደላይ አቀና፡፡

ሁሉም ዳኑ ያኔ ተቀስፎ ከመሞት
ግን ከዚያ በኀላ ንስሓውን ተውት?፡፡
ቢተውት አይተውም ያልተዋቸው ጌታ
ያወርደው የለም ወይ መቅሰፍቱን አንድ አፍታ፡፡

ስለዚህ ንስሓ የነፍስ ምግብ ነው
ሥጋ ሦስት ቀን በልቶ ይኖራል ወይ በዚያው?
እንኳን በዚያ ሊኖር ሥጋ አስችሎት
ቁርስ ምሳ በልቶ ካልደገመ እራት
አበቃልኝ ይላል የሞተ መስሎት፡፡

እንደዚህ ነው በቃ ንስሓ ማለት
ቶሎ ተጸጽቶ በሰሩት ኀጢአት
መልካም እየሰሩ ለላይኛው ቤት
ዘላለም መራቅ ነው ከዓለም ክፋት፡፡

ተፈጸመ ቀን 22 /10/2014 ዓ፡ም
🛑 "አበ ብዙኃን (የብዙሃን አባት) አባ ገዳ (የዋቄፈናው ዛር አንጋሽ) ደንቦቢ አጋ የሁሉም አባት ብለን እኛ የቤተክርስቲያን አለቆችና አዛዥ ናዛዦች ላሉበት የባዕድ አምልኮ ስፍራና ለእርስዎም ለጣዖቱ ካህን የማዕረግ ስም ሰጥተንዎታል። ቤተክርስቲያንንም ሲያገለግሉ ኑረው ክደው በመውጣቶት የተሰማን ደስታ ወደር የለውም። አባ ገዳው አባታችን አሁንም አይራቁን ባሉበት የዋቄፈና ጣዖት አምልኮ ሆነው ይርዱን..." ይላሉ አባ ዜና ማርቆስ ነኝ የሚሉ ሊቀ ጳጳሳችሁ። ያው ይሄ የደብዳቤውን ይዘት በአጭሩ ስናብራራው ነው። አይ ቤተክህደት ! ማፈሪያዎች !!!

#ለታሪክ_ትቀመጥ !
የካቲት 20/2016
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
ማርያምን‼️ ለዚህ አማላጅ የለኝም፡፡
#የንጉሠ_ነገሥት_ዳግማዊ_አፄ_ምኒልክ_የክተት_አዋጅ‼️ #የዓድዋ_ድል_በዓል

አፄ ምኒልክ የኢጣሊያን ወረራ በመቃወም ወደ ዓድዋ ሲያመሩ የኢትዮጵያን ሕዝብ በሙሉ ለመቀስቀስ ሁኔታው አስገድዷቸው ነበርና የሚከተለውን የክተት አዋጅ መስከረም 7 ቀን 1888 ዓ.ም. አሳወጁ፡፡

‹‹እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፡፡ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ፡፡ ከእንግዲህ ግን ብሞትም ሞት የሁሉም ነውና ለኔ ሞት አላዝንም፡፡ ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፡፡ እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠረጥረውም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፣ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰለንን ባህር አልፎ መጥቷል፡፡ እኔም ያገሬን ከብት ማለቅ የሰውን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያስፈራራ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ የአገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም፡፡ አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም፡፡ አሁንም ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ዕርዳኝ፡፡ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለምሽትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በሐዘን ዕርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ አልተውህም፡፡ ማርያምን!! ለዚህ አማላጅ የለኝም፡፡ ዘመቻዬም በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታው ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ፡፡››

#የአድዋ_ድል የመንፈሳዊ ስልጣኔአችን ውጤት ነው! #ክብር_ምስጋና_ለጀግኖች_አባቶቻችን_ይሁን!
2024/09/28 03:16:40
Back to Top
HTML Embed Code: