Telegram Web Link
በሶማሌ ክልል ዋርዴር መስጂድ ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት ስድስት ሰዎች መደላቸው ተነገረ

በምሥራቅ ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ዶሎ ዞን ዋርዴር ከተማ በአንድ መስጂድ ውስጥ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት ስድስት ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው የአገር ሽማግሌ እና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ሶማሊ ተናገሩ።

ማክሰኞ መስከረም 7/2017 ዓ.ም. በምሥራቃዊ የክልሉ ክፍል ውስጥ በሚገኘው ዶሎ ዞን ውስጥ የተፈጸመው ጥቃት ምክንያቱ፤ በአካባቢው ባሉ ጎሳዎች መካከል ከዚህ ቀደም ተከስቶ ከነበረ ግጭት ጋር ሳይያያዝ እንደማይቀር ተነግሯል።
አቂል ሞሐመድ ሞሐሙድ የተባሉት የአካባቢው የአገር ሽማግሌ ጥቃቱ መፈጸሙን እና ወጣቶቹ መገደላቸውን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

የተገደሉት ወጣቶች የሃይማኖት ተማሪዎች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ የአገር ሽማግሌው “በስድስቱ ወጣቶች ላይ የተፈጸመው ድርጊት እጅግ ዘግናኝ ነው” በማለት ሐዘናቸውን ገልጸዋል።

ወጣቶቹ የተገደሉት ኩጂር በተባለው መስጂድ ውስጥ ለሶላት እየተዘጋጁ ሳለ መሆኑን የገለጹት የአገር ሽማግሌው፤ “ታጣቂዎቹ በአነስ ባለ መኪና ወደ መስጂዱ መጥተው በልጆቹ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል” ብለዋል።

በጥቃቱ መስጂድ ውስጥ የተገደሉት ስድስቱ ወጣቶች ወንዶች የቀብር ሥነ ሥርዓት ረቡዕ ዕለት እዚያው ዋርዴር ከተማ ውስጥ መፈጸሙን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
❗️ሊባኖሳውያን ​​በሞተር ሳይክሎች፣ መኪናዎች እና በተለያዩ መሳሪያዎች ላይ ፍንዳታ እንደደረሰባቸው አስታውቀዋል
«ትራንስፖርት ፍጹም ይበላሻል በየትኛውም አለም መኪና ፣ ባቡር፣ አውሮፕላን፣ መርከብ ሁሉም ለመገልገል ያስቸግራል አደጋቸውም የበዛ ይሆናል፡፡ ለምህረት ያልታደሉትን ለማጥፋት ሞት ሁሉንም መገልገያዎች ወደ መግደያነት ይለውጣቸዋል፡፡ »

► ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 3 ተፃፈ 19/07/2001 ዓ፡ም
አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
❗️ሊባኖሳውያን ​​በሞተር ሳይክሎች፣ መኪናዎች እና በተለያዩ መሳሪያዎች ላይ ፍንዳታ እንደደረሰባቸው አስታውቀዋል።
❗️ባለፉት 2 ቀናት በሊባኖስ ውስጥ በደረሰው የመገናኛ መሳሪያዎች ፍንዳታ የ37 ሰዎች ህይወት እንዳለፈ እና በመጀመሪያው ማዕበል 12 ሰዎች እንዲሁም በሁለተኛው ማእበል ተጨማሪ 25 ሰዎች መገደላቸውን የሊባኖስ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር አስታውቀዋል

በጉዳዩ ዙርያ ባለስልጣኑ የሰጡት ተጨማሪ መግለጫዎች፦

🟠 በመጀመሪያው ቀን ወደ ሆስፒታል የተወሰዱት ተጎጂዎች ቁጥር 2,323 ደርሷል።
🟠 608 ሰዎች እሮብ እለት ቆስለዋል።
🟠 1,343 የሚሆኑት ተጎጂዎች በመካከለኛ ወይም ከባድ ሁኔታ ላይ ናቸው።
🟠 በሁለተኛው የጥቃት ማዕበል የገመድ አልባ መሳሪያዎች ፍንዳታ ሃይል ጠንከር ያለ በመሆኑ የከፋ ጉዳት ተመዝግቧል።
🟢🟡🔴
መስከረም 10 |
#ጼዴንያ በምትባል አገር ሥጋ የለበሰች ከምትመስል ሥዕል ከሠሌዳዋ ቅባት እየተንጠፈጠፈ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ተአምር ተገለጠ

ዳግመኛም በዚህ ቀን፦

🌼 የቅዱሳት ሥዕላት ሁሉ በዓል ነው።

🌼 #ተቀጸል_ጽጌ #ዓፄ_መስቀል ይከበራል። የጌታችን ቅዱስ መስቀል አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ የገባበት ቀን ነው፡፡

● ከከሃዲው ከሆሎፎርኒስ እጅ በጥበቧ እስራኤልን ያዳነቻቸው የሜራሪ ልጅ #ጥበበኛዋ_ዮዲት (የጳጒሜን ጾም ላይ የምናስባት ቅድስት) ዐረፈች

🌼 #ንግሥተ_ሳባ (ንግሥት ማክዳ) ዕረፍቷ ነው።

🌼 ቅድስት መጥሮንያ ሰማዕት፦ በእምነት ከማትመስላት አይሁዳዊት ቤት አገልጋይ ሆና ብትኖር እምነቷን ልታስቀይራት ብዙ ሞክራ አልሳካ ሲላት የገደለቻት፣ በሃይማኖቷ ጸንታ እምነቷን ጠብቃ ሰማዕትነትን የተቀበለች ቀን ነው።

ከእመቤታችን፣ ከቅዱስ መስቀሉ፣ ከቅዱሳኑ ሁሉ ረድኤት በረከትን አይንሣን።

🍀🌼🍀
T.me/Ewnet1Nat
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (♝ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን♝ 🇨🇬🇨🇬)
"ይሁ ሁሉ የእግዚአብሔርን ስራ ማደናቀፍ ያለ ዋጋ ክፍያ ይታለፋል ማለት ስህተት ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስራ ማንም በስጋ ጥበብና ጉልበት ሊያደናቅፈው የሚቻል አይደለም፡፡ ሲሞክርም ቅጣቱ ይሰነዘራል፡፡"

📎 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ቁጥር 5 ፡ ገፅ 38 * ተጻፈ መስከረም 21/2004 ዓ.ም
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
ሊባኖስ ዉስጥ ፔጀርስ በተባለዉ ሞባይል መሠል የመገናኛ መሣሪያዎች ዉስጥ የተጠመዱ በእንግሊዝኛ ምህጻሩ PETN የተባለ ከፍተኛ ፈንጂ መስሪያ የተሰሩ መሆናቸውን አንድ ለሙያው ቅርበት ያለው ሰው ለሮይተርስ ተናገረ። ይህ አደገኛ ፈንጂ ከባትሪው ጋር እንዲዋሃድ የማድረጉ ተግባር በቀላሉ እንዳይታወቁ በሚያስችል መልኩ እንደተሰራም ባለሙያው አክሏል።
ሊባኖስ ዉስጥ ፔጀርስ በተባለዉ ሞባይል መሠል የመገናኛ መሣሪያዎች ዉስጥ የተጠመዱ ቦምቦች ባለፈዉ ማክሰኞና ሮብ ፈንድተዉ በትንሹ 32 ሰዎች ተገድለዋል።ከ3000 በላይ ቆስለዋል።አብዛኞቹ ሟችና ቁስለኞች የሊባኖሱ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን የሒዝቡላሕ ተዋጊዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች ናቸዉ።በፍንዳታዉ ከተገደሉት አንዱ የሊባኖስ የምክር ቤት እንደራሴ ልጅ ሲሆን፣ ከቆሰሉት ደግሞ በሊባኖስ የኢራን አምባሳደር ይገኙበታል።
ሒዝቡላሕ፣ የሊባኖስ መንግሥትና ኢራን ለፍንዳታዉ እስራኤልን ተጠያቂ አድርገዋል።አንድ የሊባኖስ የሥለላ ከፍተኛ ባለሥልጣን ዛሬ እንዳሉት ሒዝቦላሕ ከወጪ በገዛቸዉ 5000 ፔጄሮች ዉስጥ የእስራኤል የሥለላ ድርጅት ሞሳድ ከአንድ ወር በፊት ፈንጂ አጭቆባቸዋል።ፔጀሮቹ ከታይዋን በቡልጋሪያ በኩል ሊባኖስ መግባታቸዉ ተዘግቧል።ፔጀሮቹን ሠርቷል የተባለዉ ጎልድ አፖሎ የተባለዉ የታይዋን ኩባንያ ግን ፔጀሮቹ «የኛ ምርቶች ዓይደሉም» ይላል።
ዘግየት ብለው የወጡ መረጃዎች ደግሞ ባትሪዎቹ ICOM በተባለው የጃፓን ኩባንያ እንደተሰሩ ያመላክታሉ። ይሁንና የኩባንያው ሥራ አስኪያጅ ድርጅታቸው እነዚህ ለሬድዮ መገናኛ የሚውሉ ባትሪዎች መስራት ካቆመ አስርት ዓመታት እንዳለፉት ተናግሯል ስል ሮይተርስ ዘግቧል።
በዩክሬን ጦርነት ከ70 ሺ በላይ የሩሲያ ወታደሮችና ወዶ ገብ ተዋጊዎች መገደላቸው ተሰማ

በቢቢሲ የተተነተነ መረጃ እንደሚያሳየው ከ 70,000 በላይ ሰዎች በሩሲያ ጦር ውስጥ እየተዋጉ በዩክሬን መገደላቸውን አመላክቷል።

VoA Amharic
2024/09/23 02:31:04
Back to Top
HTML Embed Code: