Telegram Web Link
አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
Photo
🟢🟡🔴
መስከረም 11 |
ለአንጾኪያ ነገሥታት አባታቸውና የሰማዕታት መካሪያቸው የሆነ
#ቅዱስ_ፋሲለደስ በሰማዕትነት ዐረፈ።

እርሱም ለሮም ንጉሥ የሠራዊት አለቃ ነው መንግሥቱም ሁለመናዋ በእርሱ ምክር የጸናች ናት። ብዙዎችም ወንዶችና ሴቶች የቤት ውልዶች አገልጋዮች አሉት።

ዝምድናውም እንዲህ ነው ስሙ ኑማርያኖስ የተባለ የሮም ንጉሥ ለቴዎድሮስ በናድሌዎስ እናቱ የሆነች የቅዱስ ፋሲለደስን እኅት አግብቶ ዮስጦስን፣ ገላውዴዎስን፣ አባዲርን ወለደችለት እሊህም ለቅዱስ ፋሲለደስ የእኅቱ ልጆች ናቸው።

የቅዱስ ፋሲለደስም ሚስት ለቅዱስ ፊቅጦር እናት እኅት ናት ከእርሷም ስማቸው አውሳብዮስና መቃርስ የተባሉ ሁለት ልጆችን ወለደ።

በዲዮቅልጥያኖስም አገዛዝ በቅዱስ ፊቅጦር አባት ኅርማኖስ ደጋፊነት ለጣዖት እንዲሰግዱ ከሞት ጋር ታወጀ።

ቅዱስ ፋሲለደስ ዘመዶቹን፣ ሠራዊቱን፣ አገልጋዮቹንም ሁሉ ሰበሰባቸውና በክብር ባለቤት በክርስቶስ ስም ደሙን ሊያፈስ እንደፈለገ አስረዳቸው።

ሁሉም በዚህ ምክር በአንድነት ተሰማሙ።

ክብር ይግባውና ጌታችን ክርስቶስም መልአኩን ልኮ፣ በመንፈስ ወደ ሰማይ አውጥቶ፣ በብርሃን ያጌጠ መንፈሳዊ ማደሪያን አሳየው። ነፍሱም እጅግ ደስ አላት።
ከዚህም በኋላ በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት ቁመው ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ከእርሳቸውም ግርማ የተነሣ ታላቅ ፍርሃትን ፈራ እነርሱ የመንግሥት ልጆች ናቸውና።

የቅዱስ ፊቅጦር አባት ኀርማኖስም ወደ ግብጽ አገር ይልካቸው ዘንድ በዚያም እንዲያሠቃዩዋቸው መከረው ሁሉንም እየአንዳንዳቸውን ለብቻቸው አድርጎ ላካቸው አባዲርንና እኀቱ ኢራኒን ወደ አንዲት አገር፣ አውሳብዮስንና ወንድሙ መቃርስን ወደሌላ ቦታ፣ ገላውዴዎስንም እንዲሁ አደረጉ። በናድሌዎስ ቴዎድሮስም እሼ በሚባል ዕንጨት ላይ በመቶ ሃምሳ ሦስት ችንካር ተቸንክሮ ገድሉን ፈጸመ።

ቅዱስ ፋሲለደስን ግን አምስት ከተማዎች ወዳሉበት ወደ አፍሪካ ምድር ወደ መኰንኑ ወደ መጽሩስ ላከው መጽሩስም በአየው ጊዜ መንግሥቱን ክብሩን ስለ ተወ እጅግ አደነቀ።

በዚያም ለቁጥር የበዙ፣ ለአእምሮ የከበዱ ስቃዮችን ተቀበለ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠለት ከዚያ ስቃይም ውስጥ አንስቶ ያለ ጉዳት ጤነኛ አደረገው። እንዲህም ብሎ ቃል ኪዳን ሰጠው፦

"ፋሲለደስ ሆይ ዕውቅ መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ ወይም ለድኆች በስምህ ምጽዋትን ለሚሰጥ ወይም ለተራቈተ ልብስን ወይም በመታሰቢያህ ቀን ለቤተ ክርስቲያን መባ ለሚሰጥ በብዙም ቢሆን በጥቂት መታሰቢያህን ለሚያደርጉ ሁሉ እኔ በደላቸውን ሁሉ እተውላቸዋለሁ መኖሪያቸውንም በመንግሥተ ሰማያት ከአንተ ጋራ አደርጋለሁ።"

ከዚህም በኋላ መጽሩስ መኰንን ከአማካሪዎቹ ጋር ተማከረ። እንዲህም አላቸው "ስሙ ፋሲለደስ ስለሚባል ስለዚህ ሰው ምን ላድርግ? እርሱን ያላሠቃየሁበት የሥቃይ መሣሪያ ምንም የቀረ የለም። ከሐሳቡም አልተመለሰም።" እነርሱም እንዲህ ብለው መከሩት፦ ራሱን በሰይፍ ቆርጠህ ከእርሱ ተገላገል። እነሆ የዚች አገር ሰዎች በእርሱ ምክንያት አልቀዋልና።

በዚያንም ጊዜ የቅዱስ ፋሲለደስን ራስ በሰይፍ እንዲቆርጡ መኰንኑ አዘዘና ቆረጡት። የድል አክሊልንም ተቀበለ።

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
የሂዝቦላ ከፍተኛ አዛዥ የሆነው ኢብራሂም አቂል ተገደለ 
  
በሊባኖስ ቤሩት ውስጥ እስራኤል በሰነዘረችው የአየር ጥቃት የሂዝቦላ ከፍተኛ አዛዥ የሆነው ኢብራሂም አቂል መገደሉ ተነገረ። 
 
እስራኤል የሂዝቦላ ቡድን ከፍተኛ አዛዥ የሆነውን ኢብራሂም አቂልን ዒላማ አድርጋ የአየር ጥቃቱን መፈጸሟን የሊባኖስ የደህንነት ምንጮች እና የእስራኤል ጦር ራዲዮ ገልጸዋል። 
 
በዚህም ከአዛዡ በተጨማሪ ስምንት ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ሌሎች 59 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር መግለጹን ጠቅሶ ሬውተርስ ዘግቧል።
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
📌 ይህች ጥቅጥቅ ግሩምና ድንቅ ታምራዊት ወንፊት የማታበጥረው (የማትመረምረው) ፍጥረት የላትም !!!

ሁሉንም ታበጥራለች !!
የቀለሉትን ለእሳት ትጥላለች !!
ምርቱን ከግርዱ ትለያለች !!

ስሟም የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ፍርድ አስፈጻሚ የእሳት ወንፊት ነው ።
እስራኤል በቤሩት ባደረሰችው የሚሳኤል ጥቃት ከፍተኛ የሂዝቦላህ መሪዎችን ጨምሮ 31 ሰዎች ተገደሉ።

በደቡባዊ ቤይሩት በሚገኝ ህንጻ ላይ በትላንትናው ዕለት እስራኤል ባደረሰችው ሄዝቦላን ኢላማ ያደረገ የሚሳኤል ጥቃት ቢያንስ 31 ሰዎች መሞታቸውን የሊባኖስ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፍራስ አቢያድ ተናግረዋል።

ከሟቾቹ መካከል የሂዝቦላህ አዛዥ ኢብራሂም አቂልን ጨምሮ ሌሎችም በስም ያልተጠቀሱ አዛዦች ይገኙበታል ተብሏል።

ከጥቃቱ በኋላ በአቅራቢያው ያሉ ሕንፃዎች ለግማሽ ሰዓት ያህል መናወጣቸውን የዓይን እማኞች መናገራቸውን ሲኤንኤን ዘግቧል።

በቤይሩት የሚገኘው የሲኤንኤን ቡድን ከፍርስራሹ ስር ያሉትን ሰዎች ለመታደግ እና የቆሰሉትን በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ለመውሰድ ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ ተመልክቷል።
🟢🟡🔴
መስከረም 12 | እግዚአብሔር #ቅዱስ_ሚካኤልን ወደ ነቢይ ኢሳይያስ ዘንድ ላከው።

በዚህች ቀን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ወደ አሞጽ ልጅ ወደ #ነቢይ_ኢሳይያስ ላከው።

ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሕዝቅያስ ሒዶ እግዚአብሔር ይቅር እንዳለውና ከደዌው እንዳዳነው በዕድሜውም ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እንደ ጨመረለት ይነግረው ዘንድ አዘዘው።

ከጻድቁ ንጉሥ ከቅዱስ ዳዊት በኋላ በእስራኤል እንደ ሕዝቅያስ ያለ ሌላ ጻድቅ ንጉሥ አልተነሣም፡፡ ከሕዝቅያስ በኋላ የተነሡት ሁሉም ጣዖትን አምልከዋል፣ ለጣዖታቱም የሚሆን መሠዊያ ሠርተዋል፡፡ ንጉሡ ሕዝቅያስ በነገሠ ጊዜ ግን ጣዖታትን ሰባብሯቸዋል፣ የእስራኤል ልጆች ያመልኩት የነበረውን የነሐስ እባብ ቆራርጦታል፡፡ እግዚአብሔርንም በማመኑ መንግሥቱ እጅግ ሰምሮለታል፡፡ እግዚአብሔርም ያሳጣው በጎ ነገርም የለም፡፡

ንጉሥ ሕዝቅያስም #በቅዱስ_ሚካኤል በኩል ከሰናክሬም እጅ ያዳነውን እግዚአብሔርን ሲያመሰግን ኖረ፡፡

ከዚህም በኋላ ሕዝቅያስ ታሞ ለሞት በደረሰ ጊዜ ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ እርሱ መጥቶ ‹‹እግዚአብሔር ‹ትሞታለህ እንጂ አትድንም› ብሎሃል›› አለው፡፡ ነገር ግን ሕዝቅያስ አሁንም ልብሱንም ቀዶ ማቅ በመልበስ ጸሎቱን ወደ እግዚአብሔር አቀረበ፡፡

በዚህ ጊዜ #ቅዱስ_ሚካኤል በእግዚአብሔር ተልኮ መጥቶ ነቢዩ ኢሳይያስን ወደ ንጉሡ ሕዝቅያስ ሄዶ በዕድሜው ላይ 15 ዓመት እንደተጨመረለት እንዲነግረው ታዘዘ፡፡

መልአኩ እንዳዘዘው ነቢዩ ኢሳይያስ ንጉሥ ሕዝቅያስን "እግዚአብሔር የአባትህ የዳዊት አምላክ ጸሎትህን ሰማሁ፤ ዕንባህንም አየሁ። እነሆ እኔ አድንሃለሁ፡፡ በዘመኖችህም 15 ዓመት ጨምሬልሃለሁ፡፡ ከፋርስ ንጉሥ እጅም አድንሃለሁ፡፡ ይህችን አገር ስለ እኔና ስለ ባለሟሌ ዳዊት አጽንቼ እጠብቃታለሁ›› ብሎሃል ብሎ የተላከውን ነገረው፡፡

T.me/Ewnet1Nat
🇱🇧 🇮🇱 እስራኤል በቤይሩት ደቡባዊ ዳርቻዎች ባደረሰችው ጥቃት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 37 መድረሱን የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ

💬 "በቤይሩት ደቡባዊ ዳርቻዎች በተፈጸመው የአየር ጥቃት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 37 ደርሷል" ሲል ሚኒስቴሩ በመግለጫው አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ ቀደም ሲል እንዳስታወቀው በጥቃቱ ሶስት ህጻናትን ጨምሮ 31 ሰዎች ሞተዋል። ሌሎች 68 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል።

መስከረም 7 እና 8 ፔጀሮች እና ዎኪ ቶኪዎች በሊባኖስ የተለያዩ ክፍሎች ፈንድተዋል። እንደ የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ገለጻ 37 ሰዎች ሲሞቱ ከ3,000 በላይ የሚሆኑት ቆስለዋል። ሄዝቦላ እና የሊባኖስ ባለስልጣናት ለጥቃቱ እስራኤልን ተጠያቂ አድርገዋል። እስራኤል በጥቃቱ እንደተሳተፈች ከማረጋገጥ ወይም ከመካድ ተቆጥባለች።
🇵🇱 ወደ 57,000 የሚጠጉ ፖላንዳውያን በአስከፊ ጎርፍ ሳቢያ በቀጥታ ጉዳት ደርሶባቸዋል

የጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ቱስክ ጽ/ቤት ኃላፊ እንዳሉት በ 749 የፖላንድ ከተሞች በደረሰው የተፈጥሮ አደጋ በድምሩ 2.39 ሚሊዮን ሰዎች ተጎጂ ሆነዋል። ከእነዚህ ውስጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩት በጎርፍ ውሃ በቀጥታ ተጎድተዋል።

💬 "በአሁኑ ጊዜ ይህ ቁጥር 57,000 ደርሷል" ሲሉ የፖላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር  ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት ጃን ግራቢክ ባደረጉት የአስቸኳይ ጊዜ ስብሰባ ላይ ገልጸው፤ ቁጥሩ ቅድመ ግምት እንደሆነም ተናግረዋል።

በደቡባዊ ፖላንድ ያልተለመደ ኃይለኛ ዝናብ ወንዞች ከልክ በላይ እንዲሞሉ በማድረጉ ሳቢያ በትንሹ 20 ሰዎች ሲሞቱ 6,544 ያህሉ ደግሞ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓል። እስካሁን ድረስ 11,502 ባለ አንድመኝታ ቤቶች እና አፓርትመንቶች፣ 6,033 የቤተሰብ መገልገያዎች እና 724  እንደ ትምህርት ቤቶች፣ መንገዶች እና ድልድዮች ያሉ የህዝብ መገልገያዎች ተጎድተዋል ወይም ወድመዋል ሲሉ ጃን ግራቢክ ቅድመ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጃፓን በ50 ዓመታት ውስጥ ባላየችው ጎርፍ ተመታች።

በከባድ ዝናብ ምክንያት በጃፓን ከ130,000 በላይ ሰዎች አካባቢያቸውን ለቀው መሄድ ነበረባቸው

በጃፓን ኢሺካዋ ግዛት ውስጥ የሚገኙ 12 ወንዞች ከወዲሁ ሞልተው በመፍሰሳቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል። 

የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንዳሉት በርካታ ቤቶች በጎርፍ ተጥለቅልቀዋል እንዲሁም በመሬት መንሸራተት ሳቢያ በርካታ ሕንፃዎችን ወድሟል። 

ሀገሪቱ እንዲህ ያለ ከባድ የጎርፍ መጥለቅለቅ ለ50 ዓመታት ገደማ አላየችም።
📹🇹🇩 በቻድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ500 በላይ ሰዎች ሲሞት 1.7 ሚሊዮን ያህሉን ደግሞ ለጉዳት ዳርጓል

ከሀምሌ ወር ጀምሮ በሀገሪቱ የተከሰተው የጎርፍ አደጋ በትንሹ 503 ሰዎች መሞታቸውን የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ( ኦቻ) አስታውቋል።

📹🇹🇩 Flooding in Chad claims over 500 lives and affects 1.7 million

Since July, flooding has resulted in the deaths of at least 503 people in Chad, according to the United Nations Office for the Coordination of Humanitarian Affairs (OCHA).

The latest OCHA report also indicated that thousands of homes destroyed.

Urgent humanitarian aid is required, and authorities have cautioned that ongoing heavy rains and rising river levels could lead to further flooding.
2024/09/23 04:34:43
Back to Top
HTML Embed Code: