Telegram Web Link
በትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በድሬዳዋ አሥተዳደር ጀሎ በሊና ቀበሌ ቢርካ አካባቢ ሌሊት 6፡30 ገደማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

ከሟቾች በተጨማሪም በ10 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን ድሬዳዋ አሥተዳደር ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

አደጋው የደረሰው ከድሬዳዋ ወደ ሐረር ሰው አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ “ዶልፊን” የሚባለው ሕዝብ ማመላለሻ በተቃራኒ መስመር ይጓዝ ከነበረ በተለምዶ “ሲኖትራክ” ተብሎ ከሚጠራው የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ9 ሰዎች ህይወት አለፈ

ዛሬ ሐምሌ 10/2016 ጌድኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ሻእሳ በተባለ ቀበሌ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ9 ሰው ህይወት ማለፉን ከስፍራው የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል። ቀላልና ከባድ ጉዳት የደረባቸው 4 ሠዎች ለህክምና ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል ሲሉ ምንጮች ጠቁመዋል።
🟢🟡🔴
ሐምሌ 10 | የከበሩ አባቶቻችን፦

🍀 ስምዖን ቀለዮጳ የተባለው #ቅዱስ_ናትናኤል ሐዋርያ ስምዖን ቀለዮጳ በሰማዕትነት ዐረፈ።

ይህንንም ሐዋርያ አይሁድ የጌታችንን ወንድም ያዕቆብን ከገደሉት በኋላ ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አድርገው ሐዋርያት ሾሙት። እርሱም ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮ ከአይሁድ ብዙዎችን ጌታችንን ወደማመን መለሳቸው ተአምራትንም አድርጎአልና በሽተኞችንም አድኗልና።

ንጉሡ እንድርያስም ሴቶችን ከባሎቻቸው እንደሚለይ ንጽሕናቸውንም እንዲጠብቁ እንደሚአዝዛቸው ስለ እርሱ ሰማ ወደርሱም አስቀርቦ ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው።

ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ከእርሱም ጋር #ቅድስት_ቴዎና የምትባል አንዲት ድንግል ተገደለች።
🍀

#አቡነ_ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ልደታቸው ነው።

ጻድቁ እንድርያስና አርሶንያ ከሚባሉ የበቁ ደጋግ አባትና እናታቸው የተወለዱት በሸዋ ሀገረ ስብከት ቀድሞ ጽላልሽ ዛሬ ቡልጋ በሚባለው አውራጃ ነው፡፡

የወላጆቻቸው በጎ ምግባርና ሃይማኖት ቅዱስ ተክለሃይማኖትን ከደብረ ሊባኖስ አነሣስቶ በቤታቸው ሄደው እንዲስተናገዱ አድርጓል።

ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበርና አቡነ ተክለሃይማኖትም በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጾላቸው ‹‹እግዚአብሔር ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ›› ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል፡፡

በትንቢቱም መሠረት አቡነ ሳሙኤል ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም ሲወለዱ መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ኅብራት ታይተዋል፡፡

አቡነ ተክለሃይማኖትም በ40 ቀን ክርስትና አንስተው ስመ ክርስትናውን ‹‹ሳሙኤል›› አሉት፡፡ ትርጓሜውም ‹‹እግዚአብሔር ጸሎቴን ሰማኝ›› ማለት ነው፡፡
🍀

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
🟢🟡🔴
ሐምሌ 12 |
#እግዚአብሔር #ቅዱስ_ሚካኤልን ያጠፋቸው ዘንድ ወደ ሰናክሬም ሠራዊት ላከው።

ይህም እንዲህ ነው፦ ሰናክሬም ኢየሩሳሌምን በከበባት ጊዜ ሕዝቅያስንና ፈጣሪው እግዚአብሔርን እየዘለፈ ወደ ሕዝቅያስ መልእክተኞችን ላከ። እንዲህም አለ፦ "እግዚአብሔር ያድናችኋል እያለ ሕዝቅያስ አያስታችሁ ከእጄ የሚያድናችሁ ማን ነው?"

የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስም እጅግ አዘነ። ወገኖቹንና ሀገሩ ኢየሩሳሌምንም ያድን ዘንድ ማቅ ለብሶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። እግዚአብሔርም ልመናውን ተቀብሎ ወደ ፋርስ ንጉሥ ወደ ሰናክሬም ሠራዊት የመላእክት አለቃ ሚካኤልን ላከለት።

በዚያችም ሌሊት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወርዶ የሰናክሬምን 185 ሺውንም የጦር ሠራዊት በአንዲት ሌሊት በእሳት ሰይፉ ፈጅቷቸው አደረ፡፡

በለኪሶ የነበረው ሰናክሬምም በጧት ቢነሣ ሠራዊቱን ሁሉ የአስከሬን ክምር ሆኖ አገኘው፡፡ በታላቅ ድንጋጤ ሆኖ ወደ ነነዌ በመሄድ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች በሰይፍ ገደሉት፡፡

ትዕቢተኛው ሰናክሬምም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ፡፡ ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ሞገስና ረዳት ሆኖታልና የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት፣ እጅግ አከበሩትም፡፡

[2ኛ ነገ ምዕ 18 እና 19 ይነበቡ]

ስለዚህም የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የሚካኤልን በዓል መታሰቢያ በዚች ቀን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ።

                      ◦☘️☘️☘️
#እንኳን_አደረሳችሁ
T.me/Ewnet1Nat
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
💾 የአባ አምኃ ኢየሱስ ገብረዮሐንስ መደበኛና ድንገተኛ አገራዊ መልዕክቶች
🟢🟡🔴
መልዕክት ፩
https://www.tg-me.com/christian930/2763

መልዕክት ፪ https://www.tg-me.com/christian930/2764

መልዕክት ፫ https://www.tg-me.com/christian930/2765

መልዕክት ፬ https://www.tg-me.com/christian930/2766

መልዕክት ፭ https://www.tg-me.com/christian930/3471

መልዕክት ፮ https://www.tg-me.com/christian930/3487

💾 PDF+Audio+Video ሁሉንም በአንድ ላይ ለማግኘት https://www.tg-me.com/christian930/4289

ድንገተኛ መልዕክታት (በፅሑፍ) https://www.tg-me.com/christian930/4290
📌 በስተመጨረሻ ግን ማሳረጊያ እንዲሆን በዚህ ሰዓት የምንግርህ!

ኢትዮጵያዊነትን በልብህ ካልተከልክ ፤ ተዋሕዶ እምነትን በልብህ ካላጸናህ ፤ ሰንደቋን ካላከበርክና ካልታመንክባት

በዚህ በሦስቱ ወድቀህ ከተገኘህ ወንድሜ እህቴ ማንም ሆናችሁ ማንም

በየትም ዓለም ኑር በየትም መዳኛዋ መሸሸጌዋ ማምለጨዋ መንገድ ይቺውና ይችው ብቻ ናት፡፡ ይሄንን ንቀሃል ይሄንን አቃለሃል፡፡

አዎ አንተ ቀለሃል ዋጋ ቢስ ሆነሃል፡፡ ከእግዚአብሔር ፍቅር ተቆርጠህ ወድቀሃል፡፡

ኢትዮጵያዊነት ዓለምን አሸንፏል፡፡

ደግሜ ልንገርህ ምን ብየ ኩርርር ብየ ልንገርህ
ኢትዮጵያዊነት ዓለምን ሁሉ አሸንፏታል፡፡

ተዋህዶ እምነት፡ ዓለምን ሁሉ የሞላውን እምነቶች ሁሉ እምነት ተብየዎችን ሁሉ አሸንፋለች፡፡
በእግዚአብሔር ፊት ከብራለች፡፡

አባቶቻችን ያጸኗት የለበሷት በልባቸው የተከሏት ለዘመናት የኖሩባት ሰንደቋ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ አሸንፏል፡፡
የቃል ኪዳን ምልክቱ ነውና

በእነዚህ ሦስቱ ውስጥ ከሌለህ እግዚአብሔርንም ልታውቀው አትችልም፡፡
ኢትዮጵያዊነትን ስታውቅ
ተዋህዶን ስታውቅ
ሰንደቋን ስታውቅ
እግዚአብሔርን ታውቃለህ፡፡

እምነት ምን እንደሆነም ታውቃለህ፡፡

በእምነት መጓዝ ምን እንደሆነም ትረዳለህ፡፡

በእውነትና በመንፈስ መጓዝም ያስችልሃል፡፡

ቸሩ መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስንም ታውቀዋለህ፡፡

የአብርሃሙ ሥላሴንም ታውቃለህ፡፡

ድንግልም ታውቃለህ፡፡

ፍቅራቸውንም ታገኛለህ

ብዙ ዙረት ድካም አያስፈልግም፡፡

ማመን መታመን ንስሓ መግባት ወደ ጉያው መሰብሰብ ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ መቅረብ
የምነግርህ ይሄንን ነው፡፡

⚡️ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ሚያዝያ 19/2015 በድምፅ ከተለቀቀው
መግለጫ እና የሉቃስ ወንጌል ትምህርት ክፍል- 11- (ለ) መጨረሻው ላይ የተወሰደ፡
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA)
« ከዘረኛ በላይ ክፉና ወንድሙን እጅግ የሚጠላ የዲያብሎስ ፈረስ የለም ። ዘረኛ በነገሰበት በየትኛውም የአገራችንም ሆነ የዓለም ሥፍራ ፍቅር ሰላም የተዋህዶ እምነት ምልክታቸውም አይኖርም ።»

🇨🇬 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን፥ ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ መልእክት 8 ገጽ 45 — ተጻፈ ታኅሣሥ 21/2011ዓ.ም
At least 32 people have been killed, and over 2,500 are injured in Bangladesh as violence escalated during student protests who are demanding quota system reform for government jobs.
ክራውድስትራይክ ለደንበኞቹ በለቀቀው የሶፍትዌር ማዘመኛ ጋር ተያይዞ ባጋጠመ እክል 8.5 ሚሊዮን ኮምፒዉተሮች ላይ ጉዳት መድረሱ ተነገረ።

ክራውድስትራይክ ከተሰኘ የሳይበር ደህንነት ኩባንያ ለደንበኞቹ በለቀቀው የሶፍትዌር ማዘመኛ ጋር ተያይዞ ባጋጠመ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ስህተት ነዉ ጉዳቱ የደረሰዉ።

ከባሳለፈዉ ኃሙስ ማለዳ ጀምሮ የተከሰተው ችግር ባንኮች፣ አየርመንገዶች እና የሚዲያ ተቋማትን ስራ ማስተጓጎሉም ተገልጿል።

ይህንን ተከትሎ ማይክሮሶፍት ኩባንያ ባወጣው መረጃ ያጋጠመው የአይቲ እክል ከአገልግሎት ማስተጓጎል በተጨማሪ በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱንም አስታውቋል።

በዚህም ከሶፍትዌር ማዘመኛ ጋር ተያይዞ ባጋጠመው አደጋ 8 ነጥብ 5 ሚሊየን ያህል ዊንዶውስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም የሚጠቀሙ ኮምፒውተሮችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ቁሶች ላይ ጉዳት ማድረሱን ማይክሮሶፍት አስታውቋል።

ማይክሮሶፍት በኮምፒውተሮቹ ላይ የደረሰው ጉዳት በታሪክ አስከፊው የሳይበር ጉዳት መሆኑን ነው የተጠቀሰዉ።
🟢🟡🔴
ሐምሌ 15 | የከበሩ አባቶቻችን፦

#ቅዱሳን_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ ተአምራት አደረጉ።

ቅዱሳኑ ሶርያ አካባቢ ውስጥ ወደምትገኝ አንዲት ሃገር ገብተው ሕዝቡን ከንጉሣቸው ጰራግሞስ ጋር አሳምነው አጠመቁ። ነገር ግን እነርሱ ሲወጡ ሰይጣን አስቶት አጥፊ ሰው ወደ መሆን ተመልሶ ንጉሡ ሐዋርያትን አሰቃየ።

ስለ ሐዋርያት ግን ፈረሶቹ ሰግደው፣ በሰው አንደበት ቅድስናቸውን መሰከሩ። በመጨረሻም ንጉሡን ከነ ሕዝቡና ሠራዊቱ በዓየር ላይ ሰቅለው ንስሐ ሰጥተውታል ። በእነዚህ ተአምራትም ሁሉም አምነው ለከተማዋና ለሕዝቡ ድኅነት ተደርጓል።

🍀 #ቅዱስ_ኤፍሬም ዘሶርያ ዐረፈ።

ይህም ውዳሴ ማርያምን የደረሰ ሊቅ ነው።

ቅዱስ ኤፍሬም ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች ሀገር ነው። አባቱም የጣዖት ካህን ነበር።

የእግዚአብሔር ቸርነት ቀሰቀሰችውና አነሳሥታ ወደ #ቅዱስ_አባ_ያዕቆብ ዘንጽቢን ወሰደችው።

እርሱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቀው። በእርሱም ዘንድ በጾምና በጸሎት ያለማቋረጥ እየተጋደለ ለብዙ ዘመናት ኖረ።

እንደ ዛሬው የእመቤታችን ምስጋና በአንደበት እንጂ በመጽሐፍ አይገኝም ነበርና ቅዱስ ኤፍሬም ግን ከወንጌለ ሉቃስ በስድስተኛው ወርን (ይዌድስዋን) እና ጸሎተ ማርያምን አውጥቶ በየዕለቱ በዕድሜዋ ልክ 64 ጊዜ ያመሰግናት ነበር።

እመቤታችንን ከልብ ከመውደዱ የተነሣ የእመቤታችን ምስጋናዋን አብዝቶ ይመኝ ነበር


በእግዚአብሔር ቸርነት “አቤቱ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ” እስከሚል ድረስ ከእመቤታችን ውዳሴ ሌላ 14 ሺህ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ። ብዙውን ድርሰቱን መላእክት ደብቀውታል፣ ወስደውም ለምስጋና ተጠቅመውበታል

🍀 የዋልድባው #አቡነ_ተስፋ_ሐዋርያት ተሰወሩ።

በዋልድባ ከሳሙኤል ዘዋልድባ ቀጥለው በገዳሙ የተሾሙ ታላቅ አባት ናቸው

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
2024/09/28 18:13:18
Back to Top
HTML Embed Code: