Telegram Web Link
💡ሐና!

"አቤት ቲቸር!" ድንገት በመጠራቷ ደንግጣ ታፈጣለች። የክፍላችን ጎበዝ ተማሪ ናት ሐና…

"የሰው ልጅ መሠረታዊ ፍላጎት ምንድ ነው?" ይጠይቋታል።

"ምግብ…ልብስ…መጠለያ" መለሰችው እንላለን እኛ በሽክሹክታ። ገና ትላንት ነው አከባቢ ሳይንስ መምህራችን ያስተማረችን።

💡"አይደለም! በጭራሽ አይደለም! ሳይንሱ እውነታውን ጋርዶብናል። እንጀራ ማን ሕሊና ውስጥ ቦታ ሰጠው? 'የምድር ፍሬ፣ የወንዝ ውሃ ይሙላህ' የተባለን ሆድ ማነው የሰው መሠረት ያደረገው? የለም! በየጫካው በየዱሩ የሚኖሩ ወገኖቻችን ርቃናቸው ጌጣቸው ነው፤ ቤትስ ቢሆን - የሰው ልጅ ተንኮሉን ሊከልል፣ ለግርዶሹ ስም አወጣ።

💎ልጆች ልብ በሉ…የሰው መሠረታዊ ፍላጎት አንድ ነው፣ እሱም ፍቅር ነው። ካለፍቅር ሰው የቁም ሙት ነው። ሰው ሰውን ሲያፈቅር፣ ሰው አምላኩን ሲያፈቅር፣ ሰው አገሩን ሲያፈቅር፣ ሰው እውነትን ሲያፈቅር፣ ሰው ነፃነትን ሲያፈቅር ነው ሕያው የሚሆነው። ሰው ነገውን ሲወድ፣ ነገውን ሲያፈቅር ነው ነገ ለሚፈጠር ትውልድ ፍቅር የሚያወርሰው…እስትንፋሱ የሚቀጥለው።"

📖 "ዶክተር አሸብር፣
የታረሙ ነፍሶች"115
በአሌክስ አብርሃም

ውብ ምሽት ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
💡ገና ስትፀነስ በሕይወት ዘመንህ ትልቅ ቦታ የመድረስ ምርጫ ተመነሻውም የተሰጠህ መሆኑን ተገንዘብ። ፈጣሪ ሕይወት ሰጥቶኻል፥ ሕይወትህን ደርዝ የምታስይዘው ግን አንተ ነህ። ቢያንስ መሞከር አለብህ። ወኔ ማለት መለወጥ እምትችለውን ነገር መለወጥ መቻል ነው። እረኛ እንድሆን ተፈርዶብኛል ካልክ እረኛ ሆነህ ትቀራለህ።…" (26)

🔑ሕይወት ትርጉምና እና ዓለማ ያላት እንደሆነች ይሰማኛል። ልብህን ማድመጥ እንድትማር ነው ይህን ሁሉ ላንተ መንገሬ። ልብህ የፈቀደው ነገር ዕጣፈንታህ ነው። ፈጣሪ ያን ፈቃድ በልብህ ያሳድረዋል፣ እንግዲህ ያንተ ሥራ የሚሆነው ልብህ የሚነግርህን መከተል ነው። ዛሬ፥ ልቤ የሚያዘውን የምከተል በመሆኔ ነጻ ሰው ነኝ። የችግሮቼ ሁሉ ምንጭ እኔው ራሴ ነበርኩ። ይህንንም ለመረዳት ዓመታት ፈጅቶብኛል።" (57)

📖 "ኀሠሣ" በሕይወት ተፈራ

ውብ ምሽት ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
💎ዓለም የታነፀችው ከሐሳብ ነው፣ ሐሳብ የሁሉ ነገር አልፋ ነው። ሁሉም ሐሳቦች ግን መልካም ናቸው ማለት አይደለም፣ መልካሞቹ ግን በህሊና ቅኝት የተቃኙት ናቸው!

💡ጥበብ ማስተዋል ነች! ማስተዋል ደግሞ ከዕርጋታ/ከስክነት ትወለዳለች!ሁሉም ሰው በሌላ ሰው አይን ስህተት ሊሆን ይችላል። በራሱ አይን ግን ሁሉም ሰው ትክክል ነው!

💎በውይይት መግባባትም/አለመግባባትም ተፈጥሯዊ ነው። መሠረታዊው ቁምነገር የሐሳብ ብዝሃነትን ማስተናገድ መቻል ነው።የሠላ አዕምሮ በምክንያታዊነት ተነጋግሮ መደማመጥን ይከጅላል።አንድን ነገር ስለተቃወምነው ስህተት ነው ማለት አይደለም። ስለደገፍነውም ደግሞ ትክክል ነው ማለት አንችልም!በስሜት ከደገፍነው ይልቅ በሐሳብ የሞገትነው በብዙ ሺ እጥፍ ፍሬ ያፈራል!

📍ምግብን ማላመጥ እንደምናውቅ ሁሉ ሐሳብን ማላመጥ እና ማብላላት መለማመድ ይኖርብናል። የሰጡትን የሚቀበለው ሆድ ብቻ ነው። አዕምሮ ደግሞ የሆድ ባህሪ የለውም። ነገር ግን እንዲሆን ከመረጣችሁ መሆን አያዳግተውም፤ ምክንያቱም አዕምሮ የልምምድ ባርያ ነው።

💡የሰው ልጅ መልካሙን የአዕምሮ ባህርይውን የሚያጣበት መንገድ ልክ በመጥረቢያ የሚቆረጥ ዛፍ ጋር የሚመሳሰል ነው። ዕለት ዕለት አስተሳሰብህን እንደዛፍ ቅርንጫፍ እየቆረጥህ ብትጥል ተፈጥሮአዊ ውበትህ እንደሚጠፋ ልብ ብለሃል?
ነገር ግን ቀንም ሆነ ማታ የተቆረጠ ዛፍ ከማቆጥቆጥ እንደማይቆጠብ ሁሉ እንዲሁ ደግሞ የሰው አዕምሮ ወደ ነበረበት ለመመለስ መፀፀቱና ማሰቡ አይቀርም።

📍ወዳጄ ሆይ… የአንተነትህ ምስል የአስተሳሰብህ ስዕል ነው፡፡ እይታህ የሚወለደው ከአመለካከትህ ነው፡፡ ምግባርህና ማንነትህ የሚታወቀው በስራህ ነው፡፡ ስራህ ደግሞ ተምጦ የሚወለደው ከሃሳብህ ነው፡፡ ሃሳብህ ከተበላሸ፣ የዘራኸው ከመከነ ፍሬህ አይጎመራም፡፡ መልካም አያያዝን አግኝቶ የማያድግ እንደሌለ ሁሉ በአያያዝ ጉድለትም እንዲሁ የማይበሰብስ ነገር የለም። አጥብቀህ የያዝከው ነገር ከአንተ ጋር ይኖራል፤ የለቀቅከው ደግሞ ሄዶ ይበሰብሳል፣ የአዕምሮህ መጥፎ ሀሳብ ካሸነፈ አንተንም ሆነ ሌሎችን ይመርዛል።

              ሰናይ ቅዳሜ ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
🌗``ክፉ ቀን ጥሩ ነው´´

ፕሮፌሰር መስፍን "አገቱኒ ተምረን ወጣን" በሚለው መጽሀፋቸው ስለ ክፉ ቀን እንዲህ ይላሉ፡፡.....

🌗 ክፉ ቀን ጥሩ ነው መማር የፈለገውንም ያስተምራል ፈጣሪ ሀያላን ነን የሚሉትንም ያስተምራል፡፡

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ደጋግ ሰወችን ይቀሰቅስና የግፍን መራራነት እንዲቀንሱት ያደርጋል፡

ክፉ ቀን ጥሩ ነው በተለያየ የኑሮ ደረጃ የተከፋፈሉትን በአላማ ያያይዛቸዋል፡፡

ክፉ ቀን ጥሩ ነው የግፍን ጥርስ ሁሉም እንዲያየውና እንዲንቀው ያደርጋል፡፡

🌗 ክፉ ቀን ጥሩ ነው ብዙ ጉድ ያሳያል።የተማረውና የተመራመረው አምሮውን በኦሞ ሙልጭ አድርጎ አጥቦ ህሊናውን በጨጓራው አፍኖ የሆነውን አልሆነም እያለ ለልጆቹ ሀፍረን ሲሆን ያሳየናል።
-
ክፉ ቀን ጥሩ ነው ያለፈውን ካለው ጋር በእውነት እንድናወዳድረው ያስገድደናል።

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ክብርን ወደ ውርደት ውርደትን ወደ ክብር ይለውጣል።

ክፉ ቀን ጥሩ ነው የጉልበተኛውን ልብ ያደነድናል አእምሮውንም ደርግሞ ይዘጋዋል የጭካኔውንም ወሰን የለሽነት ያሰየናል።

🌓 ክፉ ቀን ጥሩ ነው ጥሩ ቀንን እየጮኸ ይጣራል።

ክፉ ቀን ጥሩ ነው የወደቀውን ለድል የጣለውን ለውድቀት ያዘጋጃል

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ክፋት በጎነትን አሸንፎ እንደማይዘልቅ ያሳያል ህግ ቀልቡ ሲገፈፍ ዳኝነት ሚዛን ሲያጣም ያሳያል

ክፉ ቀን የጠራ መስትዋት ነው መልካችንን ብቻ ሳይሆን ባህሪያችንንም ጤናችንን ብቻ ሳይሆን ህመማችንንም ውበታችንን ብቻ ሳይሆን አስከፊነታችንንም ቁልጭ አርጎ ያሳየናል

ክፉ ቀን ጥሩ ነው ባጠቃላይ የመጪው ጥሩ ቀን ምልክት ነው።

ውብ አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
📍ቢላ ካልተሞረደ ዶልዱሞ እንደሚቀር ሁሉ የሰውም ልጅ ጠንካራና ብልህ እንዲሆን በተለያዩ ውጣውረድ ማለፍ ግድ ይለዋል።እኚ ውጣውረዶች በሕይወታችን ውስጥ መከሰታቸው ተፈጥሯዊ ነው፣ እኛኑ ለማጎበዝ እኛኑ ለማንቃት እኛኑ ለማጠንከር እኛኑ ለማጀገን ነው ፣የዶሎዶመ ቢላ ለመቁረጥ ከማስቸገርም አልፎ ድካም ነው የሚሆንብን እንጂ እንደተመኘነው አይቆርጥልንም።

📍ያልተፈተነ ማንነትም ከተራራው ጫፍ የሚያደርስ ጽናትን አያላብሰንም። እውነታው መሞረድ ነው እውነታው መሳል ነው፣እውነታው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ማለፍና ራስን ማጠንከር ነው። የሰው ልጅም ዛሬ በሁኔታዎች እራሱን እየፈተነ ማንነቱን ያጠነክራል። ዛሬ በሁኔታዎች ልቡን እያጠነከረ ለነገው ይዘጋጃል፣ዛሬ በሁኔታዎች መንፈሱን እያጠነከረ የወደፊቱን መንገድ በቀላሉ ያቅዳል።

🔑ውስጣችንን አጠንክረን የገባንበትን ፈተና በድል እንወጣው። ቁስላችን ስብራታችን ውድቀታችን ሁሉ ያጠነክሩናል እንጂ አይገሉንም፡፡

ውብ  አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
ወዳጄ ሆይ ሰውው ሁንን…. አስተውል!
ቆሞ መሄድህ መብላት መጠጣትህ ጥሩ መልበስ ጥሩ መናገር ወይንም ሀብት ክብርና ዝናህ ያንተን ሰውነት በፍጹም ሊያረጋግጡልህ አይችሉምና፡፡ ይልቅ አትዘግይ! አሁኑኑ ራስህን ፈልግ.. ዙሪያህንም አስስ..

🔆ያንተ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ ድረስላቸው ፡ ጊዜህን ባግባቡ ተጠቀም ከሚያጸጽቱህ ነገሮች ቀድመህ ለመቆጠብ ሞክር ለህሊናህ እንጅ ለስሜትህም አትገዛ ላለፈ ነገር እየተጸጸትክ ቀሪ ጊዜህን አታባክን፤

🔆ከራስህ ከፍታ ይልቅ ለሰዎችና ለሃገርህ ከበሬታ ይኑርህ ፡፡ የወደቁትን አንሳ ያዘኑትን አጽናና የተራቡትንም ሽራፊ ቁራሽ አትንፈግ፡ ባይኖርህም ፍቅር ስጣቸው እርሱ ከሁሉም ይበልጣልና!!
ለወሬ እጅ አትስጥ በጉዞህ ሂደት ውስጥ ለሚጮሁ ዉሾች ሁሉ አትደንግጥ አላማህን ለማሳካት በጽናት ጉዞህን ቀጥል  

ችግር መከራ ስቃይና ደስታንም አምኖ ለመቀበል ራስህን ዝግጁ አድርግ፤ ክፉን በክፉ ለመጋፈጥ ከመሞከር ይልቅ ውስጥህን በይቅርታና በመጸጸት ከተንኮል አጽዳ ፡፡  ከሰወች ጉዳትና ሞት ደስታን ወይም ሃብትን አትሻ!አትጠራጠር ያኔ! የንጹህ ልብ ህሊናና የዘላለም ደስታ ባለቤት የሃብታሞች ሁሉ ሃብታም …. የሰውም ሰው ነህ !!

በአብርሃም አባቡ

ውብ  አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
📕ሁሉን ነገር ካስተዋሉት ያስገርማል , የኑሮ ትንሽ የለውም, እዛ የወደቀችው ሳር አስገራሚ ናት ወፍ ለቅሞ ጎጆ ይሰራባታል ። ይሄን ሳር አጭዶ ያመጣው ማጭዱ አስገራሚ ነው ሰዎቹ ማጭድ ማሰባቸው ?! የሚያስገርመው ጉዳይ እልፍ ነው . .
ሳሩን አጭዶ ያመጣልኝ ሰውዬ ዘገየ ይባላል , ጨዋታ ያውቃል እሱ ሲያወራኝ የሚገርም ነው ታሪኩ : 'ለምን ?' ብትል እንዲያው ወንድ ሆነ እንጂ ታሪኩ ተኔ አንድ ነው።

🌗 የእኔ ታሪክ ምንም ብለፋ፣ ምንም ብቀባጥር የእኔ ብቻ አይሆን 'ለካ የእሱ የእኔን ይመስላል!' ብለህ መታዘብ አለ ... ያንተ የአንተ ከሆነ ፣ የእናትህ የእናትህ ከሆነ፣ የሰብለ የሰብለ ከሆነ፣ እንዴት እዚህ ደረስን ? እሱ እኮ ነው!

🔅"ጠዋት እዚህ ፀሐይ ስሞቅ የቆረጥኩት የአውራ ጣቴ ጥፍር ለስንት ጉንዳን እራት ይሆናል . . ? ባላርስም አበላሁ ማለት ነው ?!

ትሰማኛለህ ? . ሰሚ ካገኘ የማንም ታሪክ ይገርማል !

አዳም ረታ መረቅ

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
💢ካህሊል ጂብራን የምንኖርበትን አለም በደንብ የሚገልጽ ድንቅ አባባል አለው። " ደስታ እና ሀዘን አይነጣጠሉም፤ በአንድ አንገት ላይ የበቀሉ ሁለት እራሶች ናቸው" ብሏል።

💢ምንም አወንታዊ ብንሆን፤ ምንም የእምነት ሰው ብንሆን ምንም የተማርን እና የተመራመርን ብንሆንም፤ ከህይወት መፈራረቅ አናመልጥም። ከሀዘን እና ከደስታ፤ ከስኬትና ከውድቀት ቅብብሎሽ አንድንም። ይህ እውን ከሆነ የምንለውጠው በዙሪያችን ያለውን ሳይሆን፤ በውስጣችን ያለውን ነው።

🌀ችግር አታሳየኝ ከማለት ችግርን የማልፍበት ጽናቱን ስጠኝ ብንል፣ አልውደቅ ሳይሆን ስወድቅ የምነሳበት ጉልበት ይኑረኝ ብንል፣በሩ አይዘጋብኝ ሳይሆን እሲከከፈትልኝ ድረስ የማንኳኳበትን ትዕግስት ስጠኝ ብንል፣ፈተና አይግጠመኝ ሳይሆን ፈተናውን የማልፍበትን ጥበብ ይግለጽልኝ
ማለት ብንጀምር የውጭውን አለም መቆጣጠር ቢያቅጠን ወሳኝ የሆነው የራሳችን አለም ላይ ሰላም እናሰፍናለን። ሰው በአስተሳሰቡ ይኖራል፤ የህይወት እይታውም ሆነ እጣፋታው የሚወሰነው በአስተሳሰቡ ነው። መልካም ኑሮ በመልካም አስተሳሰብ ይገነባል።

💢 የትኛውም የህይወት ጎዳና ላይ ብንቆምም፤ ወደፈልግንበት መዳረሻ የመሄጃው እድል ዛሬም አለን። ቀዳሚው ተግባር ግን አስተሳሰባችን ላይ መስራት ነው።

ሚስጥረ አደራው

ውብ ምሽት❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
♦️መዝራትና ማጨድ

“እያንዳንዱ ቀንህን መመዘን ያለብህ በሰበሰብከው ፍሬ ሳይሆን በዘራኸውና በተከልከው ዘር ነው” - Robert Louis Stevenson

♦️ሁሉም ነገር የሚፈጠረው ሁለት ጊዜ ነው፣ በመጀመሪያ በሃሳብ መልክ፣ ከዚያም በገሃዱ ዓለም፡፡ ዛሬ በሃሳብ፣ በንግግርም ሆነ በተግባር የሚዘራው ዘር የነገውን እውነታ እንደሚፈጥርበት የማያስተውል ግለሰብም ሆነ ሕብረተሰብ ጥበብ እንደጎደለው ማሰብ አያስቸግርም፡፡ ይህንን የመዝራትና የማጨድ ሕግ ያልተገነዘበና ስርአት የሌለው ሕብረተሰብ በውጤቱ ለአመለካከቱና ለራሱ የሚገባውንና የሚመጥነውን አለም ይፈጥራል፡፡

🔷የምትኖርበት ሕብረተሰብ ያለበትን የወቅቱን ሁኔታ ተመልከት፡፡ ይህ ሕብረተሰብህ ያንን ሁኔታ ማንም አልፈጠረበትም፤ ቢፈጥርበትም ያንን ተቀብሎ የመኖርን ደካማነት ማንም አላስታቀፈውም፡፡ ይህ ሕብረተሰብ ትናንት የዘራውን ዘር ፍሬ ዛሬ እየበላ ነው፡፡ ይህ እውነታ ደግሞ በዙሪያችንም ሆነ በግል ሕይወታችን የምናያቸውን መልካምም ሆነ ክፉ ሁኔታዎች የሚወክል የማይለወጥ እውነታ ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ፣ እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ማሕበረሰብ የምንኖርበትን ዓለም የምንፈጥረው እኛው ራሳችን ነን፡፡    

🔶አንድ ሕብረተሰብ ከጥበብ ጎዳና ሲርቅ፣ ትናንት ያቆሸሸው አካባቢ ዛሬ በስብሶ ነገ በሽታን እንደሚሰጠው ማሰብ ያቅተዋል፡፡ ይህ አይነቱ ህብረተሰብ ባለበት ሲርመሰመስና የራሱን ቁስል በራሱ ምርጫና ውሳኔ ሲፈጥር አመታትን ያሳልፋል፡፡ ዛሬ በራስ ወዳድነት፣ በእኔ እበልጣለሁ ስሜትና በስግብግብነት የጎዳው የሕብረተሰብ ክፍል ነገ መልሶ ያንኑ ዛሬ እርሱ የዘራውን ዘር ፍሬ ጨምቆ መራራ ጽዋ እንደሚያስጎነጨው አያስተውለውም፡፡ በከፍታ ዘመኑ ለሰዎች ግድ-የለሽነት የዘራ ጥበብ-የለሽ ሰው፣ የእርሱ ዘመን አልፎ የሌላው ዘመን ሲመጣ ከእርሱ የባሱ ግድ-የለሾች እንዲፈጠሩ የሚያደርገው እርሱው ራሱ መሆኑን መዘንጋት የለበትም፡፡

🔷የዛሬ ጉልበተኛ፣ ነገ ከእርሱ በኋላ የሚነሳው የዘመኑ ጉልበተኛ እንዲረግጠው የሚያደርግን ዓለም የሚፈጥረው ራሱው ነው፡፡ ይህንን ሕብረተሰቡ ከዘመን ወደ ዘመን ሲርመሰመስ የሚኖርበትን ኡደት ግን ለመስበር አቅም ያለው ሰው የጥበብን መንገድ ለማስተዋል ራሱን የሰጠ ሰው ብቻ ነው፡፡  

🔶በጤንነት ዘመንህ ጊዜ ያልዘራኸውን በሕመም ጊዜ አታገኘውም፣ ያልተዘራው አይበቅልምና! በወጣትነት ጊዜ ያልዘራኸውን በሽምግልናህ ዘመን አታገኘውም፣ በሽምግልና ዘመን የሚበላው በወጣትነት ዘመን የተዘራው ዘር ነውና፡፡፡ በብዙ ወዳጅ በተከበብክና በተወዳጅነትህ ጊዜ ያልዘራኸውን በብቸኝነት ጊዜ አታገኘውም፡፡ በአመራር ከፍታ ዘመንህ ያልዘራኸውን የአመራር ዘመንህ ሲያልፍ (ማለፉ አይቀርምና) አታገኘውም፡፡  ከዚህ ውጪ ስሌት የለም፡፡ 

♦️በሚገባ ስናስበው ምርጫችን እጅግ ውስን ነው፡፡ አንዱ ምርጫችን ጤና-ቢሱን ዘር ዘርተን ጤና-ቢሱን ፍሬ ሲበሉ መኖር፡፡ ሌላኛው ምርጫችን፣ የነገን በማሰብ ዛሬ መልካም ዘርን በመዝራት የነገውን ፍሬያችንን በቁጥጥር ስር ማዋል ነው፡፡ ከእነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት ምርጫዎች ለየት ያለውን ምርጫ የሚከተሉ ብዙ ሰዎች፣ በጠማማ መንገድ ረጅም ርቀት ከተጓዙና በመጨረሻ ሁሉን ነገር ካጡ በኋላ ትክክለኛውን ነገር ፍለጋ ወደኋላ ይመለሳሉ፡፡ በንግግራቸውና በተግባራቸው የማይሆንን ዘር ሲዘሩ ከርመው አረምን ሲለቅሙ የመኖር ሞኝነት፡፡

🔷መፍትሄው አጭርና ግልጽ ነው፡፡ የምትበላውን ፍሬ ካልወደድከው፣ የዘራኸውን ዘር አስተውልና ቀይረው፡፡ ዘርህ ሲቀየር ፍሬውም ከዚያው ጋር ይለወጣል፡፡ ዛሬ  በምትወስነው ውሳኔህ፣ በምትመርጠው ምርጫህና በምትዘራው ዘርህ የነገህን በትክክል መተንበይ ትችላለህ፡፡

ውብ ቅዳሜ!❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
ምክር  ለወዳጅ

ወዳጄ ሆይ!

ጨለማው ላይ ብታፈጥ ያለ ሰዓቱ አይነጋም።ፈጣሪህን ትተህ በመከራህ ላይ ብታፈጥ አንዳች ጥቅም የለውም።ካስተዋልከው ጨለማም ውበት አለው። ከካባ ይልቅ ደማቅ ነው። እሾህም አበባ አለው። ክፉ ሰውም አንድ ጥሩ ነገር አለው። ልብ አድርግ ለክረምት በጋ፤ ለሌሊት ቀን አለው። ላንተም ጊዜ አለህ። ጊዜን የሚሰጥ ራሱ ጊዜ ሳይሆን የጊዜ ባለቤት ፈጣሪ እንደሆነ እመንና ጠብቅ።

ወዳጄ ሆይ!!

💫 አግኝቶ ያጣው ቶሎ ይከፋዋልና ታገሠው ። አጥቶ ያገኘ ምድር ይጠበዋልና ምክረው ። ከፍታህ ዝቅተኞችን በመርገጥ ፣ ህልውናህ በሌሎች ሬሳ ላይ አይሁን ። የፍቅር ሰው ለመባል ሁሉም ትክክል ነው አትበል ። ግልጽ ጥላቻ የፍቅር ያህል ነው ። ግልጽ ንግግር ሰሚውን ያከበረ ነው ። እጅግ ግልጽነትም የሚያስገምት ነው፣ ።የምሥጢር ሙዳይ ሁን እንጂ የእሳት ማንደጃ ወናፍ አትሁን ። ሰዎች ሊሰሙህ በሚችሉበት ችሎታቸውና ፍላጎታቸው መጠን ብቻ ተናገር ፣ ቁጥብ እንጂ ዝርው አትሁን ።


ወዳጄ ሆይ!

ለዕውቀት ትጋ ፣ በከፊል በተረዳኸው ነገር ራስክን እንደ አዋቂ አትቁጠር ። በከፊል ከማወቅ አለማወቅ ይሻላል ። "ሥራ ስትሠራ ደግሞ ነገ ትቼው ለምሞተው ወይም ብሠራ የሚጠቀመው ሌላ ነው" ፣ በሚል ተስፋ ቢስ ሆነህ ሳይሆን ዘላለም እንደምትኖር ያክል በመትጋት ነው ። ትጋት ጥሩ ነው ። ችኮላህ ግን ውጤት አያመጣም ፣በችኮላ መሥራትና በፍጥነት መሥራት የተለያዩ ናቸው ። እርኩሰት የዕውቀት እና ስልጣን መገለጫ አይደለምና ማንነትንና ሰብዓዊ ክብርን ከሚያጎድፉ ተግባራት መታቀብን ገንዘብ አድርግ ። "

እናም በየዕለቱ በኑሮህ ጠንቃቃ ሁን ። ያለጸጸት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁም ነገር አሳልፍ ፤ ውሳኔዎችህ ትክክለኛ መሆናቸውን መርምር ፤ ልክ እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ወይም እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ደግመህ የምትኖረውንና ለማከናወን የምትመርጠውን ዐይነት ሕይወት ለመኖር ሞክር ።

             ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
@EthioHumanitybot
🕯 እኛ ሻማዎች ነን

<<...ባንድ ምሽት ሰውዬው በባሕር ዳርቻ ባለው የወደብ ከፍታ ቦታ ትንሽ ሻማ ይዞ መውጣት ይጀምራል። በዚህ ጊዜ 'ወዴት ነው እየሄድን ያለንው?' ሲል ሻማው ጥያቄ አቀረበለት።
"እየሄድን ያለነው ከቤቱ ባሻገር ከፍ ብሎ ወደሚታየው ቦታ ነው። በዚህም ለመርከቡ የወደቡን አቅጣጫ ማሳየት እንችላለን" አለው።
"እንደምታየው የእኔ ብርሃን በጣም ውስን ናት። እንዴትስ ከርቀት ያለ መርከብ በእኔ ብርሃን ተመርቶ ወደቡ ጋር መድረስ ይችላል?" አለ ሻማው።

"ምንም እንኳ ያንተ ብርሃን ትንሽ ብትሆንም የምትችለውን ያህል ማብራትህን አታቋርጥ፣ የቀረውን ነገር ለእኔ ተውው" አለው ሰውየው። በዚህ ንግግራቸው መሀል እያሉ ከከፍታ ቦታው ደረሱና ሰውዬው ትልቁን የፋኖስ ብርጭቆ እያሳየው ሻማውን በማስጠጋት ፋኖሱን ለኮሰው። ወዲያውኑም የተለኮሰው ፋኖስ የባሕሩን አካባቢ በብርሃን ጸዳል ሞላው።

🕯እኛ ሻማዎች ነን። ከእኛ የሚጠበቀውም የሻማነታችንን ያህል ማብራት ነው። ቀሪው የሥራችን ስኬት ላይ ፈጣሪ ይታከልበታል። የአንዲት ትንሽ ሻማ መብራት ወይም ክብሪት ጫካ ሙሉ እሳት እንደምትፈጥር ሁሉ በእያንዳችን ያለች የብርሃን ምሳሌ ስናውቅም ሳናውቅም ለሌሎች ሕይወት መለወጥ ምክንያት ትሆናለችና ብርሃናችንን ሳንሳሳላት እንድትበራ እድል እንስጣት።

💡ዕድገትም ቅብብሎሽ ነው። እኛ ማድረግ የምንችለውን ሰርተን ለተገቢውና ለሚጠበቅብን ስናስረክበው እሱም በፈንታው ዳር ያደርሰዋል። ሻማዋ ለፋኖሱ እንዳቀበለችው ማለት ነው። ይህ ነው፣ ለዕድገት የድርሻን መወጣት ማለት፤ ሻማነታችንን ማበርከት የሚጠበቅብንን መወጣት። >>

📖 እርካብና መንበር [ 117-118 ]
ዲራአዝ

ውብ  አዳር❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot
📍እውነትን ፣ቅንነትን ፣ ገንዘብ ከማድረግ በላይ ኮተትን ብቻ  ገንዘብ አድርጎ ህይወቱን በክህደት፣ በውሸት ፣በጥቅመኝነት ፣በአስመሳይነት በብልጣብልጥነት እየኖረ ኑሮ የበራለት የሚመስለው ሰውነት እንዴት ያልታደለ ነው።

📍የህሊና ፣ የቤተሰብ ሰላምና ደስታ በብልጣብልጥነት አይመጣም። ፈጣሪ ባህሪና ተግባራችንን ያያል። ከሰው የወሰድነውን ከሰውየው ብንደብቅ ከአምላክ አንደብቅም። የምናተርፈው ነገር ቢኖር የሆነ ጊዜ ላይ የሚመጣ መጥፎ ስቃይን ነው። ያውም ለልጅ የሚተርፍ የበደል ክፍያን ነው፣የቆምን መስሎን የዘነጋን…. ሰው የዘራውን ያጭዳልና እናስተውል።

💡መልካምነት ከማንም በላይ ላራስ ነው ጥቅምና ፍይዳው፣ ቅን ሀሳብ አሳቢውን ይባርካል። ከአንተ የመነጨና ተንደርድሮ የተተኮሰ ኃይል በእኩል መጠን እና ልክ አጥፊ እንደሆነ ሁሉ ራስህንም ያጠፍል፤ ሀሳብህን አልሚ ከአደረከው ደግሞ ቅድሚያ አንተን እና የእኔ የምትለውን ሁሉ ባርኮ ለሌሎች ይተርፋል።

መጥፎ ነገራችንን ሁሉ በመልካም ይቀየርልን 🙏

                              ሄለን ካሳ

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
@EthioHumanitybot
💡ሰዎች በየቦታው ፍጹም ትክክል መስለው ሲታዩ  ሰውኛ አይመስለኝም ። ከራሱ እየተቧቀሰ አካባቢው በቀረፀለት የትክክለኛነት ሳጥን ውስጥ የሚንፈራገጥ ሰው ራሱን ያጣ አሳዛኝ ይመስለኛል። ለእያንዳንዱ ነገሩ የሚጠነቀቅ ሰው ራሱን እየሆነ እንዳልሆነ ነው የሚገባኝ። ራስን መሆን እርማት አይጠይቅም። ራስን መሆን ጥንቃቄ አያሻም። መጠኑ ቢለያይም ሁላችንም ጋ ጥቂት እብደት፣ ጥቂትም ስህተት፣ ጥቂትም ፀፀት እና ጥቂትም ውድቀት አለ ብዬ አስባለሁ።

💎እውነታው ሰዎች ሊያወድሱህ ከፈለጉ ከፈጣሪ ታናሽ ያደርጉሃል ። ሊዘልፉህ ከፈለጉ ደግሞ ሳጥናኤል የሚቀናበት ክፉ ያደርጉሃል ። ከሰማሃቸው ደግሞ ራስህን የመሆን እድል አይሰጡህም ። ሁሉም በፈለጉት መንገድ ሊቀርፁህ መጥረቢያ ይስላሉ ። ልብህን ከከፈትክላቸው የየድርሻቸውን ጠርበው ቅርፅ አልባ ያደርጉሃል።

💡እኔና አንተ አንድ ቦታ ላይ በተለያየ አቅጣጫ ፊታችንን አዙረን ብንቆም የእኔ ቀኝ ያንተ ግራ ነው። 'ቀኝ ይሄ ነው ወይም ግራ ይሄ ነው' ብዬ ብከራከርህ ቂል ነኝ ። እንዳንተ አቋቋም ያንተ እውነት ይሆናል ። እንደ እኔ አቋቋም ደግሞ የእኔ እውነት ይሆናል ። ባንተ እውነት ለማመን ያንተን ጫማ መዋስ አለብኝ። የቆምኩበት ሆኜ ለስህተትህ ሒሳብ እየሰራሁ ስዳኝህ እቀሽማለሁ።


📖 ጠበኛ እውነቶች
ሜሪ ፈለቀ

ውብ ቅዳሜ ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot
🌊የምታቀው የውሃ ኩሬ ራቅ ብለህ ስትመለስ ደፍርሶ ቢጠብቅህ...ንጹህ ውሃን ለመጠጣት ያለህ አማራጭ ድፍርሱ እስከሚጠራ መጠበቅ ብቻ ይሆናል ። "አፈር የተቀላቀለበትን ውሃ እንዲጠራ ከፈለግክ፤ተወው አታማስለው" ይላል ፈላስፋው አለን ዋትስ። በመተው፤በመረጋጋት፤ በዝምታ፤ ለፍተን ያጣናቸውን ውድ የህይወት ስጦታዎች እናገኛለን።

🌪ልክ እንደዚህ ሁሉ በህይወታችን የሚገጥሙንን ችግርና እንቅፋቶችን አንዳንዴ የምናጠራቸው መሃል ላይ እጃችንን ስለከተትን ብቻ ላይሆን ይችላል ። አንዳንዴ ዝምታችን እና ትእግስታችንም ብዙ ነገሮች በራሳቸው ጊዜና ሁኔታ እንዲስተካከሉልን እድል ይሰጡልናል ። እኛ ችግራችንን ለመፍታት የምናደርገው ጥረት ይበልጥ ችግር ውስጥ እንዳይዘፍቀን መጠንቀቅ ይኖርብናል ። አለዝያ የችግሩ አሳዳጊ እና አባባሽ እንጂ የችግሩ ፈቺ አንሆንም ።

🌊ለተረጋጋ አይምሮ አለም ትገበራለች ብሏል ጥንታዊው ፈላስፋ። ምንም እንኳን ብዙ ነገሮች በጥረትና በሩጫ የሚገኙ ቢሆንም፤ አንዳንድ ወሳኝ ነገሮች ግን በእርጋትና በመተው እንዲሁም በዝምታ የሚገኙ ናቸው።

ውብ  ምሽት❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity
     
@EthioHumanitybot
❤️እንኳን ለ127ኛው ለታሪካዊ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት በር ለሆነው የጥቁር ህዝቦች ኩራት የአድዋ ድል በአል በሰላም አደረሰን።

@EthioHumanity
@EthioHumanity
2024/09/27 09:24:52
Back to Top
HTML Embed Code: