Telegram Web Link
ዘለዓለማዊ እና በሁሉ ቦታ የሰፍኖ የሚኖር፣ አምላክ መሆኑን ተናገረ፡፡

ይህንን ያለበት ሁለት ምክንያች አሉት፡፡ በሁለቱ የፍልስፍና ትምህርት ቤቶች ትምህርት መሠረት "ቁስ አካል፣ አማልክትም ሆኑ ነፍስ ከአንድ ነጠላ ሕዋስ የተፈጠሩ ናቸው" ብሎ ያምናል" ይሁን አንጅ የአማልክት ነፍስ ከረቂቅ አካላቸው ጋር እንዳታመልጥ ሆና የተሰፋች ስለሆነች አማልክት ለዘላለም ይኖራሉ የሰው ነፍስ ግን ከግዘፍ አካሉ ጋር ያላት ግንኙነት የላላ ስለሆነ ነፍስን ለዘለዓም ይዞ መቆት አይችልም ስለዚህ ሰው ይሞታል ዳግመኛም አይነሣም" ብለው ያምናሉ፡፡

በተጨማሪም "ደስታን የሕይወት መለኪያ አድርጎ መውሰድ በሥነ ምግባር የታጀበ፣ ያልተወሳሰበ ሕይወት የትልቅ ደስታ ምንጭ ነው" ብለው ያስተምራሉ፡፡ "ምኞትን መቀነስ ፍላጎትን መግታት፣ ከአካላዊ ደስታ ይልቅ የሥነ ልቦና ደስታን መሻት፣ ለሰው ልጅ የሕይወት ትርጉም ብቻ ናቸው እንጅ ቁስ የተባለ ሁሉ በቦታና በጊዜ የተወሰኑ በመሆኑ የደስታ ምንጭ ሊሆን አይችልም" ይላሉ፡፡

ቁስ አካላት ከተወሰነላቸው ጊዜና ቦታ ውጭ መሆን አይችሉም እድሜያቸው በጊዜ እንቅስቃሴአቸው በቦታ የተገደበ ነው፡፡ ሰው በራሱ ቁሳዊ ነው ነፍሱ ስትለየው ሕይወትን ያቆማል፣ ሌሎቹ ቁስ አካላት የራሳቸው የሆነ ገደብ አላቸው አማልክት ከቁሳዊ ሰዎች ጋር በነፍስ ይዛመዳሉ፣ እነሱ ግን ነፍስ ከረቂቅ አካላቸው ጋር እጅግ የተጣበቀች ስለሆነች ዘለዓለማውያን ናቸው፡፡ አማልክትንም የምንፈራው እነሱ የማይሞቱ ስለሆነና እኛ ሞት አጥብቀን ስለምንፈራ ነው ይላሉ፡፡

ሁለቱ ትምህርት ቤቶች በብዙ ጉዳዮች የሚለያዩ ሲሆን በእነዚህ ትምህርቶች መጠነኛ መቀራረብ አላቸው ስለዚህ ሐዋርያው ለእነዚህ ፈላስፎች ሊያስተላልፍ የፈለገው እጅግ ብዙ ረቂቅ ትምህርት ቢኖርም ዋናዎቹና ከላይ በግልጽ የምናያቸው አንደኛው "ሰዎች ከአምላክ ጋር ዝምድና ካላቸው አምላክን ከእነሱ አሳንሰው በወርቅና በብር ወስነው ማስቀመጥ እንደሌለባቸው" ሲሆን፡፡ ቅኔያቸውንም ሳይቀር በመጥቀስ "ከእናንተ ከባለ ቅኔዎች አንዳንዶች እኛ ደግሞ ዘመዶቹ ነንና ብለው እንደ ተናገሩ፥ በእርሱ ሕያዋን ነንና እንንቀሳቀሳለን እንኖርማለን። እንግዲህ የእግዚአብሔር ዘመዶች ከሆንን፥ አምላክ በሰው ብልሃትና አሳብ የተቀረጸውን ወርቅ ወይም ብር ወይም ድንጋይ እንዲመስል እናስብ ዘንድ አይገባንም" (የሐዋ ሥራ 17፡ 28-30) ሲል የሥነ ፍጥረቱ በጊዜና በቦታ መወሰን የፈጣሪ ፈቃድ እንጅ የሰው ልጅ ከሌሎች ፍጥረታት የማነስ ጉዳይ አለመሆኑን በመግለጽ ክርስትና ከአቴና ፍልስፍና የተሻለና ፍጹም የሆነ የሥነ ፍጥረት ትንታኔ እንዳላት በማሳየት ፈላስፎቹን ከነተከታዮቻቸው መማረክ ነው፡፡

ዕብራዊው ቅዱስ ጳውሎስ የአሕዛብን በጥንታዊ የግሪክ ቋንቋ ቅኔ ውስጥ የተደበቀ ፍልስፍናና ትምህርት ሳይቀር ፈትቶ ሰው ከፈጣሪ ጋር ያለውን ዝምድና በምሥጢረ ሥጋዌ አስተማረ፡፡
ስለዚህ ሐዋርያው ቀጥሎ እንዲህ አለ እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ አሁን በየቦታቸው ንስሐ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል፤ ቀን ቀጥሮአልና፥ በዚያም ቀን ባዘጋጀው ሰው እጅ በዓለሙ ላይ በጽድቅ ሊፈርድ አለው፤ ስለዚህም እርሱን ከሙታን በማስነሣቱ ሁሉን አረጋግጦአል። አላቸው፡፡ (የሐዋ 17፡31)

ቀደም ሲል ለመግለጽ እንደተሞከረው የቅዱስ ጳውሎስ የትንሣኤ፣ የእውነተኛ ፍርድ፣ የአምላክ ኃያልነት ትምህርት በእነዚህ ፈላስፎች ዘንድ እጅግ የማይወድ ይልቁንም የሰውን ልጅ ደስታ ከሚፈታተኑት ነገሮች ውስጥ ሁለቱ ትላልቅ ጉዳዮች የአማልክት ፍርሃትና የሞት ጭንቀት ናቸው ብለው ስለሚያምኑ ሊሰሙት አልፈለጉም፡፡ በተለይ ስጦይቆች ስለ ፍርድ እጅግ ይጨነቃሉ፣ ፍርድ ከተዛባ ደስታ አይኖርም ስለዚህ ሕይወት ግቧን አትመታም ይላሉ፡፡ ኤፌቅጠሮሶች ደግሞ ስለሞት መጨነቅ እና ማሰብ ደስታን ይፈትናል፣ ተስፋ ያስቆርጣል ብለው ስለሚያምኑ ስለተንሣኤ መመራመር አይፈልጎም፣ በትምህርታቸው ነፍስ ከሥጋ ከተለየች በኋላ ተመልሳ የመዋሐድ ዕድል የላትም ይላሉ ስለዘህ ትንሣኤ ሙታንን አያምኑም፣ ከዚህ የተነሣ የሙታንንም ትንሣኤ በሰሙ ጊዜ እኵሌቶቹ ጉዳዩ ያልገባቸው ወይም የትንሣኤ ሙታንን ማመን ማለት ከአሁን ቀደም አምነው ሲያስተምሩት የነበረውን የፍልስፍና ትምሀርት በሙሉ የሚያፈራረስባቸው ስለመሰላቸው አፌዙበት፥ እኵሌቶቹ ግን በአዲስ ኪዳን ትምህርት የተመሰጡት በይበልጥም ወደ ውስጥ ገብተው ለመመርመር ፍላጎት ያላቸው ስለዚህ ነገር ሁለተኛ እንሰማሃለን አሉት። (የሐዋ 17፡ 33)፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ባስተማረበት በዚህ ቀን ወዲያው ያመኑ ነበሩ፣ ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠትና በማፌዝ የዘገዩ ነበሩ፣ በሦስተኛ ደረጃም ደግመን እንሰማሃለን ብለው ቀጠሮ የሰጡ ነበሩ፡፡ በወንጌል ተልእኮ እንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ሊገጥመን ይችላል፡፡ ጌታችን በቅዱስ ወንጌል አንዳስተማረን በገር መሬት ላይ እንደወደቀ ዘር ወዲያው ሰምተው በቃሉ ተማርከው ራሳቸውን የሚለውጡ ይኖራሉ፣ አንዳንዶቹ ካስተማርነው ትምህርት ላይ ሲያጉረመርሙ፣ ሲተቹ፣ ሲከራከሩ በአለት ወይም በጭንጫ ላይ እንደወደቀ ዘር ሳይጠቀሙበት ወይ በአእዋፍት ተለቅሞ ወይም የትችትና የፌዝ ቁጥቋጦ ውጦት የሚቀር ይኖራል፣ አንዳንዶች ደግሞ ቆይ እስኪ በደንብ እናጢነው ብለው ወደ ቤታቸው ይዘውት የሚሄዱም ሊኖሩ ይችላሉ፡፡

እንዲሁም ቅዱስ ጳውሎስ አስተምሮ መንፈሱን የረበሸውን የአማልክት መንጋ ገሥፆ ከመካከላቸው ወጣ። አንዳንዶች ወንዶች ግን ተባብረው አመኑ፤ ከእነርሱ ደግሞ በአርዮስፋጎስ ያለው የፍርድ ቤት ፈራጅ ዲዮናስዮስ ደማሪስ የሚሉአትም አንዲት ሴት ሌሎችም ከእነርሱ ጋር ነበሩ። (የሐዋ ሥራ 17፡ 33-34)

በእኛም ዘመን የማያውቀውን በማምለክ፣ የሚያውቀውን ደግሞ የማይታወቅ በማለት መሥመር በሚያስለቅቁ ትምህርቶችና ልምዶች የተወጠረ ብዙ ሰው አለ፡፡ በተለይ ከምዕራቡ ዓለም በሚፈጠረው የባህል ወረራ፣ በዓለማዊና ቁሳዊ ሐሳብ የሚባክን፣ ዘመናዊው እና ሳይንሳዊ ተብሎ የሚታወቀው ዕውቀት ይበቃኛል ብሎ የሚመካ፣ የዚህ ዓለም ገዥ የተባለው ገንዘብ የደስታ ሁል ምንጭ የፈለጉትን ለማድረግ ቁልፍ መሣሪያ አድርጎ የሚቆጥር፣ መልካም የሆነውን ቃለ እግዚአብሔር ለማግኝት በረሀብ የሚቃትት፣ ዕውነቱንም ሐሰቱንም አንድ ላይ ሰምቶ በመካከል የቆመ፣ በሥነ ምግባር ሥነ ልቦና ሁከት የሚሠራውን ክፉ ሥራ የራሱ መገለጫ አድርጎ የሚታበይ እና ብዙ ዓይነት ሰው ያለበት ትውልድ ነው፡፡ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደየአካባቢው የጎሉበት፣ የግልና ጋራ ፍላጎቶች የተምታቱበት ብዙ የኅብረተሰብ ክፍል አሁንም አለ፡፡

ስለዚህ በቋንቋ የበሰሉ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት ዕውቀት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የተካኑ፣ ዘመናዊው ዓለም የደረሰበትን ሥልጣኔና የማኅበራዊ ክንውን ደረጃ የተረዱ፣ ሌላውን የሚያከብሩ፣ የራቸውን የሚጠብቁ የወንጌል ልዑካን ያስፈልጉናል፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአቴና ከሦስት መቶ ዓመት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩ የፍልስፍና ትምህርት ቤቶች ሊቃውንትና ደቀመዛሙርት አድናቂዎችና ተከታዮች ፊት እንዲናገር ሞገስ የሆነው ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ አገልግሎታችንን ይባርክልን ያስፋልን፡፡

አኮቴት ለስሙ::

ማስታወሻ :- መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ መምህር እና የኢኦተቤ የውጪ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊ ናቸው::

#የሚከለክለኝ_ምንድን_ነው
#ወደ_ሠረገላው_ቅረብ

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
069
+ መርጦ መወለድ +

ከእገሌ ልወለድ ብሎ መርጦ የተወለደ የለም:: ምረጡ ብንባል ምን ዓይነት ወላጅ እንመርጣለን? ቀድመን የመገምገም ዕድል ቢኖረን ምን ዓይነት ወላጆች እንመርጣለን። መቼም በወላጆቼ ደስተኛ ነኝ የሚል ሰው "እኔ ደግሜም ብወለድ ከአባዬ ከእማዬ ነው መወለድ የምፈልገው" ማለቱ አይቀርም። ግን ደግሞ ዕድሉን ቢያገኝ መቼም ትንሽም ቢሆን የሚያስተካክለው ነገር አይጠፋም። መርጦ መወለድ አይቻልም እንጂ ቢቻል የምንመርጠው ልዩ ምርጫ ይሆናል።

መርጦ የተወለደ ክርስቶስ ብቻ ነው። በምድር ወደሚኖሩት ሁሉ ተመልክቶ መዓዛዋን መርጦ ፣ በቅድስናዋ ውበት ተማርኮ ከእርስዋ ሊወለድ የመረጣት የተመረጠች እናት ድንግል ማርያም ብቻ ናት። የፈጣሪ ምርጫ እንደ ሰው አይደለም። ሰው ፊትን ያያል እርሱ ግን እስከ ልብ ድረስ ዘልቆ ይመለከታል። እንዴት ብትነጻ ፣ እንዴት ብትቀደስ ነው? እስከ ውስጥዋ ዘልቆ አይቶ ከእርስዋ ሊወለድ የመረጣት? ንጉሥ ውበትዋን የወደደላት ፣ ለእናትነት የመረጣት ቅድስት እንዴት የከበረች ናት?
አዎ መርጦ የተወለደ የለም ፣ ክርስቶስ ግን መርጦ ብቻ ሳይሆን ፈጥሮ የተወለደ ነው። መቅደሱን አንጾ የገባባት እርሱ ነው። መርጦ ለተወለደብሽ ለአንቺ በጸጒራችን ቁጥር ምስጋና እናቀርባለን።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መስከረም 21 2012 ዓ ም
የግሸንዋን ንግሥት በረከት በመናፈቅ
ሜልበርን አውስትራሊያ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
+ ረቢ ወዴት ትኖራለህ? +

ከመጥምቁ ዮሐንስ ተማሪዎች መካከል ሁለቱ "የእግዚአብሔር በግ እነሆ" የሚለውን የመምህራቸውን ስብከት ሰምተው ጌታን ተከተሉት::

"ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሲከተሉትም አይቶ፦ ምን ትፈልጋላችሁ? አላቸው። እነርሱም፦ ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ? አሉት፤ መጥታችሁ እዩ፡ አላቸው። መጥተው የሚኖርበትን አዩ፥ በዚያም ቀን በእርሱ ዘንድ ዋሉ፤ አሥር ሰዓት ያህል ነበረ" ዮሐ. 1:37-39

ጌታን ተከትለው የሚኖርበትን ካዩት ደቀ መዛሙርት አንደኛው ስም እንድርያስ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የራሱን ስም በወንጌሉ ላይ እኔ የማይጽፈውና ቤተ ክርስቲያን ግን የራሱን ነገር ሲገልፅ በሚጠቀመው ቋንቋ የምታውቀው ወንጌላዊው ዮሐንስ ነበረ::

"ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ? አሉት፤ መጥታችሁ እዩ፡ አላቸው። መጥተው የሚኖርበትን አዩ" የሚለው ቃል በእርግጥ በጣም አስገራሚ ነው:: የክርስቶስን መኖሪያ ማየት መፈለጋቸው ፈልገው እንዳያጡት አድራሻውን ለማወቅ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ነበረ::
ሆኖም ክርስቶስ በምድር ላይ ሲኖር ቋሚ አድራሻ አልነበረውም:: ራሱ እንደተናገረ :-ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም" (ማቴ. 8:20)

እነዚህ ሁለት ደቀ መዛሙርት የጠየቁት "ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ?" የሚለው ጥያቄ አድራሻ ከመጠየቅ ከፍ ያለ ጥልቅ ጥያቄ ነው:: ነቢያቱ "የጥበብ ሀገርዋ ወዴት ነው? ማደሪያዋስ ወዴት ነው?" ብለው የተጨነቁለት የጥበብ ክርስቶስ ማደሪያ የት እንደሆነ ማወቅ የነፍስ ዕረፍት ነውና ተራ ጥያቄ አይደለም?
ይህ ጥያቄ ዳዊት ለዓይኖቹ እንቅልፍ ለሽፋሽፍቶቹ ዕረፍት ያልሠጠበት "የያዕቆብ አምላክን ማደሪያ እስኪያገኝ ድረስ" የለመነበት ጥያቄ ነው::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? የሚለው ጥያቄ እንድርያስና ዮሐንስ በአንድ ቀን ብቻ የሚመለስ ጥያቄ መስሎአቸው አብረውት ሔደው አብረውት ዋሉ እንጂ የጌታ መኖሪያ ግን ያን ቀን የዋለበት ብቻ አይደለም::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ?
"ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፥ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ" መዝ. 43:3

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? "ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ። እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥ በዚያ እጅህ ትመራኛለች፥ ቀኝህም ትይዘኛለች" መዝ. 139:8 ለአድራሻ የሚያስቸግረው የረቢ መኖሪያው ብዙ ስለሆነ የት ትኖራለህ ለሚለው ጥያቄ መልሱ "መጥታችሁ እዩ" ብቻ ነው::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? ብለው ለጠየቁት ደቀ መዛሙርቱ ቦታውን ከመናገር ይልቅ "መጥታችሁ እዩ" ያለው ጌታ እርሱን ጸንተው እስከተከተሉ ድረስ በሕይወታቸው ዘመን ሁሉ አልፎም ከሞቱ በኋላ የሚያዩት ብዙ መኖሪያ ስላለው ነበር::

የረቢ መኖሪያው ብዙ ነው:: "የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል፡ ወደ እርሱም እንመጣለን፡ በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን" እንዳለ ቃሉን የሚጠብቅ ሰው ሰውነትም የእርሱ ማደሪያ ነው:: (ዮሐ. 14:23)

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? " በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና" ስትል ሰምተንህ ነበር:: (ዮሐ. 14:2) የአንተ መኖሪያ መንግሥተ ሰማያት አይደለምን? ቅዱስ ጳውሎስ "ልሔድ ከክርስቶስ ጋር ልኖር እናፍቃለሁ" ሲል እንደሰማነው እስከ ዐሥር ሰዓት ድረስ እንደመዋል ዐሥሩ መዓርጋት ላይ የደረሱ በጽድቅ መንገድ የሔዱ የሚያዩት ማደሪያህ መንግሥተ ሰማያት አይደለምን? መጥተን ለማየት "እናንተ የአባቴ ቡሩካን ወደ እኔ ኑ" እስክትለን በተስፋ እየጠበቅን አይደለምን?

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? ካሉት ጠያቂዎች መካከል አንዱ ዮሐንስ መሆኑን ሳስብ ደግሞ ዮሐንስ ያያቸው የረቢ መኖሪያዎች ከገሊላ እስከ ታቦር ተራራ ፣ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ ፣ ከወንጌል እስከ ራእይ እጅግ ብዙ እንደነበሩ ታየኝ::

"ወዴት ትኖራለህ?" ብሎ ጠይቆ ጌታን የተከተለው ዮሐንስ "መጥተህ እይ" በተባለው መሠረት የጌታን መኖሪያ የእርሱን ያህል ያየም ሰው የለም::

ዮሐንስ "ረቢ ወዴት ትኖራለህ?" ለሚል ጥያቄው ግን አንጀት የሚያርስ ልብ የሚያሳርፍ መልስ ያገኘው አርብ ዕለት መስቀሉ ሥር ነበር:: ወዴት ትኖራለህ? ላለው ዮሐንስ የዘጠኝ ወር ከተማውን የዘላለም ማረፊያውን "እነኋት እናትህ" ብሎ ሲሠጠው መጥቶ ካያቸው የረቢ መኖሪያዎች ሁሉ የምትበልጠውን መኖሪያ አየ:: "እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦ ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ" ብሎ የመረጣትን ማደሪያ ከማየት በላይ ምን ክብር አለ? (መዝ. 132:13)

ዮሐንስ ይህችን የረቢ መኖሪያ ወዲያው ወደ ቤቱ ወሰዳት:: ዮሴፍ ሊወስዳት ስላልፈራ ምን እንዳገኘ ያውቃልና እርሱም ይህችን የዕንቁ ሳጥን ወደ ቤቱ ወስዶ ቢዝቁት የማያልቅ ጸጋን ተጎናጸፈ::

ጌታ እናቱን ለዮሐንስ መሥጠቱ የሁለት ድንግልናዎች ማስረጃ ሆነ:: የድንግል ማርያም ዘላለማዊ ድንግልናም የዮሐንስ ድንግልናም በጌታ ንግግር ታወቀ::

አንዳንዶች እንደሚመስላቸው ድንግል ማርያም ከጌታ ሌላ ልጆች ቢኖሩአት ኖሮ "እናቴን ከልጆችዋ ነጥለህ ወደ ቤትህ ውሰዳት" "አንቺም ልጆችሽን ይዘሽ ወደ ሰው ቤት ሒጂ" ብሎ ለዮሐንስ አይሠጣትም ነበር:: ድንግል ማርያም የአብን አንድያ ልጅ አንድያ ልጅዋ አድርጋለችና አምላክ ባደረበት ዙፋን ሌላ ፍጡር ያላስቀመጠች የአምላክ ብቸኛ ዙፋን ፣ እግዚአብሔርን አስገብታ በርዋን የዘጋች ዘላለማዊት ድንግል መሆንዋ ለዮሐንስ በመሠጠትዋ ታወቀ:: ዮሐንስም ቤት ንብረት የሌለው መናኝ ባይሆንና ሚስት ድስት ያለው ሰው ቢሆን ድንገት ወደ ቤቱ ይዞአት እንዲሔድ እናቱን ባልሠጠው ነበር::

የሰው ልጅ ድኅነት ታሪክ በሁለት "እነሆ"ዎች መሃል መከናወኑ እጅግ ይደንቃል:: የሰው መዳን የተጀመረው "እነሆኝ የጌታ ባሪያ" ብላ ራስዋን ለፈጣሪ በሠጠችው ድንግል ቃል ሲሆን የተጠናቀቀው ደግሞ "እነኋት እናትህ" ብሎ በደም በታጠበ አንደበቱ በነገረን የኑዛዜ ቃል ነው::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? ለእኛም አታሳየን ይሆን? እስከ ዐሥር ሰዓት መዋል ፣ ዐሠርቱን ትእዛዛትህን ፣ ዐሥሩን የቅድስና ደረጃዎችን መውጣት ላቃተን ለእኛስ መኖሪያህን ታሳየን ይሆን? መጥታችሁ እዩ የሚለውን ጥሪ ሰምተን ለማምጣት አቅም ላነሰን መጻጉዕዎች ፣ ዓይን ላጣን በርጤሜዎሶች ተነሡ እዩ ብለህ መኖሪያህን አታሳየን ይሆን? መቅደስህን እንመለከት ዘንድ ፣ መኖሪያህን መንግሥትህን እናያት ዘንድ ፣ ዮሐንስ ያያትን መኖሪያህ እናትህን እናይ ዘንድ እንመኛለን::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ?

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መስከረም 21 2016 ዓ.ም.
ለእመብዙኃን ዝክር የተጻፈ

"ንዒ ማርያም ለዕውር ብርሃኑ
ወንዒ ድንግል ለጽሙዕ አንቅዕተ ወይኑ
ኦ ኦ ተኃድግኒኑ ኦ ኦ ትመንንኒኑ
ኀዘነ ልብየ እነግር ለመኑ"
ወተዘከርኒ ለኃጥእ ገብርኪ ተክለ ማርያም
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
††† እንኩዋን ለአበው ሰማዕታት #ቅዱስ_ዮልዮስና_ቅዱስ_ኮቶሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

†††

††† #ቅዱስ_ዮልዮስ_ሰማዕት †††

=>ከሁሉ አስቀደሞ ስለ ሰማዕታት ዜና ሲሰማ ለዚህ ቅዱስ አንክሮ (አድናቆት): ክብርና የጸጋ ውዳሴ ይገባዋል:: ምክንያቱም ገድለ ሰማዕታትን የጻፈልን እርሱ ነውና:: ነገር ግን መጻፍ ሲባል: ነገሮች እንዲህ እንደ እኛው ዘመን ቀላል እንዳይመስሏችሁ:: ቅዱሱ ዜና ሰማዕታትን ለማዘጋጀት ሃብቱን: ንብረቱን: ቤተሰቦቹንና ሕይወቱንም ሰውቷል::

+ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- በመጨረሻው ዘመነ ሰማዕታት (በ3ኛው መቶ ክ/ዘ) ዓለም በደመ ሰማዕታት ስትሞላ የሰማዕታቱን ዜና የሚጽፍ: ሥጋቸውን እንኩዋ የሚቀብር አልተገኘም:: "ወኃጥኡ ዘይቀብሮሙ-የሚቀብራቸውም አጡ" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት:: (መዝ. 78:3)

+#እግዚአብሔር ግን ስለ ወዳጆቹ #ሰማዕታት ይህንን ቅዱስ አስነሳ:: ቅዱስ ዮልዮስ በዘመኑ ደግ ክርስቲያን: ትዳርና ልጆች ያሉት: እጅግ ባለ ጸጋና 300 አገልጋዮች ያሉት: ምጽዋትንም የሚወድ ሰው ነበር::

+በወቅቱ ክርስቲያኖች በየመንገዱ ወድቀው መታየታቸው ዕረፍት ቢነሳው ከቤተሰቦቹ ጋር መክሮ መልካም ግን ደግሞ ከባድ ውሳኔን አስተላለፈ:: ውሳኔውንም ታጥቆ ይተገብረው ጀመር:: ነገሩ እንዲህ ነው:-

1.የታሠሩ ክርስቲያኖችን ቁስላቸውን እያጠበ ያጐርሳቸዋል::

2.ቀን ቀን አገልጋዮቹን አስከትሎ የሰማዕታቱን ሥጋ እየሰበሰበ: ሽቱ ቀብቶ ይገንዛቸዋል:: አንዳንዶቹን ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲልክ ሌሎቹን ራሱ ይቀብራቸዋል::

3.ሌሊት ሌሊት በ300ው አገልጋዮቹ እየታገዘ የሰማዕታቱን ዜና: ቀለም በጥብጦ: ብራና ዳምጦ: ብዕር ቀርጾ: ሲጽፍና ሲጠርዝ ያድራል:: በተረፈችው ጥቂት ሰዓት ደግሞ ይጸልያል:: ቅዱስ ዮልዮስ በእውነት ድንቅ ሰው ነው:: በምን እንመስለዋለን! እርሱን የፈጠረውን ጌታ "ዕጹብ ዕጹብ" ብለን ከማድነቅ በቀር::

+ሰማዕታቱም ስለ ደግነቱ የሚመልሱለት ቢያጡ ዝም ብለው ይመርቁት ነበር:: ምርቃናቸውም "ለሰማዕትነት ያብቃህ" የሚል ነው:: በእርግጥ ይህ ለዘመኑ ሰዎች ምርቃት ላይመስለን ይችል ይሆናል:: እርሱ ግን ይህንን ሲሰማ ሐሴትን ያደርግ: እጅም ይነሳቸው ነበር:: በዘመኑ ትልቁ ምርቃት ይሔው ነበርና::

+እንዲህ: እንዲህ እያለ ዘመነ ሰማዕታት ሊፈጸም ወራት ቀሩት:: በዚህ ጊዜ ለሰማዕትነት ከመነሳሳቱ የተነሳ ጌታችንን ተማጸነ:: ጌታችንም ተገልጾለት "ሒድና ሰማዕት ሁን: ፈቅጄልሃለሁ" አለው:: እርሱም ደስ እያለው ዜና ሰማዕታቱን ለሁነኛ ሰው ሰጥቶ: ሃብት ንብረቱን ለነዳያን አካፈለ::

+ቀጥሎም ቤተሰቦቹንና አገልጋዮቹን ጨምሮ 500 ሰዎችን አስከትሎ ወደ ሃገረ #ገምኑዲ ሔደ:: በመኮንኑ ፊት የክርስቶስን አምላክነት ቢመሰክር ፈጽመው አሰቃዩት:: በማግስቱም ወታደሮቹ ለጣዖት ካልሰገድክ ሲሉት "ቆዩማ ላሳያችሁ" ብሎ በጸሎቱ ጣዖታትን ከነ ካህናቶቻቸው ምድር ተከፍታ እንድትውጣቸው አደረገ::

+በዚህ ተአምር የደነገጠው መኮንኑ #አርማንዮስ ከነ ሠራዊቱ በክርስቶስ አመነ:: ክብሩንም ትቶ ቅዱስ ዮልዮስን ተከተለው:: ቀጥሎም ጉዞ ወደ ሃገረ #አትሪብ ሆነ:: በዚያም ብዙ መከራን ተቀብሎ ጣዖታቱን አወደማቸው::

+እዚህም የአትሪብ መኮንን ደንግጦ ከነ ሠራዊቱ አምኖ ቅዱሱን ተከተለው:: በመጨረሻ ግን ሰማዕትነት እንዳይቀርበት ስለሰጋ ቅዱስ ዮልዮስ ተአምራት ማድረጉን ተወ:: በፍጻሜውም የ3ኛው ሃገር መኮንን ቅዱስ ዮልዮስ ከቤተሰቡና ከ1,500 ያህል ተከታዮቹ ጋር: 2ቱን የሃገረ ገዥዎች ጨምሮ አንገታቸውን አሰይፏቸዋል:: ቅዱሱም የክብር ክብርን አግኝቷል::

+"+ #ቅዱስ_ኮቶሎስ_ሰማዕት +"+

=>ይህ ቅዱስ በቀደመ ሕይወቱ አረማዊ ሲሆን የክርስቶስን ስም ሰምቶ አያውቅም:: በ4ኛው መቶ ክ/ዘ በፋርስ (አሁን #ኢራን) ሳቦር የሚባል ክፉ ንጉሥ ነግሦ ክርስቲያኖችን ያሰቃይ ነበር:: እርሱ የሚያመልከው ፀሐይና እሳት ነውና::

+የዚህ ንጉሥ ልጆቹ 'ልዑል ኮቶሎስና ልዕልት አክሱ' ይባላሉ:: በቤተ መንግስት ውስጥ ስላደጉ የሚያመልኩት የአባታቸውን ጣዖት ነበር:: በፋርስ መንግስት ውስጥ ከነበሩ የጦር አለቀቆችና ሃገረ ገዥዎች አንዱ #ጣጦስ ይባላል::

+ይህ ሰው እጅግ ብሩህ የሆነ ክርስቲያን ነበርና ዘወትር ከንጹሕ አገልግሎቱ ተሰነካክሎ አያውቅም:: ትንሽ ቆይቶ ግን ክርስቲያን መሆኑን ሳቦር ስለ ሰማ ሠራዊት ይልክበታል:: "ሒዱና ጣጦስን መርምሩት: ክርስቲያን ከሆነና አማልክትን እንቢ ካለ በእሳት አቃጥላችሁ ግደሉት" አላቸው::

+በአጋጣሚ የንጉሡ ልጅ ኮቶሎስና ጣጦስ በጣም የሚዋደዱ ባልንጀሮች ነበሩና ሊያስጥለው ወዶ ሔደ:: ኮቶሎስ ቅዱስ ጣጦስ ታስሮ በእሳት ሊቃጠል ሲል ደረሰ:: ወዲያውም ወደ እሳቱ ውስጥ ጨመሩት:: እነርሱ ፈጥኖ አመድ ይሆናል ብለው ጠብቀው ነበር:: ግን አልሆነም::

+ቅዱስ ጣጦስ በእሳት መካከል ቁሞ አላቃጠለውም:: እንዲያውም በትእምርተ መስቀል ቢያማትብበት እሳቱ ብትንትን ብሎ ጠፋ:: ኮቶሎስ ተገርሞ ቅዱሱን ባልንጀራውን "ወንድሜ! ሥራይ (መተት) መቼ ተማርክ ደግሞ?" ሲል ጠየቀው::

+እርሱ እስከዚያች ሰዓት ኃይለ እግዚአብሔርን አልተረዳምና:: ቅዱስ ጣጦስ ግን "ወንድሜ! አትሳሳት: እኛ ክርስቲያኖች መተትን አናውቅም:: በፈጣሪያችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ግን ሁሉን ማድረግ እንችላለን" ሲል መለሰለት::

+ኮቶሎስ ተገርሞ "አሁን እኔ በክርስቶስ ባምን እንዳንተ ማድረግ እችላለሁ?" ቢለው ቅዱሱ "አዎ ትችላለህ!" አለው:: ወዲያውም "እሳት አንድዱልኝ" አለና እጣቱን በመስቀል ምልክት አስተካክሎ ወደ እሳቱ ቢያመለክት እሳቱ 12 ክንድ ርቆ ተበትኖ ጠፋ::

+በዚያችው ሰዓት ቅዱስ ኮቶሎሰ በክርስቶስ አመነ:: ክብሩንና የአባቱን ቤተ መንግስት አቃሎ ወደ እስር ቤት ገባ:: አባቱ ሳቦር ይህን ሲሰማ ተቆጥቶ "ምከሪው" ብሎ እህቱን አክሱን ላከበት::

+ቅዱስ ኮቶሎስ ልትመክረው የመጣችውን እህቱን አሳምኖ የክርስቶስ ወታደር አደረጋት:: አስቀድሞ #ቅዱስ_ጣጦስ: አስከትሎም #ቅድስት_አክሱ ተገደሉ:: በፍጻሜው ግን ቅዱስ ኮቶሎስን እግሩን አስረው በየመንገዱ ጐተቱት:: በጐዳናም አካሉ እየተቆራረጠ አለቀ:: ክርስቲያኖች በድብቅ መጥተው የ3ቱንም ሥጋ በክብር አኑረዋል::

=>አምላከ ቅዱሳን ሰማዕታትን ባጸናበት ጽናት ሁላችንም ያጽናን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::

=>መስከረም 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
2."1,500" ሰማዕታት (የቅዱስ ዮልዮስ ማሕበር)
3.ቅዱስ ኮቶሎስ ሰማዕት
4.ቅድስት አክሱ ሰማዕት
5.ቅዱስ ጣጦስ ሰማዕት
6.ቅዱስ ባላን ሰማዕት

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
3.ቅዱስ ደቅስዮስ (የእመቤታችን ወዳጅ)
4.አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት
5.አባ ዻውሊ የዋህ

=>+"+ ሰውን ከአባቱ: ሴት ልጅንም ከእናቷ . . . እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና:: ለሰውም ቤተሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል:: ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም:: ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም:: መስቀሉን የማይዝ በሁዋላየም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም:: +"+ (ማቴ. 10:35)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
EOTC ቤተ መጻሕፍት pinned «+ መርጦ መወለድ + ከእገሌ ልወለድ ብሎ መርጦ የተወለደ የለም:: ምረጡ ብንባል ምን ዓይነት ወላጅ እንመርጣለን? ቀድመን የመገምገም ዕድል ቢኖረን ምን ዓይነት ወላጆች እንመርጣለን። መቼም በወላጆቼ ደስተኛ ነኝ የሚል ሰው "እኔ ደግሜም ብወለድ ከአባዬ ከእማዬ ነው መወለድ የምፈልገው" ማለቱ አይቀርም። ግን ደግሞ ዕድሉን ቢያገኝ መቼም ትንሽም ቢሆን የሚያስተካክለው ነገር አይጠፋም። መርጦ መወለድ አይቻልም…»
Audio
የወርቅ መቅረዝ 
                                                  
Size:- 61.4MB
Length:-2:56:12
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery

አመ ፳ወ፯ ለመስከረም ዘቀዳማይ ጽጌ በዓለ መድኃኔዓለም ማህሌት
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
ለማንኛውም ወርኃዊ እና አመታዊ ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ
.....................................................
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

መልክዓ ሥላሴ፦
ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል፡፡

ዚቅ፦
እግዚኦ በሰማይ ሣህልከ፤ ወበደመናትኒ አንተ አርአይከ ኃይለከ፤ወበምድርኒ ዘሠናየ ጽጌ ወጥዕመ ፍሬ አንተ አርአይከ፤ወበቀራንዮ አንተ አርአይከ ትሕትናከ፤በዲበ ዕፀ መስቀል

ዓዲ(ሌላ) ዚቅ፦
ሐፁር የዓውዳ ወጽጌ ረዳ ፤ብእሲ ተወልደ በውስቴታ፤ንጉሠ እስራኤል ፤ አልቦ ማኅለቅት ለመንግሥቱ ፤ንጉሠ እስራኤል ህየ ማህደሩ ለልዑል ፤ንጉሠ እስራኤል ፤መድኃኔዓለም እግዚአብሔር ኀደረ ላዕሌሃ፤ ኪያሃ ዘሠምረ ሀገረ

መግቢያ ዘማኅሌተ ጽጌ

ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፤ተሠርገወት ምድር  

(🌹#በህብረት_ሁሉም🌹)
በስነ ጽጌያት፤ለመርዓዊሃ ትብሎ መርዓት፤ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት።

ማኅሌተ ጽጌ፦
ጽጌ አስተርአየ ሠሪጾ  እምዓጽሙ፤ለዘአምኃኪ ጽጌ ለገብርኤል ምስለ ሰላሙ፤ወበእንተዝ ማርያም ሶበ  ሐወዘኒ ጣዕሙ፤ለተአምርኪ አኀሊ እሙ፤ማኅሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፡፡

ወረብ
መዓዛ ጣዕሙ ለተአምርኪ ሶበ ሶበ ሐወዘኒ/፪/
ወበእንተዝ ማርያም አኅሊ ለተዓምርኪ/፪/

ዚቅ፦
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ናሁ አስተርአየ ጽጌ መርዓቱኒ ትቤ ወልድ እኁየ ይምዕዝ ከርቤ፤ ዕንባቆም ነቢይ ግብረ ምግባሩ ለወልድ አንከርኩ ይቤ፤ ንጉሠ ሰላም ክርስቶስ ዓቢይ ልዕልናከ ወመንክር ስብሐቲከ፤ለዕረፍት ሰንበት ሠራዕከ፤

ማኅሌተ ጽጌ፦
ዓይኑ ዘተገብረ ፈውስ እንበለ ትትወለዲ ድንግል እምቤተ ክህነት ወንግሥ፤ መድኃኒተ ዓለም ኮነ ደመ ክርስቶስ፤ እሰግድ ለተአምርኪ በአብራከ ሥጋ ወነፍስ፤ በከመ ሰገደ ለወልድኪ ዮሐንስ በከርሥ

ወረብ፦
ዓይኑ ዘተገብረ ዘተገብረ ፈውስ ድንግል እንበለ ትትወለዲ/፪/
መድኃኒተ ዓለም ኮነ ደመ ጽጌኪ ክርስቶስ/፪/

ዚቅ፦
መድኃኒት ኮነ ለአሕዛብ፤መድኃኒተ ኮነ መድኃኒተ ኮነ፤ ለአሕዛብ መድኃኒተ ኮነ

ማኅሌተ ጽጌ
እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላህ፣ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ

ወረብ
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ /፪/
አመ  ቤተ  መቅደስ  ቦእኪ ሠናይትየ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ/፪/

ዚቅ፦
ንዒ ርግብየ ሰላማዊት፤ ተመየጢ ወንርአይ ብኪ ሰላመ፤ በአምሳለ ወርቅ ይግበሩ ለኪ ኮሰኮሰ ዘብሩር፤ አመ ወለደቶ አርአያ ወሰደቶ፤ በትእምርተ መስቀል፤ ትፍሥሕትኪ ውእቱ፤ ብርሃንኪ ውእቱ ሰላምኪ።

ማኅሌተ ጽጌ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ወረብ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ  መንግሥቱ/፪/

ዚቅ
ነያ ሠናይት ወነያ አዳም፤ አግዓዚት ማርያም ጽርሕ ንጽሕት፤ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት፤ ማ፦ ወዲበ ርእሳኒ አክሊል፤ ፅሑፍ በትምህርተ መስቀል

ዓዲ(ሌላ) ዚቅ፦
አክሊል ዘእምጳዝዮን ተደለወ :ጌራ ባሕሪይ ወቀጸላ ወርቅ ጽሩይ በቤተልሔም ተወልደ እምድንግል በብስራትክሙ መሐይምናን እምአፈ ዮሐንስ ሥርግው ተቀሰመ አፈው ሰባኬ ወንጌል ነዋ በማዕከለ አኃው

ሰቆቃወ ድንግል
በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ ሕፀተ ግጻዌ ዘአልቦ፤ሰቆቃወ ድንግል እጽሕፍ በቀለመ አንብዕ ወአንጠብጥቦ፤ወይሌ ወላህ ለይበል ዘአንቦ፤ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ሶበ ለኩለሄ ረከቦ፤ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ

ወረብ፦
ከማሀ ኀዘን ከማሀ ኀዘን ወተሰዶ ኀዘን/፪/
ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ ዓይነ ልብ ዘቦ/፪/

ዚቅ፦
እወ አማን እምውሉደ ሰብእ አልቦ፤ምንዳቤ ወግፍዕ ዘከማኪ በዉስተ ኩሉ ዘረከቦ፤

መዝሙር

ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ትዌድሶ መርዓት፤እንዘ ትብል ነዓ ወልድ እኁየ፤
ንፃዕ ሐቅለ፤ትዌድሶ መርዓት ንርዓይ ለእመ ጸገየ ወይን፤ወለእመ ፈረየ ሮማን፤ትዌድሶ መርዓት አሠርገወ ሰማየ በከዋክብት፤ወምድረኒ በስነ ጽጌያት፤ትዌድሶ መርዓት
እስመ ውእቱ ወልድ ዋሕድ፤እግዚአ ለሰንበት፤ማ፦ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ፤
ወልድ እኁየ ቃለከ አዳም።

አመላለስ፦
ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ/፪/
ወልድ እኁየ ቃለከ አዳም/፬/
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
#መስከረም_23

መስከረም ሃያ ሦስት በዚህች ዕለት የክርስቶስ ሙሽራው የሆነች #ቅድስት_ቴክላ መታሰቢያ በዓሏ ነው፤ ዳግመኛም #ቅዱሳን_አውናብዮስ_እና_እንድርያስ በሰማዕትነት አረፉ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_ቴክላ_የክርስቶስ_ሙሽራው

መስከረም ሃያ ሦስት በዚህች ዕለት የክርስቶስ ሙሽራው የሆነች ቅድስት ቴክላ የመታሰቢያ በዓሏ ነው፡፡

ይህችውም ቅድስት ለሐዋርያው ለቅዱስ ጳውሎስ ረድእ ሆና ያገለገለች ታላቅ ሐዋርያዊት እናት ናት፡፡ የመቄዶንያ ሀገር ባለጸጎች የነበሩት ወላጆቿ ጣዖት አምላኪ ነበሩና በሕጋቸውና በሥርዓታቸው አሳደጓት፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወደዚህች ሀገር ገብቶ ቅዱስ ወንጌልን ሰበከ፡፡ ቅድስት ቴክላም ትምህርቱን በሰማች ጊዜ በቤቷ ሆና ሳትበላና ሳትጠጣ 3 ቀን ቆየች፡፡ ከዚህም በኋላ ለሚጠብቃት ዘበኛዋ እንዳይናገርባት በማለት የወርቅ ወለባዋን ሰጠችውና ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሄደች፡፡ እርሱም በደስታ ተቀብሎ የክርስቶስን ሃይማኖት አስተማራት፡፡ በማግሥቱም ቅድስት ቴክላን እናቷ ስትፈልጋት ከቅዱስ ጳውሎስ እግር ሥር አገኘቻት፡፡ ከዚያም ወደ መኰንኑ ዘንድ ሄዳ ልጇ ክርስቲያን መሆኗን በመናገር ከሰሰቻትና ለመኰንኑ አሳልፋ ሰጠቻት፡፡

መኰንኑም ሁለቱን ቅዱስ ጳውሎስንና ቅድስት ቴክላን እንዲያመጧቸው ወታደሮቹን ላከ፡፡ ካመጧቸውም በኋላ መጀመሪያ ቅዱስ ጳውሎስን ወደ እሳት ወረወሩት፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በተአምራት አዳነው፡፡ ቅድስት ቴክላን ግን ለሀገሩ ልጆች መቀጣጫ ትሆን ዘንድ መኰንኑ ሰውን ሁሉ ከሰበሰበ በኋላ ወደ እሳቱ እንዲወረውሯት አዘዘ፡፡ እርሷ ግን በመስቀል ሦስት ምልክት ካማተበች በኋላ በራሷ ፈቃድ ማንም ሳይነካት ዘላ ከእሳቱ ውስጥ ገባች፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሔር ጥበቃ ልክ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ እርሷም ማንም ሳያያት ከእሳቱ ውስጥ ወጥታ ቅዱስ ጳውሎስ ካለበት ደረሰች፡፡ የራሷንም ጸጉር ቆርጣ በእርሱም ወገቧን ታጥቃ ቅዱስ ጳውሎስን ተከተለችው፡፡

መኰንኑም በሕይወት መኖሯን ሰምቶ ድጋሚ አስፈልጎ አስያዛትና ሃይማኖቷን እንድትለውጥ አስገደዳት፡፡ እሺ እንዳላለችው ባወቀ ጊዜ በተራቡ አንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ጨመራት ነገር ግን አንበሶቹ ሰግደው የእግሯን ትቢያ ሲልሱላት ተመለከተ፡፡ መኰንኑም ይህንን በተመለከተ ጊዜ እርሱና ወገኖቹም ሁሉ አምነው ተጠመቁና የክርስቶስ መንጋዎች ሆኑ፡፡ ቅድስት ቴክላም የጌታችንን ወንጌል በማስተማርና ቅዱስ ጳውሎስንም በማገልገል ብዙ ከተጋደለች በኋላ መስከረም 27 ቀን ዐርፋለች፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱሳን_አውናብዮስ_እና_እንድርያስ

ዳግመኛም በዚች ቀን ቅዱሳን ጻድቃን መነኰሳት አውናብዮስና እንድርያስ በሰማዕትነት አረፉ። እሊህ ቅዱሳንም ከልዳ ሀገር ከታላላቆቹ ተወላጆች ናቸው ከታናሽነታቸውም በአምላካዊ ምክር ተስማምተው በሶርያ ውስጥ ከሚገኙ ገዳማት ወዳንዱ ገዳም ሒደው መነኰሳት ሆኑ።

ከዚህም በኋላ ወደ ከበረ ወደ ተመሰገነ አባ መቃርስ ሔዱ ደቀ መዛሙርቱም ሁነው ታዘዙለት ምክሩንም በመቀበል በጾም በጸሎት በገድል ሁሉ ተጠምደው የሚኖሩ ሆኑ በእንዲህ ያለ ሥራም በዚያ ሦስት ዓመት ኖሩ በጎ የሆነ ተጋድሎአቸውና የአገልግሎታቸው ዜና በተሰማ ጊዜ አውናብዮስን መርጠው ኤጲስቆጶስነት፣ እንድርያስን ቅስና ሾሙአቸው በበጎ አጠባበቅም የክርስቶስን መንጋዎች ጠበቋቸው።

ከዚህም በኋላ ሥጋቸውን ፈጽሞ እስከ አደከሙ ድረስ ተጋድሎአቸውንና አገልግሎታቸውን እጅግ አበዙ። ከሀዲ ንጉሥ ዮልዮስም ስለእርሳቸው በሰማ ጊዜ ወታደሮች ልኮ ወደርሱ አስቀርቦ የክብር ባለቤት ክርስቶስን ክደው ወደ ረከሰች አምልኮቱ እንዲገቡ አዘዛቸው ያን ጊዜ እርሱንና የረከሱ ጣዖታቱን ረገሙ እርሱም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃያቸው ወደ ብዙ ክፍልም ቆራርጦ ከፋፈላቸውና ነፍሳቸውን በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ። እያንዳንዳቸውም ሦስት ሦስት አክሊላትን ተቀበሉ አንዱ በገድል ስለ መጸመድና ስለ ምንኲስና ዋጋ፣ ሁለተኛው ስለ ክህነት አገልግሎት፣ ሦስተኛው ደማቸውን ስለ ማፍሰሳቸው ነው።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

#ስንክሳር_ዘወርኀ_መስከረም
@petroswepawulos
@petroswepawulos
@petroswepawulos
ቅድስት_ድንግል_ማርያም_ሕይወቷ_ተአምራቷ_መገለጧ.pdf
3.6 MB
ቅድስት ድንግል ማርያም ሕይወቷ ተአምራቷና መገለጧ

በአቡነ_ሺኖዳ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
Forwarded from Quality move bot
ተዋህዶ ሀይማኖቴ ነው ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ መረዳት መጻህፍትን ማንበብ እፈልጋለው የየእለቱን ስንክሳር ማንበብ እፈልጋለው ያለ ሁሉ ሊቀላቀላቀላቸው ሚገባ ድንቅ ኦርቶዶክሳዊ ቻናል 3 ቻናሎች
👇 ከታች Join በሉ
#ጉባኤ_ሐዲስ_ኪዳን
(ለማስታወስ) 👇
ማቴ 8፥26-ፍጻሜ (የመጨረሻው ክፍል) 👇

#የእምነ_መጉደልና_ፍርሃት

"እርሱም። እናንተ እምነት የጎደላችሁ፥ ስለ ምን ትፈራላችሁ? አላቸው፤ ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ነፋሱንና ባሕሩን ገሠጸ፥ ታላቅ ጸጥታም ሆነ" ማቴ 8 ፥ 26።

• ፍርሃት በሁለት ይከፈላል ፤ 1ኛ የተፈጥሮ ፍርሃት ሲሆን 2ኛ የእምነት ማነስ ነው
• የእምነት መጉደል ፍርሃትን ያመጣል
• ሐዋርያት ገና ፍጹማን አለመሆናቸውን ያሳያል
• እንደሚያድናቸው ቢያምኑም ከተኛ ግን እንደማያድናቸው ማሰባቸው ስህተት ነበር
• ስለዚህም ከማዕበለ ባህር አስቀድሞ የሐዋርያትን ልብ ባህር ሞገደ ፍርሃት ገሠጸ
• ከዚያም ማዕበለ ሞገዱን ጸጥ አደረገ ፤ በዚህ ወቅት ጸጥ ያለው በዓለማት ያሉ አብሕርት ውቅያኖሰ ማዕበል ሞገድ ነበር
• ለአበው ለነቢያት….ለሐዋርያት ለጸሎታቸው መልስ ሰጠ
• በዚህ ቃል የሰማዕታትን በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ፍርሃት ማስወገዱን እናምናለን
• ወአውየዉ ኀበ እግዚአብሔር ሶበ ተመንደቡ
• ወአድኀኖሙ እምንዳቤሆሙ
• አጥፍኣ ለአውሎ ወአርመመ ባሕር
• ወአርመመ ማዕበል
• ወተፈሥሑ እስመ አእረፉ
• ወመርሖሙ ውስተ መርሶ ኀበ ፈቀዱ… መዝ 106፤28-31
#ተደነቁ!

• ይህ ቃል በማቴዎስ ወንጌል ስድስት ጊዜ ያህል ተመዝግቧል፤ ማቴ 8፡27፤ 9፡8፤9፡33፤15፡31፤21፡20፡22፡22
• በአብዛኛው የተደነቁት በተአምራቱ ነበር

• ባህርና ነፋሳት የሚታዘዙለት ይህ ማነው ብለው ተደነቁ
• ተአምራቱ ከሙሴ ከኢያሱ ከኤልሳዕ ልዩ ነውና ይህ ማነው ብለው ተደነቁ
• ሙሴ በበትር፤ ኢያሱ በታቦት ፤ ኤልሳዕ በኤልያስ መጎናጸፊያ ነበር ባህር የከፈሉት፤ ጌታ ግን በቃል ብቻ !

• ይህ ማነው ብለው የተደነቁበትን ቃል ማቴ 16፡13 ላይ በክፍሉ እንመለከተዋለን
ማቴ 8፡28-ፍጻሜ (ንባብ)
• ወደ ማዶም ወደ ጌርጌሴኖን አገር በመጣ ጊዜ አጋንንት ያደሩባቸው ሁለት ሰዎች ከመቃብር ወጥተው ተገናኙት፤እነሱም ሰው በዚያ መንገድ ማለፍ እስኪሳነው ድረስ እጅግ ክፉዎች ነበሩ

• እነሆም ኢየሱስ ሆይ! የእግዚአብሔር ልጅ ከአንተ ጋር ምን አለን? ጊዜው ሳይደርስ ልትሳቀየን ወደዚህ መጣህን? እያሉ ጮኹ
"ከእነርሱም ርቆ የብዙ እሪያ መንጋ ይሰማራ ነበር
አጋንንቱም ታወጣንስ እንደሆንህ ወደ እሪያው መንጋ ስደደን ብለው ለመኑት፤ ሂዱ አላቸው
እነርሱም ወጥተው ወደ እሪያዎቹ ሄዱና ገቡ፤ እነሆም የእሪያዎቹ መንጋ ሁሉ ከአፋፉ ወደ ባህር እየተጣደፉ ሮጡ በውኃም ውስጥ ሞቱ
እረኞቹም ሸሹ ወደ ከተማዪቱም ሄደው ነገሩን ሁሉ ፤ አጋንንትም ባደሩባቸው የሆነውን አወሩ
እነሆም ከተማው ሁሉ ኢየሱስን ሊገናኝ ወጣ ፤ ባዩትም ጊዜ ከሀገራቸው እንዲሄድላቸው ለመኑት "

#ጌርጌሴኖን

• ጌርጌሴኖን የአጋንንት ሰፈር/መንደር ነው

• የሙታን ነፍስ በሕያው አድራ የዘመዶቿን ጠላት ታጠፋለች የሚል ባህል ስለነበር ጠላቶቻቸውን ለማጥፋት ልጆቻቸውን የገደሉ ያረዱ ነበሩ፤ በዚህ ምክንያት አጋንንት ያንን ደም እየጠጡ ይኖሩ ነበር

ምሳሌነቱም ፡-
• የዚህ ዓለም(ምድረ ደይን/ፍዳ)
• የመቃብር
• የሲኦል ምሳሌ ነው ብለን ነበር

#አጋንንት_ያደሩባቸው_ሁለቱ_ሰዎች

• ጋኔን ማለት እሩቅ ውዱቅ ፤ ከማዕርጉ የወደቀ ከክብሩ የራቀ፤የተራቆተ ማለት ነው፤ አጋንንት ለብዙ ነው
• ጋኔን የሚለውን ቃል ለሰይጣንና ለማደሪያው እንጠቀምበታለን ፤ ሰው የሰይጣን መኖሪያ ሲሆን ጋኔን ተብሎ ይጠራል
• ልቡሳነ ሥጋ አጋንንት አሉ እንደ ሰው ሥጋ የለበሱ በሥጋዊ ጥበብ የሚሠወሩ የሰይጣን ወዳጆች የሆኑ አሉ፤ በዋናነት እነሱ አጋንንት ይባላሉ
• በዚህ ዓውድ አጋንንት ያደሩባቸው ማለት መናፍስት ርኩሳን ያደሩባቸው ለማለት ነው፤ በመሳሪያዎቻቸው አጋንንት ብሎ ጠርቷቸዋል
• ርኩሳን መናፍስት ለሥነ ልቡናችን ቅርብ በመሆናቸው እውነቱን ሐሰት ሐሰቱን እውነት በማስመሰል የሚፈትኑን የሚያስቱን ናቸው፡፡
• አጋንንት ያደሩባቸው ሁለት ሰዎች የአዳምና የሔዋን ምሳሌዎች ናቸው
• አጋንንት ያደሩባቸው ሁለቱ ሰዎች የኔፊሊም ምሳሌዎች ናቸው

• ባህር ገብተው መሞታቸው በማየ አይኅ መጥፋታቸውን ያሳያል
• እሪያዎቹ በዘመኑ የነበሩ ሰዎች ምሳሌ …አብረው ጠፍተዋልና

• ሁለቱ ሰዎች የፈርዖንና የሄሮድስ ምሳሌ

• እሪያዎቹ የግብፃውያን እንዲሁም የእኩያን እስራኤላውያን ምሳሌ…በባህር/በመከራ ሰጥመው ሞተዋልና

• አጋንንት በቁሙ እሪያዎቹ የኢአማንያን ምሳሌ

ጌታ ሆይ ሀገራችንን አስባት!
እኛን አትይ! ስለ ወዳጆችህ ፊት ብለህ ማረን!
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
ኢሬቻ/ዋቄፈና/ ለክርስቲያን ምኑ ነው?
(በዲ/ን ሕሊና በለጠ)

ቤተ ክርስቲያን በባሕርይዋ የአንድ ማኅበረሰብን ባሕል ንቃም ኾነ ተቃውማ አታውቅም። በተቻላት መጠን ማኅበረሰቡ ከነ ባሕሉ ድኅነትን ያገኝ ዘንድ ሃይማኖቷንና ሥርዓቷን አስተምራ ታስተናግደዋለች እንጂ። ከእርሷ አምልኮ በተቃራኒው የሚያመልክ የአንድን ተገዳዳሪ የእምነት ተቋም አምልኮም በማይገባ መልኩ ተችታና አኮስሳ አታውቅም፤ እውነተኛውን መንገድ ግን በተገቢው መልኩ በጥብዓት ታስተምራለች። የዚያ የእምነት ተቋም አምልኮና እምነት ስሕተት ከኾነ ሰዎች ኹሉ ይድኑ ዘንድ እውነትን ትሰብካለች፤ ወደ እውነት ትመራለች፣ ታደርሳለች።

ኢሬቻ ምንድን ነው? ባሕል ነውን?

መልካም፣ ባሕልስ ከኾነ ቤተ ክርስቲያን የባሕሉን አክባሪ ባሕሉን ሳይዘነጋ ይቀበላት ዘንድ አይገዳትም። እርሷም ከነ ባሕሉ ዐቅፋና ደግፋ ትቀበለዋለች።

ግን ኢሬቻ ባሕል ነው?

አይመስለኝም። ሰሞንኛ ተናጋሪዎችን እንዘንጋቸውና እስኪ እንዴት እንደተከበረ እንመርምር። የመርሐ ግብሩ ተሳታፊዎች ውኃ ውስጥ ሣር እየነከሩ ወይም ዛፍን ቅቤ እየቀቡ ፈጣሪን ሲያመሰግኑ የሚያሳዩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን ስናይ ነበር። ስለዚህ ይህ በዓል:-

#1ኛ ፈጣሪ የሚመሰገንበት ነው (ይህም ተደጋግሞ በአክባሪዎቹ እየተነገረ ነው)። በፈጣሪ መኖር ማመን ደግሞ: ለሃይማኖት ህልውና የመጀመሪያው መስፈርት መኾኑን ልብ ይሏል። ስለዚህ ኢሬቻ/ዋቄፈና/ ለሃይማኖትነት ትልቁን መሥፈርት አሟልቷል ማለት እንችላለን።

#2ኛ የታወቀ የምስጋና (አምልኮ?) ሥርዓት (ለምሳሌ:- ሣር ውኃ ውስጥ መንከር፣ ቅቤ መቀባት ...) አለው። ይህም እስልምናም ኾነ ክርስትና የታወቀ የአምልኮ ሥርዓት እንዳላቸው ማለት ነው።

#3ኛ እስልምና መስጊድ፣ ክርስትናም ቤተ ክርስቲያን እንዳላቸው ኹሉ: ኢሬቻም /ዋቄፈናም/ ይህ ሥርዓት የሚፈጸምበት ቦታ (Sacred Place, ለምሳሌ:- ውኃና ዛፍ ያለበት ሥፍራ) አሉት።

#4ኛ ሃይማኖታዊ የአምልኮ ሥርዓት በካህናት እንደሚመራ: ክብረ በዓሉን የሚመሩ የሥርዓት መሪዎች (አባ ገዳዎች?) አሉት።

ስለዚህ ወይ አምልኮ ነው፣ ወይም ደግሞ ከቆይታ ብዛት ወደ ባሕልነት የተቀየረ አምልኮ ነው።

#ዐቢይ_ነጥብ - ከላይ ከጠቀስናቸው ከዐራቱ ለጊዜው አንዱን ብቻ እንምረጥ -

-ፈጣሪ የሚመሰገንበት መኾኑ

ይህ ብቻ "ባሕል ነው" ለሚሉት ቆም ብለው እንዲያስቡ የሚያስገድድ ምክንያት ነው።

ፈጣሪን ማመስገን የሚቻለው በእምነት ነው። በመጀመሪያ ይህን ፈጣሪ ማመንና በጥቂቱም ቢኾን በእምነት ማወቅ ይገባል። ቢያንስ ፈጣሪ መኾኑን በእምነት መረዳት ያሻል። ከዚያም እርሱ በሚፈልገው ሥርዓት እርሱን ማመስገን/ማምለክ ይከተላል። እርሱን ማምለኪያ ውሱን ሥርዓት የለም ቢባል እንኳን: የማመስገኛ ሥርዓቱ "ሥርዓት የለሽ በመኾን" ይገለጻል፤ (non-religiousness is my religion) እንዲል አንድ የፍልስፍና መምህር /ፈላስፋ ላለማለት ነው/)።

ሙስሊሙ ፈጣሪን የሚያመሰግንበት ሥርዓትና ቦታ አለው፤ ሳምንታዊ(ጁምዓ) እና ዓመታዊ (ኢድ አል ፈጥር፣ ኢድ አልአድሃ) የበዓላት ዕለታትም አሉት። ክርስቲያኑም እንዲሁ ከሳምንታዊ ሰንበትን፣ ከዓመታዊ ልደትና ትንሣኤን የመሰሉ (ዕለታዊና ወርኃዊውን ጨምሮ) ብዙ በዓላት አሉት። ሙስሊሙም ክርስቲያኑም በየበዓላቱና በየታወቀ ሥርዓቱ ፈጣሪን ያመሰግናሉ፣ ያመልካሉ። ነገር ግን ክርስቲያኑ ኢሬቻ የሚል ፈጣሪን የማመስገኛ በዓል በዚቁ (liturgical Calendar) ውስጥ የለም። ሙስሊሙም እንደዚያ።

ሌላው ነጥብ: ኹሉም እምነት ፈጣሪን የተመለከተ መሠረተ-ትምህርቱ (Doctrine/Creed) ከሞላ ጎደል ይለያያል። ሙስሊሙም (ካልተሳሳትኩ) "ላ ኢላህ ኢለላህ መሐመዱር ረሱለላህ" የሚል ሸሀዳ (Creed) አለው። ይህንን አዘውትሮ ያደርሳል። ፕሮቴስታንቱ "ክርስቶስ አማላጄ" (ሎቱ ስብሃት) ይላል። እኛ ኦርቶዶክሳውያን ደግሞ "ኹሉን የፈጠረ አንድ አምላክ በሚኾን በእግዚአብሔር አብ እናምናለን" ከሚለው ጀምሮ የክርስቶስንና የመንፈስ ቅዱስን አንድ የባሕርይ አምላክነትና ከአብ ጋር መተካከል፣ የቤተ ክርስቲያንን ኲላዊነት፣ አንድነት፣ ቅድስናና ሐዋርያዊነት፣ የጥምቀትን የኃጢአት ማስተሥሪያነት፣ የትንሣኤ ሙታንን ተስፋነት የምንመሠክርበት የዘወትር ጸሎተ ሃይማኖት (Creed) አለን።

እነዚህ እምነቶች ይለያያሉ ብቻም ሳይሆን ይቃረናሉ። እንዴት በአንድነት ምስጋናቸውን ለአምላክ ያደርሳሉ?

እኔ አምላክ የምለውን ክርስቶስን አንዱ ከአጠገቤ "አማላጄ" እያለው እንዴት አንድነት ይኖረኛል? አንዱስ "ነቢይ" እያለው እንዴት አብረን እናመሰግናለን? የኔን አምላክ አማላጅም ፣ ነቢይም ማለት እርሱን ማሳነስ ለእኔም ንቀት ነው።

ሙስሊሙም አላህን አምላክ ይላል። ኢሳን ነቢይ ይላል። እኔ ከጎኑ ቆሜ ኢየሱስ ክርስቶስን "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ስል እንዴት ይዋጥለታል?

አብረን ቡና የምንጠጣ፣ አብረን ኳስ የምንጫወት፣ በንግድ የምንተባበር ሙስሊሞችና ፕሮቴስታንቶች ይኖራሉ። በጣም የምንዋደድ ጓደኛሞችና የሥራ ባልደረቦች ልንሆን እንችላለን። ግን ለአምልኮ ሙስሊሙም መስጊድ፣ ፕሮቴስታንቱም "ቸርች" እኛም ቤተ ክርስቲያን እንሔዳለን እንጂ ፈጣሪን ለማመስገን መስጊድ ወይም ቤተ ክርስቲያን በአንድነት አንሔድም።

አንድ የምንኾንበትንና የማንኾንበትን እንለይ እንጂ! በኢትዮጵያዊነት አንድ ነን፤ በባሕል እንተባበራለን፤ በልማት አንድ መኾን እንችላለን፤ እንኳን በሀገር በቤተ ዘመድም በሃይማኖት መለያየት ይገጥመናል፤ ዝምድናን ጨምሮ ግን ብዙ አንድ የሚያደርጉን ጉዳዮች አሉን። ኾኖም በሃይማኖት አንድ ካልኾንን ከእናቴም ጋር ለጸሎትና ለምስጋና አልቆምም።

እንኳን ከሙስሊምና ከፕሮቴስታንት ጋር ይቅርና በብሉይ ኪዳን በሃይማኖት አንድ ከነበርነው ከይሁዲውም ጋር ፈጣሪን ለማመስገን በአንድነት አንቆምም። የይሁዲው መሠረተ ሃይማኖት ( ሸማ፣ Creed) በእኛው ብሉይ ኪዳን ላይ ዘዳ.6÷4-9 ያለው ንባብ ነው። ይሁዲዎች ይህንን በእጃቸው ያሥሩታል (Teffilin)። በበራቸውም ይጽፉታል (Mezzuzah)። ንባቡ እኛም የምናምንበትና የምናነበው ነው። ነገር ግን ምንም ያኽል ብንወዳቸው ክርስቶስን ከማያምኑት ከይሁዲ እምነት (Judaism) ተከታዮች ጋር የሃይማኖት ኅብረት የለንም።

ወንጌላችንም ያዘናልና "ቢቻለንስ በእኛ በኩል ከሰው ኹሉ ጋር በሰላም መኖርና ሰላምን መከታተል" የክርስትና መርሐችን ነው። (ሮሜ 12÷18፣ ዕብ. 12÷14)። ኾኖም ፈጣሪን የምናመሰግንበት የሃይማኖት ኅብረት የሚኖረን ግን ከተጠመቁት ጋር ብቻ ነው።

#በተለይ_ለኦርቶዶክሳውያን

አምልኮ/ምስጋና/ ማለት ክርስቶስ ራስ ለኾነላት ቤተ ክርስቲያን ለተባለችው አንዲት አካል ብልት ለመኾን የምንጋደልበት ሰማያዊ ሥርዓት ነው። ኦርቶዶክሳውያን በአምልኮ ጊዜ እርስ በእርሳችን ብቻ ሳይኾን ከመላእክትም ጋር ረቂቅ አንድነት አለን። "በሰላም ማሠሪያ (ይህን) የመንፈስ አንድነት ለመጠበቅ እንድንተጋም" ታዘናል። (ኤፌ.4÷3)።

ወደዚህ ሰማያዊ ኅብረት ይመጡ ዘንድም ለዓለም ኹሉ እንደ ሐዋርያቱ እንጮኃለን፤ "ወደ ክርስቶስ ኅብረት በሃይማኖት ኑ" እንላለን። "እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን። ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው " እንዲል ሐዋርያው።
(1ኛ ዮሐ. 1÷3)።
2024/09/28 19:34:53
Back to Top
HTML Embed Code: