Telegram Web Link
#ለሲኖዶሳዊ_ልዕልና_መከበር_የምእመናን_ድርሻ_አስፈላጊ_ነው!

ክፍል ፩

ሐምሌ ፲፩፤ ፳፻፲፭ ዓመተ ምሕረት

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ቤተ ክርስቲያን የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና አለመከበር እንዲሁም በርካታ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ጉዳዮች ባይታዋር የሆኑበት፣ ቤተ ክርስቲያኗን ለካህናቱና ጳጳሳቱ ብቻ እየተው የመጡበት ሁኔታ ይታያል፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስትያንን ፖለቲከኞች፣ አማሳኞች፣ ምንደኞች አገልጋዮች እንዲሁም የውስጥም ሆነ የውጭ ጠላቶቿ አጀንዳ ሲያደርጓት፣ ባልዋለችበት ሲያውሏት፣ የማይገልጻትን ጥላሸት ሲቀቧት፣ ታሪኳን ሲሰርዙ፣ ሲደልዙ፣ የፕሮፖጋንዳ ሰለባ ሲያደርጓት፣ በባሰ ሁኔታ ኵላዊትነቷን፣ ዓለማቀፋዊነቷን ወደ ጎን በማለት በርካሽ የጎሳ ከረጢት ሊከቷት ሲሞክሩ እያዩ ዝም ማለታቸው ነው፡፡

ስለዚህ ቤተ ክርስቲያኗ ክብሯ ተጠብቆ ሲኖዶሳዊ ልዕልና እንዲከበርና በአገልግሎቷና በአስተዳደርዋ ሁለንተናዊ ለውጥ እንዲመጣ የምእመናን ተሳትፎ ያስፈልጋል፡፡

ይህ ጽሑፍ ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና የምእመናንን ግንዛቤ ለማሳደግ ታስቦ የቀረበ ነው፡፡

፩.፩. ቅዱስ ሲኖዶስ ማለት ምን ማለት ነው?
ሲኖዶስ ቃሉ የጽርዕ ቋንቋ ሲሆን ትርጉሙም ስብሰባ (ጉባኤ) ማለት ነው፡፡ አንድ/ቃለ ዓዋዲ፣ ሀብታችንና ሥርዓቱ/ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት/
ቤተ ክርስቲያናችን በሕግና በሥርዓት እንድትመራ ልዩ ልዩ መመሪያዎች ተሰጥተዋታል፡፡ የመመሪያው ባለቤትም ራሱ መሥራቿ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ነው፡፡ ‹‹በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው እና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ›› በማለት አደራ የሰጣቸው የሐዋርያት ተከታዮች የሆኑ ሊቃነ ጳጳሳትን ነው፡፡ (፪ኛ የሐዋ.ሥራ ፳፥፳፰) የጳጳሳቱ አንድነት ጉባኤ /ስብስብ /ደግሞ ሲኖዶስ ይባላል፡፡

፩.፪. የቅዱስ ሲኖዶስ ታሪካዊ አመጣጥ፡-

በብዙ ታሪኮች ላይ እንደ መጀመሪያ ሲኖዶስ ጉባኤ ተመዝግቦ የሚገኘው በ፶ ዓ.ም በኢየሩሳሌም የተደረገውን ጉባኤ ነው፡፡ ጉባኤውም በሐዋርያት የተደረገ ስብሰባ ሲሆን መሪውም የኢየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ያዕቆብ እንደነበረና የስብሰባው ምክንያትም ከአይሁድ ወደ ክርስትና የመጡት እና ከአሕዛብ በመጡት መካከል በነበረው አለመግባባት ላይ ለመምከር ነበር፡፡ (የሐዋ.ሥራ ፩፥፲፭) ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በርካታ ስብሰባዎች ተደርገዋል፤ በርካታ ሥርዓቶች እና ሕግጋት ለቤተ ክርስቲያን ተደንግገውበታል፡፡ በዚህም ሲኖዶስ እየተባሉ የሚጠሩ እና እስካሁን ቤተ ክርስቲያን የምትመራባቸው ሕጎች ወጥተውበታል፡፡ በኋላም በብዙ ዓለም አቀፍ ጉባኤያት /ኒቅያ፣ ቍስጥንጥንያ፣ ኤፌሶን ወዘተ/ ዳብረውና ጸንተው የተላለፉ ውሳኔዎች አሉ፡፡ ፍትሐ ነገሥት ዋናውና ትልቁ ሲሆን በርካታ የሐዋርያት ሲኖዶስ ውሳኔዎችና ሌሎች ሕጎችን ይዟል፡፡

፩.፫. የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ተግባርና ኃላፊነት ፡-

ቅዱስ ሲኖዶስ ከላይ እንደተገለጸው በዓመት ሁለት ጊዜ እየተሰበሰቡ የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ አጀንዳ አድርገው እንዲወያዩ ሥርዓት ተሠርቷል፡፡ (ፍ/መ. ፭፥፻፷፭) ይህም ሥርዓት እስካሁን ቀጥሏል፡፡ የስብሰባውም ምክንያት
✍️ ሃይማኖትን ለማጽናት፣ ምግባርን ለማቅናት
✍️ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለማስፋት፣ ምእመናንን ለማብዛት
✍️ መናፍቃንን /ከሐድያንን ለመለየት፣ ሕግንና ሥርዓትን ለማውጣት ብሎም ለማስፈጸም
✍️ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ አንድነት ለማጽናትና ሁለንተናዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ መብቷን ለማስከበር አስተምህሮዋን ለማስፋት እና ለማስቀጥል የሚደረጉ ስብሰባዎች ሲኖዶስ እየተባሉ ይጠራሉ፡፡

ምክንያቱም ተሰብሳቢዎቹ ‹‹አደራ ጥብቅ ሰማይ ሩቅ›› እንዲሉ አበው አደራቸውን ለመወጣት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መጠበቅ፣ ለመንጋው መራራትና ለራሳቸው መጠንቀቅ የተሰጣቸው አደራ ነውና፡፡ (የሐዋ. ሥራ ፳፥፳፰) ዋጋቸውንም በሰማይ ይቀበሉ ዘንድ፡፡ አንድም መክሊታቸውን ቀብረው ክፉ አገልጋይ (ማቴ.፳፭፥፳፬) ተብለው እንዳይፈረድባቸው ተግተው በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ይሠራሉ፡፡

፩.፬. የቅዱስ ሲኖዶስ የክብሩ/የልዕልናውና መገለጫ፡-
ቅዱስ ሲኖዶስ ክብሩ ከፍ ያለ ነው፤ ልዕልናውም እጅግ ታላቅ ነው፤ ቅዱስም ነው፤ ቅድስናው፣ ልዕልናው ክብሩ እንዲሁ አይደለም፤ ምክንያቱም

ሀ. መሪው ሰብሳቢው መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ነው፡፡
ሲሰበሰቡና ሲወስኑ መንፈስ ቅዱስን መሪ ሰብሳቢ አጋዥ አድርገው ስለሆነ ነው፡፡ አርዮስን ለማውገዝ ሃይማኖት ለማጽናት በኒቅያ /የቤተ ክርስቲያን ታሪከ፣ ሃይማኖተ አበው/ የተሰበሰቡ ፫፻፲፰ ሊቃውንትም ጌታ አብሯቸው እንደሚሰበሰብ እንደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል፡፡

ለ. የሐዋርያት ወራሴ መንበር ስለሆነ
‹‹እናንተን የተቀበለ እኔን መቀበሉ ነው ያላቸው የሐዋርያት ተከታዮች ናቸው፤ ሊቃነ ጳጳሳት በክርስቲያኖች ላይ ያላቸው ሹመት ሙሴ በእስራኤል ላይ እንደነበረው ምስፍና ያለ ነው›› ተብሎ ተደንግጓል፡፡ (ፍ/መ/፬፣፶፬ እና ፶፭/

ሐ. ለቅድስና የሚያበቃ ሕግና ሥርዓት ስለሚወጣበት ነው፡፡
ሥጋዊ ያይደለ መንፈሳዊ፣ ምድራዊ ያይደለ ሰማያዊ ሥርዓት የሚሠራበትና ሕግ የሚደነገግበት ስለሆነ ነው፡፡

መ. በቅድስናቸው፣ በንጽሕናቸው ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠባቂነት የተመረጡ ስለሚሰበሰቡበት
ለቅድስና በምታበቃ ክህነት የተሾሙ፣ ሹመታቸው/መመረጣቸው ከሰው ሳይሆን ከእግዚአብሔር የሆነ፣ እኛና መንፈስ ቅዱስ ብለው የሚወስኑ፣ ጥብቅናቸው ለቤተ ክርስቲያን የሆኑ ብፁዓን አበው የሚሰበሰቡበት ስለሆነ ቅዱስ ነው፡፡

ሠ. ሃይማኖት እምነት የሚጸናበት ጉባኤ ስለሆነ
የሃይማኖት አንድነት የሚጸናበት፣ ክሕደት፣ ጥርጥር፣ የሚወገዱበት፣ አጋንንትና ውሉደ አጋንንት የሚገሠፁበት እና የቅዱሳን ቅድስና የሚነገርበት/የሚወሰንበት/ ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ቅዱስ ሲኖዶስ ስንል ቅድስናው የሚመነጨው ከሰው ሳይሆን ከራሱ ሁሉን ከሚቀድስ መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ክቡር፣ ቅዱስና ልዑል ነው፡፡

፩.፭. የልዕልናው መገለጫ የውሳኔዎቹ መፈጸም ነው፡፡
ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው ሲኖዶስ ክቡር ነው፤ ቅዱስ ነው፤ መሪውም መንፈስ ቅዱስ ነው፤ የክብሩ መገለጫ የልዕልናው መታያ መሆን ያለበት በመንፈስ ቅዱስ በብፁዓን አባቶች የተወሰነ ውሳኔ ሁሉ ሲከበር እና ሲተገበር ነው፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ለብዙ ሺህ ዓመታት ጸንታ የቆየችው ወርቃማውን ሥርዓቷን ጠብቃ ለትውልዱ ሁሉ ኩራት የጥበብ፣ የዕውቀት ሥጋዊ ወመንፈሳዊ ቤት፣ የመልካም ሰብእና ማእከል ሆና የዘለቀችው የማይናወጽ ሲኖዶሳዊ ሥርዓት በመጠበቁ በመከበሩ ውሳኔዋ በመፈጸሙ ነው፡፡ በርግጥ አንዳዶች በሊቃውንት ጉባኤ ስትመራ እንደኖረችናየሲኖዶሳዊ ታሪኳ ከ፶ ዓመት ያልዘለዘለ መሆኑን ይሞግታሉ፡፡ (አቡነ ሳሙኤል) ቢሆንም በሐዋርያት ሲኖደስ የምንተዳደር፣ ‹‹ማርቆስ አባታችን እስክንድርያ እናታችን›› ብለን የኖርን ሲኖዶስ አልነበረንም ማለት ተገቢ አይደለም፡፡ ስለሆነም፡-

✍️ የሕግና ሥርዓት ምንጭ፣ የቤተ ክርስቲያን ጠበቃና ዳኛ
✍️ የጾታ ምእመናን ባላደራ፣ የሐዋርያት ወራሴ መንበር የሆነ
✍️ የምሥጢራት ባለቤት፣ የክህነት መገኛ ወዘተ የሆነው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ቅዱስ ሲኖዶስ ክብሩ ልዕልናው ካልተከበረ ውሳኔው ካልተፈጸመ ህልውናው ጥያቄ ውስጥ ይገባል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቀርቶ ሀገርና ትውልድ አደጋ ላይ ይወድቃሉ፡፡ ምክንያቱም ሕግ ሁሉ ከሰው ከሆነ ሕገ ሰብእ መሆኑ ይቀርና ሕገ አራዊት ይሆናልና፡፡ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ መገለጫዋ መሪዋ የሕግ ሁሉ ምንጭ ሲኖዶሷ ነውና፡፡

ቸር ይግጠመን!

ይቆየን!
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ አብርሃም በትግራይ ክልል ለሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንትና ምዕመናን ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ የሰላምና የአንድነት ጥሪ አቀረቡ።
(EOTC TV//ኢኦተቤ ቴቪ / ሐምሌ ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም )
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግሮች በተለይም በትግራይ ክልል ባሉ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትና ሊቃውንት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን እና ከሕግ ውጭ በሆነ መልኩ " ኤጲስ ቆጶሳትን " እንሾማለን በማለት እየተደረገ ያለው ዝግጅት አስመልክቶ እንዲቆምና የውይይት መድረኮች ተመቻችተው ችግሮችን በሰላማዊና የቤተ ክርስቲያንን አንድነት በጠበቀ መልኩ ለመፍታት በቦታው ካሉ ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ለሊቃውንት ኦቶዶክሳውያንና ለሌሎች እምነት ተከታዮች እንዲሁም ለፌደራልና ለክልሉ መንግሥት የሰላምና የአንድነት ጥሪ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አቅርበዋል።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ አብርሃም መገለጫቸው ጉዳዮቹን ለማጥራትና ሁሉም አካል ወደልቡ እንዲመለስ ያለመ መሆኑን በመግለጽ መልእክታቸውን ማስተላለፍ የቀጠሉ ሲሆን በሰሜኑ ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት በሞቱ የተጎዱና ከቀያቸው በተፈናቀሉ በአጠቃላይ በደረሰው መከራና ሞት እጅግ ማዘናቸው ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ጉዳዮች እዚህ ከመድረሳቸው በፊት በሰዓቱ አባቶች ከግል ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ድረስ የተደረጉ ሰላማዊ ተግባራት እንደነበሩ አብራርተዋል።

ቤተ ክርስቲያን ጉዳዩን በትኩረት ከማየቷ በተጨማሪ "በችግሩ ወቅት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጊዜ የሀገር ሰላምን በተመለከተ በያዘው አጀንዳ በተወያያበት ሰዓት ከብፁዓን አባቶች የተወጣጣ የሰላም ኮሚቴ ተዋቅሮ ችግሩ እንዲፈታ የሰላም አየር እንዲነፍስ በሚባልበት ወቅትም በአሁኑ ሰዓት በትግራይ ክልል አህጉረ ስብከት ከሚገኙት ሊቃነ ጳጳሳት መካከል "እኛ ጋር ሰላም ነው ችግር ወዳለበት አካባቢ ሂዱ" የሚል ምላሽ እንደሰጡ ኦርቶዶክሳውያን ሊያውቁ ይገባል ብለዋል።
ከዚህ ይልቅ ችግር በችግር አይወገድምና እንደጥፋትም ከሆነ የጋራ እንጂ ራስን ንጹሕ አድርጎ ሌላውን እንደበደለኛ መቁጠር ተገቢነት እንደሌለው ገልጸዋል።
አያይዘው ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ሊቃውንት በጎጥ በጎሳ በቋንቋና በብሔር በሌላ ምድራዊ ሐሳብ ሳትከፋፈሉ ለሰማያዊ መንግሥት ዓላማ ያለውን መልካም ተግባር በማድረግ አደራችሁን እንዲወጡ በማለት አሳስበዋል።

ቀጥለው ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ባስተላላፉት መልእክት ትናንት እናት ቤተ ክርስቲያን የገጠማትን ከፍተኛ ችግር በእስከ መሥዋዕትነት በደረሰ ሁለንተናዊ ራስን መስጠት የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንደተወጣችሁ ሁሉ ዛሬም ቤተ ክርስቲያን አንድነቷን ጠብቃ ለመሄድ በምታደርገው የእውነት መንገድ ከምንም በላይ ክርስቶስ በገዛ ደሙ ፈሳሽነት ለመሠረታት ሐዋርያዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር በመሸነፍ ለአንድነቷና ለሰላሟ በጸሎት በሐሳብና በተግባር በተገለጠ ሕይወት እንዲቆሙ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ከዚሁ ጋር በልዩ ልዩ ሃይማኖት ላሉ ኢትዮጵያውያን በሙሉ መልዕክታቸውን የቀጠሉት ብፁዕነታቸው የቤተ ክርስቲያን አንድነት እንድትጠበቅ ከዚህ በፊት ያደረጋችሁትን መልካም አስተዋጽኦ ዛሬም ጥንታዊት እና ባለውለታ ቤተ ክርስቲያን አንድነቷና ሰላሟ ተጠብቆ እንዲቀጥል የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድትወጡ እንጠይቃለን በማለት መልእከታቸውን አድርሰዋል።
የኢፌዴሪ መንግሥት ትናንት ተፈጥሮ በነበረው የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ችግር በውይይትና በምክክር በከፍተኛ ኃላፊነት እንዲፈታ ማድረጉን ያስታወሱት ብፁዕነታቸው አሁንም በትግራይ ክልል ባሉ የአህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትና ሊቃውንት እየተከተሉት ያለውን መፍትሔ የማይሆነውን ችግር በማስቆምና ሰላማዊ የውይይት መድረኮችን በማመቻቸት የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ እምነታችን ነው ብለዋል።
ይህ ካልሆነ ግን ይላሉ ብፁዕነታቸው "በታሪክ የቤተ ክርስቲያንን አንድነትን ማን ከፋፈለ ሲባል የፌደራልና የክልሉ መንግሥት" የሚል የታሪክ ተወቃሽ ሆኖ በታሪክ የሚመዘገብ ይሆናል። ስለሆነም ይህን በትግራይ ክልል ይፈጸማል የሚለውን ከቀኖና ቤተ ክርስቲያንና ሕገወጥ የሆነ ሹመት እንዲቆም ብሎም ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ በማመቻቸት ታሪካዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ቤተ ክርስቲያን ታሳስባለች ብለዋል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ለትልቁ ጉልበትና ቅዱስ ትዕዛዝ "ለይቅርታ" ራሱን በማስገዛት መንጋው እንዳይበተን ይፋዊ ይቅርታ ከመጠየቅ አልፎ የቤተ ክርስቲያናችን ቅዱስ ሲኖዶስ ርዕሰ መንበር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመሩት የሰላም ልዑክ ወደ መቐለ አቅንቶ ችግርን በውይይትና በሰላማዊ መንገድ ተወቃቅሶ ለመፍታት ቢሞከርም አለመሳካቱ አስታውሰው ጉዳዩ እጅግ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል።

በመጨረሻም የባለውለታዋ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነት የሚያሳስበው ሰላሟ የሚናፍቀው ሁሉም አካል ከትልቁ ጉልበት ጸሎት ጀምሮ የሚቻለውን አበርክቶት እንዲወጣ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ አብርሃም አሳስበዋል።
EOTC TV
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
Audio
የኖኅ ዘመን

Size:-43.5MB
Length:-2:04:47

   በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
👉 ሴት በወር አበባዋ ጊዜ መጸለይ ትችላለች?
👉 ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን?
👉 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን?
👉 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን?
👉 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል?
👉 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው?
👉 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው?

ለእነዚህ ሁሉ መልስ ለማግኘት ይቀላቀሉ
Channel link
@tewahdo_haymanotea
#ትዕቢት የነበረንን መልካም ምግባር ሁሉ የሚያሳምም ደግሞም የሚገድል ክፋ ደዌ ነው፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
እግዚአብሔር ሰዎችን ኹሉ ሲፈጥራቸው በመንፈሳዊ ማንነታቸው እኩል አድርጎ ነው፡፡ እንዲህም ስለ ኾነ እያንዳንዱ ሰው በጎም ኾነ ክፉ ግብር ለመሥራት እኩል ዝንባሌ አለው፡፡ እግዚአብሔርን ለመታዘዝም ኾነ ላለመታዘዝ እኩል የመምረጥ ዕድል አለው፡፡ ከዚህ ውጪ በኾነ ነገር ግን ሰው ኹሉ እኩል አይደለም፡፡ አንዳንዱ እጅግ አስተዋይ ነው፤ ሌላው ደግሞ ደከም ያለ ነው፡፡ አንዳንዱ በሰውነቱ ብርቱና ጤናማ ነው፤ ሌላው ደግሞ ደካማና ሕመም የሚበዛበት ነው፡፡ አንዳንዱ ሰው መልከ መልካምና ማራኪ ነው፤ ሌላው ደግሞ አይደለም፡፡

ይህ ኹሉ ቢኾንም ግን በኾነ ነገር ስጦታው ያለው ሰው ስጦታው የሌለውን ሌላውን ሰው ሊንቀው አይገባም፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ለእያንዳንዳችን የተለያየ ስጦታን የሰጠን አንዳችን አንዳችንን እንድንጠቅም ነውና፡፡ እግዚአብሔር እያንዳንዳችን ከሌላው ወንድማችን የምንፈልገው ጥቅም እንዲኖር ያደረገው በመካከላችን መጠላላትና መለያየት እንዳይኖር ነው፤ እንድንፋቀርና አንድ እንድንኾን አስቦ ነውና፡፡

ስለዚህ ወዳጄ ሆይ! ወንድምህ ከአንተ ይልቅ አስተዋይና ዐዋቂ፥ ብርቱም ቢኾን በዚህ ቅር አይበልህ፡፡ ከዚህ ይልቅ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ከወንድምህ አስተዋይነትና ዐዋቂነት ብርታትም ትጠቀማለህና፡፡ በዚህ ብቻ ሳታቆምም ራስህን፡- “ስጦታዬ ምንድን ነው? ወንድሜን እኅቴን በምን ልጠቅም እችላለሁ?” ብለህ ጠይቅ፡፡ ይህን ጥያቄ በትክክል ስትመልስ፥ እንደ መለስከው ምላሽም ስትተገብር በአንድ መልኩ በሚበልጥህ ሰው ቅር መሰኘትህን፥ በሌላ መልኩ ደግሞ የምትበልጠውን ሌላውን ወንድምህን መናቅህን ታቆማለህ፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"የተሳሳተ እምነት ይዘን መልካም ሕይወት ብንኖር ምንም ጥቅም የለውም፡፡ ልክ እንደዛውም ቀጥተኛ ሃይማኖት ይዘን የኃጢአት ኑሮ ብንኖር ምንም ፋይዳ የለውም፡፡ እምነት ብቻ ለመዳን በቂ አይምሰለን ንጹሕ ሕይወትም አስፈላጊና ወሳኝ ነው፡፡"

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እንዲህ አሉ፦ ማንም ቢሰድብህ ስለ መሰደብህ ሳይሆን ስለ ሰደበህ ሰው አስብ። ያ ሰው ወንድምህ ነው። በፍቅር የተሞላህ መንፈሳዊ ሰው እንደመሆንህ መጠን አንተን በመስደብ ኃጢአት ላደረገው ወንድምህ ምን ልታደርግለት እንደምትችል ታስብ ዘንድ ይገባሃል። በእርግጥ አንተን የተሳደበበት ስድብ በድኅነቱ መግቢያ ላይ ቆሞ ይከለክለውና በዚሁ ሳቢያ ውድ ነፍሱ ወደ ሲዖል ትወርድ ዘንድ አትሻም። በመሆኑም ያንን ኃጢአት ቆጥሮ እንዳይቀጣው ይልቁንም ይቅር እንዲለው እግዚአብሔርን ትጠይቅለታለህ ከዚህ በተጨማሪም እግዚአብሔር አምላክ እንዲህ ካለው ኃጢአት እንዲያወጣውና ዳግመኛ አንተን ሆነ ሌሎችን በመስደብ እንዳይበድል ልትጸልይለት ይገባል።

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"ስለታሙ የሐሜት ጥርስህ የሚያርፈው በወንድምህ ሥጋ ላይ ሳይሆን ነፍስ ላይ ነው፡፡.በዚህም ጥርስህ ወንድምህን በእጅጉ ትጎዳዋለህ፡፡ እንዲህ በማድረግህ አንተም እርሱንም ሌሎችንም ብዙ ሺህ ጊዜ ትጎዳቸዋለህ፡፡ በሐሜትህ አንተን የሚሰማህ ባልንጀራህ የሐሜት ተባባሪ ይሆናል፡፡ በዚህም ምክንያት እርሱንም በደለኛ ታደርገዋለህ፡፡ እርሱም በእርሱ ላይ ከነገሠበት ኃጢአት የተነሣ ለሌላ ለወዳጁ ምን መርጦ ማውራት እንዳለበት ሳያውቅ ከሐሜተኞች ጎራ ይቀላቀላል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰው ጻድቅ ልንለው እንችላለንን? እንዲህ ዓይነት ሰው በመጦሙ ትልቅ የጽድቅ ሥራን እንደፈጸመ ቆጥሮ ይኩራራል፡፡ ሰዎችን ወደ ኃጢአት እየመራ ትልቅ ሥራን እንደሠራ ሰው ራሱን በከንቱ ያስኮፍሳል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ሊታይ የሚገባው ትልቁ ቁም ነገር ስለቤተክርስቲያን ጥቅም ሲባል የእንዲህ ዓይነቱን ሰው ንግግር ከመስማት መከልከል እንደሚገባ ነው፡፡ ምክንያቱም የዚህ ሐሜተኛ ወሬ እርሱን ብቻ ኃጢአተኛ የሚያሰኝ ጉዳይ ሳይሆን ቤተክርስቲያንንም ጭምር የሚያሰድብ ነውና፡፡

ስለዚህ በጦም ሰዓታችሁ ጊዜም ይሁን አይሁን ሦስት ነገሮችን በሕሊናችሁ ትይዙ ዘንድ እመክራችኋለሁ፡-
እነርሱም....
✟ ክፉ ከመናገር መከልከልን፣
✟ ማንንም ሰው እንደጠላት ከማየት መቆጠብንና
✟ እንደልምድ አድርጋችሁ ከያዛችሁት መሐላ ትርቁ ዘንድ እመክራቸኋለሁ፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
«ወዳጄ ሆይ! እግዚአብሔር ነዳያንን የሚልክልህ መስጠትን እንድትለማመድ ነው፡፡ ዛሬ በነዳያኑ አድሮ የሚለምንህ ለኋለኛይቱ ቀን ስንቅ እንዲያስቀምጥልህ ወድዶ ነው፡፡ ታድያ ንጉሥ ወደ ቤቱ መጥቶ የሚያባርር ሰው እንደምን ያለ ጎስቋላ ሰው ነው? እንግዲያውስ ነዳያንን ስታይ ወደ አንተ የመጣው ንጉሠ ሰማይ ወምድር ክርስቶስ እንጂ ሰው አይደለምና አትግፋው፡፡ በረከትህንም ከቤትህ አውጥተህ አትሸኘው፡፡»

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
“እኔ ክርስቲያን ነኝ፡፡ ለሚጠይቁት እንደዚህ ብሎ የሚመልስ ሰው በአንድ ጊዜ በኹሉም ነገሮቹ ላይ ማወጁ ነው፡፡ ሀገሩ የት እንደ ኾነ፣ ሥራው ምን እንደ ኾነ፣ ቤተሰቡ እነማን እንደ ኾኑ መመስከሩ ነው፡፡ ክርስቲያን የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ነዋሪ እንጂ በምድር ላይ ካሉት ከተሞች የአንዲቱም አይደለምና፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
Audio
እግዚአብሔር በመጨረሻ ይመጣል

Size:-26MB
Length:-1:14:41

   በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
የአራቱ ኪሩቤልን ስም ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ይላቸዋል
፩) ባራማራ
፪) እግረማጣ
፫) ሱርትዮን
፬) መሊጦን
ይላቸዋል። ሃይማኖተ አበው ላይ ስለዚህ ኪሩቤል ሲናገር መናብርት ነባብያን ይላቸዋል። የሚናገሩ መናብርት ይላቸዋል። ከሱራፌል ነገድና ከኪሩቤል ነገድ ሁለት ሁለት ተመርጠው በጠቅላላው አራት ኪሩቤል አሉ። እንደገና በኢዮር ከሚገኙት አርባ ነገዶች አሥሩ ነገድ ኪሩቤል ይባላል።

ሰአሉ ለነ ኀበ እግዚአብሔር ጸባዖት___ቅ. ያሬድ
(ኪሩቤል ሆይ ወደአሸናፊ እግዚአብሔር ለምኑልን)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
የ፸፪ቱ አርድእት ስም (ምንጭ:-መጽሐፈ ግንዘት)
#፲፪ቱ ሐዋርያት #፬ቱ ወንጌላውያንና ስያሜያቸው
፩) እስጢፋኖስ
፪) ጢሞቴዎስ
፫) ሲላስ
፬) በርናባስ
፭) ቲቶ
፮) ፊልሞና
፯) ቀሌምንጦስ
፰) ዘኬዎስ
፱) ቆርኔሌዎስ
፲) ቴዎፍሎስ
፲፩) ኤውዴዎስ
፲፪) አግናጥዮስ
፲፫) ጳውሎስ
፲፬) አርንያኖስ
፲፭) ማልኮስ
፲፮) ኤሌኖስ
፲፯) አርሳጢስ
፲፰) አስትራትዮስ
፲፱) አርስጦስ
፳) ጋይዮስ
፳፩) አድማጥስ
፳፪) ሉኪዮስ
፳፫) ዲዮናስዮስ
፳፬) መርአንዮስ
፳፭) አርክቦንዮስ
፳፮) አናሲሞስ
፳፯) ከርሳጊስ
፳፰) አኪላስ
፳፱) ሉቃስ
፴) ዮሴፍ
፴፩) ኒቆዲሞስ
፴፪) ያዕቆብ እኁሁ ለእግዚእነ
፴፫) ብርኮሮስ
፴፬) ንኪትስ
፴፭) ቀርስጶስ
፴፮) ክርስቶፎሮስ
፴፯) ፊልጶስ
፴፰) ጰርኮሮስ
፴፱) ኒቃሮና
፵) ጢሞና
፵፩) ጰርሚና
፵፪) ኒቆላዎስ
፵፫) ማርቆስ
፵፬) ሮፎስ
፵፭) እለእስክንድሮስ
፵፮) አንሞስ
፵፯) ስልዋኖስ
፵፰) ሰንቲኖስ
፵፱) ኢዮስጦስ
፶) አክዩቁ
፶፩) አፍሮዲጡ
፶፪) ገማልኤል
፶፫) እንድራኒቆስ
፶፬) አናንያ
፶፭) ጵርስቅላ
፶፮) አቂላ
፶፯) ኤጴንጤስ
፶፰) ዩልያል
፶፱) ጰልያጦስ
፷) መርማራያን
፷፩) ኬፋ
፷፪) ዑርባኖስ
፷፫) ሰጠክን
፷፬) አጤሌን
፷፭) አክሌምንጦስ
፷፮) ሄሮድያኖስ
፷፯) ጥርፌና
፷፰) ጠሪፌስ
፷፱) አስከሪጦስ
፸) ሉቅዮስ
፸፩) ሱሲ
፸፪) ጴጥሮስ
ናቸው። ቅዱስ ጳውሎስ ፲፬ቱን መልእክታት የጻፈው ከ፸፪ቱ አርድእት ውስጥ አይደለም። ከዚህ የተጠቀሰው ሌላ ጳውሎስ ሊሆን ይችላል። ሌሎችም በኋላ የተነሡ ስም ቢኖር ሞክሼ ሊሆን ስለሚችል በደንብ ማየቱ የተሻለ ነው።
#፲፪ቱ #ሐዋርያትና የሚከበሩበት ቀን
፩) መስከረም ፩_በርተሎሜዎስ
፪) ጥቅምት ፲፪_ማቴዎስ
፫) ህዳር ፳/፲፯____ፊልጶስ
፬) ታኅሣሥ ፬_እንድርያስ
፭) ጥር ፬___ዮሐንስ
፮) የካቲት ፲_ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ
፯) መጋቢት ፲____ማትያስ
፰) ሚያዝያ ፲፯____ያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
፱) ግንቦት ፳፯_ቶማስ
፲) ሐምሌ ፪___ታዴዎስ
፲፩) ሐምሌ ፭_ጴጥሮስ
፲፪) ሐምሌ ፲_ናትናኤል
አራቱ ወንጌላውያን ከነምሳሌያቸው ደግሞ እንደሚከተለው ቀርበዋል።
#ወንጌላውያን
፩) ዘብእሲ ማቴዎስ__ጌታ ከዳዊት ዘር መወለዱን ስለሚገልጽ ዘብእሲ ተባለ።

፪) ዘአንበሳ ማርቆስ__አንበሳ ላምን ሰባብሮ እንደሚበባ ማርቆስም በግብጽ አውራጃዎች ያሉ ጣዖታትን አስተምሮ አጥፍቷልና ዘአንበሳ አለ።

፫) ዘላሕም ሉቃስ__ለጠፋው ልጅ ፍሪዳ መታረዱን አውስቶ ይጽፋልና ዘላሕም አለው።

፬) ዘንስር ዮሐንስ__ንስር ከፍ ብሎ እንደሚበር ዮሐንስም ከፍ ብሎ ምሥጢረ መለኮትን ይናገራልና ዘንስር አለው።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
#የቀበሮ #ፍርድ
ክቡር ዶክተር ከበደ ሚካኤል በአንድ መጽሐፋቸው በግጥም መልኩ ያስቀመጡት ድንቅ ነገር አለ። ይኽውም በአንድ ወቅት በእንስሳት እና በአራዊት ዓለም ታላቅ መከራ ይደርሳል። እና አራዊቱ እንስሳቱ ይሰበሰቡና ይህ ሁሉ የሆነው በኃጢአታችን ምክንያት ስለሆነ ንስሓ እንግባና ፈጣሪ ምሕረቱን ያውርድልን ይባባላሉ። ከዚያ ሁሉም መናዘዝ ይጀምራሉ። አንበሳ ሲናዘዝ "አንድ ወጣት ልጅ ላም እየነዳ ሳለ አንድ ቀን ላሚቱንም ሰውየውንም በልቻቸዋለሁ" ይላል። ይህን ጊዜ ቀበሮ የተከበሩ አንበሳ ያ ልጅ በእርስዎ በመባላቱ እንዲያውም እድለኛ ነው። እርስዎ ያጠፉት ምንም ዓይነት ጥፋት የለም ብላ ትናገራለች። እንዲህ እንዲህ እያሉ ሁሉም ከተናዘዙ በኋላ መጨረሻ ላይ አህያ መናዘዝ ጀመረች። እኔ አንድ ቀን ጌታዬ ጭኖኝ ወደ ገበያ ስሔድ ባለቤቱ ሳያየኝ ከሰው ማሳ አንድ ጉራሽ የሚሆን ሣር በልቻለሁ ትላለች። ይህን ጊዜ ቀበሮ አህያን "አንች አመዳም ለካ ይህ ሁሉ ግፍ የደረሰብን በአንቺ ምክንያት ነው" አለቻትና ሁሉም ተረባርበው በሏት ይላሉ።

ቀበሮዎች ፍርዳቸው እንዲህ ነው። በገንዘብ በጉልበት በሥልጣን ከእነርሱ የሚበልጥ ሰው ከመጣ ቢሳሳትም እንደ ጽድቅ ይቆጥሩለታል። የሰው ልጅ አእምሮ እስካለው ድረስ ውንብድናን በእኩልነት መቃወም አለበት። አድሏዊነት የትንንሽ ሰዎች ሥራ ነው። የሁላችንም መመሪያ እውነት ነው መሆን ያለበት። እውነት ደግሞ እግዚአብሔር ነው። አንዳንዶችን ዘረኝነት አውሯቸው የእነርሱ ዘር የመሰላቸው ሲያጠፋ ዝም ይላሉ። የሌላ ነው ብለው ያሰቡት ሲያጠፋ የእውነት ሰዎች መስለው ዓይናቸውን በጨው አጥበው ይመጣሉ። [እትየ ስመኝ ለማያውቁሽ ታጠኝ]

መፍትሔ የሌለው ችግር የለም። መፍትሔውን ለማምጣት ግን በችግሩ ዙሪያ ያለን እይታ ተቀራራቢ መሆን አለበት። የቤተክርስቲያን ራስ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በእርሱ ሕግ ከተመራን በቀላሉ ችግሮችን መፍታት እንችላለን። ከቀበሮ ፍርድ መውጣት ይገባል። እውነት፣ ቀኖና፣ ዶግማ፣ አስተምህሮ እንዲዳኙ እድል ይሰጣቸው።
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"እንዲህ [ጳጳስ] ሆነህ ከማይህ ተገንዘህ ወደ መቃብር ሲያወርዱህ ባይ እወዳለሁ" እናት የምትወደው ልጇን
===+===+++======++++===+====+===

መቃርዮስ (ሃይ.አበ.98) ሊቀጳጳሳት ዘእስክንድርያ፡፡ብሉይ ሐዲስ ሲማር አደገ ከእርሱ አስቀድሞ የነበረው ሊቀጳጳስ አረፈ፡፡ከዚያ እርሱ ተሾመ በተሾመ ጊዜ ተሾምሁ የምስራች ብሎ ለእናቱ ላከ፡፡

ለመልእክተኞች የማትመልስላቸው ሆነች፡፡የእናቴ ነገር እኔን እንጂ ካልመጣ ብላ ነው ብሎ ልብሰ መዓርጉን ለብሶ ማኅበሩን አስከትሎ ሄደ፡፡ መጣ ብለው ነገሯት ከቤት የማትወጣ ሆነ፡፡

ከዚያ ልጅሽኮ ነኝ አላወቅሽኝም አላት። "አንተ አላወቅህም እንጂ እኔስ አውቄሀለሁ እንዲህ ሁነህ ከማይህ ተገንዘህ ወደ መቃብር ሲያወርዱህ ባይ እወዳለሁ" አለችው። "ከዚህ አስቀድሞ በራስህ ኃጢአት ይፈረድብህ ነበር ከእንግዲህ ወዲህ ግን በሕዝቡ ኃጢአትም ይፈረድብሀል" አለቸው፡፡

እርሱም ይህ ተግሳጽ ሁኖት እስከጊዜ ሞቱ ከማስተማር ሳያርፍ ኖሯል፡፡ [የአሁን መነኮሳት ደግሞ ጵጵስና ሳንሾም ከምንቀር ተገንዘን ብንቀበር ይሻላል የሚሉ ይመስላል።

ምንጭ፦ ሃይማኖተ አበው አንድምታ ትርጓሜ

© በትረማርያም አበባው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
👉 ሴት በወር አበባዋ ጊዜ መጸለይ ትችላለች?
👉​​ ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን?
👉 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን?
👉 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን?
👉 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል?
👉 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው?
👉 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው?

ለእነዚህ ሁሉ መልስ ለማግኘት ይቀላቀሉ
Channel link
@tewahdo_haymanotea
#ተስዓቱ #ቅዱሳን
፩) አባ አረጋዊ
፪) አባ ሊቃኖስ
፫) አባ ይምአታ
፬) አባ ጽሕማ
፭) አባ ጉባ
፮) አባ አፍጼ
፯) አባ ጰንጠሌዎን
፰) አባ አሌፍ
፱) አባ ገሪማ (አባ ይስሐቅ?)

በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ዘረኝነት በጣም የተጠላ ተግባር ነው። ስለሆነም ጻድቃንን የትም ይወለዱ በየትኛውም ዘመን ይነሡ በእኩልነት እንወዳቸዋለን። ተስዓቱ ቅዱሳን ከውጭ ሀገር መጥተው ለኢትዮጵያ ቅድስት ቤተክርስቲያን ትልቅ ውለታ የዋሉላት አባቶቻችን ናቸው።

© በትረማርያም አበባው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
2024/09/24 22:31:38
Back to Top
HTML Embed Code: