Telegram Web Link
Audio
የሕይወት ውሃ
        
Size:-32.3MB
Length:-1:32:43

"በቅድስት ሃገር ኢየሩሳሌም የተሰጠ ትምህርት"
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#በመዲናችን_በአዲስ_አበባ__የቅዱስ_ገብርኤል_ በዓል_የሚከበሩባቸው  #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩) ፠ (መ.መ.ገ.) መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤
፠ አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤
፠ ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤
፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል)
፭) ፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል
፠ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ.
፠ ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት አርሴማና አቡነ አዳም ቤ.ክ.
፲) ፠ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፭) ፠ ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፠ አቃቂ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ሃራብሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፭) ፠ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ)
፠ ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ቦሌ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ገሊላ አማኑኤል ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፴) ፠ ጀሞ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ.ክ.
፠ አቃቂ ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ የካ አባዶ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል
፴፭) ፠ ኮልፌ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. (አዲሱ ሚካኤል) (በድርብነት ይከብራል)
፠ ካራ ቆሬ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም (በድርብነት ይከብራል)
፠ አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ (አዲስ ሰፈር)
፵)፠ ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም ስር የሚገኘው ሙት አንሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መንበረ ልዑል ገብርኤልና ማርያም ቤ.ክ.፤
፠ አየርጤና ደብረ ብሥራት ገብርኤልና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.
፠ ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቀበና ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ.
፵፭) ፠ መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ.
፠ ቂሊንጦ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ማርያም፤
፠ ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)፡፡
፠ አንቀጸ ምሕረት (ራስ ካሣ) ቅዱስ ሚካኤል፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፶) ፠ ቦሌ ቡልቡላ ድብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፶፬) ፠ ብሥራተ ወንጌል ቅድስተ ማርያም ቤ.ክ.፤ (በድርብነት ይከብራል)
#በሃገራችንና_በዓለም_አቀፍ__በዓላቸው_የሚከበሩባቸው_ጥንታውያን  #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩) ዘብር ቅዱስ ገብርኤል (መንዝ ሰ ሸዋ)
፪) ወይቅን ቅዱስ ገብርኤል (ቆላ ተንቤን)
፫) ክብራን ገብርኤል (ጣና ጎጃም)
፬) ቦሎ ገብርኤል (መርሐ ቤቴ)
፭) ጎንደር አቡን ቤት ገብርኤል
፭) ደሴ ገብርኤል
፮) ናዝሬት ገብርኤል
፯) ቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል
፰) ባሕር ዳር ዐባይ ማዶ ገብርኤል
፱) ሐዋሳ ገብርኤል
፲) ድሬደዋ ሳባ ገብርኤል
  
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የማጽናኛ መልእክት አስተላለፉ።

“ምንም እንኳ የመከራ ድሀ ባንሆንም ይህ መከራ ለነጋሪውም ለሰሚውም ከባድ መሆኑን እንገነዘባለን ። “

++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

“እግዚኦ ሚ በዝኁ እለ ይሣቅዩኒ፦አቤቱ፥ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ ! ”
(መዝ. 3፡1)

         አባታዊ የማጽናኛ መልእክት

          በጎፋ ዞን፣ በገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት ናዳ እጅግ ብዙ የሚሆኑ ወገኖቻችን በመሞታቸው ታላቅ ኀዘን ተሰምቶናል ። ምንም እንኳ የመከራ ድሀ ባንሆንም ይህ መከራ ለነጋሪውም ለሰሚውም ከባድ መሆኑን እንገነዘባለን ።

ይሁን እንጂ ጭንቀታችን ብዙ ቢሆንም እግዚአብሔር መልካም የምንሰማበትን ዘመን እንደሚያመጣ ተስፋ እናደርጋለን ።

በተለይም ደግሞ እኛ ክርስቲያኖች በወገኖቻችን መጎዳት ብናዝንም በትንሣኤ ሙታን ስለምናምን የምጽናና   በመሆኑ የሞቱት ልጆቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲያገኙ እየጸለይን፤ የመከራው ገፈት ቀማሽ ለሆኑት የአካባቢው ማኅበረሰብእ ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ ሁሉም አቅሙ በፈቀደው መጠን እንዲደርስላቸው ስንል አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ  ለቤተሰቦቻቸውና ለሕዝቡ መጽናናትን ይስጥልን፤ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
አሜን።

          አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

  ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም.                                               ዋሽንግተን ዲሲ~  አሜሪካ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
#በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፳፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
(ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን)
ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#በአዲስ_አበባ_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፲፫) #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ፤
አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ካዛንቺስ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ካዛንቺስ፡፡
፪. ኤረር በር ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ዑራኤል፡፡
አድራሻው፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ኤረር በር፤
ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ→ ኤረር በር፤
፫. አዲስ ሰፈር አንፎ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል፣ መጥምቁ ዮሐንስና ልደታ ለማርያም፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አንፎ፡፡
፬. ፉሪ ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ፉሪ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ፉሪ፡፡
፭. ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም መካነ ብርሃን ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ
አድራሻ፤ ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጎፋ ካምፕ →  ጎፋ መብራት ሀይል ኮንዶሚኒየም

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#እንዲሁም_በድርብነት_
፮. ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቶታል/ድል በር/ (ጎጃም በር)፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → አዲሱ ገበያ → ቶታል፡፡
፯. አስኮ ደብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለምና ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንየ ክፍለ ከተማ፥ አዲስ ሰፈር፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ /ከአቡነ ጴጥሮስ/ → አስኮ፡፡
፰. አውግስታ ደብረ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ፡፡
፱. ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ታቦት ማደርያ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ኮልፌ → ታቦት ማደርያ፡፡
፲.  ቱሉ አቦ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤ ቅዱስ ዑራኤልና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፤
አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቱሉ አቦ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → አቃቂ → ቱሉ አቦ፡፡
፲፩. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚከኤል፤
አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡
፲፪. ላፍቶ ኢያሪኮ መድኀኔ ዓለምና መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ → ላፍቶ፡፡
፲፫.  ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፡፡
ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ፡፡

ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፮ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩ መንዝ ዕመጓ ደብረ ቆጵሮስ ኢየሱስ ቅዱስ ዑርኤል ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መንዝ፡፡
፪. ግሸን ቅዱስ ዑርኤል፤
አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ግሸን ደብረ ከርቤ፤
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ግሸን፡፡
፫. ጎንደር ደብረ ኀይል ቅዱስ ዑርኤል ወበዓታ፤
አድራሻ፤ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥  ጎንደር ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡
፬. ደብረ ታቦር አንቀፀ አድህኖ ቅዱስ ዑርኤል፤
አድራሻ፤ ደ. ጎንደር ሃገረ ስብከት፥  ደብረ ታቦር ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡
፭. የወልዲያ ቅዱስ ዑርኤል ፤
አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥  ወልዲያ  ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ወልዲያ ፡፡
፮.  ደብረ ብርሃን ደብረ ገነት ቅዱስ ዑርኤል ፤
አድራሻ፤ ሰ. ሸዋ ሃገረ ስብከት፥  ደብረ ብርሃን  ከተማ
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አስኮ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን፡፡


ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ
#ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከበርባቸው_ #፫ #ገጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ጀርመን ደብረ ኃይል ቅዱስ ዑርኤል ወቅዱስ ያሬድ፤
አድራሻ፤ ጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት
፪. ደብረ ብርሃን ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አሜሪካ ሜንሶታ
፫. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑርኤል ቤ/ክ፤
አድራሻ፤ አሜሪካ ሎሳንጀለስ ካሊፎርኒያ

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
የኦሎምፒክ መክፈቻ ስነ ሥርዓት ላይ የቀረበው የረከሰ ድርጊት ሲታይ በተቀደሰው ምሥጢረ ቊርባን ላይ የተፈጸመ የድፍረት ኃጢአት ነው

ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

በ2024 የዓለም ኦሎምፒክ ስፓርታዊ ውድድር መክፈቻ ሥነሥርዓት ላይ የተካሄደውን አስነዋሪ ትዕይንት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ  መግለጫ ተሰጥቷል።

ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል።

“ይእዜ ኀሥረ ክብሮሙ ወተኀፍረ ገጾሙ ወተቃወመቶሙ ኀጢአቶሙ ከመ ኀጢአተ ሰዶም ወገሞራ አስተርአየት ወተዐውቀት ላዕሌሆሙ፤ አሌ ላ ለነፍሶሙ እስመ መከሩ እኩየ ምክረ ላዕለ ነፍሶሙ፡- ዛሬ ክብራቸው ተዋረደ፣ የፊታቸውም ዕፍረት ይመሰክርባቸዋል ኀጢአታቸው እንደ ሰዶምና እንደ ገሞራ ኀጢአት ተቃወመቻቸው በላያቸውም ተገልጣ ታወቀች፡፡ ክፉ ምክርንም መክረዋልና ለነፍሳቸው ወዮላት፡፡
ኢሳ.3 ፥ 9”

የ2024 የዓለም ኦሎምፒክ ስፓርታዊ ውድድርን በማስመልከት ባለፈው ዓርብ በአውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር July 26 በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት በተካሄደበት ወቅት በመላው ክርስቲያኖች ዘንድ ከፍተኛ ክብር የሚሠጠውን ምስጢረ ቊርባንን ያቀለለ፣ የተመሳስይ ጾታ ጋብቻን፣  የግብረ ሰዶማውያንን እኩይ ተግባር በወገንተኛነት የተደገፈ ትርኢት ማሳየታቸውን በዓለም ዜና ማሰራጫ ተመልክተናል።

በየዐራት ዓመቱ በሚከናወነው የዓለም ኦሎምፒክ ስፖርታዊ ውድድር የመክፈቻ ሥነሥርዓት ላይ የቀረበው የረከሰ ድርጊት ሲታይ በተቀደሰው ምሥጢረ ቊርባን ላይ የተፈጸመ የድፍረት ኃጢአት ነው፡፡

በተጨማሪም የሃይማኖትን ነጻነት የሚጋፋ፣ ጾታ የሚለውጡ ሰዎችን የሚያበረታታና በአጠቃላይ በክርስትና ሃይማኖትና በክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ቀጥተኛ ጥቃት ስለሆነና ከሰለጠነው ዓለም የማይጠበቅ፣ የሌሎችን የእምነት የባህልና የማኅበራዊ ዕሴት ማክበር ልዩ ቦታ በሚሰጠው የኦሎምፒክ ስፖርታዊ ጨዋነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር፣ በቅዱሳት መጻሕፍት፣ በሰው ልጅ ሰብዓዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው፡፡

በመሆኑም አንዱ የሌላውን የእምነትና የአምልኮ ነጻነት በማክበር እንዲኖር በሃይማኖት ቀኖናት ብቻ ሳይሆን በዓለማችን ላይ ባሉት ሀገራት የሰብአዊ መብትና የእምነት ሕግጋት የተደነገገ ሆኖ ሳለ ከኦሎምፒክ ስፖርት ጋር በማይገናኝ ሁኔታ በውድድሩ መክፈቻ ትዕይንት የተፈጸመው አስነዋሪ ተግባር ሃይማኖታችንን የሚጋፋ፣ መንፈሳዊ እሴቶቻችንን የሚያጠፋ ክብረ ነክና ሊወገዝ የሚገባው ሰይጣናዊ ድርጊት በመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጽኑ አውግዞታል፡፡

የዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ ኮሚቴና ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላትም ይህንን በመላው ክርስቲያኖች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ የቀሰቀሰውን ጸረ-ሃይማኖት የሆነ አስነዋሪ ድርጊት በመኮነን የአምኮልን መብትና ነጻነት እንዲያስከብሩ፣ ድርጊቱን በግልጽ እንዲቃወሙ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

                ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም.
                    አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

Statement from the Permanent Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
Regarding the scandalous scene 
at the opening ceremony of the 2024 World Olympic Games

The shew of their countenance doth witness against them; and they declare their sin as Sodom, they hide it not. Woe unto their soul! For they have rewarded evil unto themselves.  (Isa. 3:9)
In the opening ceremony of the 2024 World Olympic Games, that took place on Friday, July 26 2024 in in the city of Paris, France, we saw a scandalous scene that degrades the sacrament of Holy Communion, which is highly respected by all Christians and promotes same-sex marriage, homosexual activities and anti-Christian cults.
The act of showing such scene is a blasphemous sin against the sacrament of Holy Communion; it violates religious freedom and encourages transsexuals. In general, the scene is a direct attack on the Christian religion and Christians. Such act is unacceptable both in human life style and Christian scriptures.
The shown disgraceful act is forbidden and condemned not only by religious canons but also by the laws of the various countries in the world. The disgraceful act that was openly broadcasted on the world stage is a satanic act that should be condemned. Therefore, the Permanent Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church strongly condemns and sends a spiritual call to all affiliated bodies to condemn the disgraceful act that has aroused great anger among the Christian religion and all Christians, to respect the rights and freedom of worship, and to openly oppose the act.

July 29, 2024
Addis Ababa, Ethiopia
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
2024/09/21 09:48:44
Back to Top
HTML Embed Code: