Telegram Web Link
አንደበቱ ተከፈተ ||የሰው ተከታይ አትሁኑ
        
Size:-22.6MB
Length:-1:04:53

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
የድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከአጥቢያ የተወጣጡ 16 አባላትን የያዘ የተተኪ መምህራን ቡድን ለ አንድ ወር ለሚቆይ የስልጠና ጊዜ አዲስ አበባ (ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ)ላከ

ሀምሌ 07/2016 ዓ.ም የድሬደዋ ሰ/ት/ ቤቶች አንድነት

በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርትቤቶች ማደራጃ መምሪያ በሀገር ዓቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነትበየዓመቱ የሚዘጋጀው የተተኪ መምህራን ስልጠና በዘንድሮውም ዓመት ከ16 በላይ ከሚሆኑ አህጉረ ስብከቶች ለተወጣጡ በቁጥር 213 የሚደርሱ ተተኪ መምህራን ስልጠና አዘጋጀ ።
በስልጠናውም ሀገረ ስብከታችንን ወክለው ለመሳተፍ ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች የተወጣጡ አስራ ስድስት የሚሆኑ አባላት በዛሬው እለት በስልጠናው ለመሳተፍ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የገቡ ሲሆን በሚኖራቸውም የአንድ ወር ቆይታ :- .በክህሎታዊ ዘርፍ
.በአስተዳደር ዘርፍ
.በእውቀታዊ ዘርፍ እና
.በመሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ዙሪያ

በአራት የተለያዩ ዘርፎች ስልጠናዎች እንደሚወስዱ እና የሚሰጣቸውንም ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው ውጤት ላመጡ መምህራንም እውቅናን እንደሚያገኙ ለዛም ባላቸው አጭር ጊዜ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው በማንሳት ከስልጠናው በኋላም በሚያገኙት ዕውቀት እና ልምድ የመጡበትን ሀገረ ስብከት ብሎም ሰ/ት/ቤታቸውን በስርዓተ ትምህርት ትግበራ በሚገባ ማገልገል እንደሚገባቸው በሀገር ዓቀፉ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት የስርአተ ትምህርት ዘርፍ አስተባባሪ የሆኑት ዲ/ን ሚኪያስ ግዛቸው አያይዘው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ምንጭ የድሬደዋ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት ነው
Audio
"ጌታችን በመርከብ ውስጥ ሕዝቡ በሐይቅ ውስጥ"

Size:-22.7MB
Length:-1:39:03

💠ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን 💠

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Audio
የሕይወት ውሃ
        
Size:-32.3MB
Length:-1:32:43

"በቅድስት ሃገር ኢየሩሳሌም የተሰጠ ትምህርት"
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#በመዲናችን_በአዲስ_አበባ__የቅዱስ_ገብርኤል_ በዓል_የሚከበሩባቸው  #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩) ፠ (መ.መ.ገ.) መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤
፠ አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤
፠ ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤
፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል)
፭) ፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል
፠ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ.
፠ ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት አርሴማና አቡነ አዳም ቤ.ክ.
፲) ፠ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፭) ፠ ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፠ አቃቂ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ሃራብሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፭) ፠ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ)
፠ ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ቦሌ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ገሊላ አማኑኤል ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፴) ፠ ጀሞ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ.ክ.
፠ አቃቂ ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ የካ አባዶ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል
፴፭) ፠ ኮልፌ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. (አዲሱ ሚካኤል) (በድርብነት ይከብራል)
፠ ካራ ቆሬ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም (በድርብነት ይከብራል)
፠ አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ (አዲስ ሰፈር)
፵)፠ ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም ስር የሚገኘው ሙት አንሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መንበረ ልዑል ገብርኤልና ማርያም ቤ.ክ.፤
፠ አየርጤና ደብረ ብሥራት ገብርኤልና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.
፠ ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቀበና ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ.
፵፭) ፠ መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ.
፠ ቂሊንጦ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ማርያም፤
፠ ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)፡፡
፠ አንቀጸ ምሕረት (ራስ ካሣ) ቅዱስ ሚካኤል፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፶) ፠ ቦሌ ቡልቡላ ድብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፶፬) ፠ ብሥራተ ወንጌል ቅድስተ ማርያም ቤ.ክ.፤ (በድርብነት ይከብራል)
#በሃገራችንና_በዓለም_አቀፍ__በዓላቸው_የሚከበሩባቸው_ጥንታውያን  #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩) ዘብር ቅዱስ ገብርኤል (መንዝ ሰ ሸዋ)
፪) ወይቅን ቅዱስ ገብርኤል (ቆላ ተንቤን)
፫) ክብራን ገብርኤል (ጣና ጎጃም)
፬) ቦሎ ገብርኤል (መርሐ ቤቴ)
፭) ጎንደር አቡን ቤት ገብርኤል
፭) ደሴ ገብርኤል
፮) ናዝሬት ገብርኤል
፯) ቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል
፰) ባሕር ዳር ዐባይ ማዶ ገብርኤል
፱) ሐዋሳ ገብርኤል
፲) ድሬደዋ ሳባ ገብርኤል
  
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የማጽናኛ መልእክት አስተላለፉ።

“ምንም እንኳ የመከራ ድሀ ባንሆንም ይህ መከራ ለነጋሪውም ለሰሚውም ከባድ መሆኑን እንገነዘባለን ። “

++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !

“እግዚኦ ሚ በዝኁ እለ ይሣቅዩኒ፦አቤቱ፥ የሚያስጨንቁኝ ምንኛ በዙ ! ”
(መዝ. 3፡1)

         አባታዊ የማጽናኛ መልእክት

          በጎፋ ዞን፣ በገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት ናዳ እጅግ ብዙ የሚሆኑ ወገኖቻችን በመሞታቸው ታላቅ ኀዘን ተሰምቶናል ። ምንም እንኳ የመከራ ድሀ ባንሆንም ይህ መከራ ለነጋሪውም ለሰሚውም ከባድ መሆኑን እንገነዘባለን ።

ይሁን እንጂ ጭንቀታችን ብዙ ቢሆንም እግዚአብሔር መልካም የምንሰማበትን ዘመን እንደሚያመጣ ተስፋ እናደርጋለን ።

በተለይም ደግሞ እኛ ክርስቲያኖች በወገኖቻችን መጎዳት ብናዝንም በትንሣኤ ሙታን ስለምናምን የምጽናና   በመሆኑ የሞቱት ልጆቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲያገኙ እየጸለይን፤ የመከራው ገፈት ቀማሽ ለሆኑት የአካባቢው ማኅበረሰብእ ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ ሁሉም አቅሙ በፈቀደው መጠን እንዲደርስላቸው ስንል አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ  ለቤተሰቦቻቸውና ለሕዝቡ መጽናናትን ይስጥልን፤ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
አሜን።

          አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

  ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም.                                               ዋሽንግተን ዲሲ~  አሜሪካ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
2024/09/25 14:19:18
Back to Top
HTML Embed Code: