Telegram Web Link
ውድ እና የቻናላችን ቤተሰቦች የመረጃ ተደራሽነታችን ለማስፋት ይረዳን ዘንድ ይሄንን ውድ ቻናል ለምታቋቸው ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ጓደኛችሁ በቻላችሁት አቅም ሁሉ #ሼር በማድረግ ይተባበሩን ብለን እየጠየቅን ....

ቻናላችንን #UNMUTE ካላደረጋችሁት ደግሞ እንደ View / እንደ member አይቆጠርም..... ስለዚህ ከላይ በምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት #MUTE የሚል ላይ ከሆነ አትንኩት ነገር ግን #UNMUTE ላይ ከሆነ 1ግዜ ብቻ በመንካት #MUTE ላይ ያድርጉት እኛንም ያግዙን እናንተም የምንለቃቸውን መረጃዎች ቶሎ ቶሎ ያግኙ!!

በስራችን ምንያህል ደስተኞች ናችሁ እስኪ ከ 10 ሬት አድርጉት !?
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Audio
ይህች ቅድስት ናት
                         
Size 38.4MB
Length 1:50:12

  በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
ስለ እርሱ ለመናገር እጅግ ከባድ ነው። የማይታይን አካል በእጅ ጠቁሞ ለማሳየት የመሞከር ያህል አስቸጋሪ ነገር ነው። ስለ "ዝምታ" እንዴት የእርሱ ተቃራኒ በሆነው "ንግግር" ልታብራራ ትችላለህ? ዝምታን በሚገባ ሊገልጽ የሚችለው አንድ ነገር ቢኖር ራሱ ዝምታ ነው። ዝዝዝምምም!

ጫጫታና ኹከት በነገሠበት በዚህ ዓለም ንግግር ሰው ሁሉ የሚግባባበት ቋንቋ ነው። የማይናገር ሰው እንደ ሞኝ ወይም ፈዛዛ ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል። በእርግጥ ለተፈቀደለት ዓላማ እና መጠን ብናውለው ኖሮ "ንግግር" ግሩም የፈጣሪያችን ሥጦታ ነበር። መናገር እኮ ተአምር ነው። በምድር ላይ ከሚንቀሳቀሱት ግዙፋን ፍጥረታ መካከል ነባቢው የሰው ልጅ ብቻ ነው። ምን ያደርጋል?! በጎውን ለክፋት፣ መልካሙን ለጥፋት ብናውለው ከንግግር ይልቅ ዝምታ የሚበልጥ ምግባር ሆነ። ንግግር በዚህ ዓለም ያለ መግባቢያ ሲሆን ዝምታ ግን ከሞት በኋላ በሚመጣው ዓለም ያለ ቋንቋ ሆነ። ከሞት በኋላ ያለችውን ዓለም ጣዕም ሳትሞት መቅመስ ትፈልጋለህ? እንግዲያውስ መንገዱን በ"ዝምታ" ጀምር። የአገሩን ቋንቋ የማያውቅ ሰው ለአገሩ ባዳ እንደሚሆነው፣ የሰማዩ ቋንቋ ዝምታን በዚህ ምድር ያልተለማመደ ሰው በሚመጣው ዓለም እንግዳ ይሆናል።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
"2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል " - የአካባቢው ምዕመናን

የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገ/ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሁለት አገልጋዮች #ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው መገደላቸውን የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለጸ።

በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በዶዶላ የደብረ  ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ጋር ለጊዜው " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት መገደላቸው ተነግሯል።

የቴሌቪዥን ጣቢያው ፤ ግድያው የተፈፀመው ትናንት መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ገደማ መሆኑን የአካባቢው ምዕመናን እንደነገሩት ገልጿል።

በተፈጸመው በዚህ ግድያ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን  አገልጋይ የሆኑት አንድ መሪጌታና ዲያቆንን ጨምሮ 5 የቤተሰብ አባሎቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ተገልጿል።

የቴሌቪዥን ጣቢያው ፥ በዶዶላ ከተማ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም በርካታ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን አስታውሷል።

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Audio
እሴተ ሃይማኖት 
       ክፍል 3                            
Size:- 25.4MB
Length:-1:12:00
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
አመ ፳፯ዑ ለመጋቢት መድኃኔዓለም ሥርዓተ ዋዜማ

ዋዜማ
ዘበእንቲአሃ ለቤተክርስቲያን ተፀፋዕከ በውስተ ዓውድ፤ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር፤ ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ፤ ወተዓገሠ ምራቀ ርኩሰ እንዘ አልቦ ዘአበሰ፤ አምላክ፤ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ።

ምልጣን-
ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ፤ ወተዓገሠ ምራቀ ርኩሰ እንዘ አልቦ ዘአበሰ፤ አምላክ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ፤አምላክ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ

አመላለስ፦
አምላክ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ፤
አምላክ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ።

ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ፦
በኃይለ መስቀሉ ይዕቀበነ፤ ወይክሥት አዕይንተ አልባቢነ፤ በኃይለ መስቀሉ ይዕቀበነ።

እግዚአብሔር ነግሠ፦
መስቀል ቤዛነ ኃይልነ፤ መስቀል ጽንዕነ፤ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ፤ አይሁድ ክህዱ፤ ወንሕነኒ እለ አመነ በመስቀሉ ድኅነ።

ይትባረክ፦
ኃበሩ ቃለ ነቢያት ወይቤሉ፤ መስቀል ብርሃን ለኲሉ ዓለም።

ሰላም
መስቀል ብርሃን ለኲሉ ዓለም፤ መሠረተ ቤተክርስቲያን፤ ወሃቤ ሰላም መድኃኔዓለም፤ መስቀል ለእለ ነአምን መድኅን።

አመላለስ፦
ወሃቤ ሰላም መድኃኔዓለም፤
መስቀል ለእለ ነአምን መድኅን።

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
አመ ፳፯ዑ ለመጋቢት መድሀኒአለም ስርአት ማህሌት

የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ"
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣሕል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ለአብ በመስቀሉ አተበነ፤ ሃሌ ሉያ ለወልድ በመስቀሉ ቤዘወነ፤ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ፤ በመስቀሉ ኮነ ሕይወትነ።

ዘጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
መድኃኔዓለም ወልድኪ ሥጋ ዚአኪ ዘለብሰ፤ ሐፃውንተ መስቀል ተአገሰ፤ በዓውደ ጲላጦስ ተወቅሰ አማዑትኪ ተካወሰ።

መልክአ መድኃኔዓለም
ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘኢረከቡ ተፍጻሚተ፤ መላእክተ ሰማይ ወምድር እለ ለመዱ ስብሐተ፤ መድኃኔዓለም ተወከፍ እንተ አቅረብኩ ንስቲተ፤ ዘሰተይከ በእንቲአነ ከርቤ ወሐሞተ፤ በሞተ ዚአከ ከመ ትቅትል ሞተ።

ዚቅ
ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ፤ ወአስተዩኒ ብሂዓ ለጽምዕየ፤ ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ።

ዓዲ (ወይም)
ዚቅ
ወአቅደምከ ጸግዎ መንፈሰከ ቅዱሰ ለሥርየተ ኃጢዓት፤ አክሊል ዘሦክ አስተቀጸሉከ ዘበሰማያት ለነ አክሊለ ጽድቅ አስተዳሎከ፤ ሰቀሉከ ዲበ ዕፅ፤ ብሂዓ ዘምስለ ሐሞት አስተዩከ፤ ከመ ለነ ታስትየነ ወይነ ትፍሥሕት ወሐሤት፤ ረገዙከ በኲናት ወተርኅወ ገቦከ፤ ከመ ለነ ተሀበነ ሥጋከ ቅዱሰ ወደምከ ክቡረ፤ ከመ ትጸግወነ።

ወረብ
ወአቅደምከ 'ጸግዎ'/፪/ መንፈሰከ/፪/
አክሊለ ጽድቅ አስተዳሎከ በሰማያት አክሊለ ጽድቅ/፪/

መልክአ መድኃኔዓለም
ሰላም ለጒርዔከ ክቡር ወልዑል፤ ወለክሣድከ ዓዲ ዘሰሐብዎ በሐብል፤ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በቀራንዮ ስቁል፤ በለኒ መሐርኩከ በእንተ ማርያም ድንግል፤ እስመ ኄር አልቦ እንበሌከ ቃል።

ወረብ
'በለኒ መሐርኩከ'/፪/ በእንተ ማርያም ድንግል/፪/
እስም ኄር አልቦ እንበሌከ ዘይሜሕር ቃል መድኃኔዓለም/፪/

ዚቅ
በእንተ ማርያም ወላዲትከ፤ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ፤ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳኒከ፤ ርድአነ ወትረ በኃይለ መስቀልከ፤ ኢታስተኃፍረነ እግዚኦ በቅድሜከ።

ወረብ
በእንተ ማርያም ወላዲትከ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ/፪/
ርድአነ ወትረ በኃይለ መስቀልከ/፪/

ዓዲ (ወይም)
ዚቅ
በአማን ቃልከ አዳም፤ ዘተሰቀልከ በእንተ ኃጥዓን ከመ ትቤዙ ነፍሰ ጻድቃን፤ በአማን ቃልከ አዳም፤ በአማን ቃልከ አዳም።

መልክአ መድኃኔዓለም
ሰላም ለልብከ እግዚአብሔር ናዝራዊ፤ ነቢይ ወመንፈሳዊ፤ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ህፃን ወአረጋዊ፤ እፎ ቀሰፉከ ካህናተ ይሁዳ ወሌዊ፤ በዓውደ ጲላጦስ መስፍን ከመ ገብር ዓላዊ።

ዚቅ
ወጸሐፈ ጲላጦስ መጽሐፈ፤ ወይብል መጽሐፉ ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ።

ወረብ
ወጸሐፈ መጽሐፈ ጲላጦስ ወይብል መጽሐፉ ጲላጦስ ዘጸሐፈ/፪/
ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሥ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ/፪/

መልክአ መድኃኔዓለም
ሰላም ለጸዓተ ነፍስከ አመ ዲበ መስቀል ቆመ፤ ወለበድነ ሥጋከ ምዑዝ እንተ ያጥዒ ሕሙመ፤ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከመ ትቤዙ ዓለመ፤ አሜሃ እግዚእየ ፀሐይ ጸልመ፤ ወወርኅኒ ተመሰለ ደመ።

ዚቅ
ምድር አድለቅለቀት ወሰማይ ተሀውከ ሶበ ትወጽእ መንፈሱ ለኢየሱስ።

ወረብ
ምድር አድለቅለቀት ወሰማይ ተሐውከ/፪/
ሶበ ትወጽእ መንፈሱ ለኢየሱስ/፪/

ዓዲ (ወይም)
ዚቅ
ሶበ ሰቀልዎ ሶበ ሰቀልዎ፤ ሶበ ሰቀልዎ ለእግዚእነ ፀሐይ ጸልመ ወወርኅ ደመ ኮነ፤ ዬ ዬ ዬ፤ አድለቅለቀት ምድር ወተከሥቱ መቃብራት።

መልክአ መድኃኔዓለም
ሰላም ለግንዘተ ሥጋከ ዘመዓዛሁ ጽጌረዳ፤ ወለመቃብሪከ ዘኮነ ለኢየሩሳሌም በዓውዳ፤ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በቅንዓተ ሰይጣን ዘይሁዳ፤ ሞተ ወተቀብረ በመቃብረ ሐዲስ እንግዳ፤ ኀበ ኢተቀብሩ ለሔዋን ውሉዳ።

ዚቅ
አውረድዎ እምዕፅ ዕደው ጻድቃን፤ ወአምጽኡ አፈዋተ ከርቤ ሕውስ ወልብሰ ገርዜን ንጹሕ ለግንዘተ ሥጋሁ።

ወረብ
'አውረድዎ'/፫/ እምዕፅ/፬/
ወአምጽኡ አፈዋተ ከርቤ ሕውስ/፪/

ምልጣን፦
መርሕ በፍኖት ሞገሶሙ ለጻድቃን፤ ዝንቱ ውእቱ መስቀል፤ ለአዳም ዘአግብዖ ውስተ ገነት፤ ወለፈያታዊ ኃረዮ በቅጽበት፤ መድኃኒት ዕፀ ሕይወት፤ ዝንቱ ውእቱ መስቀል።

አመላለስ፦
መድኃኒት ዕፀ ሕይወት፤
ዝንቱ ውእቱ መስቀል

ወረብ፦
ሃሌሉያ መርሕ በፍኖት ሞገሶሙ ለጻድቃን ሞገሶሙ/፪
ዝንቱ ውእቱ መስቀል ለአዳም ዘአግብዖ ውስተ ገነት/፪

እስመ ለዓለም
ብከ ንወግዖሙ ለኲሎሙ ፀርነ ይቤ ዳዊት በመንፈሰ ትንቢት፤ በእንተ ዕፀ መስቀል ዘተሰቅለ ዲቤሁ ቃለአብ፤ ወበስምከ ናኃሥሮሙ ለእለ ቆሙ ላዕሌነ፤ ወካዕበ ይቤ ወወሃብኮሙ ትዕምርተ ለእለ ይፈርሁከ፤ ከመ ያምሥጡ እምገጸ ቅስት፤ ወይድኃኑ ፍቁራኒከ፤ ወንሕነኒ ንትፈሣሕ ዮም ወንግበር በዓለ፤ በዛቲ ዕለት በዓለ እግዚእነ።

ወረብ፦
ብከ ንወግዖሙ ለኲሎሙ ፀርነ ብከ ንወግዖሙ ለኲሎሙ ፀርነ ይቤ ዳዊት በመንፈሰ ትንቢት/ ፪/
በእንተ ዕፀ መስቀል ዘተሰቅለ ተሰቅለ ዲቤሁ ቃለአብ/፪/

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
36k telegram channel

18000 birr

እውነተኛ ገዚ
Inbox me
@yesadikusitota

Chanalu
@Eotclibilery
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ (£itsum)
መጻጉዕ

ይህ በሽተኛ የተኛው ሠላሳ ስምንት ዓመት ነው ይህ ቁጥር ለአርብዓ ኹለት ይጎድለዋል ፣ የእነዚህ ኹለት ነገሮች መጉደልም ነው መጻጉዕን ለዚያ ኹሉ ዘመን እንዲተኛ ያደረገው ። እነዚህ ፍቅረ እግዚአብሔር (love of God) ፍቅረ ሰብእ (love of man ) ናቸው ። እነዚህ በመጻጉዕ አንጻር እንደ መጻጉዕ በገሃድ ሳይኾን በድብቅ በክፍ በሽታ ታመን የተኛነውን እኛን ኹላችንንም ይጎድሉን ስለ ነበረ በቸርነቱ አደለን ። እንግዲህ ከፍቅር የመራቆት ሕማም እንደ ምን ጽኑዕ እንደኾነ አስገነዘበን ። ( ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ ገጽ-99 )


#ኦርቶዶክሳዊ #አእምሮ
አንባብያን ሆይ! በመፃጉዕ ቦታ እኛ ብንሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልትድኑ ትወዳላችሁን? ብሎ ቢጠይቀን መልሳችን ምን ይሆን? ለራሳችን፣ ለማኅበረሰባችንና ለሀገራችን መለኮታዊውን ፈውስ በእውነት እንመኛለን ይሆን? ይህ ጥያቄ ከአካላዊው ድኅነት በዘለለ ለአእምሯዊ፣ ለስሜታዊና ለመንፈሳዊ ማንነታች ፈውስን መሻታችንን በጥልቀት ይመለከታል። እውነት ፈውስን እንፈልጋለን? ፍትሐዊነት የሰፈነበት፣ አቀመ ደካሞች መጠጊያ የሚያገኙበት፣ የተበደሉ የሚካሱበት ማኅበረሰብንስ እንናፍቃለን?

++++

ድኅነት ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለቤተሰቦቻችን፣ ለጎረቤቶቻችን፣ ለኅብረተሰባችን ብሎም ለሀገራችን ጭምር መሆኑን "ብቻ" በሌለበት የኦርቶዶክሳዊነት ትርጉም ውስጥ የምንረዳው እውነታ ሲሆን ልክ እንደ መፃጉዕ በእምነት ሆነን አዎ ጌታ ሆይ መዳን እንፈልጋለን ብለን ፈቀዳችንን በቅንነት ብንገልጽና አሳልፈን ብንሰጥ የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ይገለጣል። አዎ አባት ሆይ ሕመምተኞች ነንና ፈውስህን እንፈልጋለን!

ሊቁ አውግስጢኖስ “እምነት ያላየኸውን ማመን ነው፣ የእምነት ሽልማት ደግሞ ያመንከውን ማየት ነው”[2] ብሎ እንደጻፈ። እኛ በእግዚአብሔር ላይ ያለን እምነት መልካም ነገርን ፈውስን ለተጠማችው ምድራችን ተስፋ እንድናደርግ ያደርገናል። ይህንም በፍጹም እምነት ተስፋ ያደረግነው መልካም ነገር ሊቁ እንዳለው የእምነታችን ሽልማት ሆኖ የምናገኝው ሲሆን ነገር ግን ቅዱስ ያዕቆብ በመልእክቱ እንዳስተማረን እምነት ያለ ሥራ የሞተ መሆኑን ቆም ብለን ማጤን ይገባናል።

++++

‘ልባቸው የቆሰሉትን ይፈውሳል ፡ ሕማማቸውንም ይጠግናል’ መዝ ፻፵፯፥፫

++++

3. የጌታችን የኢየሱ ክርስቶስ ፈውስ (ዮሐ ፭፥፰)

‘ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ’

በዚህ ቁጥር ላይ የምናገኘው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ከላይ ለጠይቅነው ፈውስን የመሻት ጥያቄ የተሰጠ ታላቅ ምላሽ ነው። የጌታችን ትዕዛዝ የሻትነውን መልካም ነገር ለማግኘት ከምናደርገው ጥያቄና ጥረት ጋር በእጅጉ የሚስማማ ነው።

ለሠላሳ ስምንት ዓመታት በአልጋ ላይ የነበረው መፃጉዕ እንደተነሳ በዘመናት ስቃይ ውስጥ የምንገኝ እኛና ማኅበረሰባችንም በእርሱ መለኮታዊ ኃይል እንነሳለን። ይኸውም የመነሳት፣ አልጋን ተሸክሞ የመሄድና የመለወጥ ሂደት በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን በእውነተኛው ሐዋርያዊ ሥልጣነ ክህነት በሚከናወኑ በቅዱሳን ምስጢራት አማካኝነት የሚፈጸም ነው፡፡ በምሥጢረ ጥምቅት ንጽሕናን ገንዘብ እናደረጋለን ይኸውም ከጥላቻ ከመለያየትና ከመገፋፋት አውጥቶ አንድ የክርስቶስ አካል ያደርገናል። ቅዱስ ቁርባንም ዘወትር በክርስቶስ አካልነት ውስጥ እንድንሆን በማድረግ በአንድነትና በአብሮነት ያስተሳስረናል። ምሥጢረ ቀንዲልም ቁስላችንን ይጠግናል ከተኛንበትም አልጋ ያነሳናል። ሌሎችም ቅዱሳት ምሥጢራት ከክብር ወደ ክብር እንድናድግ ይረዱናል። በመሆኑም አንዲት ጥምቀትን የተጠመቅን ከአንድ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ የተቀበልን ኦርቶዶክሳውያን በኅብረት በመመላለስ ለህዝባችንና ለሀገራችን መፍትሄዎች መሆን ይገባናል።

++++

ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም ስለ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን ባስተማረው ትምህርቱ “እኔ የምሰጠው ውኃ በእርሱ ውስጥ የሕይወት ውኃ ምንጭ ይሆንላታል ወደ ዘላለም ሕይወትም የሚመራ የሕይወት ውኃ ምንጭ ይሆናል” [3] በማለት የቅዱሳት ምሥጢራትን ጥልቅ ትርጉም ይነግረናል። ቅዱሳት ምሥጢራት መንፈሳዊ ዕድገትና ለውጥ በማምጣት ያለምንም ልዩነትና አድልዎ ስለ እግዚአብሔር ልጆች ክብር፣ እኩልነትና ለውጥ በአንድነት እንድንቆም ይመሩናል።

በቤተሳይዳ የመጠመቂያ ሥፍራ የተከናወነውን ተአምራዊ ፈውስ ስናስብ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  የሰጠው መለኮታዊ ትእዛዝ አካላዊ ፈውስን ብቻ ሳይሆን ከመንፈሳዊውና ከሥነልቦናዊ እሥራትም ነፃ የመውጣትን ጥሪ ያካተተ መሆኑን እንገነዘባለን። ይህንንም ጥሪ ተከትለን ፍትሐዊነት እንደ ወንዝ የሚፈስባት ሁሉም በነጻነትና በክብር የሚራመደባትን ምድር ለመገንባት በጋራ መሥራት ይገባናል።

++++

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች በዚህ ሳምንት እያሰብነው ያለው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የፈውስ ተአምራት ከመፃጉዕ ግለሰባዊ ማንነት በዘለለ በዘመናችን እኛን፣ ማኅበረሰባችንና ሀገራችንን የሚያጠቃልል ሰፊና ጥልቅ ትርጓሜ እንዳለው እናስተውል። እንደ ሀገር፣ ማኅበረሰብና ግለሰብ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ተአምራትና ድንቅ ነገር እንደሚያስፈልገን እንመን። ለሚያጋጥሙን የተለያዩ ህመሞቻችን ያለ ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛና ዘላቂ ፈውስ በፍጹም ማግኘት አንችልም።

በሀገራችን ውስጥ ከተፈጠረው የመለያየት፣ የመቃቃርና የኢ-ፍትሐዊነት ህመም ድኅነትን እናገኝ ዘንድ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ፈውስ የሚያስፈልገን ሲሆን የሚከፋፍሉንን እንቅፋቶች አስወግደን አንድ መሆን የምንችለው በእሱ ጸጋ ብቻ ነው።

እኛም እንደ ግለሰብ ከብዙ መከራዎች፣ ፍርሃቶችና ጥርጣሬዎች ጋር ትግል ላይ እንደሆንን ይታወቃል። ይህም ትግላችን አብቅቶ ፍጽም ምሉዕነት ያለውን ውስጣዊ ሰላም ለማግኘት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ፈውስ ያስፈልገናል። በዚህም ውስጥ እርሱ በመንገዳችን ሁሉ ከእኛ ጋር አብሮ እንዲጓዝ ፈተናዎቻችንን በእምነትና በድፍረት የምንጋፈጠበትን ኃይል እንዲሰጠን በፍጹም ትህትና በጾምና በጸሎት እንትጋ።

++++

‘የጠፋውን እፈልጋለሁ የባዘነውንም እመልሳለሁ የተሰበረውንም እጠግናለሁ የደከመውንም አጸናለሁ` ሕዝ ፴፬፥፲፮

++++

የተወደድሽ የድኅነታችን ምክንያት እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ የመከራችንን ጥልቀትና የልባችንን የመፈወስና የመዳንን ምኞት አድምጠሽ የአንቺን የእምነት፣ የትህትና እና የእግዚአብሔርን ፈቃድ መታዘዘ እንድንከተል ጸጋውን ይሰጠን ዘንድ በልጅሽ ፊት አማልጅን።

++++

የሰማይ አባት ሆይ ጸሎታችንን ሰምተህ ለሀገራችን፣ ለአህጉራችንና ለዓለማችን የአንተ የፈውስና የጸጋ መሳሪያዎች እንሆን ዘንድ ጸጋህን ስጠን። በነገር ሁሉ ፈቃድህን እንድንፈልግ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም፣ የቅዱሳን እና የምእመናን ሁሉ ጸሎት የብርታትና የመጽናናት ምንጭ ይሁንልን። በአንድ ልጅህ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሱም ጋር ትክክል በሆነ በመንፈስ ቅዱስ ስም ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን!

 
መ/ር ቃለአብ መዝገቡ
የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የፈተናዎች ማስተባበሪያና ክትትል ክፍል ዋና ኃላፊ
መጋቢት ፳፩
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Audio
የጌታ ጅራፍ
                         
Size 31.4MB
Length 1:30:08

  በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
2024/06/26 02:48:05
Back to Top
HTML Embed Code: