Telegram Web Link
ዘመናት ተቆጠሩ።
ስለዚህ ፈሹንጁ መጥቶ እውነታን ይነግሹኛል ብለህ አትጃጃል ኚእነ ቶማስ ሙር፥ ኚእነ ዳቢንቜ ፥ኚእነ ግራም ሀንኩክ ፥ትልቅ ሚስጥራዊ መልዕክቶቜ እንደኚተቡለህ እውቅ... ይልቁንስ ለልጆቜህ ዚምትነግሚው፥ በመላው አለም ብትዞር ደሚትክን ነፍተህ ስለ ሀገሹህ ዚምትመሰክሚው፥ ስታውቃት ነውና ጠጋ ብለህ ጠይቅ፥ ዝቅ ብለህ ተሚዳ፥ ብራና ገልጠህ አንብብ፥ ገዳማት ሂደህ ተመራመር ፥ ኹዛም ጉያዋ ስር እዚኖርክ ያልተሚዳህት እቅፏ ስር ተወሜቀህ ባይተዋር ዚምትሆንብህ ሀገሹ እግዚእ ኢትዮጵያን ኚባህሩ ማንነቷ በሚንኪያ ጹልፈህ ስትቀምሳት ጣምናዋ አንደበትህ ላይ ተነቅሶ ያስቀባጥርሃል፥ ኚልብህ ተወቅሮ ያስለፈልፍሃል፥ በህሊናህም ታትሞ ያስገርምህል።

ለምን ካልኚኝ ግብጜና ግሪክን፥ ፋርስና ባቢሎንን ፥ሰው ሰራ ኢትዮጵያን ግን አምላክ በጥበቡ አነጻት እልሃለኋ !

@yemariyam2121
✝አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።✞✞
ግንቊት 9-ጌታቜን ተገልጊላት ስለ ቅዱስ መስቀሉ ቃልኪዳን ዚገባላት ዚታላቁ ጻድቅ ንጉሥ ዚቆስጠንጢኖስ እናት ዚኚበሚቜ ንግሥት እሌኒ ዐሚፈቜ፡፡
ጌታቜን ዚተሰቀለበት መስቀል ሙት እያስነሳ ድውይ እዚፈወሰ አጋንንት እያወጣ ዚተለያዩ ገቢሚ ተአምራት ሲሰራ ክፉዎቜ አይሁዶቜ አይተው ሕዝቡ ክርስቲያን እንዳይሆኑ በመፍራት በ34 ዓ.ም ኚኢዚሩሳሌም ወጣ ብሎ በሚገኝ ቊታ ቆፍሹው ቀበሩት፡፡ ኚዚያም ዹኹተማውን ቆሻሻ ሁሉ ኚዚያ መስቀሉ በተቀበሚበት ቊታ ላይ እዚደፉ ኹዘመን ብዛት ቊታው በቆሻሻ ክምር ዚተነሣ ተራራ ሆነ፡፡ እስራኀልን ኚሮም ቅኝ አገዛዝ ነጻ ለማውጣት ኹ66-70 ዓ.ም ባደሚጉት እንቅስቃሎ ጥጊስ ዚተባለው ዚሮም ንጉሠ ነገሥት ዘምቶ ኢዚሩሳሌምን በ70 ዓ.ም ደመሰሳት፡፡ ትልቁን ዚአይሁድ ቀተመቅደስንም አቃጠለው፡፡ እስራኀላውያንም በመላው ዓለም ተበተኑ፡፡ ኹዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ በተኚታታይ በሮም ዚነገሡ ነገሥታት /ቄሳሮቜ/ በክርስቲያኖቜ ላይ ዚማያባራ መኚራ አድርሰዋል፡፡ ክርስቲያኖቜ ዹተቀበሹውን መስቀል አስፈልገው ለማውጣት ቀርቶ ሃይማኖታ቞ውን ዹማመን ነጻነት ስላልነበራ቞ው ቅዱስ መስቀል ለ300 ዓመታት ያህል ተቀብሮ ዚጉድፍ መጣያ ሆኖ ቆዚ፡፡ ዚመስቀሉ ዚመገኘት ታሪክ ዚቀተክርስቲያን ዚመኚራ ዘመን አልፎ ዚዕሚፍትና ዹሰላም ዘመን ሲመጣ ለብዙ ዘመን ተቀብሮ ዚተሚሳውን መስቀል ባለቀቱ መድኃኔዓለም አልሚሳምና እርሱ ዚፈቀዳት ዕለት ስትደርስ በዕሌኒ ንግሥት አማካኝነት ኚተቀበሚበት እንዲወጣ አደሚገ፡፡

ዕሌኒና ተርቢኖስ ዚሚባሉ ሁለት ደጋግ ክርስቲያኖቜ ተጋብተው ይኖሩ ነበር፡፡ ተርቢኖስና ዕሌኒ ኑሮአ቞ው ፍቅርና ሰላም ዚሰፈነበት በመሆኑ ለብዙ ሰዎቜ እንደ ምሳሌ ሆነው ይኖሩ ነበር፡፡ ተርቢኖስ ነጋዮ ነበር፡፡ ኚዕለታት አንድ ቀን ራቅ ወዳለ ሀገር በመርኚብ ለንግድ ሄደ፡፡ ዕሌኒም ባለቀቷ ተርቢኖስ ለንግድ ወጥቶ እስኪመለስ ስለባሏ ኹመጾለይና ኚማሰብ በቀር ኚግቢዋ አትወጣም ነበር፡፡ አንድ ጊዜ ተርቢኖስ ለንግድ ሄዶ ብዙ ዓመታትን ቆይቶ ኚጓደኞቹ ጋር ወደሀገሩ ሲመለስ ኚነጋዎዎቜ አንዱ "በእግዚአብሔር ፈቃድ ኚሜፍታና ኹማዕበል ኚልዩ ልዩ አደጋ ተርፈን በሰላም ተመልሰን ሚስቶቻቜን ሌላ ሳይወዱ ሳይለምዱ እናገኛ቞ው ይሆን?" ብሎ ጠዚቀ፡፡ ተርቢኖስ ግን "እንኳን በሰላም አደሹሰን እንጂ ሚስ቎ን በዚህ አልጠሚጥራትም" ብሎ ሲመልስ ሌላው ጓደኛው "ያንተ ሚስት ኹማን ትበልጣለቜና ነው አሁን ሄጄ ኚሚስትህ ጋር ለምዳኝ ወዳኝ ወድጃት ብመጣስ ምን ትቀጣለህ?" አለው፡፡ ተርቢኖስም በሚስቱ ዕሌኒ ተማምኖ "ይህንን ብታደርግ ይህን ያህል ዓመት ዚለፋሁበት ሀብት ኚነትርፉ ውሰድ አንተም ብታደርግ እንዲሁ ሀብትህ ኚነትርፉ ለእኔ ይሁን" ተባብለው ተወራሚዱ፡፡

ኚዚያም መርኚቡ ወደብ ኚመድሚሱ በፊት ነጋዮው ወደ ዕሌኒ ቀት ደሹሰና በሩን አንኳኩቶ ሠራተኛይቱን "ዕሌኒን ማነጋገር እፈልጋለሁና ንገሪልኝ" ብሎ ጠዚቃት፡፡ እርሷም እያፈሚቜ ዚተላኚቜውን ለዕሌኒ ነገሚቻት፡፡ ዕሌኒም ተቆጥታ "ኚመቜ ወዲህ ነው እንግዳ ዹማነጋግሹው?" ብላ አሳፈሚቻት፡፡ ሠራተኛይቱም ለነጋዮው መልሱን ስትነግሚው ነጋዮው እንደማይሆንለት ኚተሚዳ በኋላ ሌላ ተንኮል አቀደና ለሠራተኛይቱ "ባልና ሚስቱ ብቻ ዚሚያውቁትን አንድ ነገር ብቻ ብትሰጪኝ ብዙ ገንዘብና ወርቅ እሰጥሻለሁ" ብሎ ወርቅ ሰጣት፡፡ ሠራተኛይቱም "ሁለቱ ብቻ ዚሚያውቁት ዚእመቀ቎ ሀብል አለ ያንን እመጣልሀለሁ መጀመርያ አንተ በኹተማው ውስጥ እዚዞርህ ነጋዎዎቜን መጡ ዚብስ ሚገጡ እያልክ አስወራ ኚዚያም ተመልሰህ እንድትመጣ" ብላ ሰደደቜው፡፡ ነጋዮውም እንደተመኚሚው ዚነጋዎዎቹን መምጣት በኚተማይቱ እንዳወራ ዚነጋዎዎቹ ቀተሰቊቜ ነጋዎዎቜን ለመቀበል ዝግጅት ማድሚግ ጀመሩ፡፡ ዹዕሌኒም ሠራተኛ "እመቀ቎ ነጋዎዎቜ መጡ ተብሎ ይወራልና፡፡ ባለቀትዎ በሰላም ስለመጡ ይዘገጃጁ ገላዎን ይታጠቡ" ብላ መኚሚቻት፡፡ ዕሌኒም ገላዋን ስትታጠብ ያንገቷን ሐብል ቁጭ ካደሚገቜበት ቊታ ሠራተኛይቱ አንስታ ለነጋዮው በተቃጠሩበት ዕለት ሰጠቜው፡፡ ነጋዮውም ለሠራተኛይቱ ዚውለታዋን ብዙ ገንዘብና ወርቅ ሰጥቶአት ደስ እያለው ወደ ጓደኞቹ ሄደ፡፡ ለተርቢኖስ "ሚስትህን ለምጃት ወድጃት መጣሁ" አለው፡፡ ተርቢኖስም "ውሞት ነው ለዚህ ምን ምልክት አለህ?" ብሎ ጠዚቀው፡፡ ተንኮለኛውም ነጋዮ ያንን ሐብል አውጥቶ "ይህ ሀብል ዚሚስትህ አይደለምን?" ብሎ ሰጠው፡፡ ተርቢኖስም ደነገጠ ዹሚናገሹውን አጣ፡፡ በውርርዱም መሠሚት ሀብቱን ሁሉ አስሚኚበና ባዶ እጁን ወደቀቱ እያዘነ እዚተቆጚ ሔደ፡፡
ባለቀቷን በናፍቆትና በታማኝነት ስትጠብቅ ዚኚሚመቜው ዕሌኒ በተርቢኖስ ያልተለመደ ሀዘንና ብስጭት ግራ ተጋብታ "ወንድሜ ምን ሆነሀል? ለወትሮው እንኳን ይህን ያህል ዘመን ተለያይተን ቀርቶ ለጥቂት ቀናት ተለያይተን እንኳ ለጥቂት ቀናት ተለያይተን ስንገናኝ እንነፋፈቃለን፡፡ አሁን ግን ኚመጣህበት ጊዜ ጀምሮ አዝነህ አይሃለሁ" ብላ ጠዚቀቜው፡፡ ተርቢኖስም "ብዙ ዚደኚምኩበትና ዚለፋሁበት ሀብት ንብሚ቎ እንዳለ ማዕበል አጠፋብኝ እኔ ያላዘንኩ ማን ይዘን?" አላት፡፡ ዕሌኒም ዚተማሚቜ ናትና "እግዚአብሔር ሰጠ እግዚአብሔር ነሣ ዚእግዚአብሔር ስም ዹተመሰገነ ይሁን እንዳለ ኢዮብን አስበው፡፡ አንተ እንኳን በሰላም መጣህ እንጂ ሀብቱ ውሎ አድሮ ይመጣል..." እያለቜ አጜናናቜው፡፡ ተርቢኖስም "እንግዲህ በተኚበርኩበት ሀገር ተዋርጄ፣ በሰጠሁበት ሀገር ለምኜ ለመኖር አልቜልምና ወደሌላ ወደማያውቁኝ ሀገር እሔዳለሁ አንቺ ግን ሁሉ ይወድሻል ያኚብርሻል ኚወደድሞው ጋር ኑሪ" አላት፡፡ ዕሌኒም "በደስታ ጊዜ አብሬህ እንደሆንኩ በቜግርም ጊዜ ልለይህም ዚእኔንና ያንተን አንድነት ቜግር አይፈታውም ኹአንተ ተለይቌ ወዎት እቀራለሁ ወደምትሄድበት አብሬህ እሄዳለሁ" ብላ ተነሳቜ፡፡ ሁለቱም ቀታ቞ውን ጥለው ሲሄዱ በመንገድ ላይ ተርቢኖስ በልቡናው ይዞት ዹነበሹውን ምሥጢር አወጣው "ዕሌኒ ስወድሜ ዚጠላሜኝ ሳምንሜ ዚኚዳሜኝ ምን አድርጌሜ ነው?" ብሎ ጠዚቃት፡፡ ዕሌኒም "እኔ አንተን አልጠላሁም አልኚዳሁምም ይህንን ሐሳብ እንዎት አሰብህ?" ብትለው ኚኪሱ አውጥቶ ሀብሉን አሳያትና ዹሆነውን ሁሉ ነገራት፡፡ ዕሌኒም ያልጠበቀቜው ነገር ስለተፈጞመ አዝና ዹሆነውን እውነተኛ ታሪክ በሙሉ ነገሚቜው፡፡ ተርቢኖስ ግን አላመናትም፡፡ ኚባህር ዳር በደሚሱ ጊዜ በቁመቷ ልክ ሣጥን አሠርቶ ዕሌኒን በውስጡ አስገባትና "ብታደርጊውም ባታደርጊውም እንደሥራሜ ሥራሜ ያውጣሜ" ብሎ ወደ ባሕሩ ወሚወራት፡፡
ዕሌኒ ያለቜበት ሣጥን በፈቃደ እግዚአብሔር እዚተንሳፈፈ ኚወደብ ደሚሰ፡፡ በዚያ ወደብ አካባቢ ምዕራብ ሮምን ያስተዳደር ዹነበሹው ኮስታንዲዮስ (ቁንስጣ) ዚተባለው ንጉሥ ነበርና ሣጥኑን አይቶ አውጥቶ እንዲኚፍቱት ወታደሮቜን አዘዘ፡፡ ሣጥኑን አውጥተውም ሲኚፍቱት እጅግ ዚተዋበቜ ሎት ሆና አገኟት፡፡ ንጉሡም ዕሌኒን ወስዶ ሚስቱ አደሚጋት፡፡ ኮስታንዲዮስ (ቁንስጣ) ዚመክስምያኖስ ቄሳር ሆኖ ምዕራብ ሮምን ያስተዳደር ነበር፡፡ ንግስት ዕሌኒም በ272 ዓ.ም ታላቁ ቆስጠንጢኖስን ወለደቜለት ቆስጠንጢኖስም ገና በወጣትነቱ ዚአባቱ እንደራሎ ሆኖ እንደሠራ አባቱ ሞተ፡፡ ዚአባቱ ባለሟሎቜና ሕዝቡ ተስማምተው ዹ18 ዓመቱን ቆስጠንጢኖስን በአባቱ ቊታ ሐምሌ 25 ቀን 316 ዓ.ም በሮም ምዕራብ ክፍል በገላትያ አነገሡት፡፡ በጩር ሜዳዎቜ ብዙ ዚጀግንነት ሥራዎቜ ስለሠራ በሠራዊቱ ዘንድ ይወደድ ነበር፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሮን ወላጅ እናቱ በፈርዖን ቀት ሃይማኖቱን ባሕሉን
ት ክርስቲያኖቜ ካልታሚቃቜሁ ሀገራቜሁን መጥቌ አጠፋለሁ" ዹሚል ማስጠንቀቂያ ላኚ፡፡

ዚንጉሡ መልዕክትም ለእስላሞቹ እንደደሚሳ቞ው ፈርተው እንደ ጥንቱ በዚሃይማታ቞ው ጾንተው በሰላም እንዲኖሩ ኚክርስቲያን ወንድሞቻ቞ው ጋር ታሚቁ፡፡ መታሚቃ቞ውን ዓጌ ዳዊት ሰሙ በዚህም ጉዳይ ንጉሡ ደስ አላ቞ው፡፡ እግዚአብሔርንም አመሰገኑ በግብጜ ዚሚኖሩ ክርስቲያኖቜም ኹ12,000 ወቄት ወርቅ ጋር ደስታ቞ውን ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ ለዳግማዊ ዳዊት በደብዳቀ አድርገው ላኩላ቞ው፡፡ ንጉሡም ዚደስታውን ደብዳቀ ተመልክተው ደስ አላቾው ወርቁን ግን መልሰው በመላክ እንዲህ ዹሚል ደብዳቀ ጻፉ፡- "በግብጜ ዚምትኖሩ ዚክርስቶስ ተኚታዮቜ ሁሉ እንኳን ደስ አላቜሁ ዚላካቜሁልኝ 12,000 ወቄት ወርቅ መልሌ ልኬላቜኋለሁ፡፡ ዚእኔ ዓላማ ወርቅ ፍለጋ አይደለም ዚክርስቶስ ፍቅር አስገድዶኝ በተቻለኝ ቜግራቜሁን ሁሉ አስወገድኩላቜሁፀአሁንም ዚምለምናቜሁ በሀገሬ ኢትዮጵያ ሚሀብና ቾነፈር ድርቅ ስለወሚደብኝ መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚተሰቀለበት ቅዱስ መስቀልና ዚቅዱሳን አጜም ኚሌሎቜ ክቡራን ዕቃዎቜ ጋር እንድትልኩልኝ ነው" ዹሚል ነበር፡፡
እስክንድርያ ያሉ ምዕመናንም ዹዐፄ ዳዊት "በሀገሬ ኢትዮጵያ ሚሀብና ቾነፈር ድርቅ ስለወሚደብኝ መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚተሰቀለበት ቅዱስ መስቀልና ዚቅዱሳን አጜም ኚሌሎቜ ክቡራን ዕቃዎቜ ጋር እንድትልኩልኝ" ዹሚለው መልዕክት እንደደሚሳ቞ው ኹሊቃነ ጳጳሳትና ኚኀጲስ ቆጶሳቱ ጋር ውይይት በማድሚግ "ይህ ንጉሥ ታላቅ ክርስቲያን ነው፡፡ ስለዚህ ልቡን ደስ እንዲለው ዹፈለገውን ዚጌታቜንን ግማደ መስቀል ኚቅዱሳን ዐፅምና ንዋዹ ቅዱሳት ጋር አሁን በመለሰው ወቄት ወርቅ ዚብርና ዚነሐስ ዚመዳብና ዹወርቅ ሣጥን አዘጋጅተን እንላክለት" ብለው ተስማምተው በክብር በሥነ ሥርዓት በሠሹገላና በግመል አስጭነው ስናር ድሚስ አምጥተው ለኢትዮጵያውያን ባስሚኚቧ቞ው ጊዜ በእጃ቞ው እያጚበጚቡ በእግራ቞ው እያሞበሞቡ በግንባራ቞ው እዚሰገዱ በክብር በደስታ ተቀበሏ቞ው፡፡

ግማደ መስቀሉ ወደ መካኚለኛው ኢትዮጵያ ሳይደርስ በድንገት ዐፄ ዳዊት ስናር በሚባል በሹሃ ላይ አሚፉ፡፡ ግማደ መስቀሉም ዚግድ በዚያው በስናር መቆዚት አስፈለገው፡፡ ኹዚህ በኋላ ዚሟቹ ዚዳግማዊ ዳዊት ልጅ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ እንደነገሡ ወደ ስናር ሔደው ግማደ መስቀሉን ኚሌሎቹ ንዋያተ ቅዱሳት ጋር አምጥተው በመናገሻ ኹተማቾው በደብሚ ብርሃን ላይ ቀተመቅደስ ሠርተው ለማስቀመጥ ሲደክሙ በሕልማቜው አንብር መስቀልዚ በዲበ መስቀል "ወዳጄ ዘርዐ ያዕቆብ ሆይ መስቀሌን በመስቀለኛ ቊታ ላይ አስቀምጥ" ዹሚል ራእይ አዩ፡፡

ኚእስክንድርያ ሀገር ኚመስቀሉ ጋር በልዩ ልዩ ሣጥን ተቆልፈው ዚመጡትም ዝርዝር ስማ቞ው ጌታቜን በዕለተ ዓርብ ለብሶት ዹነበሹው ቀይ ልብስ፣ ኚሮም ዚመጣው ኚለሜዳው፣ ሐሙት ዚጠጣበት ሰፍነግ /ጜዋ/፣ ዮሐንስ ዚሳለው ኩርዓተ ርዕሱ ስዕል እንዲሁም ዚተለያዩ ዚቅዱሳን አጜም፣ ኚግብጜ ታላላቅ ገዳማት ዹተቆነጠሹ አፈር፣ ዚዮርዳኖስ ውሃ ይገኛል፡፡ ንጉሡም መስቀለኛ ቊታ እዚፈለጉ በኢትዮጵያ አውራጃዎቜ ሁሉ በመፈለግ ኚብዙ ቊታ አስቀምጠውት ነበር፡፡ ለምሳሌ በሾዋ በደብር ቅዱስ ደብሚ ጜጌ ማርያም ገዳም፣ በማናገሻ ማርያም፣ በወጚጫ መስቀሉን አሳርፈውት ነበር፡፡ ነገር ግን ዚመጚሚሻውን ቊታ ባለማግኘታ቞ው በራዕይ እዚደጋገመ አንብር መስቅልዚ በዲበ መስቅል መስቀሌን በመስቀለኛ ሥፍራ አስቀምጥ እያለ ይነግራ቞ው ነበር፡፡ ዓጌ ዘርዓ ያዕቆብም ለሰባት ቀን ሱባዔ ገቡ፡፡ በዚያም ዹተገለጾላቾው "መስቀለኛውን ቊታ ዚሚመራህ ዓምደብርሃን ይመጣል" አላ቞ው፡፡ እርሳ቞ውም ኚዚያ እንደወጡ መስቀለኛውን ቊታ ዚሚመራ ዚብርሃን ዓምድ ኚፊታ቞ው መጥቶ ቆመ፡፡ በዚያ መሪነት ወደ ወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ ውስጥ ግሾን ኚምትባል አምባ መርቶ መስኚሚም 21 ቀን 1440 ዓ.ም አደሚሳ቞ው፡፡ በእውነትም ይህቜ ግሾን ዚተባለቜው አምባ ጥበበኛ ሰው እንደቀሚጻት ዚተዋበቜ መስቀለኛ ቊታ ሆና ስላገኟት ዚልባ቞ው ስለደሚሰ ደስ አላ቞ው፡፡ እግዚአብሔር ገና ዓለምን ሲፈጥር ዹግሾንን ዓምባ ለዚህ ክብር ዚተዘጋጀቜ አድርጎ ፈጥሯታልና፡፡ በዚያም አምባ ታላቅ ቀተ መቅደስ ሠርተው ቅዱስ መስቀሉንና ሌሎቜ ንዋዹ ቅዱሳቱን በዹመዓሹጋቾው ዚክብር ቊታ መድበው አስቀመጡዋ቞ው፡፡ ዘመኑም በ14ኛው ክፍለ ዘመን ነው፡፡ ዚንግሥት ዕሌኒ ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን በጞሎቷ ይማሚን፡፡ ዚመስቀሉ ፍቅር ይደሚብን!
(ምንጭ፡- ስንክሳር ዘወርኀ ግንቊት፣ ድርሳነ መስቀል፣ ዹገነተ ጜጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቀት መካነ ድር)
ን በሚገባ እያስተማሚቜ እንዳሳደገቜው ሁሉ ንግሥት ዕሌኒም ልጇን ቆስጠንጢኖስን ኚልጅነቱ ጀምሮ ስለክርስትና ሃይማኖትና ስለክርስቲያኖቜ መኚራ ታስተምሚው ስለነበር በክርስቲያኖቜ ላይ ዹነበሹው አመለካኚት በሮም ኚነገሡት ቄሣሮቜ ሁሉ ዚተሻለ ነበር፡፡ በተለይም በ312 ዓ.ም ኚጠላቱ ኚመክስምያኖስ ጋር ለመዋጋት "ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት" ብሎ ለዘመቻ እንደተሰለፈ በራእይ በሰማይ ላይ "በዚህ መስቀል (ምልክት) ጠላትህን ድል ታደርጋለህ" ዹሚል ዚመስቀል ቅርጜና ዚተጻፈ ጜሑፍ ስላዚ ለሠራዊቱ ዚመስቀል ምልክት በመሳሪያ቞ውና በሰንደቅ ዓላማው ላይ እንዲያደርጉ አዘዘ፡፡ ወደያው ጊርነት ቢገጥም ጠላቱን ድል ነሥቶ በጠቅላላው ዚሮም መንግሥት ግዛቶቜ ሁሉ ገዥ ሆነ፡፡
ታላቁ ቆስጠንጢኖስ ዚሮም ንጉሠ ነገሥት ኹሆነ በኋላ በ300 ዓመታት ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ ለክርስቲያኖቜ ዚነጻነት ዐዋጅ ዐወጀ፡፡ ክርስትናም ብሔራዊ ሃይማኖት ተባለቜ፡፡ ንግሥት እሌኒም በተፈጠሚላት አመቜ ሁኔታ በመጠቀም ዚጌታቜን መስቀል ኚተቀበሚበት ለማውጣት በ327 ዓ.ም ወደኢዚሩሳሌም ሔደቜ፡፡ ዕሌኒ ልጅዋ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ኚሆነላት ወደ ኢዚሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢዚሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነጜ ለእግዚአብሔር ተሳለቜ፡፡ ኹዚህ በኋላ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ.ም ተጠመቀ፡፡ ቅድስት ዕሌኒም ወደ ኢዚሩሳሌም ሔደቜ፡፡ ኚእርሷም ጋር ብዙ ሠራዊት ነበር፡፡ እንደደሚሰቜም ስለ ቅዱስ መስቀል መሚመሚቜ፡፡ ነገር ግን ቊታውን ዚሚያስሚዳት አላገኘቜም፡፡ ዚአይሁድ ወገን እንቢ ቢሉም በኋላ ግን ባደሚገቜው ጥሚት አሹጋዊው ኪራኮስ ዚጎልጎታን ኮሚብታ አመለኚታትና አስቆፍሪው ብሎ ነገራት ኪራኮስም ዘመኑ ኹመርዘሙ ጋር ተያይዞ እውነተኛው ተራራ ይህ ነው ብሎ ማሳዚት ባለመቻሉ "ኚሊስቱ ተራሮቜ አንዱ ነው" ስላላት አይሁድ ተራሮቹን ይቆፍሩ ዘንድ አዘዘቻ቞ው፡፡ ዚጌታቜን ቅዱስ መስቀል በሚያደርጋ቞ው አስደናቂ ተአምራት ዚተነሣ ሕዝቡ እያመነ በተ቞ገሩ ግዜ ክፉዎቜ አይሁዶቜ ማንም እንዳያገኘው ዚኢዚሩሳሌም ነዋሪ ሁሉ ዚእቀቱን ቆሻሻ ዹኹበሹ መስቀል ባለበት ቊታ እንዲጥል አዘው ስለነበር ኚሁለት መቶ ሃምሳ ዓመት በላይ ጥራጊ ስለጣሉበት ታላቅ ተራራ ሆነ፡፡

ዕሌኒ ተራሮቹን ለማስቆፈር ኚሊስቱ ተራሮቜ ዚቱ እንደሆነ ለመለዚት ደመራ አስደምራ ብዙ ዕጣን በመጹመርና በማቃጠል ኚአኢዚሩሳሌም ወጣ ብለው ያሉትን ኮሚብቶቜ አሳያት፡፡ ዚዕጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ባለበት ተራራ ላይ በማሹፍና በመስገድ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ሥፍራ አመለኚታት፡፡ ቅዱስ ያሬድም "ሰገደ ጢስ" ጢሱ ሰገደ ብሎታል፡፡ ኚዚያም መስኚሚም 16 ቀን ቁፋሮው እንዲጀመር አዘዘቜ፡፡ ሰባት ወር ያህል ኹተቆፈሹ በኋላ መጋቢት 10 ቀን ሊስት መስቀሎቜ በአንድነት ተገኙ፡፡ ንግሥት ዕሌኒም ዚክብር ባለቀት ጌታቜን ዚተሰቀለበት ዚትኛው እንደሆነ ለማወቅ በወደደቜ ጊዜ "ኚራሱ በላይ ይህ ዚናዝሬቱ ኢዚሱስ ዚአይሁድ ንጉሥ ነው" ዹሚል ዚተቀሚጞበት ጜሑፍ ያለው እንደሆነ ዚኢዚሩሳሌም ኀጲስቆጶስ ቅዱስ መቃርስ ነገራት፡፡ ኚእርሱም ምልለክት ታይ ዘንድ ወደደቜ፡፡ ዹሞተ ሰው አምጥታ በሁለቱ መስቀሎቜ ላይ በተራ ቢታስቀምጠው አልተነሣም፡፡ በመጚሚሻ ጜሕፈት ባለው በአንዱ መስቀል ላይ ቢታስቀምጠው ያንጊዜ ዹሞተው ሰው ተነሣ፡፡ በዚህም ዚጌታቜንን መስቀል ለዚቜው፡፡ ዕሌኒም ለጌታቜን መስቀል ሰገደቜለት፡፡ ክርስቲያኖቜ ሁሉ ሰገዱለት፡፡ በዚሀገሩ ያሉ ክርስትያኖቜ ሁሉ ዚመስቀሉን መገኘት በሰሙ ግዜ መብራት አብርተው ደስታ቞ውን በመግለጥ ለዓለም እንዲታወቅ አደሚጉ፡፡ በዚህም ምክንያት ይህ ታላቅ ዚድኅነት ምልክት ዹሆነው መስቀል ዚኢትዮጵያ ቀተክርስትያን ደመራ በመደመር በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ታኚብሚዋለቜ፡፡

ንግሥት ዕሌኒ መስኚሚም 16 ቀን 320 ዓ.ም በዕጣን ጢስ ምልክት ቁፋሮ አስጀምራ መጋቢት 10 ቀን አግኝታ በማውጣት ታላቅ ቀተ መቅደስ ጎልጎታ ላይ ሠርታ በክብር አስቀመጠቜው፡፡ ጌታቜን ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለቅድስት ንግስት ዕሌኒ ቃልኪዳን ሲገባላት እንዲህ አላት፡- ‹‹በደሜ ዹኹበሹ ዚመስቀሌን ስም ዚሚጠራውን እርሱን እምሚዋለሁ፡፡ በዕፀ መስቀሌ ቀ/ክ ውስጥ ዹለመነውን ዹጾለዹውን ሰው መላእክት እንኳን ተድላ ደስታውን ወደማያውቁት ወደ መንግሥተ ሰማያት አዳራሜ ያለወቀሳ ይገባል፡፡ ለኹበሹ መስቀሌ ኚቅርብም ኚሩቅም ወደ ቀተ ክርስቲያኑ ተጉዞ ዚመጣውን ወደ መቃብሬ ኢዚሩሳሌም እንደጓዘ እኔ አደርግለታለሁ፡፡ ይህንንም መጜሐፍ ዚጻፈ ያጻፈ ወይም ያነበበውን ዹተሹጎመውን ቃሉን በዕዝነ ልቡና ዹሰማውን ዚመጜሐፉንም ገበታዎቹን ዚሳመውን በተጞለዚበት ውኃም ዹተጠመቀውን እኔ በሕይወት መጜሐፍ በዓምደ ወርቅ ላይ በወርቅ ቀለም ስሙን እጜፈዋለሁ፡፡›› (ድርሳነ መስቀል)

ዚጌታቜንን ቅዱስ መስቀል ንግሥት ዕሌኒ መጋቢት 10 ቀን አግኝታ በማውጣት ታላቅ ቀተ መቅደስ ጎልጎታ ላይ ሠርታ በክብር ካስቀመጠቜው በኋላ ኚዚያ ዕለት ጀምሮ እንደ ፀሐይ እያበራ ድውይ እዚፈወሰ አጋንንት እያባሚሚ ልዩ ልዩ ገቢሚ ተአምራት እዚሠራ ሙት እያነሣ ዕውር እያበራ ተአምራቱን ቀጠለ፡፡ ይህንንም ዹሰማው ኚኃያላን ነገሥታት መካኚል ዚፋርስ ንጉሥ መስቀሉን ማርኮ ፋርስ ወስዶ አስቀመጠው፡፡ ነገር ግን ንጉሡ ሕርቃል ዚጌታቜንን ቅዱስ መስቀል አስመልሶታል፡፡ በዚህ ጊዜ ዚኢዚሩሳሌም ምእመናን ዚድሉን ዜና ሰምተው ስለነበር ዚአንድ ቀን መንገድ ያህል ሄደው በመቀበል ካህናቱ በዝማሬና በእልልታ ቜቊ አብርተው ተቀብለዋ቞ዋል፡፡

ዚቀተክርስቲያን አባቶቜ እንደሚሉት ንጉሡ ሕርቃል ይህንን ታላቅ ድል ለማግኘትና ዚጌታን ቅዱስ መስቀል ኚአሕዛብ (ኚፋርሶቜ) እጅ ለማስመለስ ዚቻለው በዚያን ጊዜ አብያተ ክርስቲያንናት ሁሉ ለአንድ ሳምንት (አንድ ሱባዔ) ባደሚጉት ጟም ጞሎት ነው፡፡ ይህንንም ለማስታወስና ጌታን ለማመስገን ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያንና ዚግብጜ ኮፕቲክ ቀተ ክርስቲያን በዚዓመቱ ዚዐቢይ ጟም ኚመጀመሩ አስቀድሞ "ጟመ ሕርቃል" ብለው አንድ ሳምንት ይጟማሉ፡፡ ዚጌታ መስቀል ለብዙ ጊዜያት ኢዚሩሳሌም ኹቆዹ በኋላ ነገሥታት ‹‹ይህን መስቀል እኔ ልውሰድ፣ እኔ ልውሰድ›› በማለት ጠብ ፈጠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ ዚአንጟኪያ፣ ዚኀፌሶን፣ ዚአርማንያ፣ ዚግሪክ፣ ዚእስክንድርያ፣ ዚመሳሰሉት ዚሃይማኖት መሪዎቜ ጠቡን አበሚዱት፡፡ ኚዚያም አያይዘው በኢዚሩሳሌም ዹሚገኘውን ዚክርስቶስን መስቀል ኚአራት ኹፍለው በዕጣ አድርገው በስምምነት ተካፍለው ኚሌሎቜ ታሪካዊ ንዋያተ ቅዱሳት ጋር በዚሀገራ቞ው ወስደው በክብር አስቀመጡት፡፡ ዹቀኝ ክንፉ ዹደሹሰው ለአፍሪቃ ስለነበር ኚታሪካዊ ንዋዹ ቅዱሳት ጋር በግብጜ ዹሚገኘው ዚእስክንድርያ ፓትርያርክ ተሹክቩ ወስዶ በክብር አስቀመጠው፡፡ ግማደ መስቀሉ ለብዙ ዘመን በእስክንድርያ ሲኖር በግብጜ ያሉ እስላሞቜ እዚበዙ ኃይላቾው እዚጠነኚሚ ሲሔድ በእስክንድርያ ዚሚኖሩ ክርስትያኖቜ ላይ ሥቃይ ያጞኑባ቞ው ጀመር፡፡ ክርስቲያኖቹም አንድ ሆነው መክሹው ለኢትዮጵያዊው ዓጌ ዳዊት እንዲህ ዹሚል መልእክት ላኩ "ንጉሥ ሆይ! በዚህ በግብጜ ያሉ እስላሞቜ መኚራ አጜንተውብናልና ኃይልህን አንሥተህ አስታግስልን" ብለው ጠዚቁት ዳግማዊ ዐጌ ዳዊትም ለመንፈሳዊ ሃይማኖት ቀንተው ዚክርስቶስ ፍቅር አስገድዷ቞ው 20,000 ሠራዊት አስኚትለው ወደ ግብጜ ዘመቱ በዚህ ጊዜ በግብጜ ያሉ ኃያላን ፈሩ ተሞበሩ፡፡ ንጉሡ ዳግማዊ ዳዊትም እንዲህ ዹሚል መልዕክት ለእስላሞቹ ላኚ፡- "በተፈጥሮ ወንድሞቻቜሁ
†✝† እንኳን ለታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደሚሳቜሁፀ አደሚሰን። †✝†

†✝† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †✝†

†✝† ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ †✝†

†✝† ቅዱስ ያሬድ:- ኚእግዚአብሔር ያገኘነው አባታቜን : ክብራቜን : ሞገሳቜን ነውና በምን እንመስለዋለን?
*አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም)::
*ልቡናው ዚቅድስና ማሕደር::
*ሕሊናው ዚምሥጢራት ሠሹገላ ነው::
*እስኚ አርያም ተነጥቆ ዹማይፈጾም ምሥጢርን ዹተመገበ ማን እንደርሱ!

ሊቀ ሊቃውንት እዝራ ሐዲስ እንደሚሉት:- "ቅዱስ ያሬድ ለኢትዮዜያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ኚራስ ጞጉሯ እስኚ እግር ጥፍሯ : ሙሉ አካሏ ነው::"

††† ዹሊቁ ዜና ሕይወት በጥቂቱ †††

††† ቅዱስ ያሬድ ዹተወለደው በ505 ዓ/ም አክሱም አካባቢ ሲሆን እናቱ ክርስቲና (ታኡክልያ) አባቱ ደግሞ ይስሐቅ (አብድዩ) ይባላሉ:: ሊቁ በሕጻንነቱ ምሥጢር (ትምሕርት) አልገባው ብሎ ይቾገር ነበር:: ትምሕርት እንቢ ያለው ሰነፍ ስለ ነበር አይደለም:: በጥበበ እግዚአብሔር እንጂ::

ምን ትምሕርት ባይገባው ጟምና ጞሎትን ያዘወትር ነበር:: ልቡናው ደግሞ በእመቀታቜንና በልጇ ፍቅር ዚታሠሚ ነበር:: አንድ ቀን ግን መምሕሩ ዚነገሩት ቀለም አልያዝሕ አለው:: ሲፈትኑትም ባለመመለሱ ተገሹፈ::

ዱላው በጣም ስለ ተሰማው ቅዱሱ ኚመምሕሩ ኮብልሎ ማይ ኪራሕ አካባቢ ሲደርስ ደክሞት አርፎ እግዚአብሔር ትጋትንና ተስፋ አለመቁሚጥን ኚትል አስተማሚው:: ትሏ ስድስት ጊዜ ወድቃ በሰባተኛው ፍሬዋን ስትበላት ተመልክቷልና::

ኹዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ መምሕሩ ተመልሶ : ይቅርታ ጠይቆ ትምሕርት ጀመሹ:: ሊቁም ትጋትንና ጞሎትን ኚሰጊድ ጋር አበዛ:: እግዚአብሔር ደግሞ በድንግል እናቱ አማካኝነት ዚምሥጢር ጜዋን አጠጣው::

ካህኑ ያሬድ እንዲያ አልገባህ ያለው ምስጢር ተገልጊለት በጥቂት ጊዜ ብሉይ ኚሐዲስ ወሰነ:: በምሥጢር ባሕርም ይዋኝ ጀመር::

ያን ጊዜ ሰማያዊ ዜማ አልተገለጠም ነበርና በጞሎት ላይ ሳለ ተደሞ መጣበት:: ሊስት መላእክት በሊስት ወፎቜ አምሳል መጥተው አነጋገሩት:: ድንገትም ነጥቀው ወደ ሰማያት : ወደ ልዑላኑ መላእክት ዘንድ አደሚሱት:: ሊቁ በሰማያት ልዩ ምሥጢር : ልዩ ምስጋናና ልዩ ዜማን አዳመጠ:: ይሕንን ምስጋና ብዙ ቅዱሳን ቢሰሙትም ቅዱስ ያሬድ ግን ይዞት እንዲወርድ ተፈቀደለት::

ሊቁ ወደ ምድር ተመልሶ በታላቅ ተመስጊ አክሱም ጜዮን ውስጥ በሃሌታ አመሰገነ:: ሕዝቡና ንጉሡም ኚጣዕሙ ዚተነሳ አደነቁ:: ቅዱስ ያሬድ ለተወሰነ ጊዜ በአክሱምና ደብሚ ዳሞ ሲያገለግል ቆይቶ : ኚመሬት ክንድ ኚስንዝር ኹፍ ብሎ ለእመቀታቜን አንቀጾ ብርሃንን ደርሶላት ኚሃገሩ ወጣ::

††† ቅዱስ ያሬድ በቀሪ ዚሕይወቱ ዘመናት:-
1. አምስት ያሕል መጻሕፍትን ጜፏል::
2. በጣና ቂርቆስ : በዙር አባና በሌሎቜም ቊታዎቜ ወንበር ዘርግቶ ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርቷል::
3.በሰሜን ተራሮቜ አካባቢ በትጋሃ መላእክትና በተባሕትዎ ኑሯል::

††† በ576 (571) ዓ/ም በተወለደ በ71 ዓመቱ በዚህቜ ቀን ተሰውሯል::

††† አባቶቻቜን:-
*ጥዑመ ልሳን
*ንሕብ
*ሊቀ ሊቃውንት
*ዚሱራፌል አምሳያ
*ዚቀተ ክርስቲያን እንዚራ
*ካህነ ስብሐት
*መዘምር ዘበድርሳን
*ማኅሌታይ
*ልዑለ ስብኚት
እያሉ ይጠሩታል::

††† ዚቅዱሱ ጞሎትና በሚኚት ሃገራቜንን ኹክፉው ሁሉ ይጠብቅልን::

††† ግንቊት 11 ቀን ዚሚኚበሩ ዓመታዊ ዚቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ያሬድ ካህን ወማኅሌታይ
2.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
3.ቅዱሳን ክርስቲናና ይስሐቅ (ዚቅዱስ ያሬድ ወላጆቜ)
4.ቅድስት ታውክልያ እናታቜን (ንግሥናን ንቃ ሰማዕት ዚሆነቜ)
5.ቅድስት ኀፎምያ ሰማዕት
6.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
7.ቅድስት አናሲማ ገዳማዊት
8.አባ በፍኑትዮስ ገዳማዊ
9.አባ አሮር ሰማዕት (ኢትዮዜያዊ)
10.አባ በኪሞስ ጻድቅ

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ገላውዎዎስ ሰማዕት
2.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
3.ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና

††† "እንዲህ ያለው ሰው ኚአሥራ አራት ዓመት በፊት እስኚ ሊስተኛው ሰማይ ድሚስ ተነጠቀ:: እንዲህ ያለውንም ሰው አውቃለሁ:: በሥጋ እንደ ሆነ ወይም ያለ ሥጋ እንደሆነ አላውቅም:: እግዚአብሔር ያውቃል:: ወደ ገነት ተነጠቀ:: ሰውም ሊናገር ዚማይገባውን: ዹማይነገሹውን ቃል ሰማ::" †††
(2ቆሮ. 12:2-5)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ግንቊት 11-ዚቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ዹሆነ ዚሱራፌል አምሳላ቞ው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ዚተሰወሚበት ዕለት ነው፡፡
+ ዚዓባይን ወንዝ በጞሎታ቞ው ገዝተው ያቆሙትና መልአኩ ቅዱስ ገብርኀል ግዝታ቞ውን እንዲፈቱ ዚነገራ቞ው ዚውቅሮው አቡነ ኀልያስ ዕሚፍታ቞ው ነው፡፡
+ ዚባሌው አቡነ አሮር በሰማዕትነት ዐሚፉ፡፡
+ ዚታላቁ ሰማዕት ዚቅዱስ ዮስጊስ ሚስት ቅድስት ታውክልያ በሰማዕትነት ዐሚፈቜ፡፡
+ ቅድስት ዚሆነቜ መነኩሎ ሆና ሳለ እርሷ ግን ራሷን እብድ አስመስላ ዚኖሚቜው ቅድስት አናሲማ ዕሚፍቷ ነው፡፡ ምሥጢሯንም ለአባ ዳንኀል ነግራዋለቜ፡፡
+ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ሰማዕትነቷን በድል ዚፈጞመቜ ቅድስት ኀፎምያ ዕሚፍቷ ነው፡፡
+ ዚኀስድሮስ እናት ቅድስት ሶፍያና እኅቱ ቅድስት ኀፎምያ በሰማዕትነት እንዳሚፉ ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳ቞ዋል፡፡
+ ኀጲስቆጶስ አባ በፍኑትዮስ ዕሚፍቱ ነው፡፡
+ አባ በኪሞስና አባ አብላዲን መታሰቢያ በዓላቾው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳ቞ዋል፡፡

ቅድስት አናሲማ፡- ይኜቜም ቅድስት በደናግል ገዳም መንኩሳ በታላቅ ተጋድሎ ዚምትኖር ስትሆን እርሷ ግን ራሷን ዕብድ አስመስላ ኖሚቜ፡፡ በሌሊትም በጟምና በጞሎት ሥጋዋን በመቅጣት ራሷን ታሠቃያለቜ፡፡ ሰዎቜም በሚያዩዋት ጊዜ አእምሮዋን ያጣቜ እንደሆነቜ ታስመስላለቜ፡፡ መበለቶቜም ይሰድቧታል፡፡ እጅግ ገድላኛው ዹሆነው ጻድቁ አባ ዳንኀል በአንዲት ዕለት ኹደናል ገዳም ደርሶ ደጁን አንኳኳ፡፡ እነርሱም ዹኹበሹ አባ ዳንኀል መሆኑን ዐውቀው ኚፈቱለት፡፡ ይኜቜም ቅድስት አናሲማ በዚያ ራሷን ዕብድ አስመስላ በደጅ ዚምትተኛ ሎት ነበሚቜ፡፡ ዹኹበሹ አባ ዳንኀልም ዕብድ መስላ በደጅ ስለተቀበጠቜው ቅድስት አናሲማ እመ ምኔቷን ሲጠይቃት እብድ መሆኗን ነገሚቜው፡፡ አባ ዳንኀል ግን ዕብድ ዚመሰለቻ቞ው አናሲማ እብድ ሳትሆን በድብቅ በታላቅ ተጋድሎ ዚምትኖር ዚኚበሚቜ ቅድስት መሆኗን ነገራት፡፡

ዕብድ መስላ ትኖር ነበሚቜውና በሁሉም ዘንድ ዕብድ ዚተባለቜው ቅድስት አናሲማም አባ ዳንኀል ምሥጢሯን እንደገለጠባት በጾጋ ዐውቃ ወዲያው ደብዳቀ ጜፋ ይኾውም ‹‹ዚተኚበራቜሁ እኅቶቌ ስላስቀዚምኳቜሁና ስላሳዘንኳቜሁ ይቅር በሉኝ›› ብላ ጜፋ ደብዳቀውን አስቀምጣ ኚንቱ ውዳሎን በመሞሜ ጥላ቞ው ጠፋቜ፡፡ እነርሱም ኚዚያ በኋላ ዳግመኛ አላዩአትም፡፡ ቅድስት አናሲማም በዚያው በበሹሃ ሳለቜ በዚህቜ ዕለት በሰላም ዐሚፈቜ፡፡ ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን፣ በጞሎቷ ይማሚን፡፡
+ + + + +

ሰማዕቱ አቡነ አሮር ዘባሌ፡- ልደቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡ እርሱም በደብሚ ሊባኖስ ዚመጻሕፍት መምህር ሆኖ ሳለ ዹበቃ ጻድቅ መሆኑ ቢታወቅበት ወደ ሐይቅ ሄዶ በተጋድሎ ዹኖሹ ሲሆን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተመርጩ በባሌ ሀገር ላይ ዚተሟመ ነው፡፡ በኋላም ወደ ኢዚሩሳሌምና ግብፅ ሄዶ ኹመናፍቃን ጋር ሲኚራኚር ኚሃዲዎቜ በእሳት አቃጥለውት በመጚሚሻም አንገቱን ሰይፈውት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ አካሉንም በእሳት አቃጥለውት ኚጣሉት በኋላ በደብሚ ቁስቋም ተቀብሯል፡፡ ስንክሳሩ ግን ‹‹በኢዚሩሳሌም መግቢያ በእሳት አቃጠሉት›› ብሎ ይገልጞዋል፡፡ ሚድኀት በሚኚቱ ይደርብን፣ በጞሎቱ ይማሚን፡፡
+ + + + +

ሰማዕቷ ቅድስት ኀፎምያ፡- እናቷ ቎ዎድርስያኒ ጌታቜንን በማመን ዚጞናቜ ደገኛ ክርስቲያን ናት፡፡ ልጇን ቅድስት ኀፎምያንም እግዚአብሔርን በመፍራት በሃይማኖት በምግባር አሳደገቻት፡፡
በወቅቱም ሰይጣን ኚሃዲውን አንቲሂጳጊስን አስነሣውና በክርስቲያኖቜ ላይ ታላቅ መኚራን አመጣ፡፡ ቅድስት ኀፎምያን ኚብዙ ክርስቲያኖቜ ጋር አሥሮ አመጣትና <ለአማልክት ስገጂ መሥዋዕትም አቅርቢ> አላት፡፡ እርሷም <ኚክርስቶስ በቀር ዚሚገዙለት አምላክ ዚለም፣ ለሚኚሱ አማልክቶቜህ አልሠዋም ይልቁንም ዚአባቶቌን ተስፋ ለማግኘት ልቀ ዹጾና ነው> አለቜው፡፡

በዚህም ጊዜ ሃዲው አንቲሂጳጊስ እጅግ ተቆጥቶ አጥንቶቿ እንዲሰባበሩ ሕዋሳቶቿም እንዲቆራሚጡ መንኮራኩር ውስጥ ጚመራት፡፡ ነገር ግን ዚታዘዘ መልአክ መጥቶ አዳናት፡፡ ዳግመኛም ነበልባሉ 45 ክንድ ኹፍ ብሎ እስኪታይ ድሚስ እሳት አንድደው ኚእሳቱ ውስጥ ጚመሯት፡፡ ኚእሳቱም መካኚል ቆማ ኚጞለዚቜ በኃላ ምንም ጉዳት ሳያገኛት ደህና ሆና ወጣቜ፡፡ ይኜንንም ታላቅ ተአምር ያዩ ሁሉ በጌታቜን አምነው በሰማዕትነት ዐሚፉ፡፡

ቅድስት ኀፎምያን ግን በማግሥቱ ወደ ሾንጎ አውጥተው አራት ትላልቅ ድንጋዮቜን በላይዩዋ ላይ አሥሚው ሥጋዋን ገፈው ካሠቃዩአት ዳግመኛ አራዊት ካሉበት ኩሬ ውስጥ ጚመሯት፡፡ ነገር ግን አራዊቶቹ ተሾክመው አውጥተው ኹውሃው ዳር በክብር አስቀመጧት፡፡ ዳግመኛም ስለቶቜን በመሬት ላይ ተክለው ቅድስት ኀፎምያን በዚያ ላይ እንድትሄድ በማድሚግ አሠቃዩአት፡፡ ደግሞም በእሳት ላይ በተጣደ ብሚት ምጣድ ውስጥ ጚመሯት፡፡ በመኚራዎቿም ሁሉ ጌታቜን ያጞናትና ዚበሚታት ነበር፡፡
መኮንኑም ለተራቡ አንበሶቜ ቢሰጣትም አንበሶቹ ግን ወድቀው እግሯን ላሱ፡፡ አንዲት አውሬ ግን እዚተሞበሚቜ መጥታ ዚቅድስት ኀፎምያን እግሯን ነኚሰቻት፡፡ እግዚአብሔርም ዚሰማዕትነቷ ፍጻሜ በዚህ እንዲሆን መልካም ፈቃዱ ሆነ፡፡ ኹሰማይም <ዚተመሰገንሜ ኀፎምያ ሆይ! ወጥተሜ ወደኹበሹ ቊታ ነይ> ዹሚል ድምጜ ተሰማ፡፡ ዚቅድስት ኀፎምያ ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን፣ በጞሎቷ ይማሚን፡፡
+ + + + +

አባ በፍኑትዮስ፡- ይኜም ቅዱስ በአባ መቃርስ ደብር በአስቄጥስ ገዳም መንኩሶ በታላቅ ተጋድሎ ኖሚ፡፡ ብዙ ትሩፋትንም ሠራ፡፡ እርሱም ቅጠልን ይመገባል እንጂ በእሳት ዹበሰለ እህል ተመግቩ አያውቅም፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንም ተምሮ ኹጹሹሰ በኋላ ቅስና ተሟመ፡፡ በጜድቁና በተጋድሎውም በሁሉ ዘንድ ዚታወቀ ሆነ፡፡ ሊቀጳጳሳቱ አባ ፊላታዎስም መልእክተኛ ልኮ ኚገዳም አስመጥቶት ኀጲስቆጶስነት ሟመው፡፡ አባ በፍኑትዮስ ኀጲስቆጶስነት ኚተሟመ በኋላ ቅዳሎ ለመቀደስ ሲል ልብሱን ይለውጣል እንጂ ኹጠጉር ዚተሠራ ማቅ በቀር ሌላ ልብስ አይለብስም ነበር፡፡ በታላቅ ተጋድሎውና በአገልግሎቱ ዹጾና ሆነ፡፡ በዘመኑም ሁሉ ኚመነኮሳት ጋር ያገለግል ነበር፡፡ በታመመም ጊዜ እግዚአብሔርን እንዲህ ብሎ ለመነው፡- ‹‹ዚክብር ባለቀት ጌታዬ ኢዚሱስ ክርስቶስ ሆይ! ኀጲስቆጶስነት ስለተሟምሁ ጾጋህን በውኑ ኚእኔ ታርቃለህን?›› በዚህም ጊዜ ኚእግዚአብሔር ዚታዘዘ መልአክ ወደ አባ በፍኑትዮስ ዘንድ መጥቶ ‹‹አስተውል፣ ዕወቅ፡፡ አንተ በገዳም ሳለህ በታመምክ ጊዜ ዹሚጎበኝህ ዚለም፣ ዚሚያገለግልህና ለደዌህ መድኃኒትን ዚሚሰጥህ አታገኝም ነበር፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ዚሚሚዳህና ደዌውንም ኹአንተ ዚሚያርቅልህ ሆነ፡፡ ዛሬ ግን እነሆ አንተ በዓለም ውስጥ ነህ፣ በአንተ ዘንድ ዹሚጎበኝህና ዚሚያገለግልህ አለፀ ለደዌህም መድኃኒትን ዚምትሻውንም ምግብ ታገኛለህ›› አለው፡፡
ይኜም ቅዱስ ኀጲስቆጶስነት ተሹሞ 32 ዓመት በቅድስና ሲያገለግል ኹኖሹ በኃላ ዚሚያርፍበት ጊዜ ሲደርስ አገልጋዮቜን በሙሉ ጠርቶ ንዋዹ ቅድሳታ቞ውን ሰጣ቞ውና "እኔ ወደ እግዚአብሔር እሄዳለሁና እስኚመጚሚሻው ድሚስ በቀናቜ ሃይማኖት ጜኑ" ብሎ ኚመኚራ቞ው በኃላ በሰላም ዐሚፈ፡፡ ሚድኀት በሚኚቱ ይደርብን፣ በጞሎቱ ይማሚን፡፡
+ + + + +
አቡነ ኀልያስ ዘውቅሮ፡- አቡነ ኀልያስ ዘውቅሮ ዚትውልድ ሀገራ቞ው አክሱም ነው፡፡ ዚአቡነ አሹጋዊ 3ኛ ዚቆብ ልጅ ና቞ው፡፡ አባታ቞ው ውቅሮ ዹሚገኘው ዚጥንታዊው ዚአብርሃ ወአጜብሓ ቀተ መቅደስ አጣኝ ነበሩ፡፡ ይህ ጻድቅ ዚሚታወቁበት አንድ ትልቅ ገድል አላ቞ው፡፡ በቀን 548 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን እዚጞለዩ 666 ጊዜ ይሰግዱ ነበር፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዓባይ ዚሀገራቜንን አፈርና ዛፉን ሁሉ ጠራርጎ ሲወስድ ቢመለኚት ድምጹን ኹፍ አድርጎ ኩ አባይ አይቮ ተሐውር ወለመኑ ተሐዲጋ ለኢትዮጵያ ብሎ ሲዘምር ዓባይ ቀጥ ብሎ ቆሟል፡፡ መልአኩም ወዲያው መጥቶ ‹‹ለምን ትደክማለህ? ለምንስ ተፈጥሮን ትኚለክላለህ? ሕጉን አታፍርስ›› ሲለው ቅዱስ ያሬድ ደንጎጩ ‹‹አጥፍቻለሁ ዓባይ ሆይ ሂድ ዚተፈጥሮ ግዎታህን ፈጜም›› ብሎ አሰናብቶታል፡፡ ዚኢትዮጵያ ብርሃኗ ቅዱስ ያሬድ በዜማው ዓባይን ቀጥ አድርጎ እንዳቆመው ሁሉ አቡነ ኀልያስ ዘውቅሮም በጞሎታ቞ው ዓባይን ኚኢትዮጵያ እንዳይወጣ አድርገውት ነበር፡፡
ታቊተ አብርሃ ወአጜብሓን ይዘው ኚኢትዮጵያ ጠሹፍ ዳር ኑብያ ሄደው ድንጋይ ኚዓባይ ዳር ደርድሚው ታቊቱን አስቀምጠው ሥዕለ ማርያምን አድርገው መሥዋዕት ሰውተው ‹‹ዓባይ ኚኢትዮጵያ እንዳትወጣ ገዝቌሃለሁ›› ሲሉት ዓባይም ተመልሶ ቆሟል፡፡ ዓባይ ምድሚ ኑብያን ሲያጥለቀልቃት መልአኩ ቅዱስ ገብርኀል ተገልጟ ‹‹ለምን ዚእግዚአብሔርን ስነ ፍጥሚት ታስጚንቃለህ?›› ብሎ ተቆጣ቞ው፡፡ ጻድቁም ‹‹ውኃው ይሂድ ግን ዛፉን አፈሩን ይዞ ኚኢትዮጵያ አይውጣ›› ብለው መልአኩን ጠዚቁት፡፡ ቅዱስ ገብርኀልም ‹‹ውኃ ሲሞላ ዛፉን ቅጠሉን ይዞ መጓዙን እንዎት ትሚሳዋለህ? ዚጞሎት ጊዜህ ደርሷልና ወደ በዓትህ ተመለስ›› ብሎ በቁጣ ዚእሳት ሰይፉን ሲያዛ቞ው ግዝታ቞ውን አንሥተው ታቊታ቞ውን ይዘው ወደ በዓታ቞ው ውቅሮ ተመልሰዋል፡፡ አባቶቻቜን እንዲህ ናቾው እንኳን ሃይማኖት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስ፣ ስብዕና ማንነታቜንን ይቅርና ዚሀገራቜንን አፈር እንኳን ለባዕድ አሳልፈው ዚማይሰጡ ቅዱሳን ጻድቃን ነበሩ፡፡ ዚአባ ኀልያስ ሚድኀት በሚኚታ቞ው ይደርብን፣ በጞሎታ቞ው ይማሚን፡፡
+ + + + +

ሰማዕቷ ቅድስት ታውክልያ፡- ታላቁ ዚአንጟኪያ ንጉሥ ኑማርያኖስ በጊርነት ውስጥ በሞተ ጊዜ ልጁ ቅዱስ ዮስጊስም በሌላ ቊታ ጊርነቱን አሾንፎ በድል ወደ ቀተ መንግሥት በተመለሰ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ጌታቜንን ክዶ ጣዖታትን ሲያመልክ ቢያገኘው እጅግ አዝኖ ሰማዕት ይሆን ዘንድ ተመኘ፡፡ ዚሀገሩም ሰዎቜ ወደ ዮስጊስ ዘንድ ቀርበው ‹‹እኛ ዲዮቅልጥያኖስን እንገድለዋለን አንተ በአባትህ ዙፋን ተቀመጥ›› አሉት፡፡ እርሱ ግን ኚምድራዊው መንግሥት ይልቅ ሰማያዊውን መንግሥት መርጧልና እሺ አላላ቞ውም፡፡ በጌታቜንም ስም ሰማዕት ይሆን ዘንድ መሚጠ፡፡ በንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስም ዘንድ ቀርቩ ስለ ጌታቜን ክብር መሰኚሚ፡፡ ንጉሡም ገና ሲያዚው እጅግ ፈርቶና ደንግጩ ‹‹ጌታዬ ዮስጊስ ሆይ! ይህን ታደርግ ዘንድ ያስገደደህ ማነው?›› አለው፡፡ ዮስጊስም ንጉሡን ‹‹በምስክርነ቎ ደሜን እንዳፈስ ካልጻፍክ ሕዝቡን በአንተ ላይ አስነስቌ ኚመንግሥትህ እንደማስወጣህ በጌታዬ በኢዚሱስ ክርስቶስ ስም እምልልሃለሁ›› አለው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም እዚፈራ ዚዮስጊስን ፈቃድ ይፈጜምለት ዘንድ ኚሚስቱ ኚታውክልያና ኹልጁ ኹአቩሊ ጋር ወደ ግብፅ እንዲወስዷ቞ው አዘዘ፡፡ እንዲያባብለውም ለእስክንድርያው መኮንን ጻፈለት፡፡ ዚእስክንድርያውም ገዥ እጅግ ፈርቶ ዮስጊስን ‹‹ጌታዬ ዮስጊስ ሆይ! እንዲህ አታድርግ ለአንተ ክብርህ ይሻልሃል ›› እያለ ሊያግባባው ሲሞክር ቅዱስ ዮስጊስ ግን ‹‹ዚመንግሥትህን ክብር እንዳታጣ ሰማዕትነ቎ን ፈጞምልኝ›› አለው፡፡ እርሱም ፈርቶ ወደ ላይኛው ግብፅ ወደ እንዎናው ገዥ ላኚው፡፡ ኚአገልጋዮቜ ጋራ ሚስቱን ቅድስት ታውክልያን ፃ ወደምትባል አገር ሲልካት ልጁን አቩሊን ደግም ወደ ሀገሹ ብስጣ ላኚው፡፡ ኚአገልጋዮቹም ውስጥ እንዲያገለግሏ቞ው በማለት አንድ አንድ ሰጣ቞ው፡፡

ዹሀገሹ ፃ መኮንንም ዚእስክንድርያው መኮንን ዚጻፈለትን ባነበበ ጊዜ መንግሥታ቞ውን ትተው መኚራን ለመቀበል መምሚጣ቞ውን አደነቀ፡፡ ቅድስት ታውክልያንም በማባበል ብዙ ቃልኪዳኖቜ ገባላት፡፡ እርሷም ‹‹ስለ ጌታዬ ኢዚሱስ ክርስቶስ ፍቅር መንግሥ቎ን ተውኩ፣ በመኚራም ሆኜ ኚልጅነት ባሌም ተለዚሁ፣ በልጆቌም አልተጜናናሁም፡፡ ለመሆኑ አንተ ዚምትሰጠኝ ስጊታ ምን ያህል ነው?›› አለቜው፡፡ መኮንኑም ቅድስት ታውክልያን በማባበል ለጣዖታት እንድትገዛ ለማድሚግ እንዳልቻለ ሲያውቅ ይዞ ብዙ በማሠቃዚት ሥጋዋ እስኪቆራሚጥ ድሚስ አስገሚፋት፡፡ በእሥር ቀትም ሳለቜ ዚታዘዘ መልአክ ተገለጠላትና ኚቁስሏ ፈወሳት፡፡ እስሚኞቜም በእርሷ ላይ ዹተፈጾመውን ተአምር አይተው ብዙዎቜ በጌታቜን አምነው ሰማዕት ሆኑ፡፡ ዳግመኛም መልአኩ ለቅድስት ታውክልያ ተገልጊላት ትቀበለው ዘንድ ያላትን ተስፋና ቃልኪዳን ኚነገራት በኋላ ሰማዕትነቷን በትዕግስት እንድትፈጜም አጜናናት፡፡ መኮንኑም ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ቅድስት ታውክልያ ሰማዕትነቷን በድል ፈጜማ ዚክብር አክሊልን ተቀዳጀቜ፡፡ ምእመናንም ለወታደሮቜ ገንዘብ ኹፍለው ቅዱስ ሥጋዋን ወስደው ዚመኚራው ወራት እስኪፈጞም ድሚስ በሣጥን ውስጥ አኖሯት፡፡ ዚቅድስት ታውክልያ ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን፣ በጞሎቷ ይማሚን፡፡
+ + + + +

ዚሱራፌል አምሳላ቞ው ዹሆነ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ፡- ዚቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ዹሆነ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ በ571 ዓ.ም በዚህቜ ዕለት እንደ ሄኖክና ኀልያስ ተሰወሚ፡፡ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ዹሆነ ዚሱራፌል አምሳላ቞ው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ዚተሰወሚበት ዕለት ነው፡፡ እርሱንም 24ቱ ካህናተ ሰማይ ያመሰገኑት ሲሆን መቋሚያውን ወርውሮ ያፈለቀው ፀበል ዛሬም ተአምራት እያደሚገ አለ፡፡ ቅዱሱ ዓባይን በጥዑም ዜማው ቢያቆመው መልአክ መጥቶ ተቆጥቶታል፡፡ በተሰወሚበት በሰሜን ጠለምት ደብሚ ሐዊ ተራራ ላይ በቊታው እሁድ እሁድ ኚመሬት ውስጥ ዚኚበሮ ድንፅ ይሰማል፡፡
ዚቅዱስ ያሬድን ዕሚፍት በተመለኹተ አንዳንድ ጞሐፍት አባቶቜ በሞት እንዳሚፈ ጜፈዋልፀ ስንክሳሩም ‹‹ዐሚፈ›› ይለዋል፡፡ ነገር ግን ጻድቁ በተሰወሚበት በደብሚ ሐዊ ተራራ ላይ ብርድ በእጅጉ በጞናበትና በሚዶ በሚፈላበት በዚያ አስ቞ጋሪ ቊታ ላይ እጅግ አስ቞ጋሪውን ዹአዹር ጠባይ ተቋቁሞ በቊታው ላይ ቢያንስ 7 ቀን ሱባዔ ዹሚይዝ ካለ ራሱ ቅዱስ ያሬድ እንደሚገለጥለት ይታወቃል፡፡ እንኳንስ ቅዱስ ያሬድ ይቅርና እርሱን ያገለገሉት አቡነ ጊዮርጊስ ዘመንበር ዚተባሉት አባትም ሞትን ሳያዩ ተሰውሚዋል፡፡ አቡነ ጊዮርጊስ ዘመንበሹ ኢትዮጵያ ዚተባሉት ጻድቅ ሀገራ቞ው ጎጃም ሲሆን ዚአባትና ዚእናታ቞ው ሀገር ግን ሰሜን ጎንደር ና቞ው፡፡ ሲወለዱ መልአክ መጥቶ ወስዶ 24ቱ ካህናተ ሰማይን አሳይቶ ቅዱስ ያሬድም ሲዘምር ጥዑም ዜማውን አሰምቷ቞ዋል፡፡ ዚቅዱስ ያሬድም ፍቅር በዚያው ልባ቞ው ተቀርጟ ቀሚ፡፡ ጻድቁ ዋሞራ ገዳም ሁሉንም ተምሹው ጹርሰው በ25 ዓመታ቞ው ኚመነኮሱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በቅዱስ ያሬድ ስም ቀተ ክርስቲያን አሠርተዋል፡፡ ታቊቱንም አስገብተው በዚያው እያገለገሉ ሲኖሩ ‹‹እንደ ኀልያስና እንደ አንተ ሞትን እንዳላይ ለምንልኝ ›› እያሉ ቅዱስ ያሬድን ዘወትር ሲማፀኑት ቅዱስ ያሬድም አንድ ቀን ኚእነ አቡነ አሚጋዊ፣ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘርዐ ቡሩክ ዘግሜ ጋር በመሆን ተገልጩላቾው ‹‹አይዞህ ፈጣሪዬ ያልኚውን ያደርግልሃል›› ብሏ቞ዋል፡፡ አስደናቂውን ባለ ሊስት ዓምድ ዹሆነውን ዚቅዱስ ያሬድንም ገድል ዚጻፉት እሳ቞ው ነበሩ ነገር ግን ቅዱስ ገድሉን ደርቡሟቜ ኚወሰዱት በኋላ ዚት እንደደሚሰ አይታወቅም፡፡ ቅዱስ ገድሉም 382 ገጜ ያሉት ሲሆን 69 አስደናቂ ሥዕላት ነበሩት፣ በ132 ሐሚጎቜም ያሞበሚቀ ነበር፡፡ ጻድቁ ቅዱስ ያሬድን ‹‹እንደ አንተ እንዳልሞት ጞልይልኝ›› ብለው በለመኑት መሠሚት ራሱ ቅዱስ ያሬድ በተሰወሚበት ቊታ በሰሜን ተራራ ምድሚ ጞለምት ተሰውሚዋል፡፡ በስማ቞ው ዚተሠራው ቀተ ክርስቲያን በሰሜን ጎንደር ይገኛል፡፡

ቅዱሳን መላእክት ምስጋና቞ው እሚፍታ቞ው፣ እሚፍታ቞ው ምስጋና቞ው ሆኖ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ እግዚአብሔርን ያለማቋሚጥ ያመሰግናሉ፡፡ ቅድስት ቀተ ክስቲያንም አምሳለ ኢዚሩሳሌም ሰማያዊት ናትና ይህን አብነት በማድሚግ ልዑል እግዚአብሔር ሃያ አራት ሰዓት ዚሚመሰገንበትን ዚምስጋና ሥርዓት ዘርግታለቜ፡፡ ሕያው እግዚአብሔርም ዚአዳም ልጆቜ በመላእክት ምስጋና እንዲያመሰግኑት በመውደዱ ሰማያዊውን ምጋና ይማር ዘንድ ቅዱስ ያሬድን መሚጠ፡፡ ያሬድ ማለት መውሚድ ማለት ነው ፡፡ ሰማያዊውን ጣእመ ዜማ ወደ እኛ ዚሚያወርድ ነውና፡፡ ‹‹ዋይ ዜማ ዘሰማዕኩ እመላእክት ቅዱሳን-ኹሰማይ ኚቅዱሳን መላእክት ዚሚያስደንቅ ዜማ ሰማሁ›› በማለት እንደተናገሚ በአክሱም መጻሕፍትን እያስተማሚ ሳለ ኚሰማያውያን መላእክት ጣእመ ዜማን ተማሚ፡፡ በተመስጊ ወደ ኢዚሩሳሌም ሰማያዊት ተነጠቀ፡፡ በዚያም ቅዱሳን መላእክት ልዩ ጣእም ባለው ዹዜማ ድምፅ ሊያመሰግኑ ሲዘምሩና ሲያሞበሜቡ አዚ፡፡ ኚጣዕመ ዜማውም ዚተነሣ ተደነቀ፡፡ ዚእግዚአብሔርን ስም እርሱም ኢዚሱስ ክርስቶስን በጠራ ጊዜ ዚሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዜማ ተገለጞለት፡፡ ተመልሶም ወደ ምሥራቅ ዞሮ እጁንም ዘርግቶ ‹‹ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጜዮን ›› ብሎ በአክሱም ኹተማ ሙራደ ቃል (ዹቃል መውሹጃ) በተባለቜው ሥፍራ ለመጀመሪያ ጊዜ ዜማን በዐውደ ምሕሚት አሰማ፡፡

ቅዱስ ያሬድ በ505 ዓ.ም በአክሱም ኹተማ ተወለደ፡፡ አባቱ አብዩድ ወይም ይስሐቅ እናቱም ክርስቲና ወይም ታውክልያ ይባላሉ፡፡ ሀገራ቞ው አክሱም ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ በተወለደ በ7 ዓመቱ አባቱ ስለሞተ እናቱ ክርስቲና ዚአክሱም ገበዝ ለነበሹው ለአጎቱ ለጌዲዎን እንዲያሳድገውና እንዲያስተምሚው በአደራ ሰጠቜው፡፡ ኹጌዮዎንም ቀት 25 ዓመት እስኪሆነው እዚተማሚ አደገ፡፡ ኚዚያም መፃህፍትን ማለት ብሉይንና አዲስን ተማሚ፡፡ ኹዚህም በኋላ መምህሩና አጎቱ ጌዮዎን ሲሞት እርሱ ተተክቶ ዚመጜሐፍ መምህር ሆነ፡፡ በዚህም ጊዜ በዲቁና ሚስት አግብቶ ልጆቜን ወለደ፡፡ ቀጥሎም ቄስ ሆነ፡፡ በእርሱም ዘመን ዘጠኙ ቅዱሳን ኹውጭ አገር በቜግር ምክንያት ተሰደው ስለመጡፀ ይህም ማለት በቁስጥንጥንያ መንግሥት ዮስጥንያኖስ በነገሠበት ኹ527 ዓ.ም እስኚ 565 ዓ.ም ድሚስ በምሥራቅ ቀተ ክርስቲያን ውስጥ በአንድ ባሕርይና በሁለት ባሕርይ ወገኖቜ ውስጥ ብዙ ሁኚትና ፍጅት ስለነበሚ ኚዚያ በመሞሜ ዚመጡ ካህናትና መነኮሳት ስለነበሩ ኚእነርሱም አንዱ በአክሱም ኹተማ አጠገብ ዹነበሹው አባ ጰንጠሊዎን ስለነበርፀ ቅዱስ ያሬድ እዚተመላለሰ ዹውጭውን አገር ቀት ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ይጠይቀው ነበር፡፡ ኚዚያም በኋላ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ዚውጭውን አገር ቀተ ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ለመጎብኘት ሁለት ጊዜ ተመላልሌ ዚሮምን ቀተ ክርስቲያንፀ ሁለተኛይቱን ሮም ዚተባለቜውን ዚምሥራቅና ዚቁስጥንጥንያን ቀተ ክርስቲያን ጎበኘሁ›› ሲል በመዝሙሩ እርሱ ራሱ ገልጟልናል፡፡

ኚቅዱስ ያሬድ በፊት በኢትዮጵያ ቀተክርስቲያን ደንበኛ ዹሆነ ቅኔና ዜማ ትምህርት ስለሌለ ደንበኛ ዹሆነ ቅኔና ዜማ ለማስገኘት ተዘጋጀ፡፡ ዚድርሰቱም መጀመሪያ ይህ ነበር፡- ‹‹ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጜዮን ሰማዹ ሣሚሚ ወበዳግም አርአዮ ለሙሮ ዘኹመ ይገብር ግብራ ለደብተራ›› ብሎ ኚነበሩት ኚብሉይና ኚሐዲስ ሊቃውንት አንዱ እርሱ ስለ ነበርና ለኢትዮጵያ ቀተ ክርስቲያንም ብዙ አሳብ ስለነበሚው ኚብሉይና ኚሐዲስ፣ ኚሊቃውንት መጻሕፍትም ኚነአትና቎ዎስ ኚነቄርሎስ ኚነዮሐንስ አፈወርቅ መጻሕፍት ለምስጋናና ለጞሎት ዚተስማሙትን ቃላት እዚመሚጠና እያቀና በአራቱ ክፍለ ዘመን፣ በመፀውና በሐጋይ በጾደይና በክሚምት እንዲነገር አድርጎ ወስኖ አዘጋጀ፡፡ ዚድርሰቱ ስም ድጓ ተባለ፡፡ ድጓ ማለትም በአክሱምና በአድዋ ቋንቋ ደጉዓ ማለት መዝሙሹ ኃዘን፣ ዹኃዘን ዜማ፣ ማለት ነው፡፡ ዹዜማውን ዓይነት በሊስት ክፍል ወስኖ ተናግሮታል፡፡ እነርሱም ግዕዝ፣ ዕዝል፣ ዓራራይ ይባላሉ፡፡ ግዕዝ ማለትም አንደኛ በመጀመሪያ ዹተገኘ ማለት ነውፀ ዕዝል ማለትም ሁለተኛ ሆኖ ኹግዕዙ ጋር ተደርቊ፣ ተጚምሮ (ታዝሎ) ዹሚነገር ማለት ነው፡፡ ዓራራይ ማለትም ሊስተኛ ተጚማሪ ሆኖ አራኅራኂ፣ ርኅራኄ አሳዛኝ ልብን ዚሚመስጥና ደስ ዚሚያሰኝ ማለት ነው፡፡ ዐፄ ገብሚ መስቀልና አባ አሹጋዊ ቅዱስ ያሬድ እነዚህ ሊስቱ በአንድነት እንደነበሩ ታሪኚ ነገሥቱና ገድለ አቡነ አሹጋዊ ይገልጜልናል፡፡ አቡነ አሹጋዊ ዚደብሚ ዳሞን ተራራ አቀማመጥ አይተው ደስ ስላላ቞ው፣ ንጉሡ ዐፄ ገብሚ መስቀል በዚሁ ተራራ ላይ እንዲኖሩበትና እንዲጞልዩበት ፈቀደላ቞ው፡፡ እርሳ቞ውም ይህንን ተራራ ኚተሚኚቡ በኋላ በተራራው ላይ ዚጞሎት ቀት ስለሌለ ንጉሡ ዐፄ ገብሚ መስቀልን አንድ ቀተ ክርስቲያን እንዲሠራላ቞ው ለመኑት፡፡
ንጉሡም ‹‹ቀተ ክርስቲያን ልሠራ ዚምቜልበትን ሥፍራ መርጠው ያመልክቱኝ›› ብሎ ነገራ቞ው፡፡ አቡነ አሹጋዊም ተነሥተው ዞሹው ቊታውን መርጠው አሳዩት፡፡ ኹዚህ በኋላ ንጉሡ በአዋጅና በትዕዛዝ ድንጋዩና እንጚቱ እዚተሰበሰበ በኚብትና በሠሹገላ እዚተጋዘ ተሰበሰበና ኚታቜ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ተሠራና ዚቀተ ክርስቲያኑ ሥራ በሁለት ዓመት አለቀ፡፡ ባለቀም ጊዜ ዚቀተ ክርስቲያኑ ሥራ ተመልካ቟ቜን አስደነቀ፡፡ ለዚሁም ንጉሡ ቀተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ዹሆኑ አልባሳት፣ ዚብርና ዹወርቅ ዚተደጎሱና ዹተኹፈፉ መጻሕፍትን አበሚኚቱ፡፡ ኹማኅበሹ በኩር ዚመጣውን ዚእመቀታቜንን ዚቅድስት ድንግል ማርያምን ጜላት አግብተው አቡነ አሹጋዊ ባርኚውና ቀድሰው ንጉሡና ጳጳሱ ቆሚቡ፡፡ ኚዚያም ዐፄ ገብሚ መስቀል በተራራው ላይና በግርጌ ላሉት ሠራዊት ግብር አብልተው ነዳያን ሁሉ ጠገቡ፡፡ ኹዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም ሲያስተምር ሳለ በንጉሡ ዐፄ ገብሚመስቀልና አቡነ አሹጋዊ ወደዚህ ተራራ መጥቶ ቀተ ክርስቲያኑን እንዲጎበኝና እንዲዘምር ተጠርቶ ሲመጣ ኚተራራው ሥር ሲደርስ ዚአቡነ አሹጋዊን ደቀ መዛሙርት ማትያስና ዮሎፍ ዚሚባሉትን ኹወንዝ ዳር ዓሣ ሲያጠምዱ አግኝቶ ‹‹ይህ አሹጋዊ አባታቜሁ ደህና ነውን?›› ብሎ ጠዚቃ቞ው። እነርሱም ደኅንነታ቞ውን ነገሩት፡፡ ኚዚያም ቅዱስ ያሬድ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ኚአቡነ አሹጋዊ ጋር በመንፈሳዊ አምኃ በፍቅር ተገናኙ ወደ ቀተ ክርስቲያኑም ሄዶ 3 ጊዜ ሰግዶ ኚተሳለመ በኋላ ዚሕንጻውን ማማር በአድናቆት ተመልክቶ ኹፍ ባለ ዹዜማ ድምፅ ዘመሚ፡፡

ቅዱስ ያሬድ በደብሚ ዳሞ ኹዘመሹ በኋላ ስምንት ቀን ያህል ኚአቡነ አሹጋዊ ጋር ሰንብቶ ንጉሡ ወደ አለበት ወደ አክሱም ተመልሶ ሲገባ አንቀጾ ብርሃን ተብሎ ዹተሰዹመውን ድርሰትን ቅድስት ወብፅዕት ብሎ በዜማ ደሚሰ፡፡ ኹዚህ በኋላ ንጉሡ ዐፄ ገብሚ መስቀልና አቡነ አሹጋዊ ኚቅዱስ ያሬድ ጋር አብሚው ወደ ሌላ ጠቅላይ ግዛት ጉብኝት ሄዱ፡፡ ኚዚያም በአንዱ ደሎት ላይ ዚቅዱስ ቂርቆስን ቀተ ክርስቲያን ሠርተው ተቀመጡ፡፡ በዚያም ቊታ ቅዱስ ያሬድ ሁለት ዓመት አስተማሚ፡፡ እርሱ እራሱ ዚጻፈው ድጓ ምልክት ዹሌለው ዛሬ በዚሁ ደሎት በጣና ቂርቆስ ይገኛል፡፡ ኹዚህም ደሎት ኚጣና ቂርቆስ ተነሥተው ንጉሡና አቡነ አሹጋዊ ቅዱስ ያሬድም ወደ ደጋው ወደ ጋይንት ወጡ፡፡ በዚያም አንድ ትልቅ ተራራ አግኝተው መውጫው ጠፍቶባ቞ው ሲጚነቁ አሹጋዊም ‹‹ምነው ዚደብሚ ዳሞው ዘንዶ ኹዚህም ተራራ ላይ ባወጣኝ›› እያሉ ሲጞልዩ ኚእግዚአብሔር ዚታዘዘ መልአክ ቅዱስ ዑራኀል መጥቶ አቡነ አሹጋዊን ‹‹ዙር አባ መንገለ ምሥራቅ- አባ መውጫውን በምሥራቅ በኩል ታገኘዋለህ›› ሲል አመለኚታ቞ው፡፡ እንደተባሉትም በስተምሥራቅ ሲዞሩ መልአኩ ሁለቱን ቅዱሳን በሐሹግ ስቊ ኚተራራው ላይ አወጣ቞ው፡፡ ተራራውም ላይ ቅዱሳን መላእክት እንደሻሜ ተነጥፈው ሲያመሰግኑ ቅዱስ ያሬድ አብሯ቞ው አመስግኗል፡፡

አቡነ አሹጋዊም በዚሁ ተራራ ላይ ዚእመቀታቜንን ቀተ ክርስቲያን ሠርተው ሥርዓተ ምንኩስናን አስፋፍተዋል፡፡ ዚተራራውም ስም እስኚ ዛሬ ድሚስ ‹‹ዙር አባ›› ተብሎ ይጠራል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በዚሁ ተራራ ላይ ሊስት ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት ዚተባለውን መዝሙር አስተምሯል፡፡ ይህም ቊታ እስኚ ዛሬ ድሚስ ዚዝማሬና ዚመዋሥዕት ምስክር ቊታ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ይጠቀምባ቞ው ዚነበሩ ጞናጜልና መቋሚያ በዚሁ ቊታ ላይ አሉ፡፡ ዚአቡነ አሹጋዊ ጭራና መቋሚያም አለ፡፡ ኹዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ አክሱም ተመልሶ ለሥጋ ወደሙ ጞሎት ዚሚያገለግሉትን 14ቱን ቅዳሎዎቜ በዜማ ተናገሚ፡፡ ቅዳሎውን በዜማ ዚተናገሚበት ቊታ መደባይታብር ይባላል፡፡ ይህም መደባይታብር ዚሚባለው ቊታ ለአክሱም ሰሜን ሆኖ ኚአክሱም ግማሜ ቀን ያህል በእግር ያስኬዳል፡፡

ቅዱስ ያሬድ ዚሕይወት ዘመኑን በጞሎትና በብሕትውና ለማሳለፍ ወደ ሰሜን ተራራ ምድሚ ጞለምት በመሄድ ብርዱ በእጅጉ በጞናበት በሚዶ በሚፈላበት በሐዊ ተራራ በጜሙና ተቀምጧል፡፡ ይህም ቊታ በሰሜን ጎንደር ሀገሹ ስብኚት በበዚዳ ወሚዳ ዹሚገኝ ነው፡፡ በዚያም ጉባኀ ዘርግቶ ትምህርት አስፋፍቶ ለሃያ ሁለት ዓመታት አስተምሯል፡፡ ዚእርሱ ደቀ መዛሙርት ሳዊሮስና ሳንድሮስ በልዳዶስ ዚሚባሉት ኚእርሱ ዚተማሩትን ዹዜማ ባሕልና ሥርዓት በትግራይና በሰሜን አውራጃ እዚተዘዋወሩ በዚገዳማቱ ሁሉ ስላስተማሩ ዚቅዱስ ያሬድ ድርሰት እስኚ ዛሬ ድሚስ ጞንቶ ኖሯል፡፡ ኹዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ ወገራና ወደ አገው እዚዞሚ ካስተማሚ በኋላ ዘመኑን ሁሉ በማኅሌት እግዚአብሔርን በማገልገል በጣእመ ዜማው ዲያቢሎስን ድል መትቶ በዚያው በሐዊ ተራራ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ ገብቶ በ571 ዓ.ም ግንቊት 11 ቀን እንደ ሄኖክና ኀልያስ ተሰወሚ፡፡

ቅድስት ቀተ ክርስቲያንም ቅድስናውንና አማላጅነቱን አምና በስሙ ጜላት ቀርጻ፣ ቀተ ክርስቲያን አንጻ፣ ድርስቶቹንም ዚቀተ ክርስቲያን መገልገያና ዚሥርዓተ አምልኮ መፈጞሚያ አድርጋ እዚተጠቀመቜባ቞ው ተገኛለቜ፡፡ በምናኔ በኖሚበት ሥፍራም በስሙ ገዳም ተገድሞ መናንያን አሰሹ ፍኖቱን ተኚትለው ጀዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው፣ በሚዶውንና ውርጩን ታግሠው በስሙ እዚተማጞኑ ይኖራሉ፡፡ በቊታው ላይ እሁድ እሁድ ኚመሬት ውስጥ ዚኚበሮ ድምጜ ይሰማል፣ ቅዱስ ያሬድ መቋሚያውን ወርውሮ ያፈለቀው ጾበል ዛሬም ድሚስ ዚተለያዩ ገቢሚ ተአምራትን እያደሚገ ይገኛል፡፡

ዓለም ኚሚያውቃ቞ው ዹዜማ ደራስያን ኚሞዛርትና ኚሌሎቜም አስቀድሞ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ ዕዝልና አራራይ በተሰኙ ዹዜማ ስልቶቜ ዚማይሰለቜና ዘመን ተሻጋሪ ዜማን፣ ዹዜማ ምልክቶቜንና ተለያዩ ድርሰቶቜን በመድሚስ ሀገራቜን ዹዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ሀብት ባለቀት እድትሆን አድርጓል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በሰዓታት ፣በወራትና በዘመናት ዹተኹፋፈሉ ድንቅ ምስጋናዎቜን ኚብሉያትና ኚሐዲሳት ንባብና ምሥጢር ለቀተ ክርስቲያን እንደ ሰምና ወርቅ አስማምቶ ዚአገልግሎት ሥርዓትን ዚሠራ ዚቀተ ክርስቲያን ዓምድ ነው፡፡ ዚቅዱስ ያሬድ ዜማ ድንቅና ጥልቅ ዹነገሹ ሃይማኖት አስተምህሮት ፣ ዚቅዱሳት መጻሕፍን ንባብ ትርጓሜ እንዲሁም ዚታሪክ ምስክርነትን ዚያዘ ኹፍ ያለ ዋጋ ያለው ድርሰት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዛሬ በጉባኀ ቀት ለዜማ ትምህርት ቀተ ክርስቲያን ዚምትገለገልበትን ሥርዓተ ትምህርትና ዚመማሪያ መጻሕፍትን ዹደሹሰ ሊቅ ነው፡፡ ድርሰቶቹም ምዕራፍ ፣ጟመ ድጓ፣ ዝማሬና መዋሥዕት ይባላሉ፡፡ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም በመምህሩ በጌዮዎን ወንበር ተተክቶ መጻሕፍተ ብሉያትና ሐዲሳትን አስተምሯል፡፡ ኚአቡነ አሹጋዊና ኹአፄ ገብሚ መስቀል ጋርም በመሆን በተለያዩ ዚሀገሪቱ ክፍሎት በጣና ቂርቆስ ፣በዙር አባ አቡነ አሹጋዊ ገዳም እንዲሁም ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ እስኚ ብርብር ማርያም በመሄድ ያስተማሚ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡ አጠቃላይ በሥነ ጜሑፍና በቋንቋ እድገት በነገሹ መለኮትና በታሪክ ትምህርት እንዲሁም በሥርዓተ ጞሎት ዚቀተ ክርስቲያን አንድነት በማስጠበቅ ሚገድ ጜኑ መሠሚትን ዚጣለ ታላቅ ሊቅ ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ነው፡፡ ኚእርሱ ውጭ ቅድስት ኊርቶዶክሳዊት ቀተ ክርስቲያን ምን ልትመስል እንደምትቜል ማሰብ እጅግ ኚባድ ነው፡፡ ቀተ ክርስቲያን ግን እርሱ እንደዋለላት ውለታ መጠን አላኚበሚቜውም፡፡ ዚቅዱስ ያሬድ ሚድኀት በሚኚቱ ይደርብን፣ በጞሎቱ ይማሚን፡፡
[ግንቊት 11 ዚቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ በዓል]
✍ በመጋቀ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
♥♥ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አባቱ አብዩድ (ይሥሐቅ) እናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) ሲባሉ ዹተወለደውም በ፭፻፭ ዓ.ም. በአክሱም ነው፡፡ ሰባት ዓመት ሲመላው አባቱ ስላሚፈፀ እናቱ ዚቀተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲያስተምሚው ለአባ ጌዮዎን ሰጠቜው፡፡ ነገር ግን ማጥናት ስላልቻለ አባ ጌዮዎን ይቈጣው ነበርና ሞሜቶ ኚዱር ውስጥ ገባፀ ኹዐዘኑም ብዛት ዚተነሣ በዛፍ ሥር ተጠልሎ ሳለ አንዲት ታናሜ ትል ኹዛፍ እኩሌታ ደርሶ ሲወድቅ ሲነሣ በመጚሚሻም በጭንቅ ኹዛፉ ላይ ሲወጣ በማዚቱ እግዚአብሔር በዚኜቜ ታናሜ ፍጥሚት እንዳስተማሚው በመሚዳት ይቅርታ ጠይቆ ወደ መምህሩ ተመልሷል፡፡

♥ “ወእምዝ ሶበ ሰአለ ኀበ እግዚአብሔር በብካይ ብዙኅ ተርኅወ ልቡናሁ ወተምህሹ በሐጺር ዕለት መጻሕፍተ ብሉይ ወሐዲስ” ይላል ኚዚኜ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ ልቡናው ብሩህ ኟኖለት በዐጭር ጊዜ ውስጥ ዚብሉይና ዚሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ተምሮ በመጚሚስ ዲቁናን ተሟመፀ እስኚ ርሱ ዘመን በማነብነብ እንጂ በኹፍተኛ ድምፅ ዹመዝሙር ማሕሌት አልነበሚምፀ እግዚአብሔርም ለዚኜ አባት ዚመላእክትን ዝማሬ ሊያሳዚው ስለወደደ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እስኚ ሊስተኛው ሰማይ እንደተነጠቀ ኹሉ ሊቁም ተነጥቆ ዚኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይን ዚምስጋና ዝማሬ ሰምቶ ተመለሰ፡፡

♥ ቅዱስ ያሬድ ኚአርያም ወርዶ ወደ ምድር እንደ ደሹሰ ወደ አክሱም ጜዮን ቀተ ክርስቲያን ገብቶ፡- “ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጜዮን ሰማዹ ሣሚሚ ወበዳግም አርአዮ ለሙሮ ዘኹመ ይገብር ግብራ ለደብተራ” (ለአብ ምስጋና ይገባል፣ ለወልድም ምስጋና ይገባል፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ኚጜዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠሹ ዳግመኛም ለሙሮ ዚድንኳኑን ሥራ እንዎት እንደሚሠራ አሳዚው) ሲል ዘምሮ ይቺኑ መዝሙር ኹሰማይ መላእክት አገኘኹት፣ በማለት አርያም በሚል ሥያሜ ጠርቷታል፡፡

♥ይኜነኑ ድርሳነ ዜማ ዚጻድቁ ካሌብ ልጅ ንጉሥ ገብሚ መስቀል በሰማ ጊዜ ጫማውን ሳይጫማ ንግሥቲቱም ደንገጡሮቿን አጃቢዎቿን ሳታስኚትል መኳንንቱ፣ ካህናቱና መምህራኑ እነሱን ተኚትለው እዚተጣደፉ ወደ ዐደባባዩ በመኌድ በተመስጊ ሲሰሙት ውለዋል፡፡

♥ ቅዱስ ያሬድ ዐምስት ዹዜማ መጻሕፍትን ዹደሹሰ ሲኟን እነርሱም
፩ኛ) ድጓ ፪ኛ) ጟመ ድጓ
፫ኛ) ምዕራፍ ፬ኛ) ዝማሬ ፭ኛ)መዋሥዕት ና቞ው፡፡

♥ እነዚኜንም ታላላቅ ድርሰቶቹን በሊስት ዹዜማ ስልቶቜ ማለት በግእዝ፣ በዕዝል፣ በአራራይ አዘጋጅቷ቞ዋል፡፡ “ወአሐተ ዕለተ እንዘ ይዜምር ያሬድ ቀዊሞ ታሕተ እገሪሁ ለንጉሥ ገብሚ መስቀል ወእንዘ ያጞምዕ ንጉሥ ቃሎ ለያሬድ ተኹለ በትሚ ኀጺን ውስተ መኹዹደ እግሩ ለያሬድ” ይላልፀ ኚዕለታት ባንዳ቞ው ቅዱስ ያሬድ በተመስጊ ልዑል እግዚብሔርን በዝማሬ ሲያመሰግን ንጉሥ ገብሚ መስቀል ሳያውቁት ልባ቞ው በጣዕመ ዜማው በመመሰጡ ዚብሚት ዘንጉን በቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ተክለውታልፀ ኚእግሩም ብዙ ደም ቢፈስስም ቅዱስ ያሬድ ግን ማሕሌቱን እስኚሚፈጜም ድሚስ ምንም አልሰማውም ነበር፡፡

♥ንጉሡም ዹደሙን መፍሰስ አይቶ ደንግጩ ቅዱስ ያሬድን “ዚደምኜ ዋጋ ዹፈለግኾውን ንገሹኝ” አለውፀ ቅዱስ ያሬድም ተምኔቱ ወደ ገዳም መኌድ እንደኟነ ነገሚውፀ ያን ጊዜ ንጉሡ እያዘነ አሰናብቶታል፡፡

♥ “ወእምዝ ቩአ ያሬድ ውስተ ቀተ ክርስቲያን ወቆመ ቅድመ ታቊተ ጜዮን” ይላል ወደ ቀተ ክርስቲያን ገብቶ በታቊተ ጜዮን ፊት በመቆም ዹአንቀጾ ብርሃንን ምስጋና ኚመዠመሪያው እስኚ መጚሚሻው በተናገሹ ጊዜ በእግዚአብሔር ኀይል ክንድ ያኜል ኚምድር ኹፍ ኹፍ አለፀ ኚዚኜ በኋላ ወደ ሰሜን ተራራዎቜ ወደ ገዳም ሲኌድ ዚአኲስም ጜዮን ካህናት እስኚ ተኹዜ ወንዝ ድሚስ ሞኙት ርሱም እጅግ ባማሚ ጣዕመ ዜማ ድምፁን ኹፍ አድርጎ “ሰላም እግዚአብሔር ኲሉ ባቲ ተሃሉ ወትሚ ምስለ ኲልክሙ” (በኹሉ ላይ ጞንታ ዚምትኖር ዚእግዚአብሔር ሰላም ዘወትር ኚኹላቜኊ ጋር ትኑር) ብሎ ዚስንብት መዝሙርን ዘመሚፀ ካህናቱም ይኜነን ቃል ሰምተው መሪር እንባን አለቀሱና ተሰነባበቱ፡፡

♥ በትርጓሜ ቅዳሎ ማርያም መቅድም ላይ እንደምናነብበው ቅዱስ ያሬድ ማይ ኪራህ በተባለው ቊታ ተሰውሮ ጞዋትወ ዜማን ሲያስተምር እመቀታቜን ሶርያዊው ቅዱስ ኀፍሬምን ዚብህንሳውን አባ ሕርያቆስን በአካለ ነፍስ እንዲመጡ አድርጋ ኀፍሬም ውዳሎዬንፀ ሕርያቆስ ቅዳሎዬን ነግራቜኹት ቅዱስ ያሬድ በዜማ ይድሚስልኝ ብላ ነግሚውት በዜማ ደርሶታልፀ ይኜም ሊታወቅ ሥሚይ በቅዳሎ ማርያም ይበዛል፡፡

♥ ርሱም ጞዋትወ ዜማን ለደቀ መዛሙርቱ እያስተማሚ መላእክት ዘወትር እዚጐበኙት በጟም በጞሎት ተወስኖ በተጋድሎ ለኻያ ኹለት ዓመት ጞንቶ ኖሚፀ በመጚሚሻም ጌታቜንም ለቅዱስ ያሬድ ተገልጟለት “ኩ ፍቁርዹ ቀዳሚኒ በኹመ ሰመርኩ ትርአይ ሥርዐተ ስብሐተ መላእክት ዘበሰማያት ወአስተኀለፍኚ ዘንተ ማሕሌተ ዲበ ምድር... ” (ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ ዚመላእክትን ሥርዐተ ማሕሌት እንድታይና ወደ ምድርም አስተላልፈኜ ይኜነኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኊ ኹሉ እኔ ዳግም ተመልሌ በምመጣበት ጊዜ ኚካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቾውን ካፈሰሰው ሕፃናት ጋር በደብሚ ጜዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ ዚክብር አክሊልና ዚብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልኻል” ብሎት ቃል ኪዳንን ሰጥቶት በክብር ዐሚገ፡፡ ዚቅዱስ ያሬድ መታሰቢያውም ግንቊት ዐሥራ አንድ ነው፡፡

♥ ሊቁ አርኹ ሥሉስም ዚቅዱስ ያሬድን ነገር በአርኬው ላይ፩
“ሰላም ለያሬድ ስብሐተ መላእክት ለሕዋጌ
እንተ አዕሹገ በልቡ ኅሊና መንፈስ ሚዋጌ
ለትምህርተ መጜሐፍ ገብአ እምኀበ ኮነ ነፋጌ
በብዙኅ ጻማ ዘአልቩ ሑጻጌ
መልዕልተ ጒንደ ዖም ነጺሮ እንዘ ዹዐርግ ዕጌ”
(ዚመላእክትን ምስጋና ለመጐብኘት ኚመንፈስ ቅዱስ ዚሚሰጥ ፈጣን ዐሳብን ወደ ልቡናው ያሳሚገ ለኟነፀ ጒድለት በሌለበት በብዙ ድካምም ወደ ዛፍ ግንድ ጫፍ ላይ ትል ሲወጣ ተመልክቶፀ ኰብልሎ ኚኌደበት መጻሕፍትን ለመማር ዹተመለሰ ለኟነ ለያሬድ ሰላምታ ይገባል) በማለት ሊቁ ማሕሌታይን አመስግኖታል፡፡

♥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጜሐፉ ላይ ማኅቶተ ቀተ ክርስቲያን ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ሲያወድስ፡-
“ሰላም ለያሬድ ቀሲስ ዘጜጉብ እክለ መንፈስ ቅዱስፀ
ዘአስተጋብአ ምድራሳተ እምኲሎሙ መጻሕፍት
ወአሰርገዋ በሐዋዝ ስብሐት ወበጥዑም ማሕሌት
ለብሔሚ ኢትዮጵያ በስብሐት ሃሌ ሉያ
ዘኹዐወ ቃለ መለኮት ዲቀሃ
ኹመ አስራበ ወርቅ ንጹሐ”፡፡
(ዚመንፈስ ቅዱስን ምግብን ዚጠገበፀ ኚመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበፀ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና ዚኢትዮጵያ ሀገርን በጥዑም ማሕሌትና በሚያምር ምስጋና ያስጌጠፀ ዚመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ ዹወርቅ ሻሻ቎ ያፈሰሰ ለኟነ ለካህኑ ያሬድ ሰላምታ ይገባል) ይለዋል፡፡
[ዚጜሑፉ ምንጭ፡- አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ዹደሹሰው ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው በመጋቀ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ዚተጻፈፀ ኚገጜ 232-235]፡፡
ዚቅዱስ ያሬድ በሚኚት ይደርብንፀ እናንተም ይኜነን ሊቅ አወድሱት
ንጉሥ ዳኬዎስ በወርቅ ያሠራውን ዚጣዖቱን ዚአጵሎንን ምስል መጥራ ዚተባለው ሰማዕት ዚአጵሎንን ክንድ ነቅሎ በመውሰድ ወርቁን ለድኆቜና ለጩም አዳሪዎቜ ሰጣ቞ው፡፡

በእሳት ተቃጥሎ፣ እጆቹንና እግሮቹን በዚተራ ተቆራርጊ፣ ተዘቅዝቆም በእንጚት ላይ ተሰቅሎ በመጚሚሻም አንገቱን ተሰይፎ ሰማዕትን ዹተቀበለው ይህ ቅዱስ መጥራ በዚኜቜ በወርሃዊ በዓሉታስቊ ይውላል።

ሰማዕቱ ቅዱስ መጥራ በታላቁ በእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ በቅዱስ ዲሜጥሮስ ዘመንና በኚሃዲው ንጉሥ ዳኬዎስ ዘመነ መንግሥት ዹነበሹ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡ ዚክብርን ባለቀት ጌታቜንን ክደው ለጣዖት መስገድን ዚሚያዝ ዚንጉሡን ትእዛዝ በሰማ ጊዜ ወዲያው ሄዶ ኹወርቅ ዚተሠራ ዚአጵሎንን ክንድ በድብቅ ወስዶ በዚጥቂቱ ሰባብሮና ቆራርጊ ወርቁን ለድኆቜና ለጩም አዳሪዎቜ ሰጣ቞ው፡፡ ዚጣዖቱ አገልጋይ ዹሆኑ ዚንጉሡ ባለሟሎቜም ዚአጵሎን ክንዱ ተቆርጩ ባገኙት ጊዜ ብዙ ዚአገሩን ሰዎቜ ይዘው መሚመሯ቞ው፡፡

ኹዚህም በኋላ ቅዱስ መጥራ ወደ መኮንኑ ዘንድ ቀርቩ ዚጌታቜንን አምላክነት መሰኚሚ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ዚአጵሎንን ዹወርቅ ክንዱን ቆርጹ ዚወሰድኩ እኔ ነኝ፣ ለድኆቜና ለጩም አዳሪዎቜ ሰጠኋ቞ው›› አለው፡፡ መኮንኑም ይንን ሲሰማ እጅግ ተቆጥቶ ብዙ ሥቃይ አደሚሰበት፡፡ ተቃጥሎ ይሞት ዘንድ በሚነድ ዚእቶን እሳት ውስጥም ጹመሹው ነገር ግን ጌታቜን ፍጹም ጀነኛ አደገው፡፡ ኹዚህም በኋላ ዚቅዱስ መጥራን እጆቹንና እግሮቹን በዚተራ ቆራሚጧ቞ው፡፡ ዘቅዝቀውም በእንጚት ላይ ሰቀሉት፡፡ ደሙም በምድር ላይ እንደ ውኃ ፈሰሰ፡፡ በዚህም ጊዜ ዚታዘዘ መልአክ መጥቶ ኚተሰቀለበትና ኚእስራቱ ፈታው፣ ሰውነቱንም በመዳሰስ ፍጹም ጀነኛም አደሚገው፡፡ አንድ ዐይነ ሥውርም ወደ እርሱ መጥቶ በአፍንጫው ኹፈሰሰው ደም ወስዶ ዐይኑን ቢቀባው ወዲያው ዕውር ዐይኑ በራለት፡፡ መኮንኑም ድጋሚ ይዞ ብዙ አሠቃዚው፡፡ በመጚሚሻም ማሠቃዚት በሰለቾው ጊዜ ዚቅዱስ መጥራን አንገቱን በሰይፍ ቆሹጠውና ዚሰማዕትነቱ ፍጻሜ ሆኖ ዚክብርን አክሊል ተቀዳጀ፡፡ ዚቅዱስ መጥራ ሚድኀት በሚኚቱ ይደርብን፣ በጞሎቱ ይማሚን፡፡
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ግንቊት 11-ዚቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ዹሆነ ዚሱራፌል አምሳላ቞ው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ዚተሰወሚበት ዕለት ነው፡፡
+ ዚዓባይን ወንዝ በጞሎታ቞ው ገዝተው ያቆሙትና መልአኩ ቅዱስ ገብርኀል ግዝታ቞ውን እንዲፈቱ ዚነገራ቞ው ዚውቅሮው አቡነ ኀልያስ ዕሚፍታ቞ው ነው፡፡
+ ዚባሌው አቡነ አሮር በሰማዕትነት ዐሚፉ፡፡
+ ዚታላቁ ሰማዕት ዚቅዱስ ዮስጊስ ሚስት ቅድስት ታውክልያ በሰማዕትነት ዐሚፈቜ፡፡
+ ቅድስት ዚሆነቜ መነኩሎ ሆና ሳለ እርሷ ግን ራሷን እብድ አስመስላ ዚኖሚቜው ቅድስት አናሲማ ዕሚፍቷ ነው፡፡ ምሥጢሯንም ለአባ ዳንኀል ነግራዋለቜ፡፡
+ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ሰማዕትነቷን በድል ዚፈጞመቜ ቅድስት ኀፎምያ ዕሚፍቷ ነው፡፡
+ ዚኀስድሮስ እናት ቅድስት ሶፍያና እኅቱ ቅድስት ኀፎምያ በሰማዕትነት እንዳሚፉ ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳ቞ዋል፡፡
+ ኀጲስቆጶስ አባ በፍኑትዮስ ዕሚፍቱ ነው፡፡
+ አባ በኪሞስና አባ አብላዲን መታሰቢያ በዓላቾው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳ቞ዋል፡፡

ቅድስት አናሲማ፡- ይኜቜም ቅድስት በደናግል ገዳም መንኩሳ በታላቅ ተጋድሎ ዚምትኖር ስትሆን እርሷ ግን ራሷን ዕብድ አስመስላ ኖሚቜ፡፡ በሌሊትም በጟምና በጞሎት ሥጋዋን በመቅጣት ራሷን ታሠቃያለቜ፡፡ ሰዎቜም በሚያዩዋት ጊዜ አእምሮዋን ያጣቜ እንደሆነቜ ታስመስላለቜ፡፡ መበለቶቜም ይሰድቧታል፡፡ እጅግ ገድላኛው ዹሆነው ጻድቁ አባ ዳንኀል በአንዲት ዕለት ኹደናል ገዳም ደርሶ ደጁን አንኳኳ፡፡ እነርሱም ዹኹበሹ አባ ዳንኀል መሆኑን ዐውቀው ኚፈቱለት፡፡ ይኜቜም ቅድስት አናሲማ በዚያ ራሷን ዕብድ አስመስላ በደጅ ዚምትተኛ ሎት ነበሚቜ፡፡ ዹኹበሹ አባ ዳንኀልም ዕብድ መስላ በደጅ ስለተቀበጠቜው ቅድስት አናሲማ እመ ምኔቷን ሲጠይቃት እብድ መሆኗን ነገሚቜው፡፡ አባ ዳንኀል ግን ዕብድ ዚመሰለቻ቞ው አናሲማ እብድ ሳትሆን በድብቅ በታላቅ ተጋድሎ ዚምትኖር ዚኚበሚቜ ቅድስት መሆኗን ነገራት፡፡

ዕብድ መስላ ትኖር ነበሚቜውና በሁሉም ዘንድ ዕብድ ዚተባለቜው ቅድስት አናሲማም አባ ዳንኀል ምሥጢሯን እንደገለጠባት በጾጋ ዐውቃ ወዲያው ደብዳቀ ጜፋ ይኾውም ‹‹ዚተኚበራቜሁ እኅቶቌ ስላስቀዚምኳቜሁና ስላሳዘንኳቜሁ ይቅር በሉኝ›› ብላ ጜፋ ደብዳቀውን አስቀምጣ ኚንቱ ውዳሎን በመሞሜ ጥላ቞ው ጠፋቜ፡፡ እነርሱም ኚዚያ በኋላ ዳግመኛ አላዩአትም፡፡ ቅድስት አናሲማም በዚያው በበሹሃ ሳለቜ በዚህቜ ዕለት በሰላም ዐሚፈቜ፡፡ ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን፣ በጞሎቷ ይማሚን፡፡
+ + + + +

ሰማዕቱ አቡነ አሮር ዘባሌ፡- ልደቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡ እርሱም በደብሚ ሊባኖስ ዚመጻሕፍት መምህር ሆኖ ሳለ ዹበቃ ጻድቅ መሆኑ ቢታወቅበት ወደ ሐይቅ ሄዶ በተጋድሎ ዹኖሹ ሲሆን በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተመርጩ በባሌ ሀገር ላይ ዚተሟመ ነው፡፡ በኋላም ወደ ኢዚሩሳሌምና ግብፅ ሄዶ ኹመናፍቃን ጋር ሲኚራኚር ኚሃዲዎቜ በእሳት አቃጥለውት በመጚሚሻም አንገቱን ሰይፈውት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ አካሉንም በእሳት አቃጥለውት ኚጣሉት በኋላ በደብሚ ቁስቋም ተቀብሯል፡፡ ስንክሳሩ ግን ‹‹በኢዚሩሳሌም መግቢያ በእሳት አቃጠሉት›› ብሎ ይገልጞዋል፡፡ ሚድኀት በሚኚቱ ይደርብን፣ በጞሎቱ ይማሚን፡፡
+ + + + +

ሰማዕቷ ቅድስት ኀፎምያ፡- እናቷ ቎ዎድርስያኒ ጌታቜንን በማመን ዚጞናቜ ደገኛ ክርስቲያን ናት፡፡ ልጇን ቅድስት ኀፎምያንም እግዚአብሔርን በመፍራት በሃይማኖት በምግባር አሳደገቻት፡፡
በወቅቱም ሰይጣን ኚሃዲውን አንቲሂጳጊስን አስነሣውና በክርስቲያኖቜ ላይ ታላቅ መኚራን አመጣ፡፡ ቅድስት ኀፎምያን ኚብዙ ክርስቲያኖቜ ጋር አሥሮ አመጣትና <ለአማልክት ስገጂ መሥዋዕትም አቅርቢ> አላት፡፡ እርሷም <ኚክርስቶስ በቀር ዚሚገዙለት አምላክ ዚለም፣ ለሚኚሱ አማልክቶቜህ አልሠዋም ይልቁንም ዚአባቶቌን ተስፋ ለማግኘት ልቀ ዹጾና ነው> አለቜው፡፡

በዚህም ጊዜ ሃዲው አንቲሂጳጊስ እጅግ ተቆጥቶ አጥንቶቿ እንዲሰባበሩ ሕዋሳቶቿም እንዲቆራሚጡ መንኮራኩር ውስጥ ጚመራት፡፡ ነገር ግን ዚታዘዘ መልአክ መጥቶ አዳናት፡፡ ዳግመኛም ነበልባሉ 45 ክንድ ኹፍ ብሎ እስኪታይ ድሚስ እሳት አንድደው ኚእሳቱ ውስጥ ጚመሯት፡፡ ኚእሳቱም መካኚል ቆማ ኚጞለዚቜ በኃላ ምንም ጉዳት ሳያገኛት ደህና ሆና ወጣቜ፡፡ ይኜንንም ታላቅ ተአምር ያዩ ሁሉ በጌታቜን አምነው በሰማዕትነት ዐሚፉ፡፡

ቅድስት ኀፎምያን ግን በማግሥቱ ወደ ሾንጎ አውጥተው አራት ትላልቅ ድንጋዮቜን በላይዩዋ ላይ አሥሚው ሥጋዋን ገፈው ካሠቃዩአት ዳግመኛ አራዊት ካሉበት ኩሬ ውስጥ ጚመሯት፡፡ ነገር ግን አራዊቶቹ ተሾክመው አውጥተው ኹውሃው ዳር በክብር አስቀመጧት፡፡ ዳግመኛም ስለቶቜን በመሬት ላይ ተክለው ቅድስት ኀፎምያን በዚያ ላይ እንድትሄድ በማድሚግ አሠቃዩአት፡፡ ደግሞም በእሳት ላይ በተጣደ ብሚት ምጣድ ውስጥ ጚመሯት፡፡ በመኚራዎቿም ሁሉ ጌታቜን ያጞናትና ዚበሚታት ነበር፡፡
መኮንኑም ለተራቡ አንበሶቜ ቢሰጣትም አንበሶቹ ግን ወድቀው እግሯን ላሱ፡፡ አንዲት አውሬ ግን እዚተሞበሚቜ መጥታ ዚቅድስት ኀፎምያን እግሯን ነኚሰቻት፡፡ እግዚአብሔርም ዚሰማዕትነቷ ፍጻሜ በዚህ እንዲሆን መልካም ፈቃዱ ሆነ፡፡ ኹሰማይም <ዚተመሰገንሜ ኀፎምያ ሆይ! ወጥተሜ ወደኹበሹ ቊታ ነይ> ዹሚል ድምጜ ተሰማ፡፡ ዚቅድስት ኀፎምያ ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን፣ በጞሎቷ ይማሚን፡፡
+ + + + +

አባ በፍኑትዮስ፡- ይኜም ቅዱስ በአባ መቃርስ ደብር በአስቄጥስ ገዳም መንኩሶ በታላቅ ተጋድሎ ኖሚ፡፡ ብዙ ትሩፋትንም ሠራ፡፡ እርሱም ቅጠልን ይመገባል እንጂ በእሳት ዹበሰለ እህል ተመግቩ አያውቅም፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንም ተምሮ ኹጹሹሰ በኋላ ቅስና ተሟመ፡፡ በጜድቁና በተጋድሎውም በሁሉ ዘንድ ዚታወቀ ሆነ፡፡ ሊቀጳጳሳቱ አባ ፊላታዎስም መልእክተኛ ልኮ ኚገዳም አስመጥቶት ኀጲስቆጶስነት ሟመው፡፡ አባ በፍኑትዮስ ኀጲስቆጶስነት ኚተሟመ በኋላ ቅዳሎ ለመቀደስ ሲል ልብሱን ይለውጣል እንጂ ኹጠጉር ዚተሠራ ማቅ በቀር ሌላ ልብስ አይለብስም ነበር፡፡ በታላቅ ተጋድሎውና በአገልግሎቱ ዹጾና ሆነ፡፡ በዘመኑም ሁሉ ኚመነኮሳት ጋር ያገለግል ነበር፡፡ በታመመም ጊዜ እግዚአብሔርን እንዲህ ብሎ ለመነው፡- ‹‹ዚክብር ባለቀት ጌታዬ ኢዚሱስ ክርስቶስ ሆይ! ኀጲስቆጶስነት ስለተሟምሁ ጾጋህን በውኑ ኚእኔ ታርቃለህን?›› በዚህም ጊዜ ኚእግዚአብሔር ዚታዘዘ መልአክ ወደ አባ በፍኑትዮስ ዘንድ መጥቶ ‹‹አስተውል፣ ዕወቅ፡፡ አንተ በገዳም ሳለህ በታመምክ ጊዜ ዹሚጎበኝህ ዚለም፣ ዚሚያገለግልህና ለደዌህ መድኃኒትን ዚሚሰጥህ አታገኝም ነበር፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ዚሚሚዳህና ደዌውንም ኹአንተ ዚሚያርቅልህ ሆነ፡፡ ዛሬ ግን እነሆ አንተ በዓለም ውስጥ ነህ፣ በአንተ ዘንድ ዹሚጎበኝህና ዚሚያገለግልህ አለፀ ለደዌህም መድኃኒትን ዚምትሻውንም ምግብ ታገኛለህ›› አለው፡፡
ይኜም ቅዱስ ኀጲስቆጶስነት ተሹሞ 32 ዓመት በቅድስና ሲያገለግል ኹኖሹ በኃላ ዚሚያርፍበት ጊዜ ሲደርስ አገልጋዮቜን በሙሉ ጠርቶ ንዋዹ ቅድሳታ቞ውን ሰጣ቞ውና "እኔ ወደ እግዚአብሔር እሄዳለሁና እስኚመጚሚሻው ድሚስ በቀናቜ ሃይማኖት ጜኑ" ብሎ ኚመኚራ቞ው በኃላ በሰላም ዐሚፈ፡፡ ሚድኀት በሚኚቱ ይደርብን፣ በጞሎቱ ይማሚን፡፡
+ + + + +

አቡነ ኀልያስ ዘውቅሮ፡- አቡነ ኀልያስ ዘውቅሮ ዚትውልድ ሀገራ቞ው አክሱም ነው፡፡ ዚአቡነ አሹጋዊ 3ኛ ዚቆብ ልጅ ና቞ው፡፡ አባታ቞ው ውቅሮ ዹሚገኘው ዚጥንታዊው ዚአብርሃ ወአጜብሓ ቀተ መቅደስ አጣኝ ነበሩ፡፡ ይህ ጻድቅ ዚሚታወቁበት አንድ ትልቅ ገድል አላ቞ው፡፡
በቀን 548 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን እዚጞለዩ 666 ጊዜ ይሰግዱ ነበር፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዓባይ ዚሀገራቜንን አፈርና ዛፉን ሁሉ ጠራርጎ ሲወስድ ቢመለኚት ድምጹን ኹፍ አድርጎ ኩ አባይ አይቮ ተሐውር ወለመኑ ተሐዲጋ ለኢትዮጵያ ብሎ ሲዘምር ዓባይ ቀጥ ብሎ ቆሟል፡፡ መልአኩም ወዲያው መጥቶ ‹‹ለምን ትደክማለህ? ለምንስ ተፈጥሮን ትኚለክላለህ? ሕጉን አታፍርስ›› ሲለው ቅዱስ ያሬድ ደንጎጩ ‹‹አጥፍቻለሁ ዓባይ ሆይ ሂድ ዚተፈጥሮ ግዎታህን ፈጜም›› ብሎ አሰናብቶታል፡፡ ዚኢትዮጵያ ብርሃኗ ቅዱስ ያሬድ በዜማው ዓባይን ቀጥ አድርጎ እንዳቆመው ሁሉ አቡነ ኀልያስ ዘውቅሮም በጞሎታ቞ው ዓባይን ኚኢትዮጵያ እንዳይወጣ አድርገውት ነበር፡፡
ታቊተ አብርሃ ወአጜብሓን ይዘው ኚኢትዮጵያ ጠሹፍ ዳር ኑብያ ሄደው ድንጋይ ኚዓባይ ዳር ደርድሚው ታቊቱን አስቀምጠው ሥዕለ ማርያምን አድርገው መሥዋዕት ሰውተው ‹‹ዓባይ ኚኢትዮጵያ እንዳትወጣ ገዝቌሃለሁ›› ሲሉት ዓባይም ተመልሶ ቆሟል፡፡ ዓባይ ምድሚ ኑብያን ሲያጥለቀልቃት መልአኩ ቅዱስ ገብርኀል ተገልጟ ‹‹ለምን ዚእግዚአብሔርን ስነ ፍጥሚት ታስጚንቃለህ?›› ብሎ ተቆጣ቞ው፡፡ ጻድቁም ‹‹ውኃው ይሂድ ግን ዛፉን አፈሩን ይዞ ኚኢትዮጵያ አይውጣ›› ብለው መልአኩን ጠዚቁት፡፡ ቅዱስ ገብርኀልም ‹‹ውኃ ሲሞላ ዛፉን ቅጠሉን ይዞ መጓዙን እንዎት ትሚሳዋለህ? ዚጞሎት ጊዜህ ደርሷልና ወደ በዓትህ ተመለስ›› ብሎ በቁጣ ዚእሳት ሰይፉን ሲያዛ቞ው ግዝታ቞ውን አንሥተው ታቊታ቞ውን ይዘው ወደ በዓታ቞ው ውቅሮ ተመልሰዋል፡፡ አባቶቻቜን እንዲህ ናቾው እንኳን ሃይማኖት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስ፣ ስብዕና ማንነታቜንን ይቅርና ዚሀገራቜንን አፈር እንኳን ለባዕድ አሳልፈው ዚማይሰጡ ቅዱሳን ጻድቃን ነበሩ፡፡ ዚአባ ኀልያስ ሚድኀት በሚኚታ቞ው ይደርብን፣ በጞሎታ቞ው ይማሚን፡፡
+ + + + +

ሰማዕቷ ቅድስት ታውክልያ፡- ታላቁ ዚአንጟኪያ ንጉሥ ኑማርያኖስ በጊርነት ውስጥ በሞተ ጊዜ ልጁ ቅዱስ ዮስጊስም በሌላ ቊታ ጊርነቱን አሾንፎ በድል ወደ ቀተ መንግሥት በተመለሰ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ጌታቜንን ክዶ ጣዖታትን ሲያመልክ ቢያገኘው እጅግ አዝኖ ሰማዕት ይሆን ዘንድ ተመኘ፡፡ ዚሀገሩም ሰዎቜ ወደ ዮስጊስ ዘንድ ቀርበው ‹‹እኛ ዲዮቅልጥያኖስን እንገድለዋለን አንተ በአባትህ ዙፋን ተቀመጥ›› አሉት፡፡ እርሱ ግን ኚምድራዊው መንግሥት ይልቅ ሰማያዊውን መንግሥት መርጧልና እሺ አላላ቞ውም፡፡ በጌታቜንም ስም ሰማዕት ይሆን ዘንድ መሚጠ፡፡ በንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስም ዘንድ ቀርቩ ስለ ጌታቜን ክብር መሰኚሚ፡፡ ንጉሡም ገና ሲያዚው እጅግ ፈርቶና ደንግጩ ‹‹ጌታዬ ዮስጊስ ሆይ! ይህን ታደርግ ዘንድ ያስገደደህ ማነው?›› አለው፡፡ ዮስጊስም ንጉሡን ‹‹በምስክርነ቎ ደሜን እንዳፈስ ካልጻፍክ ሕዝቡን በአንተ ላይ አስነስቌ ኚመንግሥትህ እንደማስወጣህ በጌታዬ በኢዚሱስ ክርስቶስ ስም እምልልሃለሁ›› አለው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም እዚፈራ ዚዮስጊስን ፈቃድ ይፈጜምለት ዘንድ ኚሚስቱ ኚታውክልያና ኹልጁ ኹአቩሊ ጋር ወደ ግብፅ እንዲወስዷ቞ው አዘዘ፡፡ እንዲያባብለውም ለእስክንድርያው መኮንን ጻፈለት፡፡ ዚእስክንድርያውም ገዥ እጅግ ፈርቶ ዮስጊስን ‹‹ጌታዬ ዮስጊስ ሆይ! እንዲህ አታድርግ ለአንተ ክብርህ ይሻልሃል ›› እያለ ሊያግባባው ሲሞክር ቅዱስ ዮስጊስ ግን ‹‹ዚመንግሥትህን ክብር እንዳታጣ ሰማዕትነ቎ን ፈጞምልኝ›› አለው፡፡ እርሱም ፈርቶ ወደ ላይኛው ግብፅ ወደ እንዎናው ገዥ ላኚው፡፡ ኚአገልጋዮቜ ጋራ ሚስቱን ቅድስት ታውክልያን ፃ ወደምትባል አገር ሲልካት ልጁን አቩሊን ደግም ወደ ሀገሹ ብስጣ ላኚው፡፡ ኚአገልጋዮቹም ውስጥ እንዲያገለግሏ቞ው በማለት አንድ አንድ ሰጣ቞ው፡፡

ዹሀገሹ ፃ መኮንንም ዚእስክንድርያው መኮንን ዚጻፈለትን ባነበበ ጊዜ መንግሥታ቞ውን ትተው መኚራን ለመቀበል መምሚጣ቞ውን አደነቀ፡፡ ቅድስት ታውክልያንም በማባበል ብዙ ቃልኪዳኖቜ ገባላት፡፡ እርሷም ‹‹ስለ ጌታዬ ኢዚሱስ ክርስቶስ ፍቅር መንግሥ቎ን ተውኩ፣ በመኚራም ሆኜ ኚልጅነት ባሌም ተለዚሁ፣ በልጆቌም አልተጜናናሁም፡፡ ለመሆኑ አንተ ዚምትሰጠኝ ስጊታ ምን ያህል ነው?›› አለቜው፡፡ መኮንኑም ቅድስት ታውክልያን በማባበል ለጣዖታት እንድትገዛ ለማድሚግ እንዳልቻለ ሲያውቅ ይዞ ብዙ በማሠቃዚት ሥጋዋ እስኪቆራሚጥ ድሚስ አስገሚፋት፡፡ በእሥር ቀትም ሳለቜ ዚታዘዘ መልአክ ተገለጠላትና ኚቁስሏ ፈወሳት፡፡ እስሚኞቜም በእርሷ ላይ ዹተፈጾመውን ተአምር አይተው ብዙዎቜ በጌታቜን አምነው ሰማዕት ሆኑ፡፡ ዳግመኛም መልአኩ ለቅድስት ታውክልያ ተገልጊላት ትቀበለው ዘንድ ያላትን ተስፋና ቃልኪዳን ኚነገራት በኋላ ሰማዕትነቷን በትዕግስት እንድትፈጜም አጜናናት፡፡ መኮንኑም ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ቅድስት ታውክልያ ሰማዕትነቷን በድል ፈጜማ ዚክብር አክሊልን ተቀዳጀቜ፡፡ ምእመናንም ለወታደሮቜ ገንዘብ ኹፍለው ቅዱስ ሥጋዋን ወስደው ዚመኚራው ወራት እስኪፈጞም ድሚስ በሣጥን ውስጥ አኖሯት፡፡ ዚቅድስት ታውክልያ ሚድኀት በሚኚቷ ይደርብን፣ በጞሎቷ ይማሚን፡፡
+ + + + +

ዚሱራፌል አምሳላ቞ው ዹሆነ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ፡- ዚቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ዹሆነ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ በ571 ዓ.ም በዚህቜ ዕለት እንደ ሄኖክና ኀልያስ ተሰወሚ፡፡ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ዹሆነ ዚሱራፌል አምሳላ቞ው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ዚተሰወሚበት ዕለት ነው፡፡ እርሱንም 24ቱ ካህናተ ሰማይ ያመሰገኑት ሲሆን መቋሚያውን ወርውሮ ያፈለቀው ፀበል ዛሬም ተአምራት እያደሚገ አለ፡፡ ቅዱሱ ዓባይን በጥዑም ዜማው ቢያቆመው መልአክ መጥቶ ተቆጥቶታል፡፡ በተሰወሚበት በሰሜን ጠለምት ደብሚ ሐዊ ተራራ ላይ በቊታው እሁድ እሁድ ኚመሬት ውስጥ ዚኚበሮ ድንፅ ይሰማል፡፡
ዚቅዱስ ያሬድን ዕሚፍት በተመለኹተ አንዳንድ ጞሐፍት አባቶቜ በሞት እንዳሚፈ ጜፈዋልፀ ስንክሳሩም ‹‹ዐሚፈ›› ይለዋል፡፡ ነገር ግን ጻድቁ በተሰወሚበት በደብሚ ሐዊ ተራራ ላይ ብርድ በእጅጉ በጞናበትና በሚዶ በሚፈላበት በዚያ አስ቞ጋሪ ቊታ ላይ እጅግ አስ቞ጋሪውን ዹአዹር ጠባይ ተቋቁሞ በቊታው ላይ ቢያንስ 7 ቀን ሱባዔ ዹሚይዝ ካለ ራሱ ቅዱስ ያሬድ እንደሚገለጥለት ይታወቃል፡፡ እንኳንስ ቅዱስ ያሬድ ይቅርና እርሱን ያገለገሉት አቡነ ጊዮርጊስ ዘመንበር ዚተባሉት አባትም ሞትን ሳያዩ ተሰውሚዋል፡፡ አቡነ ጊዮርጊስ ዘመንበሹ ኢትዮጵያ ዚተባሉት ጻድቅ ሀገራ቞ው ጎጃም ሲሆን ዚአባትና ዚእናታ቞ው ሀገር ግን ሰሜን ጎንደር ና቞ው፡፡ ሲወለዱ መልአክ መጥቶ ወስዶ 24ቱ ካህናተ ሰማይን አሳይቶ ቅዱስ ያሬድም ሲዘምር ጥዑም ዜማውን አሰምቷ቞ዋል፡፡ ዚቅዱስ ያሬድም ፍቅር በዚያው ልባ቞ው ተቀርጟ ቀሚ፡፡ ጻድቁ ዋሞራ ገዳም ሁሉንም ተምሹው ጹርሰው በ25 ዓመታ቞ው ኚመነኮሱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በቅዱስ ያሬድ ስም ቀተ ክርስቲያን አሠርተዋል፡፡ ታቊቱንም አስገብተው በዚያው እያገለገሉ ሲኖሩ ‹‹እንደ ኀልያስና እንደ አንተ ሞትን እንዳላይ ለምንልኝ ›› እያሉ ቅዱስ ያሬድን ዘወትር ሲማፀኑት ቅዱስ ያሬድም አንድ ቀን ኚእነ አቡነ አሚጋዊ፣ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘርዐ ቡሩክ ዘግሜ ጋር በመሆን ተገልጩላቾው ‹‹አይዞህ ፈጣሪዬ ያልኚውን ያደርግልሃል›› ብሏ቞ዋል፡፡ አስደናቂውን ባለ ሊስት ዓምድ ዹሆነውን ዚቅዱስ ያሬድንም ገድል ዚጻፉት እሳ቞ው ነበሩ ነገር ግን ቅዱስ ገድሉን ደርቡሟቜ ኚወሰዱት በኋላ ዚት እንደደሚሰ አይታወቅም፡፡ ቅዱስ ገድሉም 382 ገጜ ያሉት ሲሆን 69 አስደናቂ ሥዕላት ነበሩት፣ በ132 ሐሚጎቜም ያሞበሚቀ ነበር፡፡ ጻድቁ ቅዱስ ያሬድን ‹‹እንደ አንተ እንዳልሞት
ይ ባወጣኝ›› እያሉ ሲጞልዩ ኚእግዚአብሔር ዚታዘዘ መልአክ ቅዱስ ዑራኀል መጥቶ አቡነ አሹጋዊን ‹‹ዙር አባ መንገለ ምሥራቅ- አባ መውጫውን በምሥራቅ በኩል ታገኘዋለህ›› ሲል አመለኚታ቞ው፡፡ እንደተባሉትም በስተምሥራቅ ሲዞሩ መልአኩ ሁለቱን ቅዱሳን በሐሹግ ስቊ ኚተራራው ላይ አወጣ቞ው፡፡ ተራራውም ላይ ቅዱሳን መላእክት እንደሻሜ ተነጥፈው ሲያመሰግኑ ቅዱስ ያሬድ አብሯ቞ው አመስግኗል፡፡

አቡነ አሹጋዊም በዚሁ ተራራ ላይ ዚእመቀታቜንን ቀተ ክርስቲያን ሠርተው ሥርዓተ ምንኩስናን አስፋፍተዋል፡፡ ዚተራራውም ስም እስኚ ዛሬ ድሚስ ‹‹ዙር አባ›› ተብሎ ይጠራል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በዚሁ ተራራ ላይ ሊስት ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት ዚተባለውን መዝሙር አስተምሯል፡፡ ይህም ቊታ እስኚ ዛሬ ድሚስ ዚዝማሬና ዚመዋሥዕት ምስክር ቊታ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ይጠቀምባ቞ው ዚነበሩ ጞናጜልና መቋሚያ በዚሁ ቊታ ላይ አሉ፡፡ ዚአቡነ አሹጋዊ ጭራና መቋሚያም አለ፡፡ ኹዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ አክሱም ተመልሶ ለሥጋ ወደሙ ጞሎት ዚሚያገለግሉትን 14ቱን ቅዳሎዎቜ በዜማ ተናገሚ፡፡ ቅዳሎውን በዜማ ዚተናገሚበት ቊታ መደባይታብር ይባላል፡፡ ይህም መደባይታብር ዚሚባለው ቊታ ለአክሱም ሰሜን ሆኖ ኚአክሱም ግማሜ ቀን ያህል በእግር ያስኬዳል፡፡

ቅዱስ ያሬድ ዚሕይወት ዘመኑን በጞሎትና በብሕትውና ለማሳለፍ ወደ ሰሜን ተራራ ምድሚ ጞለምት በመሄድ ብርዱ በእጅጉ በጞናበት በሚዶ በሚፈላበት በሐዊ ተራራ በጜሙና ተቀምጧል፡፡ ይህም ቊታ በሰሜን ጎንደር ሀገሹ ስብኚት በበዚዳ ወሚዳ ዹሚገኝ ነው፡፡ በዚያም ጉባኀ ዘርግቶ ትምህርት አስፋፍቶ ለሃያ ሁለት ዓመታት አስተምሯል፡፡ ዚእርሱ ደቀ መዛሙርት ሳዊሮስና ሳንድሮስ በልዳዶስ ዚሚባሉት ኚእርሱ ዚተማሩትን ዹዜማ ባሕልና ሥርዓት በትግራይና በሰሜን አውራጃ እዚተዘዋወሩ በዚገዳማቱ ሁሉ ስላስተማሩ ዚቅዱስ ያሬድ ድርሰት እስኚ ዛሬ ድሚስ ጞንቶ ኖሯል፡፡ ኹዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ ወገራና ወደ አገው እዚዞሚ ካስተማሚ በኋላ ዘመኑን ሁሉ በማኅሌት እግዚአብሔርን በማገልገል በጣእመ ዜማው ዲያቢሎስን ድል መትቶ በዚያው በሐዊ ተራራ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ ገብቶ በ571 ዓ.ም ግንቊት 11 ቀን እንደ ሄኖክና ኀልያስ ተሰወሚ፡፡

ቅድስት ቀተ ክርስቲያንም ቅድስናውንና አማላጅነቱን አምና በስሙ ጜላት ቀርጻ፣ ቀተ ክርስቲያን አንጻ፣ ድርስቶቹንም ዚቀተ ክርስቲያን መገልገያና ዚሥርዓተ አምልኮ መፈጞሚያ አድርጋ እዚተጠቀመቜባ቞ው ተገኛለቜ፡፡ በምናኔ በኖሚበት ሥፍራም በስሙ ገዳም ተገድሞ መናንያን አሰሹ ፍኖቱን ተኚትለው ጀዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው፣ በሚዶውንና ውርጩን ታግሠው በስሙ እዚተማጞኑ ይኖራሉ፡፡ በቊታው ላይ እሁድ እሁድ ኚመሬት ውስጥ ዚኚበሮ ድምጜ ይሰማል፣ ቅዱስ ያሬድ መቋሚያውን ወርውሮ ያፈለቀው ጾበል ዛሬም ድሚስ ዚተለያዩ ገቢሚ ተአምራትን እያደሚገ ይገኛል፡፡

ዓለም ኚሚያውቃ቞ው ዹዜማ ደራስያን ኚሞዛርትና ኚሌሎቜም አስቀድሞ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ ዕዝልና አራራይ በተሰኙ ዹዜማ ስልቶቜ ዚማይሰለቜና ዘመን ተሻጋሪ ዜማን፣ ዹዜማ ምልክቶቜንና ተለያዩ ድርሰቶቜን በመድሚስ ሀገራቜን ዹዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ሀብት ባለቀት እድትሆን አድርጓል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በሰዓታት ፣በወራትና በዘመናት ዹተኹፋፈሉ ድንቅ ምስጋናዎቜን ኚብሉያትና ኚሐዲሳት ንባብና ምሥጢር ለቀተ ክርስቲያን እንደ ሰምና ወርቅ አስማምቶ ዚአገልግሎት ሥርዓትን ዚሠራ ዚቀተ ክርስቲያን ዓምድ ነው፡፡ ዚቅዱስ ያሬድ ዜማ ድንቅና ጥልቅ ዹነገሹ ሃይማኖት አስተምህሮት ፣ ዚቅዱሳት መጻሕፍን ንባብ ትርጓሜ እንዲሁም ዚታሪክ ምስክርነትን ዚያዘ ኹፍ ያለ ዋጋ ያለው ድርሰት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዛሬ በጉባኀ ቀት ለዜማ ትምህርት ቀተ ክርስቲያን ዚምትገለገልበትን ሥርዓተ ትምህርትና ዚመማሪያ መጻሕፍትን ዹደሹሰ ሊቅ ነው፡፡ ድርሰቶቹም ምዕራፍ ፣ጟመ ድጓ፣ ዝማሬና መዋሥዕት ይባላሉ፡፡ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም በመምህሩ በጌዮዎን ወንበር ተተክቶ መጻሕፍተ ብሉያትና ሐዲሳትን አስተምሯል፡፡ ኚአቡነ አሹጋዊና ኹአፄ ገብሚ መስቀል ጋርም በመሆን በተለያዩ ዚሀገሪቱ ክፍሎት በጣና ቂርቆስ ፣በዙር አባ አቡነ አሹጋዊ ገዳም እንዲሁም ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ እስኚ ብርብር ማርያም በመሄድ ያስተማሚ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡ አጠቃላይ በሥነ ጜሑፍና በቋንቋ እድገት በነገሹ መለኮትና በታሪክ ትምህርት እንዲሁም በሥርዓተ ጞሎት ዚቀተ ክርስቲያን አንድነት በማስጠበቅ ሚገድ ጜኑ መሠሚትን ዚጣለ ታላቅ ሊቅ ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ብርሃኗና ሙሉ አካሏ ነው፡፡ ኚእርሱ ውጭ ቅድስት ኊርቶዶክሳዊት ቀተ ክርስቲያን ምን ልትመስል እንደምትቜል ማሰብ እጅግ ኚባድ ነው፡፡ ቀተ ክርስቲያን ግን እርሱ እንደዋለላት ውለታ መጠን አላኚበሚቜውም፡፡ ዚቅዱስ ያሬድ ሚድኀት በሚኚቱ ይደርብን፣ በጞሎቱ ይማሚን፡፡
ብለው በለመኑት መሠሚት ራሱ ቅዱስ ያሬድ በተሰወሚበት ቊታ በሰሜን ተራራ ምድሚ ጞለምት ተሰውሚዋል፡፡ በስማ቞ው ዚተሠራው ቀተ ክርስቲያን በሰሜን ጎንደር ይገኛል፡፡

ቅዱሳን መላእክት ምስጋና቞ው እሚፍታ቞ው፣ እሚፍታ቞ው ምስጋና቞ው ሆኖ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ እግዚአብሔርን ያለማቋሚጥ ያመሰግናሉ፡፡ ቅድስት ቀተ ክስቲያንም አምሳለ ኢዚሩሳሌም ሰማያዊት ናትና ይህን አብነት በማድሚግ ልዑል እግዚአብሔር ሃያ አራት ሰዓት ዚሚመሰገንበትን ዚምስጋና ሥርዓት ዘርግታለቜ፡፡ ሕያው እግዚአብሔርም ዚአዳም ልጆቜ በመላእክት ምስጋና እንዲያመሰግኑት በመውደዱ ሰማያዊውን ምጋና ይማር ዘንድ ቅዱስ ያሬድን መሚጠ፡፡ ያሬድ ማለት መውሚድ ማለት ነው ፡፡ ሰማያዊውን ጣእመ ዜማ ወደ እኛ ዚሚያወርድ ነውና፡፡ ‹‹ዋይ ዜማ ዘሰማዕኩ እመላእክት ቅዱሳን-ኹሰማይ ኚቅዱሳን መላእክት ዚሚያስደንቅ ዜማ ሰማሁ›› በማለት እንደተናገሚ በአክሱም መጻሕፍትን እያስተማሚ ሳለ ኚሰማያውያን መላእክት ጣእመ ዜማን ተማሚ፡፡ በተመስጊ ወደ ኢዚሩሳሌም ሰማያዊት ተነጠቀ፡፡ በዚያም ቅዱሳን መላእክት ልዩ ጣእም ባለው ዹዜማ ድምፅ ሊያመሰግኑ ሲዘምሩና ሲያሞበሜቡ አዚ፡፡ ኚጣዕመ ዜማውም ዚተነሣ ተደነቀ፡፡ ዚእግዚአብሔርን ስም እርሱም ኢዚሱስ ክርስቶስን በጠራ ጊዜ ዚሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዜማ ተገለጞለት፡፡ ተመልሶም ወደ ምሥራቅ ዞሮ እጁንም ዘርግቶ ‹‹ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጜዮን ›› ብሎ በአክሱም ኹተማ ሙራደ ቃል (ዹቃል መውሹጃ) በተባለቜው ሥፍራ ለመጀመሪያ ጊዜ ዜማን በዐውደ ምሕሚት አሰማ፡፡

ቅዱስ ያሬድ በ505 ዓ.ም በአክሱም ኹተማ ተወለደ፡፡ አባቱ አብዩድ ወይም ይስሐቅ እናቱም ክርስቲና ወይም ታውክልያ ይባላሉ፡፡ ሀገራ቞ው አክሱም ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ በተወለደ በ7 ዓመቱ አባቱ ስለሞተ እናቱ ክርስቲና ዚአክሱም ገበዝ ለነበሹው ለአጎቱ ለጌዲዎን እንዲያሳድገውና እንዲያስተምሚው በአደራ ሰጠቜው፡፡ ኹጌዮዎንም ቀት 25 ዓመት እስኪሆነው እዚተማሚ አደገ፡፡ ኚዚያም መፃህፍትን ማለት ብሉይንና አዲስን ተማሚ፡፡ ኹዚህም በኋላ መምህሩና አጎቱ ጌዮዎን ሲሞት እርሱ ተተክቶ ዚመጜሐፍ መምህር ሆነ፡፡ በዚህም ጊዜ በዲቁና ሚስት አግብቶ ልጆቜን ወለደ፡፡ ቀጥሎም ቄስ ሆነ፡፡ በእርሱም ዘመን ዘጠኙ ቅዱሳን ኹውጭ አገር በቜግር ምክንያት ተሰደው ስለመጡፀ ይህም ማለት በቁስጥንጥንያ መንግሥት ዮስጥንያኖስ በነገሠበት ኹ527 ዓ.ም እስኚ 565 ዓ.ም ድሚስ በምሥራቅ ቀተ ክርስቲያን ውስጥ በአንድ ባሕርይና በሁለት ባሕርይ ወገኖቜ ውስጥ ብዙ ሁኚትና ፍጅት ስለነበሚ ኚዚያ በመሞሜ ዚመጡ ካህናትና መነኮሳት ስለነበሩ ኚእነርሱም አንዱ በአክሱም ኹተማ አጠገብ ዹነበሹው አባ ጰንጠሊዎን ስለነበርፀ ቅዱስ ያሬድ እዚተመላለሰ ዹውጭውን አገር ቀት ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ይጠይቀው ነበር፡፡ ኚዚያም በኋላ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ዚውጭውን አገር ቀተ ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ለመጎብኘት ሁለት ጊዜ ተመላልሌ ዚሮምን ቀተ ክርስቲያንፀ ሁለተኛይቱን ሮም ዚተባለቜውን ዚምሥራቅና ዚቁስጥንጥንያን ቀተ ክርስቲያን ጎበኘሁ›› ሲል በመዝሙሩ እርሱ ራሱ ገልጟልናል፡፡

ኚቅዱስ ያሬድ በፊት በኢትዮጵያ ቀተክርስቲያን ደንበኛ ዹሆነ ቅኔና ዜማ ትምህርት ስለሌለ ደንበኛ ዹሆነ ቅኔና ዜማ ለማስገኘት ተዘጋጀ፡፡ ዚድርሰቱም መጀመሪያ ይህ ነበር፡- ‹‹ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጜዮን ሰማዹ ሣሚሚ ወበዳግም አርአዮ ለሙሮ ዘኹመ ይገብር ግብራ ለደብተራ›› ብሎ ኚነበሩት ኚብሉይና ኚሐዲስ ሊቃውንት አንዱ እርሱ ስለ ነበርና ለኢትዮጵያ ቀተ ክርስቲያንም ብዙ አሳብ ስለነበሚው ኚብሉይና ኚሐዲስ፣ ኚሊቃውንት መጻሕፍትም ኚነአትና቎ዎስ ኚነቄርሎስ ኚነዮሐንስ አፈወርቅ መጻሕፍት ለምስጋናና ለጞሎት ዚተስማሙትን ቃላት እዚመሚጠና እያቀና በአራቱ ክፍለ ዘመን፣ በመፀውና በሐጋይ በጾደይና በክሚምት እንዲነገር አድርጎ ወስኖ አዘጋጀ፡፡ ዚድርሰቱ ስም ድጓ ተባለ፡፡ ድጓ ማለትም በአክሱምና በአድዋ ቋንቋ ደጉዓ ማለት መዝሙሹ ኃዘን፣ ዹኃዘን ዜማ፣ ማለት ነው፡፡ ዹዜማውን ዓይነት በሊስት ክፍል ወስኖ ተናግሮታል፡፡ እነርሱም ግዕዝ፣ ዕዝል፣ ዓራራይ ይባላሉ፡፡ ግዕዝ ማለትም አንደኛ በመጀመሪያ ዹተገኘ ማለት ነውፀ ዕዝል ማለትም ሁለተኛ ሆኖ ኹግዕዙ ጋር ተደርቊ፣ ተጚምሮ (ታዝሎ) ዹሚነገር ማለት ነው፡፡ ዓራራይ ማለትም ሊስተኛ ተጚማሪ ሆኖ አራኅራኂ፣ ርኅራኄ አሳዛኝ ልብን ዚሚመስጥና ደስ ዚሚያሰኝ ማለት ነው፡፡ ዐፄ ገብሚ መስቀልና አባ አሹጋዊ ቅዱስ ያሬድ እነዚህ ሊስቱ በአንድነት እንደነበሩ ታሪኚ ነገሥቱና ገድለ አቡነ አሹጋዊ ይገልጜልናል፡፡ አቡነ አሹጋዊ ዚደብሚ ዳሞን ተራራ አቀማመጥ አይተው ደስ ስላላ቞ው፣ ንጉሡ ዐፄ ገብሚ መስቀል በዚሁ ተራራ ላይ እንዲኖሩበትና እንዲጞልዩበት ፈቀደላ቞ው፡፡ እርሳ቞ውም ይህንን ተራራ ኚተሚኚቡ በኋላ በተራራው ላይ ዚጞሎት ቀት ስለሌለ ንጉሡ ዐፄ ገብሚ መስቀልን አንድ ቀተ ክርስቲያን እንዲሠራላ቞ው ለመኑት፡፡

ንጉሡም ‹‹ቀተ ክርስቲያን ልሠራ ዚምቜልበትን ሥፍራ መርጠው ያመልክቱኝ›› ብሎ ነገራ቞ው፡፡ አቡነ አሹጋዊም ተነሥተው ዞሹው ቊታውን መርጠው አሳዩት፡፡ ኹዚህ በኋላ ንጉሡ በአዋጅና በትዕዛዝ ድንጋዩና እንጚቱ እዚተሰበሰበ በኚብትና በሠሹገላ እዚተጋዘ ተሰበሰበና ኚታቜ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ተሠራና ዚቀተ ክርስቲያኑ ሥራ በሁለት ዓመት አለቀ፡፡ ባለቀም ጊዜ ዚቀተ ክርስቲያኑ ሥራ ተመልካ቟ቜን አስደነቀ፡፡ ለዚሁም ንጉሡ ቀተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ዹሆኑ አልባሳት፣ ዚብርና ዹወርቅ ዚተደጎሱና ዹተኹፈፉ መጻሕፍትን አበሚኚቱ፡፡ ኹማኅበሹ በኩር ዚመጣውን ዚእመቀታቜንን ዚቅድስት ድንግል ማርያምን ጜላት አግብተው አቡነ አሹጋዊ ባርኚውና ቀድሰው ንጉሡና ጳጳሱ ቆሚቡ፡፡ ኚዚያም ዐፄ ገብሚ መስቀል በተራራው ላይና በግርጌ ላሉት ሠራዊት ግብር አብልተው ነዳያን ሁሉ ጠገቡ፡፡ ኹዚህ በኋላ ቅዱስ ያሬድ በአክሱም ሲያስተምር ሳለ በንጉሡ ዐፄ ገብሚመስቀልና አቡነ አሹጋዊ ወደዚህ ተራራ መጥቶ ቀተ ክርስቲያኑን እንዲጎበኝና እንዲዘምር ተጠርቶ ሲመጣ ኚተራራው ሥር ሲደርስ ዚአቡነ አሹጋዊን ደቀ መዛሙርት ማትያስና ዮሎፍ ዚሚባሉትን ኹወንዝ ዳር ዓሣ ሲያጠምዱ አግኝቶ ‹‹ይህ አሹጋዊ አባታቜሁ ደህና ነውን?›› ብሎ ጠዚቃ቞ው። እነርሱም ደኅንነታ቞ውን ነገሩት፡፡ ኚዚያም ቅዱስ ያሬድ ወደ ተራራው ላይ ወጥቶ ኚአቡነ አሹጋዊ ጋር በመንፈሳዊ አምኃ በፍቅር ተገናኙ ወደ ቀተ ክርስቲያኑም ሄዶ 3 ጊዜ ሰግዶ ኚተሳለመ በኋላ ዚሕንጻውን ማማር በአድናቆት ተመልክቶ ኹፍ ባለ ዹዜማ ድምፅ ዘመሚ፡፡

ቅዱስ ያሬድ በደብሚ ዳሞ ኹዘመሹ በኋላ ስምንት ቀን ያህል ኚአቡነ አሹጋዊ ጋር ሰንብቶ ንጉሡ ወደ አለበት ወደ አክሱም ተመልሶ ሲገባ አንቀጾ ብርሃን ተብሎ ዹተሰዹመውን ድርሰትን ቅድስት ወብፅዕት ብሎ በዜማ ደሚሰ፡፡ ኹዚህ በኋላ ንጉሡ ዐፄ ገብሚ መስቀልና አቡነ አሹጋዊ ኚቅዱስ ያሬድ ጋር አብሚው ወደ ሌላ ጠቅላይ ግዛት ጉብኝት ሄዱ፡፡ ኚዚያም በአንዱ ደሎት ላይ ዚቅዱስ ቂርቆስን ቀተ ክርስቲያን ሠርተው ተቀመጡ፡፡ በዚያም ቊታ ቅዱስ ያሬድ ሁለት ዓመት አስተማሚ፡፡ እርሱ እራሱ ዚጻፈው ድጓ ምልክት ዹሌለው ዛሬ በዚሁ ደሎት በጣና ቂርቆስ ይገኛል፡፡ ኹዚህም ደሎት ኚጣና ቂርቆስ ተነሥተው ንጉሡና አቡነ አሹጋዊ ቅዱስ ያሬድም ወደ ደጋው ወደ ጋይንት ወጡ፡፡ በዚያም አንድ ትልቅ ተራራ አግኝተው መውጫው ጠፍቶባ቞ው ሲጚነቁ አሹጋዊም ‹‹ምነው ዚደብሚ ዳሞው ዘንዶ ኹዚህም ተራራ
2025/02/25 11:05:46
Back to Top
HTML Embed Code: