Telegram Web Link
የኃይል መገኛው የት ነው? - አንገብጋቤ ጥያቄ
ቫረስና ቴሪየን አለቃና ምንዝር ናቸው፡፡ ቲሪየን ከመሳፍንቱ ወገን ሲሆን ቫረስ የነገስታቱ አማካሪ ነው፡፡ የወይን ብርጭቋቸውን እያጋጩ ስለ ዙፋንና ስለ ኃይል አሰላለፍ ሞቅ ያለ ጨዋታ ይዘዋል፡፡ በመሐል ይሄንን ወሳኝ ጉዳይ አነሱ፡፡
.
“እንቆቅልሽ ትወዳለህ ጌታዬ?” አለ ቫረስ፤ ከወንበሩ ሳብ ብሎ ወደ ቲሪየን አንገቱን እያቀረበ።
“ለምን ጠየከኝ? ከእንቆቅልሾቹ አንዱን ልትነግረኝ መሆኑ ነው?” ብሎ በወይን የተሞላ ብርጭቆውን እንደጨበጠ ቫረስን ለመስማት ወንበሩ ላይ ተስተካከለ።
“…ሦስት ኃያላን ሰዎች በአንድ ቤት ውስጥ ተቀምጠዋል” አለ ቫረስ ንግግሩን ሲጀምር “አንዱ ንጉሥ ነው፤ ሁለተኛው ደ'ሞ ጳጳስ፤ ሦስተኛው የናጠጠ ሀብታም። በመካከላቸው ጎራዴ የታጠቀ ወታደር ቆሟል። ወታደር ስልህ ይኼ በየጦር ሜዳው ጀብዱ እየፈጸመ ወይዛዝርቱና እረኞች የእሱን ስም እየጠሩ የሚዘፍኑለት ዓይነት አይደለም። ተራ ወታደር ነው፤ ቅጥረ ነብሰ ገዳይ የሚሉት ዓይነት ወታደር። እውቀትም የለው፤ ፊደል ቆጥሮ የማያውቅ መኻይም ወታደር። ታዲያ ሦስቱ ኃያላን ሰዎች አንድ በአንድ ጮኸው ለወታደሩ ትዕዛዝ ይሰጡታል፤ ‘እነዚህን ሁለት ሰዎች ግደላቸው!’ ይሉታል።
በመጀመሪያ ንጉሡ “እኔ ሕጋዊ ገዥህ ነኝ! ትዕዛዜን ፈጽም!!” አለው።
ቀጠለ ጳጳሱም “በአማልዕክቶች ስም ይዤሃለሁ! የምልህን አድርግ!!” ሲል አዘዘው።
ባለጸጋውው“ትዕዛዜን ከፈጸምክ ይኼ ሁሉ ወርቅ ያንተ ይሆናል!” አለው…
...አሁን ጥያቄው ከሦስቱ ማን ይድናል? ማንስ ይሞታል?” አለ ቫረስ እንቆቅልሹን እንዲፈታለት ቲሪየንን አተኩሮ እየተመለከተ።
ቲሪየን ጥቂት አሰብ አደረገና፣
“እንደ ባለጎራዴው ሰውዬ ማንነትና ፍላጎት ይወሰናላ...” ሲል መለሰ።
“እንደዚያ ይሆናል ብለህ ነው ጌታዬ?” አለ ቫረስ የነገሩን ውስብስብነት ለማስረዳት በአእምሮው ቃላት እየመረጠ። "ሰውዬው ተራ ሰው ነው፤ ብዙም የወርቅ ፍላጎት የለውም። ደ'ሞም ከራሱ ውጭ የሚንከባከበው ወይም የሚያስተዳድረው ሚስት የለው ድስት! እምነትም ላይ እስከዚህም ነው - አልተቀባም፤ አማልዕክት ስለሚባሉት ነገሮች ብዙም ቦታ አይሰጥም። በሌላ በኩል የነገሥታትም ደም የለው - ሊነግስ አይችልም። ያለው ብቸኛ ነገር ቢኖር ያ ስለታም ቆርቆሮው ነው" (ጎራዴውን ማለቱ ነው)
“ታዲያ እኮ የያዘው ስለታም ቆርቆሮ ሕይወትንና ሞትን፣ መኖርና አለመኖርን ይወስናል! ጎራዴ እስካለው ድረስ ኃይል አለው ማለት ነው፤ የፈለገውን መወሰን ይችላል...”
“እርግጥ ነው ጎራዴው መግደልና አለመግደል ይችላል፤ እሱ ላይ አልተሳሳትክም። ዳሩ ግን የኃይል ምንጭ ‘ጎራዴ ነው’ ካልን ወታደሮች እያሉ ሰዎች ሁሉ ለንጉሥ መገዛታቸው እንግዳ ነገር አይሆንብህም? ሌላው ቀርቶ እጅግ ፈርጣማዎቹ ወታደሮች እንኳን ለጩጬ አልጋ ወራሽ ይገዛሉ፤ ለምን?... ዋናው ጥያቄ ‘ለምን ይገዛሉ?’ የሚለው ነው” አለ ቫረስ ፈገግ እያለ።
“ምክንያቱም ንጉሡም ሆነ ጩጬው አልጋ ወራሽ ሌሎች ወታደሮችን መጥራት ስለሚችሉ ነዋ!!” ቲሪየን እንደመበሳጨትም፣ እንደመቆጣትም እያለ ፈጥኖ መለሰለት።
“ስለዚህ እውነተኛ ኃይል ያለው ‘ሌሎች’ የተባሉት ወታደሮች ጋር ነው ማለት ነው? ግን ለምን እነሱስ ሳያመነቱ ይታዘዙታል? ጎራዴ ታጥቀው ሳለ በቀላሉ ለሚያሸንፉት ሰው መታዘዛቸው ምክንያቱ ምንድን ነው?”
ቲሪየን መልስ ሳይሰጥ ዝም አለ።
“አንዳንዶች ‘እውቀት ኃይል ነው’ ይላሉ። ሌሎች ደግሞ ‘ኃይል ከእግዚአብሔር ነው’ ሲሉ ይደመጣሉ። ጥቂት የማይባሉ ሰዎችም ‘ኃይል ከሕግ ይመነጫል’ ሲሉ ይመሰክራሉ። ችግሩ ግን አንዳንድ ጊዜ በሕግ ሥልጣን የተሰጠውም፣ በእግዚአብሔር የተቀባውም፣ ምሁር የተባለውም እንደ አንድ ተራ ሰው ምንም ማድረግ የማይችሉ አቅመ ቢሶች ሆነው ይገኛሉ” ብሎ ቫረስ ቲሪየንን ተመለከተው። ታዲያ አለ የተባለው ኃይል የታለ? በሚል አኳኋን ዐይኑን ከቲሪየን ላይ ሳይነቅል ዝም ብሎ ሲቆይ...
“ድሮም እንቆቅልሽ የሚሉት ነገር እንደማይጥመኝ ቀድሜ አውቀዋለሁ” አለና አቀርቅሮ ጭንቅላቱን ካሻሸ በኋላ ቀና አለ። ምን ብሎ እንደሚመልስለት ስለጨነቀው ራሱ ቫረስ መልሱን እንዲነግረው በዝምታ ይጠብቅ ጀመር።
ቫረስ ፈገግ ብሎ፣
"ጌታዬ፣ ኃይል መገኛው ሰዎች አለ ብለው የሚያምኑበት ቦታ ነው። ነገሩን ሲያስቡት ትንሽ ፈገግ ያስብላል። ግን ደግሞ እውነት ነው፤ ኃይል የሚኖረው ሰዎች አለ ብለው የሚያስቡበት ቦታ ነው። ልክ እንደ ጥላ ነው - ግድግዳ ላይ እንደሚታይ የሰው ጥላ፤ እጅግ በጣም ኮስማና የሆነ ሰው እንኳን እጅግ ግዙፍ የሆነ ጥላ ሊፈጥር ይችላል” አለና የወይን ብርጭቆውን አንስቶ ወደ ጉሮሮው አንቆረቆረ...
*
በተለይ የፊልሙ ወዳጆች ይሄንን አንብባችሁ በትዝታ መለስ እንደምትሉ አልጠራጠርም!!
ማስታወሻ፡- ፊልሙን ላልተመለከታችሁ አንባቢዎች… ቫረስ እና ቲሪየን ‘Game of Thrones’ በተሰኘ ተወዳጅ የእንግሊዘኛ ተከታታይ ፊልም ላይ የሚተውኑ ገጸ-ባሕርያት ናቸው። የሚነጋገሩት ሐሳብም ከዚያው ከፊልሙ ላይ ተቀነጭቦ ለትረካ እንዲስማማ ተደርጎ የተተረጎመ ነው።) ሚያዚያ 3፣ 2011 ዓ.ም 💙

መሳፍንት ተፈራ

@wegoch
@wegoch
@paappii
እስኪ አንድ ጊዜ ሰዎች attention

እስኪ እናስበው🙄 እናስታውሰው ,እናውሳው😭 የዛሬ 3 አመት ገደማ ነበር ይህ የምነግራቹ ነገር እድሜያቸው ከ17 በታች ለሆኑ አይመከርም💀

እንዳልኩት የዛሬ 3 ዓመት ገደማ ሁለተኛው ክ/ጊዜ አልቆ በሶስት ስፖርት እንደ ሆኑ በማወቅ በደስታ ትጥቃቸውን ቀይረው hpe teachern ይጠባበቁት ጀመር የዛኔው g-9A(meselegn🙄)ያሁኖቹ g-12 this year ተፈታኞች😭,,teacher g/egzier(hpe) ተናገረ :ውጡ ተውሎ ቧሉ😂 ተማሪዎቹም እነሆ ወጡ ለካ ዛሬ ሚማሩት መከረባበት ነው ያቺ ጥቁር ፍራሽም ያው ፀሀይ ላይ ግላላች

ተጀመረ 😱አባቴ ተጀመረ ሀብቶም😂😂ብድግ 😱ለጥ,ዮሀንስ እንጣጥ እንደ መከርበት ነገር,ያው የሴቶቹ ግልፅ ነው ኩስትርትር ብላ ትሄድና ሮጥ ሮጥ ብላ እጇን እንደሚሰጣ ፎጣ ወደ ኋላ ከዛ
1.ወይ በጭንቅላቷ ስንቅር ልክ እንደ ደመራ ቋሚ ከዛ teacher ደንገጦ ጠጋ ይልና ባላየ ገፋ
2.ወይ እንደተለመደው የተጣመመ ሮል(ከፍራሹ ውጭ ሌላ ታሪክ😭)
3.አለበለዚያ ደሞ የሚገርም action (like አንዷ ሳትጨርስ አንዷ እንደመዝነብ)ነበር

አሉ ደሞ እኔ ስም አልጠራም አንከረበትም ብለው ጥጋቸውን ይዘው በሌሎች የሚስቁ

እእእ ግማሹ :እንዲ አርገህ እኮ እንዲ ስታረግ ቀላል ነዉ
አንደኛው:ቀስ ብዬ ቶሎ ልበል(😂በጣም ድንጋጤ)

💀💀😱😱በዚህ ሁሉ መሀል ነበር አሰቃቂው አደጋ ምስኪኑ የ15 አመት ከሩብ የሆነው ግቢዉ ዉስጥ famousu mr.hpe የሚወደው (😘ነገር ናቸው),mr.ግርማም የሚመቻቸው

እስኪ guess ማን ይመስለሰችኋል አው ልክ ናቹ(👀) ሱጥዎታ😭

አው ሟች ስጦታው አህመድ ወደ ተደገሰለት የሞት ድግስ እየሮጠ ነበር የገባው ነገርየው dive roll ምስኪኑ ልጅ ደሞ dive ጦር ይመስል ነበር የተሰካው እስኪ ያሳያቹ ላጥ ላጥ ብሎ ሮጠና ብድግ dive ፍራሹ ውስጥ ሽንቁር(ቋ ሲል የሰሙም አሉ)ሁሉም ፀጥ ረጭ ብሎ ነበር😭😱ሟችም ተንጋሎ ወቀ።😭😭😭😭

ግማሹ በስመአብ ወወልድ : ግማሹ ያረቢ ቢስሚላ : ግማሹ በየሱስ ስም : ግማሹ ብዛየው ድረስልኝ(የሰፈራ famous አዋቂ(ያው ጠንቋይ)): ግማሹ የ odin ልጅ thor አውጣኝ እያሉ የየራሳቸውን እምነት አመለከቱ

ገሚሱ:ባካቹ የምግብ እጥረት ነው አሁን ይነቃል
ገሚሱ:እየተንሾካሾከ ቡዳ በልቶታል አላልኩሽም
ገሚሱ:ባካቹ ቀልዱን ነው (ያብስራ ቢኖር እሱ ነበር ያለው)
ገሚሱ: ብር ፈልጎ ነው መሰለኝ(ባክ ተነስ ባነናለል)
ገሚሱ:ፀሀዩ ነው ቢሉ ምስኪኑ ልጅ ንቅንቅ ሊል አልቻል

mr .g/egzier 😱ክው ብላ እኔ ክው ልበል ሱጥወታ ሱጥወታ ሱጥ ስጥዎ ሱሱ ልጁ አይንን ጨፍኖ ሌላ ታሪክ ውስጥ teacher university እያለ የተማረው ትዝ አለው 😱ለካ ከ100 ሰዎች አንዱ ላይ የሚፈጠረው "the tounge the eat"የሚባለው ልክ ሰዎች እርቧቸው በፀሀይ ከዘለሉ:ከተንከባለሉ የራሳቸውን ምላስ ዋጥ 😱አርገው ይበሉና በዛው ከጠገቡ ይሞታሉ

teacher መፍትሄው ምን እንደሆነ ስለሚያውቅ ከድንጋጤው ባነነ ከዛም ሰልቤን ሱቅ ላካት
እስኪ ገምቱ ምን ይዞ የመጣ ይመስላችኋል የምላስ መጎተቻ:ፀበል:mr.bio ካላቹ ተሳስታችኋል መድሀኒቷ ሚስጥር ነበረች እንዳይረክስ ነው መሰለኝ ደብቆ አመጣና በዝግታ ልጁ ፌንት ከነቀለበት ፍራሽ ከፍ አርገውት አፉ ውስጥ መድሀኒቷን ሲከታት ደነገጡ እንዴ ምንድነው ሚሰራው እንዴት ይሆናል ለልጁ የሰጡት የዛኔዋ የሀለት ብር ከሀምሳ ኮክቴል የፆም ብስኩት ነበር,ነገር ግን ከሀሉም አጀብ ያስባለው የሱጦታ አይን ቀለስለስ ብላ ግልጥ ማለት አፎቹም ቀስ ብለው ማላመጥ መጀመር ነበር ልጁ ቁልጭ ቁልጭ ብሎ ምን ቢል ጥሩ ነው teacher እኔ እኮ አልፆምም የፍስኩን አትገዛልኝም ብላ ቁልጭ ፍጥጥ ጨምሩ

ተማሪዎችም በመደንገጥ በመደመም በመደሰትም ከላይ በጠቀስኩላችው እምነታቸው ማመስገን ጀመሩ ከሰዐታት በኋላ ፍራሹን ፈቀቅ ሲያረጉት ቴራዞ ተሰንጥቋል ያ ቦታ እስከ ዛሬ ስጦታው ኮክቴል እየተባለች ነው ምትጠራው ታድያ አሁን ውሀ ፈልቆ ህዝቡን በልማት ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር ለዜጎች የስራ እድል ፈጥሯል በዚህ መቆፈርያ ጭንቅላቱ አሁን social science እየተከታተለ ይገኛል(ክብር ለተሸላሚ መቆፈርያ ራስ አርሶ አደሮች)


የምር ግን ተዐምር ነው መትረፉ ተብሏል(እንኳን ተረፍክልን)😭😱

የኮክቴሏ ተዐምር ወይስ የልጁ ረሀብ እሱ ይዳኝ ለማንኛዉም መልካም የህማማት ጊዜ,,funfact do u know if u laugh its sin is on me meselegn ,,,,bye


Info----teacher hpe
Writer-ab
Best boy -👀👀
Writting time-from 1:00-infinite

👴peace

@wegoch
@wegoch
@Mahletzerihun

#abenaw
...
ወላንሳ አመለ ምቹ ህፃን ሆኜ ላባ በጣም እወድ ነበር። ነጭ ላባ። ከዶሮ ተነቅሎ የቀረ። ምናልባትም ከሞተ ዶሮ። ልስላሴዉ እስካሁን ላባዉን በአንሸራሸርኩበት የአንገቴና የፊቴ ክፍል ይሰማኛል። አይኔን እከድንና አንገቴን በላባ አባብል ነበር። ይለሰልሳል። የሚጣፍጥ መለስለስ። አይዞሽ! አይዞሽ! የሚል መለስለስ። ማንም ሲያደርግ አይቼ አይደለም። ያ በጣም ለስላሳ ነገር ላባ እንደሚባል ያወኩት ሳድግ ነዉ። አንዳንድ ነገር ግን ሲገርም።ነገሮችን መቼ ነክተን ፤ ቀምሰን ፤ አሽትተን ጣእማቸዉን ፤ ባህሪያቸዉን እንዳወቅን አናዉቅም። ግን ደሞ እናዉቃለን። ማንም ሳይነግረን እንኖረዋለን። የላባን ልስላሴ ማን ነገረኝ? ደመነፍሴ? እንጃ!! ከዛ በኋላ ለልቤ የሚለሰልሱ ነገሮች ሁሉ ያንን ላባ ያስታዉሱኛል። ልክ እንደ አንተ!!
...
መንገድ ስወጣ እጄ መሃል ምራቄን አድርጌ አካሄድና መንገዴን በምራቄ አቅጣጫ የምወስን አይደለሁም። ዉይ ያን ያህል ወግ ከየት አመጣለሁ? ከርታታ ተጓዥ ነኝ። ወደ አምላክ ጥላ ለመቅረብ ፤ ወደ ሰዉ ልብ ለመድረስ ፤ ለነፍሴ ጩኸት ፋታ ለመስጠት እግሬን የማወናክር ድኩም ነኝ። በንፋስ አቅጣጫ ጥላዬን የምዘረጋ መንገደኛ ነኝ። ከፊት ከሚቀድመኝ የቀን ጥላዬ ከኋላ ከሚከተለኝ የምሽት ጥላዬ ፉክክር የምገጥም አላዋቂ ነኝ። ለአረማመዴ ወግ የለኝም። ምን ትሰራለህ ከስሬ? ጩኸቴ አይረብሽህም? አርያም የሚደርስ ሳቄ ከጥሞናህ አያናጥብህም? ጥያቄዎቼ ከአቅምህ በታች አይሆኑብህም? ፍለጋዬ ዉል አልባ ሆኖ አያበሳጭህም? እንደ እኔ ነህ ወይስ እኔን ሆነሀል? ከመንገዴ ፈቀቅ ብልልህ አብረኸኝ ትጓዛለህ? ወይስ በአካሄዴ ለመሳለቅ ጊዜ ትጠብቅልኛለህ? አትተወኝም ወደመንገድህ ልምጣ? ወይስ ወደ እኔ መጥተህ እዚሁ እንቅር? ብዙ ጥያቄ አለኝ! ካላሰለቸዉህ።
...
ደስ ትለኛለህ። ስትስቅ ፤ ስታወራ ፤ ስትዘምር እና ሁሌም ደስ ትለኛለህ።
በቀዳዳዉ ማንነቴ አጮልቄ ሳይህ ዉብ ነህ። አልነገርኩህም አይደል? በጣም
ዉብ ነህ። እንደ ጨረቃ!! ለስላሳ እንደ ላባ!! ... እጄን ስትይዘኝ አዋጅ የለህም።
ዝም ብለህ ያዝ። ስትወድ እወቁልኝ አትደግስም። ዝም ብለህ ዉድድድ።
የሚወደድ ነገር ሁሉ ነህ። እንቅፋት የበዛበት እድሌ ላንተ ልብ እንዳይተርፍ
የቤቴን አድባር እለማመናለሁ። ቂጣ ከቆሎ እጥላለሁ። እንደወደድከኝ ልወድህ... እንደያዝከኝ ጥብቅቅቅቅ ላደርግህ። ከሚዛኔ እንዳልጎል ፥ ከአይኖቼ ስር እንዳላጣህ እለማመናለሁ። ልቤን እለምናለሁ። እቅፍህ መሃል እንዲያደርሰኝ፥ ብተወዉም እንዳይረሳኝ ለፈጣሪን ጧፍ እጣን እሳላለሁ። ያልገባሁት ሱባኤ
ያሳስበኛል። ያልፆምኩትን ፆም የሻርኩ ይመስለኛል። ልቤ ይደነግጥብኛል። ግን
ምንድነዉ?

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Ruth habte mariyam
መብራት ሲጠፋ አልወድም። የምሰራው ኖሮኝ ሳይሆን አይምሮዬ
እንዳይሰራ ብዬ። ያዳፈንኩትን ትዝታ እንዳያጠነጥንብኝ! ስለጨለመ
የማየውን እንዳያስቀር ሳይሆን ከራሴ ጋር እንዳያስተያየኝ። መብራት ካለ
መፅሃፍ ከማንበብ ወደ ስልክ፤ ከስልክ ወደ ቴሌቪዥን። ብቻ ብዙ
ግርግር። የስልኬ ባትሪና የተለኮሰው ሻማ ወደማለቁ ነው። ያስታወስኩህ
ዛሬ ባይሆንም ትዝ ባልከኝ ቁጥር ነፍሴ ራሷን የሆነ ነገር ውስጥ ለመደበቅ
ትጣደፋለች። ሁሌ አይሞላላት ሆኖ ለትላንቴ ያጋለጠችኝ ጊዜ ፀፀት
ያናውዘኛል። አየህ ዛሬ ሊመሽብኝ ሲቃረብ ነቅቻለሁ። የሚቆጨኝ ላንተ
የደከምክልኝን ያህል አለመሆኔ ነው። ልብ ስገዛ፤ እሳቴ ሲበርድልኝ፣
የልጅነት አመሌ ሲሟጠጥ የለፋህባት ሰው ውጤቷን ሳታይ እህል ውሃችን
አለቀ። ያላወራረድኩት ሂሳብ ሃሳብ ሆኖብኝ ቁጭት ያንገበግበኛል።
ምነው እንደአሁኗ አይነት ሴት ሆኜ ጥለኸኝ በሄድክና ከኔ ስህተት
ባልተገኘ... ምነው ገፊ ሆኜ ግፍ ባላስቆጠርኩ... ምነው ያን ሁሉ መንገድ
ችዬህ መጥቼ ቁልቁለቱ ላይ አቅም ከዳኝ?! ምነው?.
የራስህ የሆነ ከየትኛውም ጥንዶች ያልተኮረጀ አወዳደድህን እወደዋለሁ።
ህይወትን የምትረዳበትን አቅም እሸነፍለታለሁ። ልጅን በከረሜላና በሚታይ
ነገር መሸወዱን ነው ያልቻልክበት። አለመቻልህ ካንተ አርቆኝ የኑሮ አዙረኝ
አታዙረኝን በሜዳ ተሽከርክሬ እነአይሆኑ ላይ ወድቄ ተነሳሁ። ከአንዴም
አራቴ። እርግጥ ዛሬ ዓለም ስቃልኛለች። እኔ ግን ሳቋን በሳቅ መመለስ
ከበደኝ። ቅጣቴን አለመቀበሌን ተቀብሎ መኖር አቃተኝ። ያጎደልክብኝ
ካጎደልኩብህ ተጣፍቶ ሳለ ለምን እኔ ደልቶኝ አንተ አልተካስክም?! እግዜር
ለምን ያንተን ልብ አክሞ አልያ የጉዳትህን እጣ ለእኔ ሰጥቶ ፍትሃዊ
አይሆንም?!
እነዛ አመታት ታሪኮቻችን ተሰነደባቸው። ገና ከ ሀ ስንጀምር አይኔን
የገለጥኩት ባንተ ነው። ከቤት እንደወጣሁ ከከተማውና ከሰው ሳልቀላቀል
አንተን አወቅሁ። አምስት ቦታ ወደኋላ ተሾርቤ፤ የሴትነት ቅርፅ እና መልኬን
ለመሸሸግ ሰፊ የወንድ ጅንስ ሱሪና ትልቅ ጃኬት ለብሼ። የልብሴን እጀታ
በጥርሶቼ እያኘኩ ዓይኖቼን ከወንድ ዓይኖች በማሸሽበት ጊዜ። እንደዛሬ
ጭኖቼ በአጭር ቀሚስ ሳይጋለጡ፤ ሴትነቴ ሳይጎመራ... በዛ ማንንም
በማልስብበት እድሜዬ የወደድከኝ አንተ! ጡቶቼን ለመጀመሪያ ጊዜ
ያሳየሁህ አንተ! አይን አውጥቼ ስጎረምስ የአፍላነት እብደቴን የታገስክልኝ
አንተ! በታሪክህ ውስጥ ብዙ ታሪክ ያለኝ እኔ! ቁጣህን በፈገግታ የምረታ፤
በሀይልህ ውስጥ ፍቅርህን አጮልቄ የማይ እኔ!
አዎ እንዲህ ነበርን። በህይወት አብዝቼ የሚፈልገውን ነፃነት ያገኘሁት
ካንተ ነው። በፍቅር፣ በባህል፣ በሃይማኖት ስም በሚደረጉ ማሰሪያዎች
ሳትሸብብ መንፈሴን ነፃ ዓለም አሳይተሃታል። የማልቆጥርልህ ውለታ፥
የማላስታውሰው ኑረት የለም። ስምህን በክፉ ማንሳት አይሆንልኝም።
ስሄድ ብዙ ሳልርቅ የምትጠራኝ መስሎኝ ነበር። የማልመለስበት እስክደርስ
ለምን ጠበቅከኝ? ለምን እንድጨክንብህ ህመም እያሰቃየ ሲያሳድረኝ ዝም
አልክ? ብቻ ሁሉም መሆን ስለነበረበት ሆኗል። የምፈልገው ከፍቶህ
እንዳላይህ ብቻ ነው።
በምትወደው ጠይምነቴ፤ በምወደው ቀና ልብህ
እለምንሃለሁ...
ለተጫነብህ ሙጫ ትዝታ... ስላጎደልኩት የመኖር ትርጉም...
ስላጣመምኩት የህይወት መንገድ...
ይቅርታህን!!!!!!!
.
የመብራቱ ብርሃንና የቴፑ ድምፅ ሳይቀዳደሙ እኩል ደረሱ።
"ሙሉውን ሰውዬ ስቀናንስህ፣
ሆኜ ተገኘሁ ላንተ የማንስህ!"
ኩኩ ሰብስቤ ነበረች።

@wegoch
@wegoch
@Mahletzerihun

#Enqopawit enqopa 🖤
በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት፣አውሮፓ ውስጥ ነው። ሁለት ወጣት መነኩሲቶች በማታ አብረው እየሄዱ ሳለ ሁለት ጋጠወጥ ወታደሮች ይይዟቸውና አስገድደው ይደፍሯቸው ጀመር። መሀል ላይ.... አንደኛዋ መነኩሲት ወደ ሰማይ እየተመለከቱ «አምላኬ ሆይ፤ የሚያደርጉትን
አያውቁምና ይቅር በላቸው!» በማለት ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ፀሎታቸውን
አሰሙ። ሁለተኛዋ መነኩሲት አንዴ ወደ ደፋሪአቸው አንዴ ደግሞ ወደ ሰማይ
እየተመለከቱ በተቆራረጠ ድምፅ «ይሄኛው. . . የሚሰራውን . . .ያውቃል!» አሉ
አሉ።
-
የምንሰራውን የምናውቅ ሰዎች የዚህ ሳምንት ንሰሀ ትዝ ብሎኝ ነው! 🙂

@wegoch
@wegoch
@paappii
#Gemechu Merera Fana
#እውነት_እውነቱ_ከተወራማ_ጉጉት_ይደበዝዛል_ጃን!
~
~
ፈሪ ነኝ? አዎ ግጥም አድርጌ... በቀን ሀያ ሰባት ሰአት ከእሩብ ሰኮንድ እንቦቀቦቃለሁ፡፡ የፍርሀቴ ትልቁ ፍርሀት ግን ፈሪ መሆኔ መታወቁ ስለሆነ ከምንም ፊት ደፍሬ እቆማለሁ፡፡ ደፋር የሚያስብሉኝ ታሪኮቼ በሙሉ ተጋድመው ሆድእቃቸው ቢመረመር ፍርሀት ይፍለቀለቃል፡፡ የደፈረኝ ሰው እኔን ፈሪ አድርጎ ማየቱ ነው የድፍረቴ እና ምላሽ የመስጠቴ ምንጭ፡፡
የሆነ ግዜ እንዴት ሆነ...ስምንተኛ ክፍል መሰለኝ... ትላንቶቼ ይደበዝዙብኛልኮ አንዳንዴ የማስታውሳቸው በፍቅርተ ነው፡፡ ስምንተኛ ክፍል... ፍቅርተ እግሯን ምን መቷት እንደሆነ እንጃ ስታነክስ... አዎ የዛኔ ነው... ስምንተኛ ክፍል፡፡
ደፋሮች ነን የሚሉ ሁሉ ይሰባሰባሉ፡፡ ምናልባት አንዱ ከአንዱ ተነካክሶ ብዙ ያለመጎዳት ፍርሀት ነው የጓደኝነታቸው ስሩ፡፡ ካልተሰበሰቡ ለብቻቸው ሰው አይደሉም... ጎዶሎ ናቸው፡፡ እና እኚህ ስብስብ ፍጡራን ሰብሰብ ሲሉ ድፍረታቸው ብቻ ሳይሆን ንቀታቸው ይጨምራል... ፈሳም ተሰብስቦ... ይጨመቅና አንድ ቦርጫም ጉልበተኛ ያበጃሉ፡፡ አንድ አካል ሲሆኑ አንዱ እጅ (ወፈር ያለ ሆዳም) አንዱ እግር (አሯሩጦ የሚጠልፍ ነገር) አንድ አይን (ንቀትኛ የሚያጉረጠርጥ) አንድ ፀጉር (ስራ ፈት ፂማም) እኚህ ተሰባስበው አንድ ፍጡር ይሰሩና ያስፈራራሉ፡፡ ከዚያ መሀል ደግሞ አንድ ቀዥቃዣ አይጠፋም... የጠብ ቅመማ ጥበብ የተካነ... አጫጫር የሚችልበት... ድምፅ ብቻ የሆነ፡፡ አይጠፋም አንድ... ኤልያስ ነበር እሱ፡፡
በድሉ ሱቅ ጋር ተቀምጫለሁ፡፡ ከእቤት ለመውጣት ለሰነፉ ሰዎች ሲጋራ ኮካ ምናምን አመላልስና የሰጡኝን ይሰጡኛል፡፡ ትዕዛዝ እየጠበኩ ተቀምጫለሁ፡፡ እነ ኤልያስ ተሰብስበው እያለፉ ነበር፡፡ ጠብ አደን ስምሪት ላይ ያሉ ይመስላሉ... ስድስት ይሆናሉ...
<<ይሄ ልጅ ያፈጣል!>> ኤልያስ ነበር...እንዲህ እስኪላቸው ድረስ እኔም ራሱ ማፍጠጤን አላስተዋልኩም፡፡
<<ምን ታፈጣለህ?>> ተጠጋኝ... እድሜ ልኬን ሲያቀኝ ሳፈጥ ነበር፡፡ የኖረ ልምድ ለአዲስ ፀብ ጠፍጥፎ ሲያመቻች እንጂ
<<መብቴ ነው>> ብቻውን ላነጥረው እያሰብኩ
ነው፡፡
<<ይዋጣልን እንዴ?>>
<<አልፈልግም>> ሳቁ ሌሎቹ...ላነጥረው እያሰላሁ ነው አሁንም
<<ከዚህ በኀላ ስታፈጥ እንዳላይህ...>> ከቲቸር የኮረጀው ነው? <ወላጅ ሳትይዝ እዚህ እንዳላይህ> ብለውኝ ያውቃሉ ቲቸር ኬሚስትሪ፡፡
<<ለምን ዝም ብለህ አታልፍም?>> አልኩት...በድሉ ብቅ አለ፡፡
<<አይንህን አጠ...>> ቃሉን አልጨረሰም አፍንጫውን መታሁት፡፡ ወደቀ፡፡ ሌሎቹ ከበው ይደበድቡኛል... (<ኸረ ገደሉት> ትላለች የሆነች ሴትዮ... ድምፅዋ ረበሸኝ?) ኤልየያስ ሳልመታው በፊት ምን ሊለኝ ነበር? አይንህን አጠፋለሁ? አጠፋሪስ? አጠናግረው እስቲ? አጠንክር? ቢጨርስ ምናለ?
እየደበደቡኝ ነው... የሻሞ ቡጢ ይደርሰኛል፡፡ ኩርኩም ራሱ አለው... ቀሽሞች፡፡ በድሉ ብቅ ብሎ እያየ ነው? የሚገዛው ቢመጣ ጨው አይሸጥም? ይሄ ስግብግብ ወረኛ...
የሆነ መንገደኛ ጎትቶ አላቀቀኝ፡፡ ደክሞኝ ነበር... ፊቴ ረጥቧል... አቧራ ልሷል... ከከንፈሬ ላይ ስቀምሰው ምንም ምነንም አለኝ፡፡ የሆነ ነገር ሆኛለሁ፡፡ ወደ ቤት ሄድኩ!
ደፋር አይደለሁም! ግን በማግስቱ ፈልጌያቸው ሄድኩ... የከንፈሬ ልሙጥ ለስላሴ ሳይጠግግ...
ደበደቡኝ (<ኸረ ገደሉት> ትላለች አንድ ሴትዮ)
በነጋታውም ሄድኩ... በስልችት ደበደቡኝ (<ኸረ ገደሉት> ትላለች ሌላዋ... የተጠና አይመስልም? <አፍንጫውን ሲሉት በቀጭን ድምፅ ጩሁ> ተብለው የሰለጠኑ አይነት?)
በማግስቱም ሄድኩ (ስንዱ ፈራች... ልጄን ይገድሉታል ብላ... የ<ኸረ ገደሉት> ውጤቱ መሰለኝ...)
ተመላልሼ እስኪሰለቻቸው ደበደቡኝ... ነገም መምጣቴ እንደማይቀር ሲገባቸው ለመኑኝ <<ተው እንጂ ሲራክ ትጎዳለህ... ጥርስህን አወልቀዋለሁ>> አለኝ የልመና አይነት... እላይ ሰፈር ያለ ሆዳም ዘጠዘጥ ነው፡፡
መጨረሻ ላይ ፈሩኝ፡፡ ልክ አለም አይደለም... ተደብዳቢን ድፍረት ላይ ይሾማል?
ቁስሌ ሲድን <ደፋር> ተባልኩ... ደፋር ሲሉኝ አንድ ደረጃ አደግሁ... ጉልበተኛ ሆንኳ! ጉልበተኝነት የመጫጫር ፈቃደኝነት ነው፡፡ <ነህ> <ነህ> ብለው እፍ እፍ ይሉህና ነህ ላሉህ አለመሆንህ ያኖሩሀል፡፡ ነህ ላሉህ ጉዳይ ልትሞላ ትጋጋጣለህ፡፡
~
~
ፍቅርተን እጠብቃት ነበር... ፍርሀቷን ከፊቷ ላነብ... አንገት መድፋቷ ላይ የተሳለ በውስጧ ያለኝን ስዕል ላየው... አዲስ ነበር ሁሌ፡፡ ከቀይነት ወዟ የሚፈልቅ ደግሞ ሌላ አይነት አፈራር...
የምታየኝ ሩቅ ሆና እንደሆነ አውቃለሁ... እያየችኝ ትመጣለች... የ<እያየችኝ ነው?> ጥርጣሬ ውስጥ እንድወድቅ አስባለች፡፡ እየቀረበች ስትመጣ... ስትደርስ... ገዝታ ስትሄድ ደግሞ እንደሌለው... እንደማልታይ አይነት ነው ነገሯ፡፡ አታወራም! (ድምፄ ሲያምርህ ይቀራል መሆኑ ነው?) አታየኝም (ማን ነህና ትታያለህ? ትለኛለች?)
የወደዱትን መጠበቅ የተለማመድኩት ከሰማሁት ካየሁት ነው... ሬድዮ ሰምቼ ምናልባት፡፡ ያፈቀረ ሰው ካልጠበቀ ምኑን አፈቀረ? መጠበቅ ባይፈልግ እንኳን የስምምነት ግዴታ ነውና እየሰለቸ ይጠብቃል፡፡ ከከዋክብት ሽራፊ ያነፃፅራታል፡፡ አሁን ፍቅርተ መልኳ ግሩም ነው... ቅላቷ ምኗ... እግዜር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሰርቶ እሁድ አረፈ... እሁድ ቁጭ ብሎ ጣቶቹን ሲያንቋቋ ሀሳብ መጣለት... ወይ ወደ ሀሳቡ ሄደ... የብርሀን ጨርቅ ከመጎናፀፊያው ላይ ቀደደና በሰው ቅርፅ አቦካው... እፍፍ አለው! ፍቅርተ ያቻት! እንዲህ አይነት ማካበድ ይጠይቃል ማፍቀር መሰለኝ፡፡ ስታፈቅር እንከን ትክዳለህ... አሁን ፍቅርተ ቆንጆ ትሁን እንጂ ሰውነት የሌላት ሰላላ... ሰባራ... አጥንታም... ቋቋታም... ሲጥ ሲጥ... ቆሮቆንዳ ናት፡፡ ያፈቀረ እንደዚህ አይልም ነውር ነው... እስኪንቅ ድረስ የሚክብ ውሸታም ነው የማፍቀርን ልኬት ያረቀቀው! ውሸት እኮ ጉልበተኛ ስር ትሽሎከሎካለች... አቅመኛ ስር ታለከልካለች... እንደ ፍጥሯ ይፈጥራታል... ያቦካታል... በፈለገው መንገድ ሲያጣምማት ተመልከት...
~
አንዳንዴ ግንፍልፍል ስል የማልለው የለኝም፡፡ መኖሬን ማጣጣል ጀምራለሁ...
<አላማ> ምናምን ቅብርጥሱ ተውና ትላንቴን ከነገዬ ለዩልኝ፡፡ ቅንጣት ይለያያሉ? በርቶ የመጥፋት ሂደት ምኑ ያጓጓኛል?
ይቺን ድብርታም ኑሮ ስሳደብ <የበላበትን ወጭት ሰባሪ በሉኝ> አቅሙ ኖሮኝ ምናለ መስበር ብችል? ባንከሻክሻት... አልችልምና ወጭቱን እቧጭራለሁ... ቢሳካልኝ ውብ ቀለሟን እልጣለሁ፡፡
ይቺን ኑሮ ብቁለጨለጫት አይኔ ይጥፋ! ለምኗም አልቀላውጥም! እንዲህ ስል ነው ፍቅርተ ትዝ የምትለኝ፡፡
ይቺ ሰቀቀናም ኑሮ... ትሰስታለች እንጂኮ ታስነካሀለች... ታሳይሀለች... ትዳስሳለህ... ምኑም ግን ያንተ አይደለም፡፡ መሰሰት ማለትኮ ጭራሹኑ አለመስጠት አይደለም... እጅግ አጉድሎ መስጠት ነው፡፡ ይቺም ሰቀቀናም እንደዛው ነች፡፡ አትሰጥህምም አትቀማትምም! ሰው ብትሆን ማሪያም ጣቷን በጥርሴ ቦጭቅና በስቃይዋ እምባ አፌን አባብስ ነበር፡፡
(ከጥቁርና ነጭ ማስታወሻ ላይ የተወሰደ)
(በረከት ታደሰ)

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ወቀሳ!

ወቀሳ ግላዊ ነው ፤ በተለይ የወቃሹ ሁኔታ ይወስነዋል ፤ የወቃሹ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ አቋሙ ይወስናል፡፡ አንዳንዴ ያልተመጣጠነ ወቀሳ ያጋጥማል እንዴት በኔ ጫማ አትቆምም አይነት አጉል ሙግት ያጋጥማል፡፡ ለምሳሌ በታሪክ አጋጣሚ ከአንድ ዲታ ጋር ቡና ልትጠጡ አንድ ጠረጴዛ ላይ ልትቀመጡ ትችላላቹ ፤ እናም ያ ዲታ ስለመኪና ዘይት መወደድ ውጥር አደርጎ ሊሞግታቹ ይችላል አረ እንዳውም እንደሱ ስላልመረራቹ ሊወቃሳቹ ይችላል እንዲህ ብሎ ድሮም እኮ ሃበሻ……….፡፡ አሁን ለጎዳና ተዳዳሪ በመብራት መቆራረጥ ምክንያት ስቶቫችን ተበላሸ ፍሪጃችን ስራ አቆመ ብትሉት እንዴት ይሰማችኋል፡፡ ና እና እሪ እንበል መብራት እኮ መሰረታዊ ፍላጎት ነው ብትሉት እንዴት ይገባዋል ፤ ከገንዳ ላይ ማንጎ የሚግጠው ያ ምስኪን ለሱ መሰረታዊ ፍላጎት እኛ ዝናብ ሲዘንብ ጥቅልል ብለን የምንተኛበት መጠለያ ነው፤ መብራት አይደለም፡፡ እዛ በጭሶች መሃል ተሸሽጋ እራፊ ጨርቅ አድርጋ አላፊ አግዳሚውን ለማማለል የምጥጥረው ያቺ ሴት ለሷ መሰረታዊ ፍላጎት ኔትወርክ ሳይሆን ወንድሟቿ የሚበሉት ነገር ማግኘት ነው፡፡ ወቀሳ ግላዊ ነው አንዳንዴ እንዲህ ያጋጥማል ታናሽ ወንድም ስራ ፍለጋ ተንከራቶ ተንከራቶ እግሩ እየተንቀጠቀጠ ቤት ሲገባ ታላቅየው የታሸገ ውሃ ይዞ ሲጉረመርም ያገኘዋል ታናሽ ምን ሆነህ
ነው የምታጉረመርመው ሲለው አሁን ይሄ የታሸገ ውሃ ኮንቴንቱን አይተኽዋል
ካልሺሙን እየው 14.3 ነው ሶዲየሙን እየው 4.80 ነው አይገርምም ይለዋል
ታናሽ ገርሞት ዝም ቢል ታላቅ ወቀሳ ይጀምራል እንዲህ ብሎ ለስሙ ዲግሪ
አለህ እንዴት የታሸገ ውሃ ኮንቴንት አታይም………. እንግዲህ አንዳንዴ እንዲህ ነው፡፡ ሰውን ስንወቅስ መጠንቀቅ አለብን

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Tewodros Tezera
(ቤካ)

በአንድ ወቅት አንድ አባትና ልጅ በአንድ ተራርቀው በተተከሉ ዛፎችና ዋርካዎች ባሉበት ስፍራ እየተዘዋወሩና እየተዝናኑ ሳለ ልጅየው በተደጋጋሚ ወደ ሰማይ ቀና እያለ ያያል ታዲያ ይሄን ያየ አባት መጀመሪያ ቀና ብሎ ሰማዩን አየና ወደ ልጁ መለስ ብሎ

"የኔ ልጅ ከቅድም ጀምሮ እንቅፋት እስኪመታህ ድረስ ቀና እያልክ የምታየው ምንድን ነው?" ብሎ ይጠይቀዋል፡፡
ልጁም" አባቢ ሰማዩ ላይ ዝም ብላ የምትሽከረከዋን ቆንጆና ትንሿን ወፍ አይተሀታል?" ብሎ ጠየቀው፡፡ አባትየውም በድጋሚ አንገቱን ቀና አድርጎ ሲመለከት መጀመሪያ ሰማዩን ስትዞር የነበረችው ወፍ አሁንም ሰማዩን ስትዞረው ያያል ከዛም አንገቱን ጎንበስ አረገና " አዎ አየዋት የኔ ልጅ ምነው?" አለው፡፡

ልጁም " ይሄ ሁሉ ዛፍና ዋርካ እያለላት አማርጣ አንዱ ላይ እንደመቀመጥ ለምን እራሷን ታደክማለች?" ይልና መልሶ ይጠይቀዋል፡፡
አባትየውም ትንሽ አሰብ አደረገና "የኔ ልጅ ምናልባት ይቺ ወፍ ቆንጆ ስለሆነች ሁሉም ዛፎች እንድትቀመጥባቸው ስለሚፈልጉ ዛፉ ሁሉ አይናዋጅ ሆኖባት ይሆናል ፤ ምናልባትም የትኛው እሾሀማው ዛፍ እንዳልሆነ እያረጋገጠች ይሆናል" ብሎ ይመልስለታል፡፡
ልጁም ትንሽ ከቆየ ቡሀላ " ግን እኮ አባቢ ቆንጆ የሆነችው እኮ እንደኔ ትንሽ ስለሆነች አደል?" ይለዋል መልሱን ከሰማ ቡኃላ ምን እንደሚለው እያሰበ፡፡

አባትየውም በጥያቄው ተገርሞ " አዎ የኔ ልጅ" ይለዋል
" ስለዚህ ሳድግ እንዳሁኑ ቆንጆ አሎንም ማለት ነው፡፡ እንደዛ ከሆነ ደሞ ይቺም ወፉ ቶሎ የሚመቻትን ዛፍ ፈለጋ ካልተቀመጠች በኃላ ቁንጅናዋ ሲጠፋ መቀመጫ ታጣለች ማለት ነው እኮ፡፡ እና ደሞ እሾህ ያለውንም ዛፍ ቶሎ ካለየች እኮ ቡኃላ ሲደክማት የማቶደውና መጥፎ እሾህ ላይ ልትወድቅ ትችላለች አይደል?" ይለዋል ትክክል እንደሆነ እንዲነግረው ጥያቄውን አስከትሎ፡፡

አባትም " ያልከው ሁሉ ትክክል ነው ፡፡ ነገር ግን ደሞ እኛ ያሰብነውና የሷ የምትሽከረከርበት ምክንያት ሊለያይ ስለሚችል ባለማረፏ አትፍረድባት እሺ" ብሎ ይመልስለትና " እስኪ ዛሬ ከውሏችን ምን ተማርክ "ብሎ ይጠይቀዋል

" ከወፏ ብዙ ነገር ተምሬያለሁ ነገር ግን በጣም የተረዳሁት ነገር የሚሆነውና የሚታየው ሊለያይ ስለሚችል በማንም ላይ አጄን መጠቆሞና መፍረድ እንደሌለብኝ ተምሬያለሁ " አለው፡፡

""ማንም ሰው በ አምስት ጣቱ ሚጠቁም የለም ፤ በ አንድ ጣቱ ጠቆመ ማለት ደግሞ አራቱን ጣቶቹ ወደራሱ ቀሰረ ማለት ነው!!!!!!!""""

@wegoch
@wegoch
@Mahletzerihun
ጃን ዳሌ
◦◦◦◦◦◦◦◦◦
ናዊአብርሃም ( @nawi1 )
.------------------------------------------
.
.
በበረነዳ ልጅቷን ለማየት ትወጣለህ፤አትኖርም።
ጨረቃን ለማየት ታንጋጣለህ፣አትኖርም።

ምክንያቱስ?

ጨረቃ
ለ ኒል አርምስትሮንግ ድንግልናዋን የሰጠች ናዋዥ አፍቃሪው ናት። በቃ!! በጨረቃም ተስፋ ትቆርጣለህ ። አልጋህ ላይ ትወጣለህ፤ የኔ የምትለው እንቅልፍህንም በናፍቆቷ ቁማር ትበላለህ ።

በመጨረሻም በትግል ፣ በጨበጣ አሸንፈህ ዕንቅልፍህን ታስመልሳለህ ፤ እንቅልፍህ ውስጥ እሷ ትኖራለች። አይ ጨረቃ ...እሷም ትኖራለች። ይሄኔ ጨረቃ በመሬት ዙሪያ መዞሯን ትጠራጠራለህ።'
. . .

ንቃቴ ኖረ አልኖረ ግድ ሳይሰጣት በማን አለብኝነት ጭንቅላቴ ውስጥ ትንጎዳጎዳለች።

ይህቺን ልጅ በጣም እየጠላኋት ነው። እነደ ቄንጠኛ አስተናጋጅ ትከሻዬ ላይ አንጠልጥዬ ጠረሙሱ ላይ እንዳለው ቆርኪ ጭኖቿን መክፈት እና ከያዘችው እርካታ ሙላውን መጎንጨት እያማረኝ ነው።

ይህቺን ልጅ እየጠላኋት ነው። ህልሜን ትመስለኛለች ።

ለህልሜ ብሶል ሰሜኑ እሷው ናት።በየትኛውም የአልጋዬ ማዕዘን ራሴን ባሳርፍ ሕልሜ ውብ ገላዋን ይጎትታል ። ህልም የሚታዘዝላት ይህች ሴት ማናት? (ከሚጎትታቸው ውብ ገላዋ መሀል ያ ዳሌዋ ቀርቶብኝ እንደሆነ ጠዋቱ ይደማምንብኛል)

ይህን ዳሌዋን ምናቤ የትም ሆኜ ምንም ነገር ላይ ይስለዋል።
ታዲያ አንዴ የት ሳለው ጂኦሎጂ እየተማርን ሰሌዳው ላይ ፣ ታዲያ ሎሬት ሜትር አርቲስቱ፣ ምናቤ የሳለውን የልጅትን ሕቁር አልባ ገላ እየኮመኮምኩ ድንገት የመምህሩ ማጥፊያ የያዘ እጅ ግራ ቂጧ ላይ አርፎ ሳየው ምናባዊ ቅናት ለበለበኝ ።

"አቦ አትደብረኛ ! . . .ያንተ ጂኦሎጂ፣ የመሬት . . .የአፍር እና አለቶች ምርመራ ምናምን ... ይሄን ዘርቅ ወደዛ አቦ ..." ብዬ ምናባዊ ዘለፋ ወረወርኩ

የኔ ጂኦሎጂ ከልጅት ዳሌ ነው፤ ጅንን ዳሌ . . . በቃ ምን አለፋችሁ ጃን-ዳሌ አልኩት፣ ታላቅ ዳሌ እንደማለት ያለ ነው።የምዋምነው ይህ ተፈጥሮ የቸረቻት አምሐ አሳይመንት ተብሎ
ቢሰጠኝ ( አዎ individual ነው መሆን ያለበት!) ያበደ አርጌ ነበር የምሰራው።🙈🙈

መምህሩ ቀድሞኝ ጨረሰና ከክላስ ወጣን ። ከህነፃው ወርጄ ቀጠን የምትለውን የእግር መንገድ ይዤ ወደ ዶርም ስኳትን ልጅትን አየኋት ያ ስጦታዋ፣ ውበቷ ፣ አዳምን ሁሉ ማሰብ እንዲያቆም የሚያደርገው ያ ቂጧ የት ሄደ ?
ደነገጥኩ . . . ወይኔ እኔና ጂኦሎጂ በቂጧ ሰበብ ያቺ ሱሪ እንደመጋረጃ ቁልቁል የምትለቅ ፣ የተላገች ቂጤ ተቃጠለች። መዋመኔ ሁሉ እንደ ጤዛ ረገፈ ። ተዓምር አያልቅ. . . ያ ዳሌ የትገባ በጊዮርጊስ ??
በኋላ የጊቢው አዳም ሁሉ ሲፈልግ ሲፈልግ ከርሞ ያ ቂጧን የት አገኘነው? የጊቢው ቆሻሻ የሚቃጠልበት ቦታ በሲሶ እየተቀጣጠለ ያለ ስፖንጅ ሆኖ አገኘነው። 🙊🙊

የኋላ ኋላ ያንን ስፖንጅ ተጠግተን አየነው እንዳሉት ከሆነ ጡጫ የሚያክል ጉድጓድ በግራ ቂጧ በኩል መኖሩንና ምናልባትም አይጦች በልተውባት ሊሆን እንደሚችል መላምታቸውንም በዛው አስቀምጠዋል፤ ጥቂት የሚባሉ ተባዕት ተማሪዎች ደሞ በዛ አይጥ በበላችው ሽንቁር ዙሪያ ነጭ ነገር እንደሚታይና ይህም በኮላ ቂጧን መልሳ ለመጠገን ያደረገችው ሙከራ ውጤት ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን አያይዘዋል። ( አሂሂሂ! እኔስ እየጨሰች ያለች ቂጤን በምን ልጠግናት? ወይኔ እኔ !! ቂጧን ብዬ ቂጤን አጣሁ።)
ከዛች ቀን ቡኋላ ለልጅቷ ያለኝ መቁነጥነጥ ስርዓት ይዞ ሲቀመጥ አስተዋልኩ ።

ከሷ በኋላ ጃን ዳሌ ሳይ ጃን እስንፖንጅ አለመሆኑን እጠራጠራለሁ።

እና ሰሞኑን አይቼ የወደድኳትን ልጅም መጠርጠር ጀምርያለሁ ። (መቼም የሚፈርድብኝ አይኖርም) እኔ 4 ተኛ እሷ ደሞ 3ተኛ ዓመት ተማሪዎች ነን። ቆንጆ ናት ፣ ሀቅ ነው። ቀይ ናት ፀሃይ ከነካት . . .እፍ . . እፍ. . . እንደተባለ ረመጥ ይባስ ትቀላለች።

ባወራት ብዬ እመኛለሁ። (እሱ ገላሽ ሰፖንጅ ይሆንን ? ብዬ ልጠይቃት እንደሆን እንጃ) . . . ሰበብ አጣሁ . . . ደሞ በእኔ ባች የሆነ እዛው ጊቢ ውስጥ ወንድም አላት ። (አይወደኝ ይሆን እላለሁ፣ ውይ ግን ስወዳት ማርያምን) እንዴትም ብዬ ስልኳን አፈላልጌ የሆነ ፍቅሬን የሚገልፅ የፅሁፍ መልዕክት ስለማስቀመጥ አሰብኩ ። (ውይ በናትሽ አውሪኝ . . . አንቺን ማውራት ብቻ ያኖረኛል እኔን . .. የሚል ግጥም ልፅፍላት አማረኝ ) እንዳማረኝ ቀረ ብዕሬ ለሷ መንጠፉ ገረመኝ (ሳልወዳት አልቀረሁም)

በህይወትህ ያለህን ሁሉ ሚስጥር ከነገርከኝ ያንተ እሆናለሁ ብትለኝ ... አንድም ሳላስቀር በሰንጢው ምላሴ ሆዴን ዘረግፍላታለሁ። እወዳታለሁ ።

ባትወደኝም ቅር አልሰኝም ። እሷው ትሰኝ ምክንያቱም ከኔ በላይ የሚወዳት አይኖርም ። (የሚጠረጥረኝ ቢኖር በከንቱ አይድከም!!)

Body of a woman, white hills, white thighs,
you look like a world, lying in surrender.
My rough peasant's body digs in you
and makes the son leap from the depth of the earth.
◦ ◦ ◦
//'Body of a Woman//
pablo neruda
---------------🌸🌸🌸-----------

---------------------------------------
በእግዜር ይዣችኋለሁ አንብባችሁ ዝም አትበሉኝ የልጅቷን ስልክ ጀባ በሉኝ🙏🤣🤣🤣
--------------------------------------------


@wegoch
@wegoch
@Mahletzerihun
Forwarded from ሥዕል ብቻ © (👋ገብርዬ)
በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ስነጥበብ መማር ለምትፈልጉ ሁሉ የወጣ ማስታወቅያ

.
.
@seiloch
-----------------------
ያፈቀሩ ነፍሶች ❖
------------------
//✍️ ናዊአብርሃም
//
(@nawi1)
//ነሐሴ 4/2012 ዓ.ም//
------------✦✣✦-------------
የሰንደሉ ጢስ ይግተለተላል። ስስ ደመና ይሰራና ደሞ መልሶ አየር ላይ ተፈትሎ ወደ ቀጭን ክርነት ይለወጣል፤ ቀጭኑ ክርም እየተበተነ ሄዶ ከነጩ ኮርኒስ ላይ ተንሳፎ ይሰወራል ።
በሌላኛው አልጋ ጥግ ደሞ ከተንቀሳቃሽ ስልኩ ለስለስ ያለ የዘሪቱ ዜማ ከጢሱ ጋር ተዋህዶ ሽቅብ ይተማል ።

" ያኔ ስንቀራረብ ደስታዬ ነበር ያንተ መሆኔ
የኔ መሆንህ መኖርህ ጎኔ
ያኔ ስወድህ አልጠረጠርኩም
ያኔ ስንተሳሰብ አልጠረጠርኩም
እንደምርቅህ
እንደምትርቀኝ
እንደምለይህ
. . . "

የደከመ ለቅሶ ይሰማል ፤ ከአይኗ የሚቀልጡ ፍል እምባዎች ጉንጮቿ መሃል ደርሰው ይረጋሉ ፤ በምፀት ስትስቅ ተሰነጣጥቀው ይረግፋሉ።
" በርቺ ሄዋን !! " ትላለች ። እንባ የቃላቶቿ ማፅኛ ፣ ሁለት መንታ እንባ ደግሞ የንግግሯ መደምደሚያዎች ሆነዋል ። የህሊናዋ ጩኸት ተከድኖ የነበረው አነደበቷን ደርሶ በረገደው ።

(። ይህ ምልክት ሁለት መንታ እንባ ነው)

" እሱ ማለት የውበቴ ጣዖስ፣ የህይወቴ ሮማን ፣ የትዝታዬ ከሙን ነው ። ትዝታው ቅመም ብቻ አይደለም፤ ልክ እንደ ባህር ነው፤ ረጋ ሲሉት ደርሶ ይፈላል። ናፍቆቱ ሲጠና በልቡ ልቤ ላይ የሚሳብ እፉኝት ነው።
ናፍቆቱ ይናደፋል ። ሳቁ ፣ ቡትቶ ልቤ ላይ የሚርመሰመስ ቅማንዥር ይሆንብኛል ። ፍቅሩ እነደ ሸለመጥማጥ የምናቤ ጢሻ ውስጥ የሚሽሎከለክ አውሬ ነው ። እሱ ላይ ቅንጣት ታክል አቅም የለኝም ።ፍቅሬ ለሱ ፍልፈልን እንደሚጋፈጥ መርዘ ከንቱ ጊንጥ ነው። ሌላ ብለምድ እንኳ ገላ መዋስ ነው ሚሆንብኝ .....አፈቅረዋለሁ። "

ሜሮኑ እንባዋ ከ ሰንደሉ ጢስ ጋር የፍቅር ሰቆቃዋን አዝሎ በበሩ አናት እየተጎተተ ወጣ ።

ነፋሳት እየተቀባበሉት ሄዶ ከወዳጇ ቤት የሲጋራ ጢስ ጋር ተላተመ። ይሄኔ ልክ እንደጢሶቹ ስሜቱ ተደበላለቀ።

ማልቀስ እየከጀለው ባዶ ወንድነት አፈነው ። መለያየት ልክ እንደሱ ላሉ ዳተኞች ሽቅብ ነው። ሲጋራውን መጠጠው ፣ ወረተኛ ሳንባው ጢሱን አቅፎ ገፋው። ሰውነቱ ደርሶ ይርዳል ፣ ልቡ ይናድበታል።

አይኑ እሷን ይስላል ። ምናቡ ያዳፈነውን ትዝታ 'እፍ! እፍ!' እያለ ይገልጣል።
የሰንደሉ ጢስ ሰሌዳ ላይ በሲጋራው የጢስ ብሩሽ እንዲህ ትዝታውን ይለቀልቃል።

● ● ●
ጎንደር ፋሲል ግቢ

' እንዳየኋት አልደነገትኩም ። በፍቅር ህይወቴ ውስጥ ትፈጠራለች ብዬ ከነመፈጠሯ የማላስታውሳት ሴት ነበረች ። ከፍቅረኞቿ ጋር ስትጣላ አቅፌ የማባብላት ፣ የማልቀናባት ወንድ ነበርኩ ። እንደ ወንድም ቀርባታለሁ እንዳልል የሚያግደኝ . . . በፍቅር ትፈልገኝ ይሆን? የሚል ጥያቄ ብቻ ነበር።

አብረን ክብረ በዓላትን ግራ ቀኙ ባለየለት መልኩ እናከብር ነበር ..እንጠጣለን ..እንጫወታለን እንሰክራለን ። ጨዋታዋ መቼም አይወራ ዕፀ መፍዙዝ ነው ፤ ስንኝ በጉንጯ ናት ፤ ግጥሟ ሁሉ አጃኢብ ነው።

እንደ አብዛኛው ሴቶች ረጋ ያለ ወንድ ላይ ማዕበል ናት። ስትቀርብ ልክ የላትም ፤ ፍቅር ከቶ የሚይዛት አትመስልም። ያጋጣሚ ሆኖ የፍቅር ክንድ አድቅቆኝ ' ፍቅር ይቅር! ' ብዬ መነሳቴ ነበር። እሷም እኔም ለፍቅር ልባችን አብጦ የፈነዳ ነበርን ።

እሷ ' ፍቅር ሴትን አይዛትም።' ባይ እኔም ብቸኝነቴን ደን አድርጌ እሸሸግበት የተጠጋሁ የፍቅር ሽፍታ!

ፍቅር ተዓምራትን ሳይታክተው ያበጃልና

ነገሮች ተቀየሩ ....' እኔ ' ስል እሷ የሚለው መጎተት ጀመረ ። ቤተሰብ ያወጣልን ስም አስጠላን ስንኳረፍና ስንጣላ ብቻ እንጠቀምበት ጀመር ። አልጠግባት አልኩ ፣ አልጠግበኝ አለች ። በጊቢው ጎዳና ዳር ያሉ አበባ እና ዛፎች በአጠገባቸው ስናለፍ ለፍቅራችን ያረግዳሉ ፣ በቅጠሎቻቸው ያጨበጭባሉ፤ ያፏጫሉ ።
"አባ ሳመኝ ?" እስማታለሁ ። የማያፍር ፍቅር እነዴት ደስ ይላል!

ቀጫጭን እጆቿን ወገቤ ላይ ታስራለች ደሞ ትፈታና ሮጥ ብላ ቀድማኝ ወደ እኔ ዞራ ትዘፍናለች ። ትቀብጣለች ። ታሳሳለች። (ትናፍቃለች...)
ቀጥለን ወሬ እየቆረስን ቡና እንጠጣለን። ( ቁጭ ብለን ባወጋንባቸው ቦታዎች ስሜን ትፅፋለች ፤ የልጆቻችንን ስም ትፅፋለች ።)

....ነፋስ እያካለበ አምጥቶ የለጠፈባትን ቅጠል ከፀጉሯ ላይ አንስቼ ግንባሯን እስማለሁ ፤ ቀዝቃዛ ወራት የጣሉትን የዝናብ ጠብታ ከከናፍሯ ላይ በከንፈሬ እለቅማለሁ። አጭር ቁመቷን በክርኔ አግዤው አንጋጥጬ እስማታለሁ። ደሞ ተንሸራታ ቁልቁል እስማታለሁ ። ቂጧን ጨብጣለሁ ፤ ጡቷን እነክሳለሁ ።

' አበድኩልህ !' ትበል እነጂ አብጄ እነደቃተትኩላት ትዘነጋለች።
የፍቅር ጥም ሲለበልበን ከጊቢ እንወጣለን ።
እበደት ለአፍታ ይገታል። ወይ እሷ ! ወይ እኔ! '
.
.
ቤቱ ቁጭ ብሎ ሲያስብ ጊቢ ሲመለስ ከፍቅሩ ጋር የተመላለሰባቸው መንገዶች ፣ ቁጭ ብለው ያወጉባቸው ስፍራዎች ለብቻው እንዴት እሾህ የተበተነባቸው እነደሚሆኑበት ሲያስብ ... ክፉኛ ልቡ ይርዳል።

" she gave me peace
in life time of war ..... "
I miss her, all day and night!!!

----▪️▪️▪️◈◈✣✣✣◈◈▪️▪️▪️----
--------------------
@Abelard1
--------------------
●●●

@wegoch
@wegoch
@wegoch
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
beki፪፬ Get፩፪:
" እ............ናት"


በዚህ ምድር ላይ ትዝታ የሚባለው ነገር ብትፈልገውም ባትፈልገውም ከአይምሮህ አውልቀህ የምትጥለው ነገር አይደለም፡፡ የሚገርመው ደሞ በተለይ መጥፎ ትዝታ ከሆነ ለምን እንደሆነ ባላውቅም የምታየው ፤ የምትሰማው ፤ የምምትበላውና የምትጠጣው ሁሉ እሱን ያስታውስሀል፡፡

ትዝታ ቢሸሹት የማይሸሽ ፤ ቢርቁት የማይርቅ ጥላ ነው፡፡ እኔም ብሸሸው ከማይሸሸኝ ጥላዬ እየራኩ ጅል መባልን አልፈለኩም፡፡ምንም እንኳ የሚያኮራ ታሪክ ባይኖረኝም ትዝታዬን መፃፌ ግን ለውጥ እንደሚያመጣ ስለገባኝ ብዕርና ብራናዬን ዘረጋሁ፡፡

በ14 አመቴ ነበር እንደ ጓደኞቼ ወጣ ወጣ ማለት ነው የጀመርኩት፡፡ አንዲት ወጣትነቷን እያገባደደች ያለች እናት አለችኝ፡፡ አባቴን ከነመፈጠሩም አላውቀውም፡፡ እስከዛሬ እሱን እንድፈልገው የሚያደርገኝ ነገር ስላላጋጠመኝ አባቴስ ብዬ አንስቼባት አላውቅም፡፡ እናቴ ብቻዋን ያለደጋፊ ስታሳድገኝ በአቅሟ የማታደርግልኝ ነገር አልነበረም፡፡
"ልጄ ታውቃለህ እግዛብሄር ስለነገ
እንድጓጓ ሲፈለግ የሁሉ ነገር መፅናኛዬን አንተን ሰጠኝ፡፡ የኔ ልጅ ተስፋዬኮ አንተ ብቻ ነህ ፤ የሰው ልጅ ተስፋ የሚያደርገው ነገር ሳይኖረው በምድር ላይ መንቀሳቀስ የማይችል ብቸኛ ፍጡር እንደሆነ እወቅ፡፡ ምናልባት ምንጩ ከየት እንደሆነ በማይታወቅ ብር በፀሀይም በጨረቃም የሚቅሙና የሚያጨሱ ሰዎችን አይተህ 'እነሱ ያለ ተስፋ እየኖሩ አይደል? ብለህ ትጠይቀኝ ይሆናል ፤ አመነኝ የኔ ልጅ እንደ ወይራ ከሚጨሰው ጭስ ጀርባ ቅንጣት የምታክል ተስፋ አትጠፋም ፤ ፈጣሪ ደሞ እንኳን ለኛ ለደካሞቹ ይቅርና ፃድቁ ኖህን እንኳን ያለተስፋ አልተወውም" አለችኝ በ'ናትነት አንደበት፡፡ ይህን ሁሉ ነገር አለምክንያት አልነበረም የተናገረችው፡፡

በጠዋት ከቤቴ የወጠሁት ትምርት ቤት ለመሄድ ነበር፡፡ ነገር ግን ከሰፈሬ ገና ሳልወጣ በ5 በ6 አመት የሚበልጡኝን ጓደኞቼን አገኘዋቸው፡፡ ሁሉም ዩኒፎርማቸው አውልቀው ወደ ፑል ቤት ሊሄዱ ሲሉ ነበር ያገኘዋቸው፡፡ " አንተ ፋራ ነህ እንዴ ሳምንት ከሳምንት ክላስ ምትገባው ? ፤አስተማሪው እራሱ እንዳንተ ከሰኞ እስከ አርብ አሄድም እኮ" አሉኝ ተራ በተራ ኋላ ቀርነቴን እየነገሩ፡፡ የዛን ቀን እኔም ዩኒፎርሜን አውልቄ አብሬአቸው ወደ ፑል ቤት ሄድኩ፡፡ ሁሌ ሰው እንዳያውቅብን ፑል ቤት እንላለን እንጂ ፑል ልንጫወት አልነበረም የምንሄደው ፤ ከፑል ቤቱ ጀርባ በኮሽም የተከበበ ቦታ ላይ ድንጋይ ደርድረን እንቀመጥና ከየት እንደሚያመጡት የማላውቀውን ሲጋራና ሀሽሽ እናጨሳለን፡፡ ታዲያ ይሄን ጊዚ እናቴ ተከትላኝ እንደወጣች አላወኩም ነበር፡፡ ሲጋራውን ጣትና ጣቴ መካከል አርጌ አፌ ውስጥ ስከተው እጅ ከፍንጅ ያዘችኝ ፡፡ " የኔ ልጅ ና ተነስ ወደ ቤት እንሂድ" አለችኝ፡፡ሲጋራ ለሷ ተስፋ የመቁረጥ ምልክት እንሆነ አውቃለው፡፡ እቤት ከገባን ቡሀላ በተረጋጋ መንፈስ ልክ ምንም እንዳላጠፋሁ ተስፋዋ እንደሆኑኩ ትነግረኛለች፡፡
መረጋጋቷ ሁሌም ያስፈራኛል ግን አንድም ቀን ፈርቻትም ሆነ አክብሬአት የምታዘኝን ነገር እሺ ብያት አላውቅም፡፡ የራሴን ልብስ ለማጠብ በጀርባዋ ጀሪካን ተሸክማ እያየዋት ፤ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ለአፌ እንኳን ላግዝሽ አልላትም ነበር፡፡ ሁሌም የሚገርመኝ እንደ እናት ከአንገቷ እንኳን ለምን እንደማትረግመኝ ነው፡፡

አንድ ቀን እግሬን ዘርግቼ ቴሌቪዥን እያየው ሳለ አይኗ ደም መስሎ ጉንጮቿ ቀላልተው ሰላም ሳትለኝ ያረጀች ሶፋችን ላይ አንገቷን ደፍታ ተቀመጠች፡፡ ምን ሆና እንደሆነ ማወቅ ፈልጌአለሁ ፤ ነገር ግን አጉል ጉርምስና ይዞኝ ዝም ብዬ ተቀመጥኩ፡፡ ትንሽ እንደቆየን እንባዋ መሬት ላይ ይንጠባጠብ ጀመር፡፡ አሁንም ምንም አልተነፈስኩም፡፡ አይኗ ወደሷ እንድዞር ይጎትተኝ ጀመር፡፡ እንደምንም ፊቴን ዘወር ሳደርግ አይናአይኔን እያየች ማልቀስ ጀመረች " አሺ ምን ላርግ የኔ ልጅ? አንተን ለማሳደግ የማልፈልገውን ሁሉ ሆንኩ ፤ አሁን ግን ምንም ማድረግ አልቻልኩም ፤ አዎ በብሩ ተማምኖ ሊደፍረኝ ሲሞክር ዝም ማለት አልቻልኩም" አለችኝ፡፡ ከስራም ሌላ ቦታም ጭምር እንዳትቀጠር አድርጎ እንዳባረሯት እንደ ህፃን እያለቀሰች ነገረችኝ፡፡ ምንም ሳልናገር ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ወደ'ናቴ መስሪያ ቤት መሄድ ጀመርኩ፡፡ እናቴ እንደሁልጊው ድምፇን ላለመስማት የወጣው መስሏት እንደተቀመጠች ማልቀሷን ቀጠለች፡፡ አኔ ደም እንደጠማው ያንቀዠቅዠኝ ጀመር፡፡ እንደመሮጥም እንደመራመድም እያልኩ የመጀመሪየውን አስፓልት በደመነፍስ አለፍኩት ፤ ሁለተኛው አስፓልት ላይ ለመድረስ ሶስት እርምጃ ብቻ በቂዬ ነበር፡፡

ከ አንድ ወር ከሳምት ቡኋላ እራሴን አንድ አልጋ ላይ አገኘውት፡፡ እናቴ ወንበር ላይ ተቀምጣ በእግሬ በኩል አንገቷን ጋደም አድርጋ ተኝታለች፡፡ መልኳ ፍፁም ተቀያይሮብኛል ፤ ሰውነቷ ብዙ ቀን ምግብ እንዳላገኘ ያስታውቃል ፤ ከንፈሯ እንደ ሞተ ሰው ነጭ ሆኗል ፤ ምን ሆኜ እንደሆነ ማወቅ ፈልጌአለሁ ፤ ከዛ በፊት ግን ጉሮሮዬ በጣም ስለደረቀ ውሀ መጠጣት ነበረብኝ። አጠገቤ ሀይላንድ ውሃ ተቀምጧል ፤ እናቴን ከምቀሰቅሳት አልኩና እጄን ለማንቀሳቀስ ስሞክር ጣቴ ብቻውን ይንቀሳቀሳል፤ በድጋሚ ለማንሳት ሞከርኩ አሁንም ጣቴ እንጂ እጄ ጠቅላላ ንቅንቅ አልልም አለኝ ። ደንግጬ እናቴን ለመጥራት ስሞክር ምላሴ ተሳሰረ ፤ቃላቶችን ከአፌ ማውጣት አልቻልኩም። ወስጤ ትንፋሽ እንዳጠረው ሲወጣጠር ይሰማኛል ። እናቴን ከእግሬ ላይ ለመቀስቀስ ስጥር እግሬ ከታፋዬ ጀምሮ ምንም መልስ አይሰጠኝም ። አሁን ሀይሌና ጉልበቴ እንባዬ እንደሆነ ተረዳሁ ። ማንም ሊሰማቸው የማይችላቸውን ቃላቶች ማውጣት ጀመርኩ ። እናቴ ከተኛችበት ተነስታ መጀመሪያ እያለቀሰች የነበረች ይመስል አይኔን ስታይ እንባዋ እንደጎርፍ ይወርድ ጀመር ። ግንባሬን ፤ እጄን ፤ ጉንጬን ፤ ከንፈሬን የማትስመኝ ቦታ አልነበረም ፡፡ የሷ እንባ ከኔ እንባ ጋር ተዳምሮ ፊቴን አራሰው ። እሷ አቅፋኝ እኔ ጠልቻት አላቅፍም ያልኩ ይመስል እጄን ዘረግቼ እየተላቀስን ሳለ ዶክተሩ ህመምተኞችን ለማየት ሲገባ ተመለከተን።
" ምን ሆነሻል ወ/ሮ ውቢት ያን ሁሉ ነገር ተነጋግረን እንዴት እንደዚ ታደርጊያለሽ" አለና ከደረቴ ላይ አነሳት ።ምን እንደተነጋገሩ ማወቅ ፈለኩ ግን እንዴት ብዬ ልወቅ፡፡
"ዛሬ ወይም ነገ ወደቤቱ ይዘሽው መሄድ አለብሽ፡፡ እዚ መተኛቱ ምንም የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም፡፡ ይልቅ ከዚ ቡኋላ ዊልቸር ስለሚያስፈልገው አሱን መግዛት ይኖርብሻል" አላት የተኛው ስለመሰላቸው አጠገቤ ሆነው ነበር ሲያወሩ የነበረው፡፡

አንድ ቀን እንደ ልጅ አዝኜላት የማላውቅላት እናቴ ስለኔ እንባዋን እያፈሰሰች ትናገራለች፡፡
"ዶክተር..... አኔኮ አሁን እቤት ሲገባ የማበላው ምግብ እንኳን የለኝም ፤ ሌላው ቀርቶ የቆሸሸ ልብሱን እንኳን የማጥብበት ሳሙና የለኝም አኮ ዶክተር" ቀን በቀን የምታለቅስበት ድምጿ ተዘግቷል፡፡
እኔ ላልቅስልሽ እናቴ ፤ እኔ ልሰቃይልሽ ብዬ ላፅናናት እፈልጋለው ግን እንዴት ብዬ፤ በዚ በኩል ህሊናዬ ይኮሮኩመኛል
' ፈጣሪ ጤናና ጉልበቱን ሰቶህ አይዞሽ ያላልካት ሰውዬ ዛሬ ሁሉን ሲነሳህ ነወ ስቃዯ የታየህ? ' ይለኛል፡፡
'ምናለ..... ያኔ እንደጠላት ስገላምጣት ህሊናዬ በኮረኩመኝ ኖሮ ፤ ምናለ አንዴ እንኳ ......አንዴ እንኳ ከአፌ እሺ የሚል ቃል አሰምቻት አንደበቴ ቢዘጋ 'ብዬ ተመኘው፡፡
"እሺ ወ/ሮ ውቢት እኔ የላዳና ለትንሽ ቀን የምቶን ገንዘብ እሰጥሻለው። አንቺ ግን ዊልቸሩን መግዛት ካልቻልሽ አንድ ማድረግ ያለብሽ

ነገር አለ" አላት፡፡ እንባዋን እንድጠራርግ በሰጣት ሶፍት አይኗን እየጠራረገች " ለልጄ ምንም እንደማደርግ ታውቃለህ ዶከተር .....ምንድነው ማድረግ ያለብኝ?" አለችው፡፡ ተስፋ
በማያጣው አይኗ ዶክተሩን እያየች፡፡
"ከምንም ጊዜ በተለየ አሁን ልጅሽን በደንብ መረዳት ይኖርብሻል ፤ ምክንያቱም እንዳይናገር አንደበቱ ተዘግቷል ፤ ተራምዶ የሚፈልገውን ነገር እንዳያደርግ እግርና እጁ ፓራላይዝድ ሆኗል ፤ ስለዚህ እንድ ልትግባቡበት የምትችሉበት መንገድ ጭንቅላቱና ጭንቅላቱ ብቻ ነው፡፡ ለምሳሌ እንድትሰጪው የሚፈልገው ነገር ካለ በአይኑና በቅንድቡ በመጠቆም ሊያሳይሽ ይችላል ፤ የማይፈልገው ነገር ካለ ደሞ ጭንቅላቱን በመወዝወዝ ሊነግርሽ ይችላል፡፡" አላትና ከኪሱ ብር ቆጥሮ ሰጣት ፤ እሷም አመስግና ተቀበለች፡፡ እናት ከመፅዋችነት ወደ ተመፅዋችነት ስትዘዋወር እንደማየት የሚያም ቁስል የለም፡፡
"ስለዚ አሁን ታክሲ ይዤ መጥቼ ወደቤት ይዤው መሄድ እችላለው?"
"አዎ በደምብ ትችያለሽ" አላትና ወደ ሌላ ህመምተኛ ሄደ፡፡
እሷም ወደኔ ተመለችና ግንባሬን እየሳመች "አሁን ቶሎ ተመልሼ እመጣለው እሺ የኔ ልጅ" አለችኝና በድጋሚ ግንባሬን ስማ ሄደች፡፡

ከዚ ቡሀላ ምናይነት ሂወት እንደሚኖረኝ እያሰብኩ ሳለ ብዙም ሳትቆይ እናቴ ተመልሳ መጣች፡፡
"በቃ የኔ ለጅ ታክሲ የዤ ስለመጣው ወደ ቤት እንሂድ" አለችኝና ከወገቤ ቀና አድርጋ እግሬን ወደመሬት አወረደችው፡፡ አግዙኝ እንኳን ሳትል እስከዛሬ ሸክም የሆንኩባትን ልጇን ልትሸከመኝ ነጠላዋን ወገቧ ላይ ስታስር ሳይ እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም፡፡
" ለምን ታለቅሳለህ የኔ ልጅ ወደ ቤት ልንሄድ እኮ ነው፤ እባክህ አታልቅስ" ትለኛለች እንባዬን ከጉንጬ ላይ እየጠራረገች፡፡ እኔን ለማፅናናት ትስቃለች... አይኗ ግን እንባን እንደ ምንጭ ያፈልቃል፡፡

እግሯን ሸብረክ አርጋ ከወገቧ ዝቅ አለችልኝ፡፡ ለልጇ ዝቅ ማለት የማይታክታት እናት.......
እጅና እጄን በትከሻዋ አሳለፈችና እንደ ህፃነቴ በጀርባዋ አዘለችኝ፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ያለ ሰው ሁሉ በኔ እያዘኑብኝ ይሁን ለ'ናቴ እያዘኑላት ይሁን.....ከንፈራቸውን ይመጣሉ፡፡

ቤታችን በር ላይ ስንደርስ ሹፌሩ ከመኪናው ወርዶ አቅፎ ሲያስገባኝ ጓደኞቼ ሁሌ የምንቀመጥ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው አየዋቸው፡፡ የኔን አይን ተከትላ እናቴም አየቻቸው፡፡ አንዳቸውም ግን ከተቀመጡበት አልተነሱም ነበር፡፡ ሰውን ሰው መሆኑን የምትለየው በችግርህ ጊዜ ነው....... ትለኝ ነበር እናቴ፡፡

እቤት ገብተን ጤነኛም ሆኜ እተኛባት የነበረችው አሮጌ ሶፋችን ላይ አስተኙኝ፡፡ ለሁለት ቀን ያህል በየደቂቃው እየመጣች እንደራበኝና ሸኖ ቤት መሄድ እንደምፈልግ ትጠይቀኛለች፡፡አሁን ከቤታችን ብዙም የማይርቅ ሻይና ቡና ቤት ውስጥ ስራ ልትጀምር ነው፡፡ ነገር ግን እኔን ለማን ጥላ ልትሄድ እንደሆነ ግራ ገብቷታል፡፡

ጠዋት ተነስታ ቁርሴን አብልታ ልብሴን መቀያየር ጀመረች፡፡ምን ልታደርግ እንደሆነ አልገባኝም፡፡
"የኔ ልጅ አሁን አብረን ስራ ቦታ እኔዳለን እሺ፤ በዛውም ትናፈሳለህ" አለችኝ፡፡ ጥለሽኝ ሂጂ ማለት አልችልም ፣ ስራ መስራቷ ደሞ ግድ ነው፡፡

ትንሽ ስትጎዳጎድ ከቆየች ቡኋላ ብር የሌለው ቦርሳዋን በእጇ ይዛ እንደለመደችው ጀርባዋን ሰጠችኝ፡፡ ውሀና ዱቄት ሲሸከም የኖረ ጀርባ ዘንድሮም ድንጋይ ከመሸከም የሚያድነው ሰው አጣ፡፡ የበደሌ ቅጣት ከዲያብሎስ ቅጣት በልጦ ሳይ እስከዛሬ እናቴ የምትነግረኝ ተስፋ እንደ ገለባ በኖ ሲጠፋ ታየኝ፡፡

እናቴ እኔን በመሸከሟ ምን እንደሚያስደስታት አለውቅም ፤ የሷን ደስታ ያህል ታቦት የሚሸከሙ ካህናት እንኳን ደስ የሚላቸው አይመስለኝም፡፡ የሷን ደስታ ተቃራኒ የኔ ልብ እንደ ትኩስ ቁስል ይደማል ፣ ለንስሃ እንኳን የማይሆን ማርፈድ እንዴት ሰው ሊያረፍድ የችላል?፡፡

ተሸክማኝ ሄዳ ተሸክማኝ ትመጣለች ፣ እኔን ተሸከማ ስራ መመላለስ ከጀመረች ሁለት ወር አለፋት፣ ቅጣቴ በእንባዬ ይካስልኝ ይመስል ጀርባዋን በተደገፍኩ ቁጥር ማንባት ከጀመርኩ እኔም ሁለት ወር አለፈኝ፡፡

እንደተለመደው አኔ ድንጋይ ልጇን ተሸክማ ከስራ ከተመለስን ቡኋላ ልብሷን ልትቀያይር ወደ ጓዳ ገባች ሁሌም ልብሷን ስትቀይር መጀመሪያ መጋረጃ ትጋርዳለች፤ ለወትሮ ግን መጋረጃውን ከድካም ብዛት አልጋረደችውም ነበር፡፡

........ሹራቧን አወለቀችው ፤ ቲሸርቷን አወለቀችው ፤ ጀርባዋ ጠቅላላ ቆስሏል ፣ ባንድ በኩል ሲላጥ ሲደርቅ ሲላጥ ሲደርቅ ጠባሳ የሆነ ጀርባዋን ባዝሊን ትቀባለች ።

' ሞትን ይመኟታል ነገር ግን ማንም አያገኛትም ' የተባለው ቃል በኔ እንደተፈፀመ ገባኝ ፤ ምክንያቱም እራሴን ለማጥፋት እንኳን ምንም አይነት ጉልበት የለኝም፡፡ አይኔ እያየ የናቴ ጀርባ ከመቁሰልም አልፎ ሲጎብጥ እንደማየት ምን ሞትን የሚያስመኝ ነገር አለ?፡፡

ከአንድ አመት ቡኋላ ቀን በቀን እየሞትኩ ስለነበረውና ስላለው አሳፋሪ ታሪኬ እንድፅፍ ነው መሰለኝ ቀኝ እጄ ተፈታ ። እናም እናትህን ለምታንገላታ ፤ እናትህን ለምትገላምጥ ላንተ ፤ ስያሜ ታቶላት"" እ'........ናት የተባለችውን ሴት እንደኔ እንዳታደርጋት ይሄን ፅሁፍ ፃፍኩልህ፡፡


(የጌትነት ልጅ)
(@mar_yamye)

@wegoch
@wegoch
@Mahletzerihun
#ህዩድ
፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲፲

ናዊአብርሃም
( @nawi1 )

፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬፬

ዛሬ ያለወትሮዬ በጠዋት ከአልጋዬ ወርጄ ፊት ለፊቴ ያለችው ትንሽዬ የመስታውት መስኮት አጠገብ በባዶ እግሬ ሄጄ ቆምኩ ። የክፍሉ ወለል እጅግ ይቀዘቅዛል ። (ቢሆንም ከልቤ ቀዝቃዛ መውጅ አይበልጥም ) ስሱን ደብዘዝ ያለ ሰማያዊ መጋረጃ ገለጥኩ ፤ ከመስኮት መስታወቱ ወዲያ ያካፋል።(ከመስታወቱ ወዲህ ግን ልብ የሚሰነጥቅ መብረቅ ያጀበው ዶፍ ይጥላል።)
መስታወቱ ላይ ነቁጥ የዝናብ ጠብታዎች እዚህም እዚያም ተበትነዋል።

ትንሽ ፈንጠር ብሎ ካለው አንድ ለጊቢው የሆነ የፅድ ዛፍ መርፌ ቅጠሎች ላይም እኚሁ ነቁጥ የውሃ ኳሶች አሉ።( ዛሬ ግን ወትሮ እንደማያቸው የገና ዛፍ መብራቶች አልመሰሉኝም ፣ይልቁንም ዛሬ አብረውኝ እያነቡ ይመስላሉ።) ሳቢ የኔ መልካም ሰው . . .

ሀዘኔን መርሳት አልቻልኩም፣ የምርም ብቻዬን ነው ያለሁት ) ሳቤላ የኔ እናት ፣ የኔ መምህርት ፣የኔ ሕቱም ፍቅር ፣ ቀሚስሽን ይዤ አብረን የኳተንባቸውን መንገዶች ወጥቼ ላፈጥባቸው እፈልጋለሁ ።

ግን ዳንዎቻችንን መንገዶች ዘንግተዋል ፣ ዝናብ አጥቧቸዋል፣ ሌሎች ተረማምደውበታል፣ በአውራ ጎዳናው የፃፍነው ታሪክ ላይ ሌሎች ታሪካቸውን ደርበው ፅፈዋል። (ልቤ ላይ ግን ሌላ ታሪክ ላይደረብ ተከትቧል። ቢደረብም ድምቀቱ ይረታል።)

ከቤት እግርሽ ሲወጣ አብረን የምንከተል ንስቲት ውብ አልቦዎችሽ ፣ ዛሬ ላይ የእግሮችሽን ነቢር መነጠቃችን ከጎዳናው እንድንርቅ አድርጓል።
ቆይ እኔ 'ምልሽ እማ . . .

"የትዕዛዛቴ ሀሉ ማሰሪያዉ ፍቅር ነው ።" ያለ አምላክ እንዴት ወላጃችንን ፣ አንቺን ባከበርን ፣ በወደድን እንዲሁም በታዘዝን መናችን ፍቅርሽን ይነጥቀናል ? ስለምን ይቀማናል ? በፋንታው ማንን እንካችሁ አለን?

እኔ እሱን አልወድም፣ እኔ ቀማኛ አምላክ የለኝም። እኔ ለሱ አለሰግድም ፣ እንደውም ሀልዮቱን ክጃለሁ ። የትኛውም ቄስ መጥቶ ሥርዓተ ቄደር እንዲፈፅምልኝ አልፈልግም። ንስሀም ከቶ አልገባም።
ልቤን በቁሜ ነጥቆ ፣ እምቡዝ አድርጎኛል። እኔ በጭራሽ ማረኝ አልለውም። ሲያሻው ገሃነም ይወርውረኝ ። እማዬ ፣ የኔ ሳቤላ ናፍቀሺኛል . . . ናፍቀሽናል።
ባንቺ ብዙ አነባሁ ፣ ሀዘኔን መቋጫ አጣሁ ።

ቤተሰቡ ተከትሎሽ አንቀላፋ፣ በቁሙ አንቀላፋ። ባዶ ሆነን ራሳችንን አገኘን ።

ልቤ ከልቧ ከልብ የሆነ መልስ ትሻለች።
ብዙዎች እንደሚሉት ይሄን ልቤን ለተጫናት ሀዘን እውነት መድሃነቱ ጊዜ ብቻ ነው? እውን ልክ ናቸው? እንጃ እኔ አልመስልህ ብሎኛል። ኡፍፍፍ . . . ፍፍፍ. . ሁሁሁ!! ታመምኩ እማዬ. . .

ያለፈው ወር ትክ ብለሽ ታይው የነበረው ፣ እንደ ልጅሽ መመንደጉ ገርሞሽ ትነካኪው የነበረው ፅጌሬዳ፣ አበባው እንባ አቅሯል። ግዑዝ ሁሉ አብሮኝ እያነባ ይመስለኛል።

የአምስተኛ ክፍል ውዳኤ መንፍቅ ላይ ለባቢ ገዝተሽ ማንበብ የጀመርሽለትን ያ እንደውም " አስደናቂው የይቅርታ ቅርስ" የሚለው መፅሐፍ? . . . እሱን መፅሃፍ አንብቤ ጨረስኩለት እኮ. .

አኔት፣ ሉሲየን፣ ዳኒ ሁሉም ደስ ብለውታል ፤ ጓደኞቹ ሆነው ነበር ግን መፅሃፉን ስጨርስለት ተጠፋፉ መሰል እራሱ ደግሞ እያነበበው ነው ። በተለይ ዳኒ ይናፍቀዋል፣ እሱን ስለሚመስለው ይመስለኛል፣ ትዝ ይልሽ የለ? የዳኒ እናት እሱን በወሊድ እያለች መሞቷን አንቺ ነበርሽ ያነበብሽለት።

ያኔ አጠገባቸሁ ፊዚክስ እያጠናሁ ቀልቤ ግን ከእናንተው ጋር ነበር። ኧረ ከዛ ቡሃላ ስንት ነገር ተፈጠረ መሰለሽ ዳኒ ገደል ወድቆ . . .ግን ተርፏል። አኔት እህቱ የቤቱ ስራ አጨናንቋት ተሰቃየች ።ብቻ ግን ደህና ናቸው።እኛም ደህና ነን።

እማዬ . . . መፅሃፉን የፃፈችው 'ፓትሪሺያ ሴንት ጆን' ደሞ ሴት መሆኗን ማህሌት ነግራው. . ." እኔ ደሞ የማዬ ዘመድ ነው ምትመስለኝ!" አለን። ያህን ሉጫ ፀጉሩን እያሻሸ . .

"ለምን?" ብላ ስትጠይቀው

" ትመስለኛለች፣ ፀጉሬን እየነካካች የምታባብለኝ . . .ነገር . . . " ብሎ ዝም አለ።

እውነት አለው! አንቺ የህይወት ኑረት ውስጥ እንድንበረታ የፃፍሽልን ነው 'ሚመስለኝ ፣ እኔም በበኩሌ ፀሃፊዋ አንቺ ትመስይኛለሽ። የኛ ሳቤላ ፣ የኛ ደራሲ።

አባዬ ደሞ ያ እረፍ ብለሸው የተወውን ነገር ተደብቆ ያደርጋል። ሳያየኝ ፣ እኔ ግን አይቼዋለሁ።
እኛን ሲያይ አንቺ እንዳለሽ ሁሉ ለመሆን ይታገላል። ሊያስቀን ይሞክራል ፣ ማሂ እና ባቢ ዝም ይሉታል። እንዳይደብረው ብዬ ትንሽ ፈገግ እላለሁ። እቤት ብዙ አይቀመጥም። ከስራ መጣ ወይ ይተኛል ፣ ወይ ደሞ ሰፈር ውስጥ ከሙሌ ፊልም ቤት ፊት ለፊት ካለችው ግሮሰሪ ገብቶ ይቀመጣል። አንዳንዴ ከ"ቲቶርያል" ክላስ ደንገዝገዝ ሲል አምሽቼ እመለሳለሁ፤ እናም በግሮሰሪው በኩል ሳልፍ ካለ ጠርቶኝ
እንድጠብቀው በእጁ ምልክት ይሰጠኛል ፤ ከዛ አብረን ቤት እንገባለን ።

የሆነ ቀን ውድቅት ላይ እያጠናሁ
ምን ተፈጠረ መሰለሽ . . . ከመኝታ ክፍላችሁ የቀዘዘ ማቃሰት የሚመስል ድምፅ ሰማሁ። በመጀመሪያ አባዬ በእንቅልፍ ልቡ ነው ብዬ ትኩረቴን ወደማጠናው ትምህርት አዙሬ ነበር። ነገር ግን ይሄ ድምፅ ቀደም ከሰማሁት ድምፅ ትንሽ ከፍ ብሎ ተደገመ። ይሄኔ ግራ ተጋባሁ ፣ ማታ ማሂ እራት አቅርባልኝ በልቼ፣ በለሊት ተነስቼ ለማንበብ ስል በጊዜ ነበር የተኛሁት፤ ከአባዬ ጋር አልተገናኘንም ነበር።

ሁሉም ተኝተው እኔ ብቻ የነቃሁ መስሎኝ ነበር። ማሂ ከመተኛቴ በፊት ከለሊቱ 10:00 እንደቀሰቅሳት ነግራኝ እንደተኛች ነበር። ባቢም ተኝቶ ነው ከጎኑ ተነስቼ ወደ ሳሎኑ ጠረጴዛ እና ወንበር ያመራሁት።

ለሶስተኛ ጊዜ ያህ የመዛበር ድምፅ ከመኝታ ክፍላችሁ መጣ።

" ምንድን ነው? አባዬ የት ነበር ማታ ? የኛን ሳቤላ ገና በአንድ ወሯ . . . እንዴት ? "ብዬ በንዴት ጦፍኩ።

ቀጥ ብዬ ወደ ክፍሉ አመራሁ ። ልክ ክፍሉ አቅራቢያ ስደርስ

" ሳቢ የኔ! . . .የኔ እ.....ና ..ት !! ምነው ጥለሽን . . . የኔ አመለወርቅ . . ምን ልሁነው . . ."

የአባዬ የለቅሶ ሲቃን ሰማሁት።

አባዬን ከቀብርሽ ዕለት ቡሃላ ሲያለቅስ ማግኘቴ ይሃ ሁለተኛዬ ነበር። (ለአባዬም ለልጆቹም እናት ነበርሽ) ወደ ወንበሬ ተመልሼ ስቅስቅ ብዬ አነባሁ። አባዬን አግባብ ባልሆነ መንገድ መጠርጠሬም ጭምር አስለቀሰኝ።

ሳያየኝ ሲያደርግ አየሁት፤ ያልኩሽንም ማሂ መኝታ ክፍላችሁን ስታፀዳ አግኝታበት ነበር፤ የሲጋራ ቁርጥራጮች ክምር።

"አማኔ !! "

"አቤት ማሂ! "

"ቁርስ ደርሷል።"

(መጣሁ ሳቢን መሳይ ፣ መጣሁ እታለሜ።)

መስኮቱን ዘግቼ፣ ስሱን መጋረጃም መለስኩ።
ክፍሉ እንደመጨለም አለ።
◦ ◦ ◦
07/09/2013 ዓ.ም
--------------------------------------------

@wegoch
@wegoch
@Mahletzerihun
ወድጄ እኮ አዉቃለሁ። 'ከአንዴም ሁለት ሶስቴ ፍቅር ደርሶብኛል' ይል የለ
ከያኒዉ። የእዉነት!! ብዙ ጊዜም የወደድኩ መስሎኝ ከስሜቴ ጋ ድብብቆሽ
ተጫዉቼ ያለፍኩባቸዉ ጊዜያት ቁጥር አልባ ናቸዉ። የመጣዉን ጊዜ ሳየዉ
ያለፈዉ ቀላልነቱ በደንብ ታየኝ። ብዙ ጊዜ ለመዉደድ አልታገልም። ለመወደድም
እንደዛዉ። ዝም ብሎ ፍስስ ... ልስልስ ያለ ነገር እወዳለሁ። መያያዝ እንጂ
መተናነቅ አይስበኝም። ከተወኝ ጋ ፊትህን መልስ ብዬ ዳኛ ፊት አልቆምም።
እንዲያዉም እንዲያዘልቅለት ፣ በመሄዱ እንዳይቆጭ ሱባኤ እገባለት ይሆናል።
ሂሂሂ! መታገል ያደክመኛላ!! ከወደደኩት ጋ መቋሰል አልሻም። መድሐኒቴ ብዬዉ
ከነበረ ሰዉ ህመም አልሸምትም። ሲደላ ብዙ ነገር ቀላል አይደል? ትዉት
ሲያደርጉት ትዉት ፤ ራመድ ሲሉ ሰበር ሰካ አይደል የሚሆነዉ? ቢኳሉት ድምቅ ፣
ቢለብሱት ስክት ይል የለ? ይገርማል። ዉስጣችን ስንት የተሸመነ ስሜት ያላቸዉ
ማንነቶችን ይዘን እንደምንዞር። ቀላል ነዉ ያሉት ከአለት ሲጠነክር ምን ይሉታል?
...
የመጀመሪያዎቹ ሰሞን እንደ አልፎ ሂያጅ መንገደኛ ትከሻ ለትከሻ ተሻሽቶ
የማለፍን ያክል ነበር ቅርርባችን። ከሁለት ምልልስ ያልዘለለ ሰላምታ ብቻ።
ስንቆይ እንደ ጆንያ ያለ እህል እንደማይቆመዉ ያለፈገግታዉ መቆም አቃተኝ።
ከእናቷ ተለይታ እንደምትያዝ ጥጃ ሲለቋት ወደ እናቷ ጡት እንደምትሮጠዉ፤
ነግቶ ምድር ከሰማይ ስትላቀቅ ወደ እሱ ለመሄድ መደፋት ቀረሽ መጣደፍ
ዉስጥ እገባለሁ። ፈገግ እላለሁ። ስለማገኘዉ ፣ ላወራዉ ስለሆነ ፣ ሲስቅ
ልሰማዉ ስለሆነ እና በእሱ ዙሪያ ስለማገኛቸዉ መልካም ነገሮች ሁሉ እያሰብኩ
እፈግጋለሁ። ምን እየሆንኩ ነዉ ብዬ ራሴን መታዘቢያ ጊዜ እስከማይኖረኝ።
ህልሞቻችንን አንድ ላይ ላስር ቸኮልኩ። ስቸኩል ነገር ሳትኩ። የሆነ ነገሬ ጎደለ።
የቱ ጋ? እንጃ!!
...
ብዙ ያልነገርኩት ናፍቆት አለኝ። ሲተኛ ስለተናደድኩባቸዉ ፤ አሁን በነቃ አሁን
በነቃ እያልኩ ስላሰብኩባቸዉ ምሽቶች ፣ ሲደክመዉ ስለሚያምር ድምፁ ፣
ስለሚያስቀኑኝ ትዝታዎቹ ፣ አካላቸዉ መሆን ስለምመኛቸዉ ህልሞቹ
አልነገርኩትም። ገና መቼ ወድጄዉ ጠገብኩ? የመዉደዴ ሀገር መሃል ይዤ
የቆምኩት ያልተቀባባ ፍቅር ነዉ። አልኳልኩትም። ስላልኳልኩት አያምር ይሆናል።
ነበርን ለመባባል ደርሰናል? መቼ ተራምደን የመራራቅ ኩርባ ጋ ደረስን? አንተ
ሆይ ያዘኝ! አንተ ሆይ ያዘኝ። የምፈራዉን መታገል እያደረኩት ነዉ። ፊትህን መልስ
እያልኩ ... ሱባኤ ልገባ ነዉ። ከቀናኝ እንደ እስከዛሬዉ ቀኔ ላይ ልኩለዉ።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Ruth Habte Mariyam
Hiking to "Koremash", Menelik armory depot.

📅Hiking Date :- may 30, 2021 (ግንቦት 22, 2013)

🛫Departure:- Piyasa tayitu hotel

Departure Time - 1:00Am Local time 🚩

💵 contribution per person:- 600 ETB and for foreign 20 dollar

🧲 Package 🧲

🚍 - Transportation
🔴 breakfast 🍛
⚪️ Bottled water
🔵 entrance with Guide
🔴 photograph 📷
⚫️ Lunch 🥙

Activities:
🔅trekking, historical place visitation, talent performance(if any) and fun game.

Suitable for:
🔻 medium
🔸 average fitness
🔹 average basic skill required

NB.
🚫 Sanitizer & facemask mandatory!

for more join the
👉channel @sunsethiking
👉📷 @sunsetphotography

🎫 reservation @Paappii (0922303747)
ጆተኒ ስንጫወት ተዋወቅን። በቃ ዝምብሎ ወደደኝ። ጭራሽ አንድ ሰሞን ምንም ባለወቁት ምክኛት የዘዉተር ጋባዤ ሆኖ ቁጭ አለ። እንደዉ ቁጭ ብለዉ ሲቀዱት ቢዉሉ የማያልቅ ብር ይዞ በጡሃት ቤት ይመጣና ይጠራኛል። ቁርሳችንን ከሃሰን ቤት ድንች በብስኩት እንጀምርና። ምሳችንን አስፓልት ሄደን ጥብስ። ፑል እንደፈለግን እንጫወታለን የሚከፍለዉ እሱ። ማሙዬ ደግነቱ ገዛኝ። ብሩን ዝም ብሎ ይበትናል። ምንም አያሳዝነዉ። ይሄ መዝናናት ታዲያ ለሁለት ሳምንት ተከታታይ ቆየ። ታዲያ አንድ ቀንም እንዲዉ እንተለመደዉ ከማሙዬ ጋር ቀኑን ሙሉ ፈታ ስንል
ዉለን ሲመሽ ተለያየን እና ወደቤት ገባዉ። ወደቤት ገብተን 30 ደቂቃ አልቆየንም ከዉጪ የሚያስደነግጥ ጩሀት ተሰማ። ተደናግጠን ምንድነዉ ምን ተቃጠለ ብለን ስኖጣ ማሙዬ ላንቃዉ እስኪቀደድ ይጮሃል። እናቱ አባቱ በጃንሆይ ግዜ የገዙትን ቀበቶ
ወገቡ ላይ እያሳረፈች ፖሊስ ጥሩልኝ እያለች ትጮሃለች። 'ምን ሆነሽ? ምን
አድርጎ ነዉ' ሲሏት ብር እየሰረቀኝ።
እኔ ራቼ ክዉ ለካ ሁለት ሳምንት ሙሉ የሚጋብዘኝ ከእናቱ በሚሰርቀዉ ብርር
ነዉ ለካ ብሩ የማያሳዝነዉ የራሱ ስላልነበረ ነዉ። በላቡ ስላላመጣዉ። ስላልለፋበት። እንዴት እንደመጣ ስላለወቀ። ያን ብር ማምጣት ምን ያህል ዋጋ እንደሚያስከፍል ስላልገባዉ። የሱ ስላልነበረ ነዉ ለካ እንደዛ የሚበትነዉ። እናት መደብደቡን በመሃል ገታ አደርጋ 'እሺ ብሩ የታል? ብላ ጠየከች ድምፁ እየተቆራረጠ 'ተዝናንበት' ከማን ጋር' እናት አሁንም ጠየቀች የራቼ ነብስ ልቶጣ
ማሙዬ አሁንም በሚቆራረጥ ድምፅ 'ከ ራ' መዳኒያለም ድረስ ወደ ዋላ ዞር አልኩ። 01 ያለዉ አጎቴ ናፈቀኝ

@wegoch
@wegoch
@paappii
#Rache_Tesfaye
2024/09/23 11:28:10
Back to Top
HTML Embed Code: