Telegram Web Link
#Elssa_Mulugeta

አሁን ዛሬ ላይ ሆኜ በመደነቅ ልል የምችለው ነገር " ትናንት እንዴት ውብ ነበረ"
ን ነው ። በቀዝቃዛ ማታ እንደማገኝህ ሳስብ ጮቤ የምትረግጥ ነፍሴን ልክ
አጠገቤ ስትደርስ ምን ሆና ዝምታ እንደሚሸብባት ግራ ይገባኝ ነበር ።
ትናንት አጋጭተን ሳንጎነጭ ስለተውነው ፅዋ ይቅርታ ልጠይቅህ እፈልጋለሁ ።
ናፍቀኸኝ እንደነበር ስላልነገረህ አፌ ይቅርታ
በጣም ስለወደደችህ ልቤ ይቅርታ
እጆችህ እንዲዳብሱት መፈለጉን ስላላሳወቀህ ገላዬ ይቅርታ
ቻው ስትለኝ ያቀረረ እንባዬን ጨክነው ስላላፈሰሱ አይኖቼ ይቅርታ
ስታቅፈኝ ቀጥ ስለሚል ትንፋሼ ይቅርታ
የተሰበረ ጊዜያችን ውስጥ ያልፈሰሰ ትውስታ ለታቀፍኩኝ ለእኔ ስትል እኔን ይቅር
በለኝ ።

@wegoch
@wegoch
@paappii
ወጣትነት - ሞራል
________________

ከጥቂት ወራት በፊት የቁጠባ ባህል እንዲሰርፅብኝ በማሰብ አባቴ የሀገሪቷን እና የከተማይቱን እውነታ ተገንዘቢ በሚል ከቤት ይዞኝ ይወጣል። በዚህም ምክንያት ደላላዎች ጋር፣ የተለያዩ real state-ኦች እና ሰፈሮች እንዲሁም መኪና መሸጫዎች እንሄዳለን። ስለኑሮ ውድነት ባውቅም፣ የእውነት በቁጥሮች አስቤ ‘እኔ የት ጋር ነኝ?’፣ ‘አሁን ባለኝ አቅምና፣ ህይወቴ ሊይዘው በሚችለው አቅጣጫስ የወደፊት እውነታዬ ምን ሊመስል ይችላል?’ ብዬ አስቤ አላውቅም። ለቤት፣ ለመሬት፣ ለመኪና ብዙ ሚሊየን ብር እንደቀልድ ሲጠራ እውነት ያስደነግጣል። ግን ከእኔ መደንገጥ ባለፈ፣’ አብዛኛው ማህበረሰብ እነዚህን ነገሮች የመግዛት አቅሙ ምን ይመስላል?’ የሚለውን አለማሰብ አልቻልኩም። የተሻለ ሙያ ተብላ በህክምና ተመርቃ በወር ሰባት ሺህ እና ስምንት ሺህ ለምታገኘው እህቴ እና ጓደኞቿ፣ ከዛ ደሞ በጣም ያነሰ ለሚከፈላቸው ብዙሀን (አማካይ) የከተማው ሰዎች ቤት፣ መኪና እሩቅ ህልሞች ናቸው ወይ? ቤተሰቦቼ
የ200 እና 300 ብር ተቀጣሪ አስተማሪዎች ሆነው ፣ ቤት እና መኪና የሚጨበጡ ህልሞች የነበሩባቸው ጊዜ ከሁለት አስርት አመታት አያልፍም። ዛሬ ግን 120 ካሬ ሜትር ቤት አራትና አምስት ሚሊየን ብር ጥሪ ሲደረግበት፣ ይህንን ቤት afford ለማድረግ የአምስት ሺህ ብር ተቀጣሪ ሳይበላ ሳይጠጣ ገንዘቡን ለ80 አመት መቆጠብ እንዳለበት፣ ከአማካዩ ገቢ በጣም ከፍ ብለን እንኳን 50,000 ብር የሚከፈለውን ሰው ብናስብ ሙሉ ደሞዙን ቢቆጥብ 8 አመት እንደሚፈጅበት አስባለሁ። ያው በ8 አመት የቤቱ ዋጋ ምን ያክል ይጨምራል የሚለውን ግምት ውስጥ ሳናስገባ። ታዲያ እነዚህ መሰረታዊ ነገሮች ለብዙሀኑ ሩቅና የማይጨበጡ ህልሞች ከሆኑ፣ ለአብዛኛው ሰው የሚጨበጠው ህልም ምንድነው? አብዛኛው ሰው ነገውን በምን ሁኔታ ነው የሚያስበው? የማይጨበጡ ህልሞች ባሉበትስ የስራ፣ የእድገት፣ የመለወጥ ሞራላችን ምን ይመስላል? የሀገራችን ግለሰባዊ የኢኮኖሚ የእድገት መሰላል ግልፅ ባልሆነበት ሁኔታ፣ በተለይ ለተማረው ሰው ህልሙ ሀገርን ለቆ መውጣት ቢሆን አያስገርምም አይደል? ታዲያ እንዴት የሚጨበጡ ህልሞች፣ በግልፅ የሚታዩ እና የሚተገበሩ ግለሰባዊ የእድገት ደረጃዎች እንዲኖሩ ማድረግ ይቻላል? ምናልባትም እንደሀገር ያለን ትልቅ ሀብት የሰው ሀይል ነው፣ ግን የስራ፣ የመለወጥ፣ የእድገት ሞራል የሌለው ወጣት እንደ ሀብት ይቆጠራል፣ እንደ ሀብት ይሰራል?

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Hewan Hulet Shi
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (Ermiyas Dejene)
ቅንድል-መፅሔት ቅፅ-፪ ቁጥር-፬.pdf
5.9 MB
#ቅንድል_ዲጂታል_መፅሔት

★ቅፅ-፪ ቁጥር-፬

በአውደ ብሩኀን ገፆች ከዶ/ር ኤሊያስ ገብሩጋ አስተማሪ ቆይታ

አጃኢብ ያስባሉ ባህሎች

ኢትዮጲያዊ ቅኖች የተመሰገኑበት፡፡

አሸላሚ የበዓል ውድድር የተካተተበት

አስደናቂ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውጤት የተዳሰሰበት

ሌሎችም በርካታ መረጃዎች

ያንብቡትና ብዙ ያትርፉበት


የበፊት ዕትሞችን ለማግኘት ይሄን ይጫኑ

@KendelM
#ሃሳብዎን በነፃነት ይስጡ!


ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ከዚህ በታች የቀረቡት ቃለመጠይቆችን ከመስከረም 2012 ዓ.ም አንስቶ እስካሁን ባሉት ጊዜያት የተፈፀሙ ወይም የተከናወኑ ጉልህ አገራዊ ሁነቶች የሚመለከቱ ናቸው። ዓላማውም የቻናላችን አንባብያን የዓመቱ ምርጥ፣ ተወዳጅ፣አሳዛኝና አስደንጋጭ ክስተቶች በተመለከተ ሀሳባቹን ወይም አስተያየታቹን መሰብሰብ ነው።ምላሽ በመስጠት የተለመደውን ተሳትፏቹን እንጠብቃለን። እናመሰግናለን!🙏🙏


1 የዓመቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ የክልል ፕሬዝዳንት
2 የዓመቱ ስኬታማ የመንግስት ተቋም
3 የዓመቱ አሳፋሪ የመንግስት ተቋም
4 የዓመቱ ተስፋ የሚጣልበት የዲሞክራሲ ተቋም
5 የዓመቱ አስደማሚ የመንግስት ስኬት
6 የዓመቱ ስኬታማ አገራዊ ንቅናቄ
7 የዓመቱ አስደንጋጭ ስኬት
8 የዓመቱ ተፅእኖ ፈጣሪ አክቲቪስት
9 የዓመቱ ምርጥ የፓለቲካ (የመንግስት ) መሪ
10 የዓመቱ ተወዳጅ የቴሌቪዥን ጣቢያ
11 የዓመቱ ተወዳጅ የሬድዮ ጣቢያ
12 የዓመቱ ምርጥ ኢ-ልቦለድ መጽሐፍ
13 የዓመቱ ተወዳጅ የኪነ ጥበብ ምሽት
14 የዓመቱ የሰላም የፍቅር አርዓያ
15 የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ድራማ
16 የዓመቱ ነጠላ ሙዚቃ
17 የዓመቱ ምርጥ የሙዚቃ አልበም
18 የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ
19 የዓመቱ አሳፋሪ የፓለቲካ ውዝግብ
20 የዓመቱ ምርጥ የበጎ አድራጎት ድጋፍ
21 ምርጥ ታሪካዊ ልብወለድ
22 ምርጥ የወግ መጽሐፍ
23 ምርጥ የፍልስፍና መጽሐፍ ―
24 ምርጥ የስነልቦና መጽሐፍ ―
25 ምርጥ የልብወለድ መጽሐፍ ―
26 ምርጥ የፖለቲካ መጽሐፍ―
27 ምርጥ የታሪክ መጽሐፍ ―
28 ምርጥ የሕይወት ታሪክ―
29 ምርጥ የግጥም መጽሐፍ ―
30 ምርጥ የትርጉም መጽሐፍ ―
31 ምርጥ የምርምር መጽሐፍ ―

# ማስታወሻ :- ስትልኩልን ስማቹን ፣ የምትኖሩበት ቦታ አብራቹ መላካቹን እንዳትረሱ 🙏🙏🙏

👇👇👇👇

@balmbaras
@Nagayta
ስም :- ባሮክ

አድራሻ:- ከመቂ


1 ዶክተር ደብረጽዮን
2 ቴሌ ና ግምሩክ
3 አዱገነትን ጨምሮ የኦሮሚያ አመራር
4 ወፍ የለም
5 የአባይ ሙሌት
6 የአባይ ሙሌት
7 የለም
8 አክቲቪስት ባይሆንም ዘመድኩን በቀለ
9 ወፍ የለም
10 Arts
11 ሸገር
12 የለም
13 የለም
14 ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እድሪስ ኦባንግ ሜቶ
15 የእግር እሳት
16 ደሞ በአባይ-ቴዲሻ ና ሔዋን- ከምኔው
17 ዳዊት ፅጌ (የኔ ዜማ)
18 የለም
19 ምርጫው😀
20 የመቅዶንያ ና ሜሪጆይ🤔
21 ከእመጓ እስከ ሰበዝ
22 የበውቀቱ All
23 IDK
24 ሜሎሪና
25 ከእመጓ እስከ ሰበዝ
26 IDK
27 ማሊክ አምባር ከቀንበር እስከ መንበር
28 እረኛው ሃኪም
29 አዳምኤል
30 IDK
31 አንድሮ ሜዳ

ስሜ ማህደር አድማስ
አዲስ አበባ
👇👇

1.ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል
2. ኢትዩ-ቴሌኮም
3.አዲስ አበባ አስተዳደር
4.የለም
5.የአባይ ሙሌት
6.'' አባይ የኔ ነዉ ''
7.
8. ጀዋር ሙሀመድ
9. ዶ/ር ሊያ ከበደ
10. ፋና
11. ሸገር
12.
13.ጦቢያ ( ፍራሽ አዳሽ 2)
14. ኦቡዋንግ ሜቶ
15. የእግር እሳት
16. ቴዲ አፍሮ ' ደሞ ለአባይ '
17. ዳዊት ፅጌ ' የኔ ዜማ '
18. አስቴር በዳኔ
19. አዲስ አበባ የኛ ናት 😂
20. 'አንድ ሰዉ ለአንድ ቤተሰብ '
21. 'ምንትዋብ ' ህይወት ተፈራ
22. 'ነፀብራቅ' ሌሊሳ ግርማ
23.
24.
25. 'በሀሰተኛ ስም ' አለማየሁ ገላጋይ
26. 'ዳኛዉ ማነዉ ' ፕ/ር ታደለች ሀ/ሚካኤል
27.
28. ' እረኛዉ ሀኪም ' ፕ/ር ምትኩ በላቸዉ
29. 'ኣዳምኤል ' በእዉቀቱ ስዩም
30. ' ሆሞሬዮስ ' ዳግም ጥላሁን


Besrat Gezu ከ ሰሚት 👇👇

1 የዓመቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ የክልል ፕሬዝዳንት
- የሲዳማ መሪ ደስታ ሌዳሞ
2 የዓመቱ ስኬታማ የመንግስት ተቋም
- አየር መንገድ
3 የዓመቱ አሳፋሪ የመንግስት ተቋም
- ኢትዮ ቴሌኮም
4 የዓመቱ ተስፋ የሚጣልበት የዲሞክራሲ ተቋም
- General Attorney
5 የዓመቱ አስደማሚ የመንግስት ስኬት
- First Round Dam Filling
6 የዓመቱ ስኬታማ አገራዊ ንቅናቄ
- Planting 5 Billion plants
7 የዓመቱ አስደንጋጭ ስኬት
- 🤷‍♂🤷‍♂
8 የዓመቱ ተፅእኖ ፈጣሪ አክቲቪስት
- ቢኖር ምን አስደበቀኝ
9 የዓመቱ ምርጥ የፓለቲካ (የመንግስት ) መሪ
- ዶ/ር ሊያ ታደሰ
10 የዓመቱ ተወዳጅ የቴሌቪዥን ጣቢያ
- ፋና
11 የዓመቱ ተወዳጅ የሬድዮ ጣቢያ
- ሸገር 102.1
12 የዓመቱ ምርጥ ኢ-ልቦለድ መጽሐፍ
- ሰበዝ
13 የዓመቱ ተወዳጅ የኪነ ጥበብ ምሽት
-
14 የዓመቱ የሰላም የፍቅር አርዓያ
- እኔ
15 የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ድራማ
- የእግር እሳት
16 የዓመቱ ነጠላ ሙዚቃ
- ኃይለየሱስ ፈይሳ - ፍቅር ተወደደ
- ትምኒት ወልዳይ - ቃህ
- ሄዋን //ወልድ - ከምኔው
17 የዓመቱ ምርጥ የሙዚቃ አልበም
- የዳዊት ፅጌ የኔ ዜማ
18 የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ
- ስሜነህ ባይፈርስ
19 የዓመቱ አሳፋሪ የፓለቲካ ውዝግብ
- የትግራይ ክልል የምርጫ ካላደረኩ አሻፈረኝ ማለት
20 የዓመቱ ምርጥ የበጎ አድራጎት ድጋፍ
- የ አዲስ አበባ የቤት እድሳት
21 ምርጥ ታሪካዊ ልብወለድ
-
22 ምርጥ የወግ መጽሐፍ
- ሰበዝ
23 ምርጥ የፍልስፍና መጽሐፍ ―
- መፅሐፈ ጨዋታ ስጋዊ ወመንፈሳዊ
24 ምርጥ የስነልቦና መጽሐፍ ―
-
25 ምርጥ የልብወለድ መጽሐፍ ―
-
26 ምርጥ የፖለቲካ መጽሐፍ―
-
27 ምርጥ የታሪክ መጽሐፍ ―
-
28 ምርጥ የሕይወት ታሪክ―
- የአስጌ የኢቲቪ ኢንተርቪው
29 ምርጥ የግጥም መጽሐፍ ―
-
30 ምርጥ የትርጉም መጽሐፍ ―
-
31 ምርጥ የምርምር መጽሐፍ ―


Biniam አርባምንጭ 👇👇

1,የአፋር ክልል ኘሬዝዳንት
2,Tele
3,ህወሃት
4,ኢዜማ
5,የአባይ ሙሌት
6,ስለ አባይ
7,የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ivory costn ያሸነፈበት
8,posetive ተፅእኖ አላየሁም nagative ከሆነ Ja war
9,Dr.abiy ahimed ali
10.Arts tv
11,yilefegn
12, ''
13, ''
14,ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድርስ
15, 9ኛው ሽ
16,ቴድ አፍሮ ደሞ በአባይ
17,የኔ ዜማ Dave
18, ኤልያስ መሠረት
19,የ ትግራይ ክልላዊ ምርጫ
20, ማዕድ ማጋራት (የ ኢትዮጵያ ህዘብ በ ሙሉ)
21,Yilefegn
22, ''
23,''
24, ''
25, ዴርቶጋዳ


ስም: ሱራፌል አሰፋ
አድራሻ: አዲስ አበባ (አዲሱ ገበያ)
👇👇👇


1. አቶ ሙስጠፌ መሀመድ
2. ኢትዮ ቴሌኮም
3. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
4. .........
5. ሸገርን ማስዋብና የአባይ ውሀ ሙሌት
6. ድምፃችን ለግድባችን
7. የአባይ ውሀ ሙሌት
8. .......
9. ዶ/ር ሊያ ታደሰ
10. Esat
11. ሸገር FM 102.1
12. .....
13. ......
14. ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድሪስ
15. የእግር እሳት
16. ቴዲ አፍሮ (ደሞ በአባይ)
17. ዳዊት ፅጌ (የኔ ዜማ)
18. ሲሳይ አጌና (ኢሳት ቲቪ)
19. ግድቡ ተሽጧል እና ኮንዶሚኒየሙ
20. ለኮሮና የተደረገው ርብርብ ከመላው ኢትዮጵያን
21. - 31 የለም


ስም፦ ስምረት (Ellameta)
አድራሻ ወሎ ደሴ

👇👇👇

1ሙስጠፌ የሶማሌው
2ኢትዮጵያ አየር መንገድ ና ቴሌ
3የአአ ከንቲባ ቤቶች አስተዳደር
4የፌደራል ፍርድቤት
5የህዳሴውን ግድብ ሙሌት ማስጀመር
6የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ
7የመጀመሪያው ዙር የግድቡ ሙሌት መጠናቀቅ
8ጀዋር መሀመድ
9ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ
10 Art tv
11. ሸገር
12
13.የለም
14. ኡባንግ ሚቶ፣ ቀዳማዊ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እንድሪስ
15.ዘጠነኛው ሺ እና ቤቶች
16 ደሞ በአባይ(ቴዲ አፍሮ)
17.የኔ ዜማ የዳዊት ፅጌ
18.ተመስገን ደሳለኝ ፍትህ ጋዜጣ
19.የአርቲስት ሀጫሉ ግድያ
20.
21.የፍቅር ድንግልና(የጂጂእናት የፃፈችው)
22.እግረ መንገድ ስብሀት ገ/እግዚአብሔር
23.ጥበብ ከጵላጦስ ሀ/ጊዮርጊስ
24.ሜሎሪና ናሁሰናይ
25.ደህንነቱ ይስማዕክ ወርቁ
26.ዳኛው ማነው ታደለች ሀ/ሚካኤኣ
27.አዲስ አላነበብኩም
28.
29 .የራሴ
30.አልኬሚስት
31. ግራ አጋቢው ዘመን ትርጉም ነው
የእኔ መልስ ይሄንን ይመስላል

👇👇መልእክታቹን በዚህ ላኩልን

@balmbaras
@Nagayta
Forwarded from ሥዕል ብቻ ©
🌼ከአዲሱ አመት ጋር ፍክት ፍክትክት ይበሉልን🌼
🌼🌼🌼መልካም ዋዜማ🌼🌼🌼
#By_Ribka_Sisay🌼 ______________ @seiloch @seiloch @seiloch
ሃሳብ በሃሳብ …………!


ግሩፑን ለመቀላቀል

↓↓↓↓↓↓
https://www.tg-me.com/joinchat-Fez2QULOAgfN0GjJ8uG8aQ
አዲስ . . .
አዲስ ዓመት ላይ አዲስ በ"አ" ዓመት ደ'ሞ በ"ዓ" የሚፃፉበትን ሚስጥር ነጋሪ
ወይ ተናጋሪ (የአማርኛ not የግዕዝ) ባናገኝም... ብዙ ጊዜ አዲስ ሲባል ጥሩ
ነገር አመላካች ነው (ለከተማና ለአካባቢ እንዲሁም ለሥራ ሲሆን ብቻ
ቢያስበላም (ለወሲብ ጨምሮ (ሴት ስትሆን)))
እና... አንድ ጠቢብ ወዳጅ አንድ ወቅት እንዲህ ሲል ምክረ ሀሳቡን (በብስጭት
መልክ) አካፍሎን ነበር፣ እኔም በልቤ አኖርኩት፦
" ሰዎች 'አትጠጣ ጉበትህን ይጎዳዋል፣ አታጭስ ሳንባህን ይነካዋል፣ አትቃም
ጨጓራህን ይወጋዋል' እያሉ አዛ ያረጉናል። ቆይ እኔ የምለው ... ጨጓራ፣ ሳንባና
ጉበት እኔን አቅማቸው እስከፈቀደ ድረስ ተደስቼ እንድኖር እንዲያገለግሉኝ ነው
የተፈጠሩልኝ? ወይስ እኔ እነሱን ተሳቅቄና ተጠንቅቄ ተንከባክቤ እንዳኖራቸው
ነው የተፈጠርኩላቸው? "
እህእ!
በርካታ ሰዎች ስለሕሊና ሲያወሩ ተመሳሳይ (ወይም ተቃራኒ) አረዳድ
አይባቸዋለሁ። ሕሊናቸውን አዲስ እና ንፁህ አድርገው መኖር እንዳለባቸው
ስለሚያስቡ ፈፅሞ አይጠቀሙበትም። Hence ሕሊናቸው ንፁህ ነው¡ "ዜሮ
ዜሮ" ነው፣ የትም ያልተነዳ!
ቀጣዩ ዓመት ሕሊናችሁ እንዲያኖራችሁ እንጂ እንድታኖሩት አልተፈጠረምና፣
ሕሊናችሁን አፍግታችሁ፣ አልፍታችሁ፣ አሟጣችሁና አጨርጭሳችሁ
የምትጠቀሙበት ይሁንላችሁ!

@wegoch
@wegoch
@paappii

#gemechu merera fana
ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን ያሳለፉትን አመት ላየ የዘመን መለወጫ ዋዜማው
በድባቴ የሚያልፍ ይመስል ነበር ውጥንቅጡ የወጣውን አመት መዝጊያም ልክ እንደ አብዛኛው የአመቱ ክፍል
በድበርት የምናሳልፈው ይመስል ነበር፡፡
አዲስ አበባን ዞር ዞር ብላችሁ ስታዩ ግን ሁኔታው ተቃራኒ ነው፡፡ ቄንጠኛ ቡቲኮች ቢጫ እና ቢጫ መሳይ ልብሶቻቸውን በነቂስ አውጥተው ከአደይ አበባ ለመፎካከር እየሞከሩ ነው፡፡ የመንገድ ዳር ቸርቻሪዎች ከዘወትር እቃዎቻቸው መሃል እዚህም እዚያም ገዢ የማያጡበትን ቻይና ሰራሽ የፕላስቲክ አደይ አበባ ይዘው ውር ውር እያሉ ነው፡፡
በግ ተራው ከወትሮው ቢደምቅ እንጂ አልፈዘዘም፡፡ ለገበያ የወጣው ቄጠማ እና ችቦ ከሌላው ጊዜ ቢበዛ እንጂ ፈፅሞ አያንስም፡፡ ኢትዮጵያውያን በእጅጉ ያስከፋቸውን 2012 ገፍትረው ለማስወጣት የጓጉ ይመስል ዋዜማውን በልዩ ድምቀት ተያይዘውታል፡፡ 2013ን ‹‹ቶሎ ናልን እና ከዚህ መቅኖ ቢስ አመት ገላግለን›› በሚል ይማፀኑት በሚመስል አኳሃን በጉጉት ተወጥረዋል፡ ከእልቂቱም፣ ከበሽታውም፣ ከረሃቡም አትርፎ እዚህ አድርሶናልና፤ 2013ን የ2012 ተቃራኒ እንዲያደርግልን፣ አመቱን ሙሉ እንደ ዛሬ የዋዜማው ቀን በፌሽታ እና በተስፋ እንዲያከርመን እመኛለሁ፡፡
የከፋውን ጊዜ ታሪክ አድርጎ የተሻለውን ከፊታችን እንዲያደርግልን ፈጣሪን እማፀናለሁ፡፡ የሰላም እና አንድ የመሆን ምኞታችንን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያሰምርልን ዘንድ የማምነውን አምላክ እለምናለሁ፡፡ መከራችንን ያለፈና ጊዜያዊ፣ ፌሽታንን የወደፊትና ዘላቂ ያደርግልን ዘንድ አጥብቄ እፀልያለሁ፡፡
መልካም አዲስ አመት!

@wegoch
@wegoch
@paappii

#hiwot emishaw
🌼🌼🌼መልካም አዲስ አመት 🌼🌼🌼
አዲሱ አመት የደስታ፣የፍቅር እና የሰላም ይሁንላችሁ ።
.
.
@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
.
ሞኙ አህያ!

በአንድ ወቅት፤ ጨው እየሸጠ የሚኖር ሰው ነበር። በየቀኑ የጨው ከረጢት ወደ ገበያ የሚያወጣ አህያ ነበረው። ወደ ገበያ በሚወስደው መንገድ ላይ አንድ ትንሽ ወንዝ ማቋረጥ ይኖርባቸዋል። አንድ ቀን አህያው በድንገት ውሃ ውስጥ ወድቆ የጨው ከረጢቱ በውሃ ተነከረ። ከረጢቱ ውስጥ ያለው አብዛኛው ጨው ስለ ማሟ ለመሸከም ቀላል ሆነ። ሰውየው በተፈጠረው ነገር ቅር ቢሰኝም ወደ ገበያ ለመሄድ ቆርጧል። ከረጢቱ ክብደት ስላልነበረው አህያው ላይ ሲያስቀምጥው ከባድ ባለመሆኑ አህያው ተደነቀ። በዚህ ክስተት በጣም በመደሰት፤ አህያው በየቀኑ ተመሳሳይ ማታለያ ለመጫወት ወሰነ። ወንዙ ላይ ሲደርሱ፤ አህያው በመውደቅ ከረጢቱን ውሃ ውስጥ እንዲወድቅ ያደርጋል። ከዚያ አህያው ቀለል ያለ ከረጢት ተሸክሞ በደስታ ወደ ገበያው ይሄዳል። ሰውየው፤ አህያው እየሸወደው መሆኑን ስለተረዳ አንድ ትምህርት ለማስተማር ወሰነ። በሚቀጥለው ቀን፤ አህያውን በጨው ፋንታ በጥጥ በተሞላ ከረጢት ጫነበት። አህያውም በተመሳሳይ ለመሸወድ እና ለመጫወት ቢፈልግም እርጥበታማው ጥጥ ግን ለመሸከም በጣም ከባድ ነበር። ከዛም አህያው ወደ ገበያው ለመግባት ታገለ። አህያው ትምህርቱን ስለወሰደ፤ እንደገና ለመሸወድ አልሞከረም።

የታሪኩ ፍሬ ነገር!

ቀላል (አቋራጭ) መንገድ ለመያዝ አትሞክሩ። አቋራጭ ለተወሰነ ጊዜ ደስታን ቢያስገኝም ግን መጨረሻም እናንተ መሆን ወደ ምትፈልጉበት ቦታ አይወስዳችሁም። ቀላል አማራጭ ሲገጥማችሁ፤ አመስጋኝ በመሆን ጊዜውን በሚገባ ተጠቀሙበት። ያለአግባብ ለመጠቀም ስትሞኩሩ ግን ተመልሶ እናንተኑ ያጠቃችኋል።
@wegoch
@wegoch
@wegoch
Forwarded from Sunset Hiking (yise)
Explore the incredible world we live in with SUNSET HIKING TEAM!

Do you love hiking + traveling + adventures and new experiences?......You are at the right place. This is the adventurers family!!!
Welcome

"Join our telegram channel" @sunsethiking
"Join the discussion group" @sunsethike
"Our photographs are shared on" @sunsetphotography
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (#ነፂ-ከዕለታት)
ሁለገቧ አርቲስት ሳያት ደምሴ በአዲሱ አመት በአዲስ ስራ ብቅ እንደምትል ነግራናለች...........ምን ይዛ ትመጣ ይሆን?

"በሴቶች ላይ እየሆነ ያለውን አግባብ ያልሆነ ተፅዕኖ ለማቆም ሴቶችን ብቻ ማስተማር ተገቢ አይደለም ችግራቸውን ለራሳቸው መልሼ መናገር አልፈልግምና........" ታድያ ሳያት የተሻለ መንገድ ነው የምትለው ምን ይሆን?



#እነዚህን እና መሰል ጥያቄዎችን ይዘን በአውደብሩሃን ገፃችን ከሳያት ጋር ያደረግነውን ቆይታ በቅንድል ዲጅታል መፅሔት ወደ እናንተ ልናደርስ አንድ ቀን ብቻ ቀረው፡፡



ቅን ፣ ምክኒያታዊ ፣ሀገር ወዳድ ትውልድ ለኢትዮጵያ

Kendel on Telegram
http://www.tg-me.com/KendelM
Kendel On FaceBook
http://m.facebook.com/kdigitalmagazine
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (Ermiyas Dejene)
ቅንድል መፅሔት ቅፅ-2 ቁጥር-5_edited87.pdf
5.8 MB
#ቅንድል_ዲጂታል_መፅሔት

ቅፅ2- ቁጥር-5

ልዩ የበዓል ዕትም

በርካታ አስገራሚ ፣ አስተማሪ እና አዝናኝ ፅሁፎች የተካተቱበ

ያንብቡት እና ብዙ ያትርፉበት📝

ቅንነት ድል ያደርጋል!

Kendel on Telegram
http://www.tg-me.com/KendelM
Kendel On FaceBook
http://m.facebook.com/kdigitalmagazine
Me trying to flirt
*sends a picture that is completely black*
እኔ ፡ A pic of me at the moment. እጄ ምን እያደረገ እንደሆነ ገምት
እሱ ፡ ምንም አይታየኝም፣ ጥቁር ብቻ ነው
እኔ ፡ እኮ ገምት ነው ያልኩት፣ use your imagination
እሱ፡
እኔ፡ ሶኬቱን እየፈለገ
እሱ፡
እኔ፡ መብራቱን ለማብራት
እሱ፡
እኔ፡ እንዴ! can I be more obvious?
እሱ፡ ምንም የምትይው አልገባኝም! መብራት ጠፋባችሁ?
አዪዪዪዪ 😂

@wegoch
@wegoch
@wegoch

#hewan huletshi
#ወግ_ብቻ
.
............“አንድ ሰው ሕጻን ሆኖ ሲወለድ እጁን (መዳፉን) ጨብጦ ነው፤ አንድ ሰው ሸምግሎ ሲሞት ደግሞ እጁን (መዳፉን) ዘርግቶ ነው” ይላል ካልታወቀ ምንጭ የተቀዳ አባባል፡፡

ለአንድ ሕጻን አንድን ነገር በእጁ አስይዛችሁት ካወቃችሁ ልጁ የያዘውን ነገር በቀላሉ እንደማይለቅ ትደርሱበታላችሁ፡፡ አንድ ሕጻን ልጅ እጁን ጨብጦ መወለዱ ሁሉን ለመያዝ፣ ሁሉን በእጁ ለማስገባትና ሁሉን ነገር በቁጥጥሩ ስር ለማድረግ የመሞከሩ ምልክት ነው፡፡

አንድ ሰው ሸምግሎ ሲሞት እጁን ዘርግቶ መሞቱ ደግሞ ሁሉን አይቶት፣ ሞክሮት፣ ጨብጦና “የእኔ ነው” ብሎ በመጨረሻ ምንም ነገር የእርሱ እንዳልሆነና አንድ ቀን ሁሉም ነገር ከእርሱ ቁጥጥር ውጪ እንደሚሆን የመገንዘቡ ምልክት ነው፡፡

እውነታው ይህ ነው፡- ተወልደን በልጅነት ባሳለፍንበት ወቅትና ሸምግለን ከዚህ አለም ወደመሰናበት በምንደርስበት ወቅት መካከል ባሉን እንደ ጥላ በሚያልፉት አመታቶቻችን መያዝና መቆጣጠር በምንችለውና በማንችለው መካከል መለየት አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ነገ ሁሉንም ነገር ትተነው እንደምናልፍ በመገንዘብ ሁሉን ነገር የእኛ ለማድረግ ጦር ስንማዘዝ ዘመናችንን እንዳናባክነው እናስተውል፡፡

እጅህ በገባው ነገር ደስተኛ ሁን፣ ለመልካም ነገር ተጠቀምበት፡፡ እጅህ ለማስገባት ያልቻልከውን ነገር ለማስገባት ሞክር፣ ነገር ግን ሁሉን ካልያዝኩ በማለት ስትሟገት በጦርነትና በፍርድ ቤት ዘመንህን አታስበላ፡፡ የአለምን ምድር ሁሉ ጨብጠን የእኛ እናደርጋለን ብለው የነበሩ ምእራባውያን ቅኝ ገዢዎች የጨበጡትን ሁሉ ቀስ በቀስ እየለቀቁ እንደሄዱ አትዘንጋ፡፡ እንዲያውም የእነሱንም ቀስ በቀስ የሚያስለቅቃቸው ሁኔታ እየተጋረጠባቸው ነው፡፡

ለጊዜው ነው እንጂ ምንም ነገር በቋሚነት የአንተ አይደለም፡፡ የእኔ ነው ብለህ የምታስበው ሁሉ ለጊዜው በአደራ የተሰጠህ ነው፡፡ ዛሬ አንተ የምትኖርበትን ቤትና መሬት ትናንት የእኔ ነው ብሎ የሚኖርበት ሰው ነበር፡፡ ዛሬ ግን የአንተ ነው፡፡ ነገ ደግሞ ይህንን ስፍራ ሌላው ተረኛው ጨባጭ ይረከበዋል፡፡ ቁም ነገሩ በዘመንህ የጨበጥከውን ነገር የመልቀቂያህ ጊዜ እስከሚመጣ ድረስ ለመልካም ዓላማ የመጠቀምህ ጉዳይ መሆኑን ላስታውስህ፡፡

ዶ/ር እዮብ ማሞ
@wegoch
@wegoch
@wegoch
.......,,......,,.......,,......,,.......,,...
“… ብገልህ ደስ ይለኛል !... እንንንንቅ አድርጌ እንደዚህ … “ አንገቴን አንቃ … አይኖቿ ደፍርሰዋል … አፏ መጠጥ መጠጥ ይሸታል … አልታገልኳትም ! … ስለማውቃት እንኳን እጄን ላነሳባት ያነቀችውን አንገቴን ላስለቅቃት አልሞከርኩም …
“በ…ል ታገለኛ ! አስለቅቀኝና ምታኝ!..” … የያዘችው የዋይን ጠርሙስ ስባሪ ያሳቅቃል … ራሷን እንዳትጎዳ ነው ፍርሃቴ …
ገና ከመግባቴ ነው በጩኸት የተቀበለችለኝ …ስራ አምሽቼ ነው የገባሁት… አስቀድሜ ገዝቼ ያመጣሁትን ዋይን መንጭቃ ተቀብላኝ ወደጭንቅላቴ አስተካክላ ወረወረችው … ነጩን ግድግዳ ስስ ቀይ ቀለም አለበሰው … ስብርባሪው መሬት ተበተነ … ፀጉሯ ተበታትኗል … ያደረገችው የሌሊት ፒጃማ ለአስፈሪነቷ ተጨማሪ ሆኗታል … ተንደርድራ ሄዳ የጠርሙሱ ግማሽ አልተሰበረ ኖሮ አነሳችው … ወደኔ መንገድ ጀመረች …
“እገድልሃለው!... “ ወደኋላ ሸሸሁ …
“ብጥስጥስ ነው የማደርግህ …!” ስባሪውን አስቀድማ… ሶፋውን ከነሲሊፐር ጫማዋ ረግጣ ከበላዬ ቆመች … የሶፋው ጠርዝ የሌሊት ፒጃማዋን ይዞ በከፊል ተራቆተች
“ጭንቅላትህን ከአንገትህ ለያይቼ ደምህን….” መሸሻዬን ጥግ ጨረስኩ … ትልቁ ሶፋ ላይ ተንጋለልኩ … የጠርሙስ ስባሪ የያዘው እጇ ወደኔ ተሰነዘረ …ተረጋግቼ ክንዷን ያዝኩና ብዙም ባላሰበችው ሁኔታ በቅልጥፍና ስባሪውን አስጣልኳት … ጥንካሬዋ እኔ የጥቁር ቀበቶ ባለቤቱን እንኳ በቀላሉ የምቋቋመው አይደለም !
በምድር የቀረችኝ ልቤ ላይ ቦታ ያላት ብቸኛ ሴት ናት … ማንም በሌላት እንቁ ሴት ነፍስ ላይ ብቸኛው ንጉስ ነኝ ! … እናት አባት እህት ወንድም ዘመድ አላውቅም … ጭልም ካልኩበት ፀሃይ ሆና የመጣችልኝ እቺው ውዷ ሚስቴ ናት ! … እሷ ፀሃይ ከሆነችኝ ድፍን አስር አመት …
በተገናኘኝ በሁለተኛ አመታችን ሌላ ዘመድ እንዳለኝ ሌላ ስሜን አስከትላ የምትጠራ ነፍስ ሆዷ ውስጥ እንዳለች ስታበስረኝ አልቅሼ በማላውቀው ሁኔታ አለቀስኩ !.... ለህይወት ጉጉ ሆንኩ … ስልችት ያለኝ ህይወት ከእንደገና ታድሶ ብርሃን ሆኖ ያጓጓኝ ጀመር …
ልጄን እቅፌ ላይ ሳያት እግዜር በፍጥረቱ ምን ያህል ተደንቆ እንደነበረ በስሱ ገባኝ!... እግዜርን ሆንኩት … ልጄን ቁልቁል እናቷ ደረት ላይ እያየኋት ብዙ አሰብኩ …ብዙዙዙዙዙዙዙዙዙዙዙ!
በዳዴ ስትሄድ… “አባዬ!” ስትለኝ … በትናንሽ ከንፈሮቿ ስትስመኝ … የአንገቷ ጠረን … እኔና እናቷ መሃል ስትሆን … ትናንሽ እግሮቿን በስስት ስስማቸው … ከፍ ብላልኝ እሽኮኮ አድርጌ ትምህርት ቤት ስወስዳት … ሳደምጣት … እጄ ላይ እንቅልፍ ሲወስዳት ( አይኖቿ ተከድነው ስታምር ደግሞ ) … ደስታዋን ሀዘኗን (ውይ ሀዘንስ አይይብኝ .. የውዴንም የልጄንም ሀዘን እኔ ልዘን !) በእቅፏ ስትነግረኝ … ስታጋራኝ …. በጣም ብዙ አሰብኩ !

ብዙዙዙዙ ብመኝም አልሆነም !... ምክንያቱ ግልፅ ባልሆነ ሁኔታ ውዴ እቅፍ ውስጥ እያለች በአራስነቷ ጥላን ሄደች ! … ለክርስትናዋ እንኳ አልደረሰችም … አግኝቼ አጣሁ !... ልጄ ትንሹዋ እኔ ሞተች ! … በልጃችን እልፈት ክፉኛ ባዝንም አልተቀየምኳትም …
ከዛን በኋላ ለኔ ስትል የተፅናናች ትምሰል እንጂ ሀዘኑ ከሰውነት አወጣት … የሷ ፀሃይ እየጠለቀች … አይኔ እያየ ጀምበሬ ታዘቀዝቅ በአስፈሪው ደመና ትዋጥ ጀመር… ለልጃችን ሞት ራሷን ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ አድርጋ ለራሷ ይቅርታ የማታደርግ ሆነችብኝ !...
እንዲህ እንደዛሬው የልጃችንን ልደት እየጠበቀች በፀፀት ራሷን ትቀጣለች … ሌላ ማንነት ውስጥ ሰምጣ ቀረችብኝ … ያልሞከርኩት ሃኪም ያልሞከርኩት ፀበል ያላየሁት ነገር አልነበረም !... ቢያንስ በወር አንዴ እዚህ ማንነት ውስጥ ሆና አገኛታለሁ … መቼ እንደምትቀየር ስለማላውቅ ሁሌም ከኔ አልፋ ራሷን እንዳትጎዳ ነው ፍርሃቴ ! … በዚህ ሌላኝው ማንነቷ ፍርሃት እሷም ሰው አትቀርብም … ሌላ ልጅ ለመውለድ አልደፈረችም !

የልጃችን የሙት መንፈስ እንደሚያሰቃያት ደህና ስትሆን እያነባች ደጋግማ ነግራኛለች … እያነባች ማታ ስላደረገችው ነገር ይቅርታ ትጠይቀኛለች … እያነባች ድጋሚ እንደማታደርገው ትነግረኛለች … እያነባች ቁስሌን ትጠርጋለች …
ከነእንባዋ እስማታለሁ …. ሌላ ቀን ቢደገምም … ሌላ ጊዜ እነደዛው አስፈሪ ብትሆንም ዛሬም ከነእንባዋ እስማታለሁ … ዛሬም ከነአውሬ ማንነቷ ባልቀነሰ ፍቅር አፈቅራታለሁ …
ትላንት ካደረገቸው ትዝ የሚለኝ ያ ነፍስ ነጣቂ አሳሳሟ ነው …
ትላንት ትዝ የሚለኝ ያ በሳቅ እንባ የሚያመጣ ጨዋታዋ ነው …ከዛ አሟሚ የፍቅር ቃሎቿ … ስሜ አፏ ላይ ፍስስ የሚለው… ስስቷ…. ጥፍጥናዋ ብቻ ነው … !
ትዝ የሚለኝን የመምረጠጥ መብት ለራሴ ሰጥቻለሁ !... የምወደውን ብቻ ነው የማስታውሰው !... ትውስታዬ ላይ ብርሃኗ እቺው ውዷ ሚስቴ ናት!
እና……!
ነገም ያን ዋይን ይዤ እሄድና እንደሌላው ጊዜ የሰራችውን ምግብ እየተሳሳቅን ከበላን በኋላ እንደአዲስ ቀለበት ተንበርክኬ አጠልቅላታለሁ … (እንደሁሌው ህመሟ ሲነሳ አውልቃ ብትጥለው እንኳ እስካልቀየማት ድረስ )
ነገም ገና እንደገባሁ ከንፈሯን ስሜ በሌሊት ልብሷ ታቅፌያትq መኝታ ቤታችን ወስጄ …
ነገም ብትቧጭረኝ … ብትመታኝ … ልትገለኝ ብትጥር…
ነገም… በቡጭሪያዋ የቆሰለ ገላዬን እየነካካች …በእንባዋ ብታጥበኝ … እንደሁሌው “… ስትሄድ ገድለኸኝ ሂድ! “ ብትለኝ …
ነገም…
ነገም..
ነገም…
ነ…ገም …. አሁን ከማፈቅራት በላይ አ.ፈ.ቅ.ራ.ታ.ለ.ሁ !...

የጠቆረ ልብ

@Wegoch
@Wegoch
ለቤተሰቤ ግድ የለሽ ነኝ … በድህነት ለማደጌ … ቁርሴን በልቼ ምሳ ላለመድገሜ ጥፋተኛ አድርጌአቸዋለሁ !... አዲስ ለላመልበሴ በሰቀቀን ከጓደኞቼ አንሼ ..ከነኣካቴውም ጓደኛ እንዳይኖረኝ በጭምት ለማደጌ ከነሱ ውጪ ማንም ተወቃሽ የለም !...
አዎ ከነዚህ እናትና አባት ተብዬዎቼ ውጪ ማንንም አልወቅስም !... ሆዴን ረሃብ እየሞረሞረኘኝ እናቴ ብታቅፈኝ ምኔ ነው … ሱሪዬ ተቀዶ ወሸላዬ ታይቶ ጓደኞቼ አይተው ስቀው ሲያሳቅቁኝ ሳለቅስ የአባቴ “ወንድ አይደለህ አታልቅስ !” የሚለው የቁጣ ቃል እንዴት ማፅናኛዬ ይሆናል !...
ሲርበኝ መታቀፍ አይደለም የምፈልገው … ምግብ ነው !...
ሲጠማኝ ቁልምጫ አይደለም የምፈልገው ….ውሃ ነው !
ሲያመኝ “እኔን !” መባል አይደደም የምፈልገው ….ህክምና እንጂ !...እና … ቀይ ስጋ ቢያምረኝ ውሻ የማይበላው ነጭ ቅንጥብጣቢ ገዝቶ “ይሄን ብላ ያለኝ ይሄ ነው !” ቢል ከደግነት ይቆጠርለታል አይደል !... እኔስ … ፈልጌ ነው እንዴ የመጣሁት !...
እንዲሁ በጥላቻ አንገቴን ደፍቼ ጭምድድ እንዳልኩ አደኩ!... አባት ተብዬውንም እናት ተብዬዋንም ጥልት እንዳደረኳቸው አደኩ … ሰውየውን “ደመቀ!” ሴትየዋንም በስሟ “ዘሪቱ!” እያልኩ በስማቸው ነው የምጠራቸው ….እህትና ወንድሞቼን ጠርቻቸውም አላውቅ!...
አሁን ታዋቂ ተዋናይ ሆኛለሁ ! … አድናቂዎቼ በመላው አለም የሚገኙ ለፊልም የደረሱ ሁሉ ናቸው … ዝናዬ ቆንጆ እንስቶች ገላቸው ላይ ስሜን እስኪነቀሱ ድረስ ነው … ደብቅነቴ … ከስራዬ ውጪ አንድ ጊዜም እንኳ የትኛውም ሚዲያ ላይ አለመታየቴ የበለጠ ተወዳጅና ተፈላጊ እንድሆን አድርጎኛል … አሁን አልራብም … አሁን አልታረዝም …
ከስንት የውዷ ሚስቴ ውትወታ በኋላ ቤተሰቦቼን ልጠይቅ ሀገሬ ገባሁ …
“እልልልልልልልልልልል …. እሰይ……እልልልልልልልልልልልልል….” አለች እናቴ ገና ስታየኝ … ኑሯቸው አልተቀየረም … እናቴ ፀጉሯ ነጭ ከመሆኑ በላይ ቆዳዋ ተሸብሽቦ የእርጅናና የድህነት ሜካፑ ማዲያት ቤቱን ቀልሶባታል … ቤት ተቀምጠን ልጆቼን እኔንና ሚስቴን አይታ አልጠግብ አለች … ሚስቴ ራሷን መቆጣጠር አቅቷት ከአይኗ እንባ ይወርዳል …
ስንረጋጋ …
“ደመቀስ …!?“ አልኳት … የሆነ ነገር የሰኩባት ይመስል ጭምድድ አለች …
“ማረፉን አልሰማህም !” አለችኝ ድምፁዋ ስልምልም ብላ …. “ደምዬማ አረፈ … ጨክኖ ጥሎኝ ሄደ ልጄ … ይሄ ክፉ አባትህማ ሄደ … ጨካኝ አይደል … ጀብደኛ ነውኮ ያንተ አባት ያለስንቅ ሄደ …. እህህህህህ… ደምዬ ሞተ … “ ቡና የምታፈላበት ወንበር ላይ እንደተቀመጠች ከአይኗ እንባ ይፈሳል … ጥቁር በጥቁር እንደለበሰች አሁን ገና አስተዋልኩ …. በድን ሆንኩ !.. ምን ሆኜ ነበር?! … ሚስቴ እንኳን ምክንያት አግኝታ … ድሮ በእንባዋ በስብሳለች
“ደምዬማ ሞተ ልጄ … የልጄን ፍሊም አድርጉ ከወንድሞችህ ጋ ጭቅጭቅ ነው … እዚች አልጋ ላይ ሁኖ … ታዲያ እዛች አንተ ፍሊምህ ላይ ለአባትህ “አባዬ…!” ብለህ ስትጣራ ተሸቀዳድሞ “ወዬ !” ይላል … የፍሊምህ አባት እንዳይቀድመው ነውኮ … “ወዬ ልጄ !...እኔንኮ ነው አባዬ የሚለው …” ይላል ደስስስ ብሎት …” አለሜ ልጃችን አባዬ ሲል አያምርም …!?” ይለኛል … ሁሌም ነውኮ … አይቶህ አይጠግብም … በቲቢው ባዬህ ቁጥር “ወዬ ልጄ…” እንዳለ አይኑ ላይ እንደተንከራተትክበት ሞተው … አይ ደምዬ የኔ ከርታታ….!”
ከዚህ በፊት እንደዚህ አልቅሼ አውቅ ነበር!? …
ከዚህ ቀደም እንደዚህ ራሴን ጠልቼው ነበር !?….
ፍርክስክስ አደረገችኝ …
ማታ አልጋችንን እያነጣጠፈች …
“ባርዬ …” በልጅነቴ እንደምትጠራኝ
“ኧ…!” እንደልጅነቴ መለስኩላት …. ሽቁጥቁጥ እያለች …

“መቼ ነው እናት ያለችበት ፍሊምህን የምትሰራው ?… “እማዬ !” የምትልበት ያለው …? “ … ልቤን እፍፍፍፍን አደረገኝ …ሌሊቱን በብርድልብሱ አፌን አፍኜ ሳለቅስ አደርኩ …
በጠዋት ተነሳሁና ….
“እማዬ …. “
“ኧ!” ክው ብላ ደንግጣለች
“መቼ ነው አባዬ መቃብር የምንሄደው …!”
“እልልልልልልልልልልልልልልልልልልለልልልልልልልልለልልልልለ!” ........................,,,,........................ ✍🏽የጠቆረ ልብ @Wegoch @Wegoch @Wegoch
ስሟ ጆይሲ ቪንስንት ይባላል 38 አመቷ ነበር ነዋሪነቷ የነበረው እንግሊዝ ወስጥ
ለንደን ነው:: ትኖር የነበረው አፖርትመንት ተከራይታ ሲሆን የቤቷ የኪራይ ውል በማለቁና ያለባትን የኪራይ ውዝፍ ልትከፍል ባለመቻሏ አከራይዎቿ ለፖሊስ አሳውቀው ፖሊስ ቤቷ ሲገባ ያገኘው ሶፋ ላይ ቁጭ ብላ ሲሆን እሷ የሞተችው ግን በ2003 ነበር:: ከሞተች ከሶስት አመት በጏላ በቤቷ ፈሪጅ ውስጥም የአገልግሉት ዘመናቸው በ2003 ያለቀ ምግብና መጠጦች አግኝቷል ሌላው ፖሊስ ያስደነቀው ነገር ቴሌብዥኑ በርቶ ፕሮግራም እያስተላለፍ ነበር:: ሀገሬን የምወዳት ለዚህ ነው:: ከፋም ለማም ተጣላክም አልተጣላክም ወዴት ነህ የሚል ነገረኛም እንኳን ቢሆን ደሞ ዛሬ ምን ነው ድምፁ ጠፋ የሚል ጎረቤት ሁሌም ቢሆን ይኖርሀል:: መኖርህ ነው የኖሮ መለኪያ የሰለጠነው አለም ግላዊነት ከመጣባቱ የተነሳ ሁሉም በየራሱ ይኳትናል እንጂ አጠገቡ ስላለው ጎረቤቱ አይጨነቅም:: አብረህው ስለኖርክ ብቻ መጠጋጋትን
እና ማህበራዊ ቅርርብን አይፈቅድም....
እናም የሀገሬ እናቶች ተሰብስበው ስናያቸው ቡና ከመጠጣት በዘለለ የአብሮነት ድራቸውን እየፈተሉ እንደሆነ መገንዘብ ተገቢ ነው::

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Danny magna
ከወንጌላዊነት ወደ "ዶክተርነት" ያደረኩት ሽግግር!
(አሌክስ አብርሃም)
ሒሳብ አስተማሪያችን ‹‹ስታድጉ ምን መሆን ትፈልጋላችሁ ›› ብሎ አንድ ክፍል
ማቲ ሲጠይቅ ከእኔ በስተቀር ሁሉም ‹‹ዶክተር›› እና ‹‹ፓይለት›› አሉ ! እኔ ግን
‹‹ወንጌላዊ›› አልኩ !አስተማሪያችንን ጨምሮ ሁሉም ተገረሙ ! እየቀለድኩ
አይደለም …ይሄ አራተኛ ክፍል አብረውኝ የተማሩ ልጆች ሁሉ የሚመሰክሩት ሃቅ
ነው ! በወቅቱ ወንጌላዊነት ይዘፈንበትም ይለቀስበትም አላውቅም ግን አንድ
ጴንጤ ጓደኛ ነበረኝ ...አባቱ ወንጌላዊ የነበሩ ! በመካነ ኢየሱስ ውስጥ የሚገኝ
የሆነ ‹ልማትና ተራድኦ› ድርጅት ይመስለኛል ሃላፊ ነበሩ ! ይሄ ሰውየ …
1ኛ. ነጭ ቲዮታ ላንድ ክሩዘር የሚነዱ
2ኛ. ሽክ ያሉ ሰውየ !
3ኛ. በትርፍ ጊዚያቸው በሚያምር ቪላቸው በረንዳ ላይ ጊታር እየተጫዎቱ
በሚያምር ድምፅ የሚዘምሩ …ሚስታቸው (የጓደኛየ እናት ፊት ለፊታቸው ቁጭ
ብለው አብረዋቸው ይዘምራሉ) መጀመሪያ አካባቢ ሳያቸው ከብዙሃኑ ኢትዮጵያዊ
ባለትዳር ስለተለዩብኝ …የሆነ የህንድ ፊልም ነገር ነበር የመሰለኝ ! ይሄ ሰውየ
ተፅዕኖ አሳድረውብኝ ይሆናል! ፓስተር ፣ ነብይ ወላ ዘማሪ መሆን አልፈልግም
ነበር …..ወንጌላዊ! ወንጌላዊ ሁሉ መኪና የሚነዳ፣ የሚዘንጥና ሚስቱ ጋር ቁጭ
ብሎ በጊታር የሚዘምር ይመስለኝ ነበር !
በኋላ እዚህ ጓደኛየ ጋር ቸርች ሔድኩ …የዛን ቀን ከደቡብ የመጡ እና ለ33
ዓመት ወንጌል ሲሰብኩ የኖሩ ወንጌላዊ ‹‹የእግዚአብሔር ጥበቃ ›› በሚል ርዕስ
እያስተማሩ ነበር ! እዚህ ግባ የማይባል ልብስ የለበሱ ጎስቋላ ፊት ያላቸው
ሽማግሌ ነበሩ! ሰውየው በየገጠሩ የተከሉት ቸርች ብዛት ዛሬ ላይ አንዳንድ
አገልጋዮች ከዶ/ር ዓብይ ኋላ እየተከተሉ ከተከሉት ችግኝ በቁጥር ይበልጣል !
ደስ በሚል የደቡብ አክሰንት ነው የሚናገሩት እንዲህ አሉ ‹‹…ጓደኛየና እኔ
በልጅነታችን እኔም እሱም ሌቦች ፣መልከመልካም እህቶችን የምናስቸግር ፣
ዱርየዎች ነበርን …
የዛሬ 35 ዓመት አካባቢ እኔ ጌታን ስቀበል እሱ ያው በሌብነት በአመፅ ቀጠለ …
የጌታ ጥበቃና ምህረት በዛልኝ …በደርግ ጊዜ ወንጌል ሰበክ ተብየ ስታሰር ይሄ
ጓደኛየም መጋዘን ሰብሮ በቆሎ ሲሰርቅ ተይዞ ታሰረ …እንደገና እስር ቤት
ተገናኘን …ለዚህ ወዳጀ ቀን ከሌት በእንባ ነበር የምፀልየው ! ይገርማችኋል እሱ
በነፃ ሲለቀቅ እኔ ክፉኛ ለወራት ተገረፍኩ …እስካሁን ይሄ ግራ አይኔ በግርፋቱ
ተጎድቶ እስካሁን በደንብ አያይም ….ቀኝ እግሬም ያዝ ያደርገኛል …ግራፋቱን
ያባሰው ለገራፊየ ‹‹ኢየሱስ ይወድሃል… ››በማለቴ ነበር ! ጌታ ይባረክ! (ፈገግ
ብለው) …
ወገኖቸ ጥበቃው በዝቶልኝ ከዛ ግርፋት ተረፍኩ ! ቆይቶ የእጮኛየ ቤተሰቦች
አንተ ገንዘብ የለህም …አሁን ደግሞ ሰርተህ እንኳን ልጃችንን እንዳታኖር ጤናም
የለህም ብለው ለሌላ ሰው ዳሯት! እስካሁን መልካም እህቴ ናት …ባለቤቷም
መልካም ሰው ነው ! ጌታ ይባረክ …እኔ ከዛ በኋላ 15 ዓመታት ቆይቸ ነው
ያገባሁት ! ይሄ ጓደኛየ አንዲት ከውጭ አገር የመጣች ሴት አግብቶ አራት ልጆች
ወለደ …እኔ በጌታ ብዙ ሽዎችን ወለድኩ የስጋ ልጅ የለኝም ጌታ ይባረክ (ፈገግ
አሉ) ይሄ ጓደኛየ ዛሬ አዲስ አበባ ትልቅ ቤት ሰርቶ ትልቅ ድርጅት ከፍቶ አንዳንዴ
ራቅ ወዳለ ቦታ ለወንጌል ስሄድ ሁሉ መኪና ከነሹፌሩ ያውሰኛል … ! ዛሬም
አጥብቄ የማለቅሰው ለእኔ የበዛው የጌታ ጥበቃና ምህረት ለሱም እንዲበዛለት
ነው !
እኔም የእግዚአብሔርን ቤት መስሪያ በየመንደሩና በየአብያተ ክርስቲያናቱ
እየዞርኩ እለምናለሁ …ለወንጌል ገጠር ስዞር የሞላ ወንዝ ወስዶኝ ሌላ መንደር
ጥሎኛል ….እዛ ያሉ አርሶ አደሮች ሙቷል ብለው ሲያወጡኝ የሞትኩ እኔ
የህይዎት ወንጌል ሰበኳቸው ! ከበቅሎ ወድቄ ክንዴ ተሰብሮ ወጌሻ ጋር ወሰዱኝ
ያን ወጌሻ ስለጌታ ነገርኩት ዛሬ እዛ አካባቢ የተተከለች ቸርች ፓስተር ሁኗል !
ሚስቴ ሰው ቤት የቤት ስራ ትሰራ ነበር …ዛሬ ወደጌታ ሂዳለች (ሙታለች) …ጌታ
ስሙ ይባረክ! ይሄን የምነግራችሁ ወዳጀን ለማማት አልያም ለጌታ እንዲህ
አደረኩ ለማለት አይደለም …ማንም ለጌታ ምንም አያደርግም ! እግዚአብሔር
እኔን የጠበቀኝ በዚህ ሁሉ መከራ ተማርሬ ከቤቱ እንዳርቅ ፀጋን በመስጠት ነው !
የእግዚአብሔር ጥበቃ ከመከራ እና ከስቃይ ማዳን ብቻ አይደለም… በመከራ
ውስጥ ፀንተን እንድንኖር ፀጋውን በማብዛትም ጭምር እንጅ ! ተደሰትንም
ከፋንም ይሄ ዓለም እንደሆነ ያልፋል !
ከቸርች ስንወጣ ጓደኛየን ‹‹የአባትህ ኢየሱስና የዚህ ሰውየ ኢየሱስ አንድ አይነት
ነው ወይ? ››ብየ ጠየኩ …የእውነት ወንጌላዊነት መኪና መንዳት ብቻ ሳይሆን
እንደአህያ እየተወገረ ወደእስር የመነዳት እጣም እንዳለበት ገባኝ …ወንጌላዊነት
ወደቸርች ሰዎችን መውሰድ ብቻ ሳይሆን ራስንም በጎርፍ እስከማስወሰድ
የሚደርስ ዋጋ እንዳለበት ገባኝ …ወንጌላዊነት በተመቸው ስጋ ውስጥ የምትኖር
ጎስቋላ ነፍስ ላላቸው ሰዎች እንደማትሆን ገባኝ ! ከምንም በላይ እንደነዛ አይነት
ሰዎች እስከሞት በከፈሉት ዋጋ ላይ አሁን የምናያቸው መሬት አይንካን የሚሉ
የዩቲዩብ እና የስክሪን ላይ አለሌዎች መፈጠራቸው ያሳዝናል !
የሆነ ሁኖ ከዛች ቀን በኋላ አስተማሪዎቻችን ምን መሆን ትፈልጋላችሁ ሲሉ
‹‹ዶክተር›› የሚል ድምፅ የኔ ሆነ! መኪናውና ጊታሩ አብራ የምትዘምር ሚስትና
ሽክ ያለ አለባበስ ...ዝና ከሆነ ፍላጎቴ በጌታ ስም ምን አስታከከኝ …ዶክተርም
፣ግንበኛም ሹፌርም ዛፍ ቆራጭም ዘፋኝም አርቲስትም ሁኘ ማግኘት
የምችላቸው ነገሮች ናቸው ! ከአስመሳይና ማይክ ይዞ መድረክ ላይ
መንጠላጠል ከሚወድ ‹‹ ወንጌል ሰባኪ›› ጥሩ የቤት ሰራተኛ በፀባይዋ ወንጌል
ትሰብካለች ! ያችኛዋን መንገድ ለተጠሩት ተውኳት !

@wegoch
@wegoch
@paappii
2024/09/24 14:35:57
Back to Top
HTML Embed Code: