Telegram Web Link
እጅሽን ዘርግተሽ ባማረ ፈገግታ
እያልሽ ስጠሪኝ ና የኔ ትዝታ
ኡኡኡ ሰቀቄኔ ሆንሽብኝ ትዝታ
አይጠፋም ዘወትር ቁመናሽ ከፊቴ
ወዴት ነው ያለሽው በዛብኝ ናፍቆቴ
እንደምነሽ ልበል ባለሽበት ቦታ
ከልቤ ከትመሻል አልረሳሽም ላፍታ
ምኒሊክ ወስናቸውን እያጫወትኩላችሁ ነው አዎ ሁሉን ከትውስታዬ አጥቼ እሷን ብቻ ሳስብ ኖሬያለሁ አሁን ደሞ ወደ ጠራቺኝ ቦታ ልሄድ ነው ቶ ሎና ብላኛለች ልፍጠንባት ልዘግይባት ባላውቅም
እግዚአብሔርን እንዴት አምጣልኝ ብላ ብትለምነው እንዲ ቶሎ መልስ የሰጣት
ቶ መስቀሌን በቀኝ እጄ እፈታ ጀምሬያለሁ ምንም ክፉ ትዝታዬን ይሼ ወደ እሷ መመለስ አልፈልግም እዛ በመላእክቶች ታግሼ ፍለጋዬን ቶሎ እጀምራለሁ
ና ስላለቺኝ ከመግቢያው በር ላይ ቁጭ ብላ እንደምጠብቀኝ አምናለሁ
ለሀጢያቴ ወደ ሲኦል ባመራ እንኳ ከሷ ጋ ከሆነ ሁሉም ነገር እሷ ካለች ገነቴ ይሆናል
እሷ ስትሰናበተኝ በደም በተለወሰው እጇ መስቀሌን ቀብታዋለች እኔም ስነሳ መስቀሌን በደም ከተጨማለው ገፄ ላይ ጥዬዋለሁ
እሷን ስሰናበት የሰማሁት ነጎድጓድ አሁንም እኔን ሊሸኝ ነው መሰል ያንባርቅ ጀምሯል ፈራሁ ትለኝ የነበረው ሰአት እኔንም ያስፈራኝ ጀመር
ነፍሷን አርጥቦ የወሰደው ዝናብ የኔንም ነፍስ አርጥቦ ሊያበሰብስ ነው መሰል መዝነቡ ጀምሯል የምድሩን በደሌና ሀዘኔን ዝናቡ ሊያጥብልኝ ነው መሰል ዝናቡም ቀጥሏል
ነፍሴ በምወደው ዝናብ ታጅባ ልታመራልኝ ነው
ነጎድጓዱም ከሰማዩ ድንበር ቆሞ እንኳን ደህና መጣህ ሊለኘ ነጎድጓዱም ብርቅታውን ያጮኸው ጀምሯል
ልቤም ቆም መታ ቆም መታ ትላለች አይኔም ከጭለማው ገብቶ ብርሀኑን አቷል አፍንጫዬም ከጨለመው አለም ገባ መሰል በፊት ማውቀው ቃና አልሸትህ ብሎኛል ሁሉም ልዩ ሆኖብኛል
ቀኝ እጄን አፈፍ አደረገኝ ብዕሬም ወደቀ
ቃሌን ልስጣችሁ በቃ
ቶሎ ኑ እሺ

ተፈፀመ
✍️ብላቴናው

@wegoch
@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
......ሳያስቡት፣ በድንገት ገደል ውስጥ የወደቁት ሁለት እንቁራሪቶች ከገደሉ
ለመውጣት መዝለል የጀመሩት ወዲያው ነበር፡፡ ግና….ምን ቢዘሉ ምን ቢፈርጡ
የገደሉ አፋፍ የማይደፈር ሆነ፡፡

ሁለቱ እንቁራሪቶች ባለ በሌለ ኃይላቸው ወደላይ መወንጨፉን ተያያዙት፡፡
እዚህ ገደል ውስጥ መቆየት ማለት ሞት መሆኑን ደመነፍሳቸው ይነግራቸዋል፡፡
ስለዚህም…መቸም መዝለል ያባት ነውና እንጥፍጣፊ ጉልበታቸውን አሟጥጠው
ህይወታቸውን ለማዳን ሽቅብ ይዘሉ ጀመር፡፡
የገደሉ አፋፍ ግን የማይደፈር ሆነ፡፡ እነሱም ግን የሚበገሩ አልሆኑም፡፡
መዝለል መፍረጡን፣ በዕልህ ሽቅብ እንጣጥ ማለቱን ቀጥለውበታል፡፡ በዚህ
መሃል የሁለቱን እንቁራሪቶች የመዝለል የመፍረጥ የእልህ ሲቃ የሰሙ ሌሎች
በአቅራቢያ ያሉ እንቁራሪቶች ወደገደሉ አፋፍ ቀርበው ቢያስተውሉ የሁለት
ምስኪን ብጤዎቻቸውን የሞት ሽረት ትግል ተመለከቱ፡፡ እልህ አስጨራሽ የሞት ሽረት ትግል ! የነዚህ ምስኪኖች ጥረት ከንቱ ሆኖ የታያቸው አሁን የመጡት እንቁራሪቶች ብዙም ሳይቆዩ ቅስም ሰባሪ አስተያየታቸውን መሰንዘር ጀመሩ፡፡

“አይ አትልፉ፣ መቼም ቢሆን ከዚህ ገደል ውስጥ አትወጡም” ሲሉ ጮሁ የገደሉን አፋፍ ሞልተው ቁልቁል የሚመለከቱት እንቁራሪቶች፡፡ ሁለቱ ምስኪኖች ግን
ለዚህ ቅስም ሰባሪ አስተያየት ጆሮም ሳይሰጡ የሽቅብ ዝላያቸውን ተያያዙት፡፡
ግ ና ብ ዙ ም ሳ ይ ቆ ይ ከ ሁ ለቱ እንቁራሪቶች አንደኛው የመዳን ተ ስ ፋ ው እየተሟጠጠ አቅም ይከዳው ጀመር፡፡ ከገደሉ አፋፍ ያሉ ብጤዎቹ የአትችለውም ሀሳብ ወኔውን ሰለበው፡፡ አቅም ከዳው፡፡ በተስፋ መቁረጥ እንደነገሩ አንዴ ዘሎ ተመልሶ በፈረጠበት በዚያው አሸለበ፡፡
ይኼኛው እንቁራሪት ግን የዋዛ አይደለም፡፡ የጓደኛው እንዲህ እንደቀልድ
በወደቀበት ማሸለብ ቢደንቀውም እሱ ግን መዝለሉን አላቋረጠም፡፡ ያለ የሌለ ኃይሉን አጠራቅሞ የሞት ሞቱን ሽቅብ መወንጨፉን ቀጠለ፡፡ እልህ አስጨራሽ ነበር፡፡ በስተመጨረሻ ግን ሆነ ተሳካለት፡፡ ኃይሉን አሰባስቦ አንዴ ሽቅብ ተወንጭፎ የገደሉ ከንፈር ላይ ጉብ አለ፡፡ ከገደሉ ወጣ፡፡ የ“አትችለውም፣ አትልፋ” ቅስም ሰባሪ ጩኸታቸውን ሲያዥጎደጉዱ የነበሩት ገደሉ አፋፍ የተሰበሰቡት ብጤዎቹ በእንቁራሪቱ ድል እጅጉን ተደንቀዋል፡፡ ምን ያለው ጀግና ነው በሚል አተያይ እያስተዋሉት በመኃላቸው አቋርጦ አለፈ፡፡ ግን… ከመሀከላቸው አንዱም ቢሆን ፈጽሞ ያልገመተው ነገር የዚህን እንቁራሪት መስማት ያለ መቻል ነበር፡፡ አዎን…ባለድሉ እንቁራሪት መስማት አይችልም ነበር፡፡ እናም፣ ለእሱ፣ የዛ ሁሉ እንቁራሪት የገደል አፋፍ ጩኸት አንዱም ጆሮው አልደረሰም፡፡ ይልቁንም፣ ከሁኔታቸው የሚያበረታቱ ብጤዎቹ ሆነው ነበር የታዩት፡፡ ስለዚህም እንቁራሪቱ አጀብ፣ በዚህ ጀግና እንቁራሪት ወኔ እንደተደመመ መስማት የተሳነውም ጀግናው እንቁራሪትም ገደሉ አፋፍ ላይ ሆነው ባይሰማቸውም፣ አበረታትተውኛል ባላቸው እንቁራሪቶች መሃል በልቡ እያመሰገናቸው በድካም እንደዛለ ጉዞውን ቀጠለ፡፡
@wegoch
@wegoch
@wegoch
የግል ስሜትና ብሄራዊ ምልክት
(በእውቀቱ ስዩም)
.
ባገራችን ህዝብ ከገዥ ጋር ተማክሮ የመረጠው ብሄራዊ ምልክት ኖሮ አያውቅም ፤ ያገር ገዥዎች የሆነ የስልጣን ምልክት ይመርጣሉ፤ ያ ምልክት በውድም ሆነ በግድ ብሄራዊ ምልክት ሆኖ ይቀራል ፤ገዥው አምራቹን ህዝብ( ገበሬውን፤አንጣሪውንና ነጋዴውን) አማክሮ የመረጠው ምልክት መኖሩን የሚያስረዳ ታሪክ ካለ አቅርብልኝ! የእድሜ ልክ ተማሪነኝና ሀሳቤን ለመቀየር አላቅማም!
አንበሳ የአራዊት ንጉስ ነው ተብሎ ይታሰብበት በነበረበት ዘመን ነገስታት አምሳላቸው አድርገው መርጠውታል፤ አንድም፤ የክርስቶስ ምልክት ስለሆነ የክርስትያን ነገስታት ምልክት ሆኖ ቆይቷል
ይሁን እንጂ ሁሉም ነገስታት ተመሳሳይ ልማድ አይከተሉም ነበር ፤ለምሳሌ ዳግማዊ ቴዎድሮስ አንበሳ ማህተም የነበረው ሲሆን ተተኪው አጤ ተክለጊዮርጊስ ነብርን በምልክትነት መርጧል:: ንግስተ ነገስታት ዘውዲቱ ርግብን (የኖህ ርግብ) የማህተሟ ምልክት አድጋለች ፤
ታሪክን ትንሽ ብንበረብር በቀጥታም ሆነ በእጅ አዙር ከአዋፋት ጋር የተቆራኙ ጌቶች ማግኘታችን አይቀርም፤ የካፋ ነገስታት እንደ ጥንታዊ ግብፃዉያን በላባ ያጌጠ ዘውድ ነበራቸው ፤ላባው ከየትኛዋ ወፍ አይነት እንደተነቀለ አላወቅሁም፤ ንጉስ ምኒልክ የሀረሩን ኢሚር አብዱላሂን በጦርነት አሸንፎ ከያዛቸው ምርኮዎች መካከል ለማዳ ውሻና ለማዳ ወፍ ይገኙበታል፤
“የምኒልክ ነገር
ይመስለኛል ተረት
አሞራው በቀፎ
ውሻው በሰንሰለት” ብላ የዘፈነችው ገንቦኛ የወፉን አይነት ለይታ አልነገረችንም፤ ግን የተሸናፊውን ያክል አሸናፊው የማረከው ብርቅ ወፍ ቢሆን ነው!
የጠቅላይ ምኒስትር አብይ አህመድ ጣዖስ የዘመኑን መንፈስ የሚያስረሳ ክርክር ቀስቅሳለች ፤ አንዳንዱ በሚያነሳው ክርክር ላይ አንዳች ፍሬ አይጠፋውም ፤ ስራ ከምፈታ ልጄን ላፋታ ብሎ የተሰማራም ሞልቱዋል ፤ ስለ ጣኦስም ሆነ ስለ አንበሳ ትርጉዋሜ በሰፊው እመለስበታለሁ ፤
አይበልብኝና ስልጣን ላይ ብወጣ የአንበሳንም ሆነ የጣኦስን ሀውልት አላፈርስም፤ በነበረው ላይ የራሴን ብሄራዊ ምልክት እመርጣለሁ ፤ ከበሬ ሌላ ማንን ልመርጥ እችላለሁ? የሚወዱኝ ለምልክቱ ጥሩ ጥሩ ትርጉም እየሰጡ ይደግፉልኛል፤ በውቄ ለመጀመርያ ጊዜ አርሶ አደሩን የሚያከብር ብሄራዊ ምልክት አስተዋወቀ እያሉ ያወድሱኛል፤ የሚጠሉኝስ? “በሬ” የሚለው ቃል ባንድ አዳር ስድብ አድርገውት ያድራሉ፤ ችግሩ ከምልክቱ አይደለም፤ ለምልክቱ ባለቤት ካለን አስተያየት ነው፤ ስሜት ከአእምሮ በላይ እንደሚበረታ ለማስረዳት ሾፐናወርንና ብጤዎችን መተንተን አይጠበቅብኝም ! እነዚህን ያገራችን ተረቶች ብቻ ማየት ይበቃል;
-ሰውን ሲወዱ ከነ ንፍጡ !
-ጠላት ይቀባል ጥላት !

@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
.
.......አንድ ሰው በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ እያለ
በመዓበል ተመታና መርከቡ ተሰባብሮ በባህሩውሰጥ ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፍና ጎጆ ነገር ሰርቶ ለቀናት ለብቻው እዛች ደሴት ላይ ይኖራል ,,,,,,,,ምግብ ዓሳ እያጠመደ እየተመገበ ብዙ ቆየ። አንድ ቀን ዓሳ ሊያጠምድ ወደ ባህሩ እየሄደ በመሀል እዛች ባህር ላይ ጭስ ይሸተዋል ዞር ብሎ ሲመለከት
ያቺ ጎጆው እየነደደች ነው ,,,,,,,እየሮጠ ቢመለስም ጎጆዋን ሊያድናት አልቻለም ለካ ዓሳ ለማብሰል ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ ጎጆውን አንድዷታል አለቀሰ ፈጣሪውን ወቀሰ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ለብቻዬ ጥለከኝ ከቤተሰቦቼ ነጥለኸኝ ስታበቃ በስንት ልፋት የሰራዋትን ጎጆ ታቃጥልብኛለክ ብሎ አለቀሰ አማረረ,,,,,,,, ከደቂቃዎች በኋላ አንድ ድምፅ ሰማ ወደ
ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ አየ ተደሰተ ,,,,,, የመርከቡ ሰዎችም መጥተው ጭነው ወሰዱት
ከዚያም ለመርከብ ሰዎች ጠየቃቸው !
እንዴት አገኛችሁኝ እዚህ አካባቢ እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት መጣችሁ ?
አላቸው ,,,,, መርከበኞቹም እኛም በዛኛው በኩል ዞረን እየሄድን ነበር ከዚያ በኩል ጭስ አየንና እዚህ ሰው ይኖራል ብለን መጣን አንተ አገኘን አሉት። አቤት ጌታዬ ለካ ከዚህ ከስቃይ ልታወጣኝ ፈልገህ ነው ትንሿ ጎጆዬን ያፈረስከው ወደ ትልቁ ቤቴ ልትወሰደኝ ነው ። አለ
አንዳንዴ የሆነ ነገር ስናጣ ሲበላሽብን ፈጣሪንም ሰውንም ስናማርር እንኖራለን ግን ካጣነው ነገር ከጎደለብን ነገር ጀርባ ብዙ ጥሩ ነገር ልናገኝ እንደምንችል እንዘነጋለን በችግራችን ጊዜ መጠጋት
ያለብንን አንድዬን እንረሳለን ከዚያም አልፈን የሁሉ ነገር ፈጣሪውን እንኮንነዋለን ።ያጣነውን የሰጠን እግዚአብሔርን አእምሯችን ከሚያስበው በላይ ሊሰጠን እንደሚችል ማመን አለብን። እግዚአብሔርን እንደ ቅዱሳን በእምነት መፅናትን ያድለን። አሜን
@wegoch
@wegoch
@wegoch
Forwarded from Mikiyas Liyew Mykey
''ደቦ''
የጉዞ ማስታወሻ
በ ''ሄኖክ ስዩም''
ክፍል ፩
(፷ ደራሲያን ከተሳተፉበት መፅሐፍ ዘንድ ያገኘነው ፁኹፍ ነው)

@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
Forwarded from Mykey (Mikiyas Liyew Mykey)
ሸማኔዎች ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ስራቸውን ሰርተው ከተለያዩ ቦታዎች (ከሰበታ፣ ከአስኮ፣ ከኮልፌ፣ ከአንቆርጫ፣ ከኮተቤ ወዘተ) እሁድ ሽሮሜዳ አምጥተው ይሸጣሉ!

አሁን ግን ከኮሮና ቫይረስ መከላከል ስራ ጋር በተያያዘ ተለዋጭ ቦታ ስላልተሰጣቸው ችግር ላይ ናቸው፣ እንደውም በዱላ እየተደበደቡ ይበተናሉ።

የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች አሉ፣ ብዙዎቹ በኪራይ ቤት ይኖራሉ። "ሰርተን መሸጫ ስላጣን ድምፃችንን አሰሙልን" ስላሉኝ ይህንን መረጃ አጋራሁ።

ጋዜጠኛ ኤልያስ መሠረት(AP)
ፎቶግራፍ:- ሚኪያስ ልየው(ከእነእርሱስ Project)
@Eliasmeseret
@Mykeyonthestreet
''ደቦ''
የጉዞ ማስታወሻ
በ ''ሄኖክ ስዩም''
ክፍል ፪
(፷ ደራሲያን ከተሳተፉበት መፅሐፍ ዘንድ ያገኘነው ፁኹፍ ነው)
አቅራቢ @Mykey21

@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
#የእሳት ላይ ቁጥሮች

    ክፍል - ፩

ከሰሞኑ በመላው የዜና አውታሮች በሬዲዮ ጣቢያዎች አንድ አይነት ነገር ነው ሚሰማው
ሁሉም ዜናዎች #ሻርማይክ በሚል ስም እራሱን በሚያንቀሳቅሰው ቡድን ላይ ሆኑአል ዘገባቸው
ከሬዲዮዋ የምቶጣውን ድምፅ በእሳቱን መሞቂያ ዙሪያ ያሉት 7 ሰውች እየሰሙት ነው ምንም አይነት ስሜት ከፊታቸው አይነበበም
ሬዲዮዋ ቀጠለች ....
የቅርስ ተቋሙ በስልክ ባደረሱን መረጃ በሀገራችን ውስጥ ከ12 በላይ ገዳማትና ሁለት የቅርስ ተቋማት ላይ ከፍተኛ የሆነ ዘረፋ ተፈፅሟል ጋዜጠኛው ፈጠን ብሎ
በሁሉም ገዳማትና በተሰረቁት ተቋማት ላይ #ሻርማይክ የሚል ፅሁፍ በሮዝ አበባ ላይ ታትሞ እንደተቀመጠ መረጃው ደርሶናል ፖሊስ በሰጠን መረጃ መሰረት እስካሁን ማን ይሁን በማን ምንም አይነት ፍንጭ አለመገኘቱንና በተለየ መልኩ ዘረፋው እንደተካሄደ ገልጿል
በተጠናከረ መልኩ አሳዶ ለመያዝ ቃልም ገብቶልናል
በመጽሀፍ ከተሞላው ቤት ውስጥ አንድ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠች አንድ ሬዲዮና ድምጿን ሞቅ እያረገ ወደ ጆሮ ከሚያስገባው የእሳት ማሞቂያ በቀር ሌላ ምንም ነገር የለም
የቤቱ ዝምታ አስፈሪ ሆኑአል 7 ወንበሮች ላይ 7 በፀጥታ ተውጠው የተቀመጡ ሰዎች ከሬዲዮዋ ምቶጣውን ድምፅ ከዜና አንባቢው እየመነተፉ በእሳት ነበልባሉ እያሞኩ ከጆሩአቸው ይከታሉ
እስከዛሬ ጠብቀው ያቆዩት ቅርስ ይመስል ተንከባክበው የጠበቁት ይመስል በሸረሪትና በአይጥ አር በተሞላ ጉሮኖ ውስጥ ሲኖር ለምን እንደዚ አላንገበገባለው   ቲሽ.....
የቤቱን ዝምታ ተሰበረ ወጣቱ መነፅሮቹን ወደ ላይ በጣቶቹ እየገፋ ንግግሩን ሊቀጥል ሲል
ሬዲዮዋ ቀደመችው...."
ከአበባውና ከታተመው ሻርማይክ የሚል ፅሁፍ ጀርባ ምን ይሆን ያለው ጋዜጠኛው እስከ ወዲያኛው ሄደ
ሀገር ማለት ሰው ነው
ሰው ነው ሀገር ማለት ለሬዲዮ ማስተዋወቂያ የምትውለዋ ዘፈን ትስረቀረቅ ገባች
ሀገር ሀገር   ሀገር ሰው ነው እያሉ ነው እዚ የሚጫወቱብን
 ሰዉ እንኳን ሀገር ሊሆን ምንም ስሜት በውስጡ ሳይኖር በዚች ሀገር ተብላ በተሰየመች ረቂቅ መሬት ላይ ይኖራል ወጣቱ ልጅ ቀጥሎ አሁንም አፉን ያዘ
ሬዲዮዋ ቀጠለች
ከሰሞኑ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ህዝቡ በነገሩ ስለተቆጣ በመንግስት ላይ ተቃውሞውን እያሰማ ይገኛል
በገዳማቶቻችንና በያዙት ቅርስ ላይ ሚደረገው ስርቆት ይብቃ መንግስት በቶሎ ዘራፊዎቹን ለህግ ያስረክብ
አንድ ወጣት በወኔ ከራዲዮዋ ዘራፍ ይላል
ተወልዶ እዚ እስኪደርስ ሄዶ ያልግበኘውን ቅርስ አሁን ሲዘረፍ እሪ ይላል ይሄኔ ወደ አንዱ ገዳም ይዘህ ሄደህ ታሪኩን ከምትነግረው ትንሽ ክለብ ውስጥ ከተህ አንድ መጠጥ ብጋብዘው ለሱ ደስታ ነው
ደሞ ያወራል እኮ ልክ ነኛ
 ወጣቱ የስድስቱን ሰዎች ዝምታ ለመስበር እየጣረ ነው
ሬዲዮዋ ቀጠለች የእሳቱ ሙቀት ለምታወጣው ዜና ቆንጆ አሟቂ ሆኖላታል ከሁሉ በላይ የሞቀው ወጣቱ ልጅ ነው
ነገሩ ልዩ ሁኔታን ፈጥሯል ሻርማይክ ሮዝ አበባ እና የዘራፊው ቡድን ሁሉም አይኖች ሬዲዮዋን የአንዲት ሴት እጅ ጠረቀማት
#ከአንድ አመት በፊት
ወደ ፖሊስ መምሪያዎች የሚመጡ የአፋልጉኝና የጠፋብኝ መረጃዎች ተበራክተዋል
ከሁሉም ልዩ ያደረገው ጠፉ እየተባሉ መረጃ የሚሰጥባቸው ሰዎች ተመራማሪዎች የታሪክ ምሁራን ደራሲዎች የኮምፒውተር ባለሙያዎች መሆናቸው ነው ፖሊስ ከነገሩ በስተጀርባ ማን እንዳለ ስለሚያውቅ ለነገሩ መልስ ከመስጠት ተቆጥቧል
መንግስተ ባደራጀው አዲስ ስርአት ለሀገር ጠቃሚ የሆኑ ምሁራንን ከያሉበት እየወሰደ ወደ አዲሱ #ናጋዚ ብሎ ወደ ሰየመው ማጎሪያ እያስገባቸው ይገኛል
የቤተሰብ ዋይ ዋይታ የምሁራኑ እናቶች እንባ የቤተሰቦቻቸው ጩኸት ተበራክቷል
ፖሊስም በለመደው መልሱ በቅርቡ ተጨባጭ ማስረጃ እስክይዝ ጠብቁኝ ይላቸዋል
በቅርቡ የሁለቱ ምሁራን አባት አቶ ታምሩ የፖሊስን በር አንኳክተዋል ልጆቼ ብለዋል
ዶክተር ናትናኤል ታምሩ እና ደራሲ ዮቶር ታምሩ ከጠፉ ሁለት ቀን እንደሞላተው አስረድተዋል እሳቸውም የአባት አንጀታቸውን ታቅፈው ሄደዋል
#የናጋዚ ተቋም ባጨቀው የምሁራን ብዛት ወለሉ ሳይቀር እውቀት እውቀት ብሏል
የት ነን ......
   
      ብላቴናው በእሳት ገፆች ላይ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
እንደው ይጠቅማልና ይኼን ልዩ ወሬ ስሙማ
አቅራቢው:-ወንድሙ ሃይሉ (ሸገር ራዲዮ)
.
.
.
.
.
@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
''ደቦ''
የጉዞ ማስታወሻ
በ ''ሄኖክ ስዩም''
ክፍል ፫
(፷ ደራሲያን ከተሳተፉበት መፅሐፍ ዘንድ ያገኘነው ፁኹፍ ነው)
''በአፅንኦት የተተረከ''
የኋላውን ዝምታ ለማስከን ያኽል :- የጋሽ ሙላቱ አስታጥቄ ጃዝ ስራዎች
አቅራቢ @Mykey21

@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
ታጋቹ ማስታወሻ
( በእውቀቱ ስዩም)
ቀሳ ከወጣሁ ጊዜ ጀምሮ ቤቴ ውስጥ ያገኘሁት ምግብ ሩዝ ብቻ ነው ፤ ሰኞ ሩዝ በቲማቲም- ማክሰኞ ሩዝ በጅንጅብል- ረቡእ ሩዝ እንደወረደ፤ ወዘተ…ባጭሩ በሩዝና በሪዝ ተከብቤ ሰነበትሁ ማለት ይቻላል፤ አንዳንዴ ምግብ የቀየርኩ እንዲመስለኝ የምበላበትን ቦታ እቀያይራለሁ፤ ሳሎን ውስጥ ሁለት ማንኪያ እጎርስና የተረፈውን በረንዳው ላይ ተቀምጨ እጨርሰዋለሁ፤
ሩዝ ጠዋት ማታ ከመብላቴ የተነሳ ወደ ማጅራቴ ሲሸሽ የነበረው ፀጉሬ ተመልሶ ቅንድቤ ድረስ ግጥ—ም አለ ፤ የህንድ አክተር ለመምሰል የቀረኝ በሱሪ ላይ ቀሚስ መደረብና ባየር ላይ የሚበር ሞተር ሳይክል መንዳት ነው፡ ፡
የሆነ ግልገል ጉንዳን ጠረጴዛየ እምብርት ላይ ከተበተኑት የሩዝ ቅንጣቶች መካከል አንዲቱን መርጦ ተሸክሞ ሲያዘግም ተመለከትኩ ፤ኩንታል መሸከሙ ነው፤ አይ ጉንዳን! አሁን ጉንዳንን የመሰለ ታታሪ ፍጡር በሚኖርበት አለም የሰው ልጅ የላባደሮችን ቀን ያከብራል ? ልይዘው ሞከርኩ ፤የጣቶቼን ጥላ ሲያይ ኩንታሉን እንደተሸከመ መሮጥ ጀመረ፤ አምልጠህ ሞተህል ባክህ! !ባውራ ጣቴና በነገረኛ ጣቴ መካከል አጣብቄ ያዝኩት ፤ የሞተ መስሎ ፀጥ አለ፤ ለካ አስመሳይነት የሰው ልጆች ባህርይ ብቻ አይደለም፤ ትወናውን አድንቄ በተሸከመው የሩዝ ቅንጣት ላይ አንዲት የቲማቲም ፍሬ መርቄለት ለቀቅሁት፤
ባለፈው ለለውጥ ያክል የሱካር ድንች ለመቀቀል ሞከርኩ፤ የአሜሪካ የሱካር ድንች አንዱ ፍሬ የድሮ ካውያ ያህላል ፤ ችግሩ በቀላሉ አይበስልም፤ እንዲያውም ካሜሪካ ሱካር ድንች፤ የኢትዮጵያ በሬ ሸኮና ቀድሞ ይበስላል፤ ቤት ጠርጌ ፤ምንጣፍ ቀይሬ፤ ኮርኔስ ራሱ ቀይሬ ተመልሼ መጥቼ ሳየው፤ አልበሰለም፤ ምን ጉድ ነው! ከዛ ገላየን ተታጥቤ፤ ብብቴንና በስተራስጌ የሚገኘውን ሁሉ ተላጭቼ ለባብሼ ሳበቃ ብረትድስቱን ከፈትኩት፤ ድንቼ መብሰሉን ለማረጋገጥ በሹካየ ወጋ አደረግሁት፤ እንዴየየየየ! የሹካው ጥርስ ተጣመመ፤ በጣም ተናደድሁና አውጥቼ በመስኮት በኩል ወረወርኩት፤ ድው! የሆነ ሰውየ oh Fuck! ብሎ ሲወድቅ አየሁት፤ ልጅ እያለሁ እናቴ “ ምግብ መወርወር ጡር ነው “ ትለኝ ነበር፤ እረ ጦርም ነው እማየ ፤ ይሄው አንድ ምስኪን ፖስታ አመላላሽ ፈረንጅ ለትንሽ ገድየ ነበር!
በክቡር ዳኛ Frank Caprio ፊት ቀርቤ ፤የፈነከትኩት ሰውየ እስኪሻለው ድረስ አልጋው አጠገብ ተቀምጨ በእንግሊዝኛ እንዳስታምመው ፈረዱብኝ! ሁለት ወር ሙሉ ተጎድቼ እንደከረምኩ ያወቅሁት በሆስፒታሉ ውስጥ የሚቀርበልኝን መኖ ሳይ ነው-ቆስጣ፤ የወይን ዘለላ፤ በማር የተጠበሰ ዳቦ! ግሪክ ሳላድ! እረ ወገን! ላስታማሚው እንዲህ አይነት ምግብ ከቀረበ ለታማሚው ምን እንደሚቀርብ ኢማጂን እንግዲህ!
ባልተያያዘ ዜና ፤
እንደ ዶክተር አቢይ አህመድ ያለ ብልጥ ሰው ግን አለ? ፤ ሰልስትና (ከሶስት ቀን በፊት) ተቃዋሚዎችን ፓርላማ ውስጥ ሰብስቦ ሲያወራ ማስኩን ካፍንጫው ሸርተት አድርጎ ከንፈሩ ላይ አስቀምጦት አየሁ ፤ ብዙ ሰው ስትራቴጂ መሆኑ የገባው አልመሰለኝም ፤የተፎካካሪ ፓርቲ ሊቀመንበሮች " አንተ ብቻ ነህ እንዴ አፍንጫህን የማናፈስ ነፃነት ያለህ ?ብለው በእልህ ማሳካቸውን ገለቡት ፤ አብቹየም ሁሉም አፍንጫውን ማጋለጡን ከተመለከተ በሁዋላ ፈገግ ብሎ በልቡ፤ “ጎበዝ! እንግዲህ ይቺን ቫይረስ እንቃመሳታ ፤ እኔ ጎልማሳ ስለሆንኩ አገግሜ እነሳለሁ ፤ ለእናንተም ደግሞ አካላዊ ርቀቱን ያስጠበቀ ቀብር አስከባሪ ይዘጋጃል” ካለ በሁዋላ የምትከተለዋን ዘለሰኛ ማስታወሻው ላይ አሰፈረ፤
ጎልማሶች ከመከራ ስንማር ፤
ለሼባዎች ነፍስ ይማር !

@wegoch
@wegoch
@wegoch
Forwarded from Mykey (Mikiyas Liyew Mykey)
ጣዕም ያላቸው ወዞች!
ኹሌም ቀኑን ለምታከብሩት ለእናንተ ይኹን

ከእነእርሱስ ፕሮጀክት © Mikiyas Liyew
@Mykeyonthestreet
2024/09/25 04:33:40
Back to Top
HTML Embed Code: