Telegram Web Link
አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #10

(የመጨረሻው ክፍል)

«ጥፋቱ የልጄ አይደለም። እራሷ ተንቀልቅላ ነው የገባችበት። ያን ሁሉ ብር መክፈላችን ልክ አይደለም! በዛ ላይ የዚህን ሁሉ ጊዜ የህክምና ወጪ ሸፍነናል።” ብለው የግሩም እናት ሀገር ይያዝልኝ ብለው ነበር መንቃቷን የሰሙ ጊዜ። ብዙ ጊዜ ነገር “ሁሉ ለበጎ ነው” የሚለው ቃል ያናድደኛል። የምወደው ሰው ሞቶ ወይ ታሞ ወይ የምሰራው ስራ ተበላሽቶብኝ ለበጎነቱ አይታየኝም። በእንዲህ ያለ ጊዜ ግን በጣም ፈገግ ብዬ ነገር "ሁሉ ለበጎ ነው!" እላለሁ።
ዶክተሩ 'ከዚህ በኋላ የመንቃት እድሏ ጠባብ ነው!' ያለን ጊዜ ነበር የሽምግልናውን ሂደት ያከናወነው። በሰዓቱ የሄለንን በህይወት ያለመኖር ታሳቢ አድርገን ባባ ትምህርቱን እስኪጨርስ ያለውን ወጪ ተምነው.... እናቱን ስለነጠቁት ካሳ እንዲሆን ተብሎ 500 ሺህ ብር ካሳ ስንጠይቅ የሄለን ያለመትረፍ አስደንግጧቸው ስለነበር በተለይ የግሩም እናት ሁለቴን አላሰቡትም ነበር። አባትየው የዛኔም 'ኡኡኡ ' ብለው ነበር። እቤት ሄደው ተማክረው (ቀልቤ እንደነገረኝ የግሩም ተፅዕኖ አለበት።) ብሩን ሊከፍሉ ተስማሙ። በባባ ስም በተከፈተ አካውንት ገንዘቡ በገባ በሳምንቱ ሄለን ስትነቃ ነው እንደአዲስ እሪሪሪሪ የሚሉት። እፊታቸው ፈገግታዬ ሲያመልጠኝ
"ሳቅሽ? ቱ! እንተያያለን! ገንዘቤን ትመልሷታላችሁ!" ብለው ተቀነጣጠሱ። ትልቅ ሰው ናቸውና መባለግ አልፈለግኩም ነበር ግን አበሳጩኝ። መጥተው 'ልጄ ከሚታሰር ቅበሪኝ!' ብለው እግሬ ላይ የወደቁ ሴትዮ የጭንቅ ቀናቸው ሲያልፍ ገንዘቤን ይላሉ?
"አስገድደን አላስፈረምኖትምኮ ፈቅደውና ጊዜ ወስደው አስበው የወሰኑት ውሳኔ ነው። በሽማግሌ በምስክር ፊት ተስማምቻለሁ ብለው ያደረጉት ነው። አይ ካሉ ይክሰሱኝ!" አልኳቸው ትቻቸው እየሄድኩ።
"ፀሎቴን ሰምቶኛላ! እግዚአብሔር ፀሎቴን ሰምቶኛላ? ጥሎ አልጣለኝም!" ነበር ያለችው ሄለን ከእንባ ጋር የምትይዘው አጥታ እየተቅበጠበጠች ምን ያህል ገንዘብ እንደተካሰች ስነግራት።
ከሆስፒታል የወጣች ቀን ቅዳሜ ቀጥታ እነእማዬጋ ነበር የመጣችው። ምሳ ተዘጋጅቶ። አባዬና እማዬ 'ጥሩ ሃሳብ አይደለም!' ብለው ነበር። እቤት ከገባችም በኋላ አሁንም አሁንም የእኔን ስሜት ይፈትሻሉ። ሄለን የሆነ ቀን ሆስፒታል ልጠይቃት ባባን ይዤ በሄድኩበት ባባ ስለእህቱ እየደጋገመ ሲያወራ ልጄ እንደሆነች እና የባባ እህት እንደሆነች ከነገርኳት በኋላ ብዙም አላወራችም። እነአባዬ ጥሩ ሀሳብ አይደለም ያሉት የገባኝ የልጄን ሁኔታ ሳይ ነው። ቃል አውጥታ ምንም ባትናገርም። ነገረ ስራዋ ሄለንን እንዳልወደደቻት ያስታውቅባታል። እንድትነነግረኝ ብወተውታትም 'ምንም' ከማለት ውጪ አትመልስም። ምናልባት አባቴን የወሰደችብኝ ሴት ናት ብላ ፣አሁን ደግሞ ተላምዳው ቀኗን በፍካት የሞላላትን ሁሌ እንዲኖራት ትመኘው የነበረውን ወንድሟን ልትወስድባት መሆኑ፣ ልታስበው ትችላለች ብዬ የማስበውን አስባለሁ።
"መጀመሪያ ላይ ማግባቱን አላውቅም ነበር።" አለችኝ ሄለን የምሳው ግርግር አልቆ እኔና እሷ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለን ልጆቹ ጊቢ ውስጥ ሲተረማመሱ እያየን።
"አረብ ሀገር ከሄድኩ በኋላ በህይወት ለመኖር ፣ ለመስራት የምጓጓ የነበረው ተመልሼ መጥቼ ከእርሱ ጋር ለመሆን ነበር። ሌላ ምንም የምጓጓለት ነገር አልነበረኝም። ሰርቼ ብር አጠራቅሜ ከእርሱ ጋር ህይወት መጀመርን ሳስብ ነበር ማታ ተኝቼ ጠዋት ለመንቃት የምጓጓው። ህይወቱ የተበለሻሸው ለእኔ ብሎ ነው። ለእኔ ብሎ ባይሆን ይሄኔ የት በደረሰ። ታውቂያለሽ ሁሌም እድለ ቢስ ነበርኩ! ሁሌም መኖር ጀመርኩ ስል የሚገድለኝ አጋጣሚ ይፈጠራል። ታመምኩ። ህመሜ ምን እንደሆነ ሳይታወቅ ያጠራቀምኩትን ገንዘብ በህክምና ጨርሼ። ከነህመሜ ተጠርዤ ወደሃገሬ ስመለስ በመከራ ነበር አስፈልጌ ያገኘሁት።" ብላኝ ዝም አለች።
ጊዜውን አስታውሰዋለሁ። በህይወቱ ውስጥ አንድ የፍቅር ታሪክ ብቻ ያለው ሰው እንዴት የዚያን ታሪኩን ገፅ እያንዳንዱን ቀኑን ሊረሳ ይችላል? ተጋብተን በሰባተኛ ወራችን አካባቢ ነው።
ከስራ ስመጣ የእንጨት ብናኝ የለበሰውን የስራ ልብሱን ሳያወልቅ ሳሎን መመገቢያ ጠረጴዛው ጋር የእናቱን ሞት የተረዳ መስሎ ቅስስ ብሎ ተቀምጦ ነበር። ሁኔታው አስደንግጦኝ ኮቴን አውልቄ እየወረወርኩ
"ምን ሆነሃል? ምን ተፈጠረ? ንገረኝ ምን ሆነሃል?" እያልኩ ስወተውተው ቆይቼ
"ሄለን ብዬ የነገርኩሽን ልጅ ታስታውሻታለሽ? ማሳደጊያ ..... " ብሎ ሳይጨርስ አስታወስኳት።
ስለማሳደጊያው ሲያወራ ፊቱ በፈገግታ የሚፈካው ስለእሷ እና ስለእማሆይ ሲያወራ ብቻ ነበር። ያለችበትን ለማወቅ ፈልጎ ሊያገኛት ያልሞከረው ሙከራ አልነበረም። ከአረብ ሀገር መጣሁ ያለች ሴት ባገኘ ቁጥር እንደቂል ያውቋት እንደሆነ ይጠይቅ እንደነበር አስታውሳለሁ። በኋላ ላይ ተስፋ ቆርጦ ፍለጋውን ተወው። 'የሆነ ነገር ሆና ቢሆንስ?' ብሎኝ ያውቃል። እሷ ላይ በሆነው ነገር ሁሌ ራሱን ይወቅስ ነበር። 'ልጠብቃት ቃል ገብቼላት ነበር። ብቸኛ ቤተሰቤ እሷ ነበረች። እኔ በህይወት እያለሁ ማንም እንደማይጎዳት ቃል ገብቼላት ነበር። የማንም ባለጌ ሲደፍራት እንኳን ልጠብቃት አይዞሽ ብዬ ላባብላት እንኳን አጠገቧ አልነበርኩም' ነው ያለኝ ታሪኩን የነገረኝ ጊዜ
"ታማ ከአረብ ሀገር ተመልሳለች። ሆስፒታል ናት!" አለኝ።
"በእማዬ ሞት! ደህና ናት? ማለቴ ምንድነው ህመሟ? ትድናለቻ?" አልኩት አተካከዙ መጥፎ ሁኔታ ውስጥ እንደሆነች ለመገመት አይከብድም ነበር።
"አትድንም! ህክምናው ያለው አንድ የግል ሆስፒታል ነው። እሱም በትንሹ 430 ሺህ ብር ያስከፍላል። ድጋሚ ስትሞት ዝም ብዬ ላያት ነው።" ብሎ ሲሆን አይቼ እንደማላውቀው ደም ስሩ ተገታትሮ ነፍሱ ጣር ላይ ያለች ሰው መሰለ።
"መላ እንፈልጋለን! ከቢሮም ቢሆን እበደራለሁ! ወይም ከአባዬ እበደራለሁ! የሆነ መላ አይጠፋም! ብቻ ትዳን እንጂ የሆነ ነገር አይጠፋም!" ብዬ አባበልኩት። አባቴን ዋሸሁት! ቤት ልንገዛ ብር አንሶን ነው ብዬ አባቴን ዋሸሁት። እማዬን የምታልመው እስራኤል ሊወስዳት ብሎ ለዓመታት ያጠረቃመውን ገንዘብ አንስቶ ሰጠኝ። ብሩን ሰጥቼው ሳውዝ አፍሪካ ለስድስት ሳምንት ስልጠና በቢሮ ተልኬ ሄድኩ። ደስተኛ ነበር። 'የእህቴን ህይወት ነው መልሰሽ የሰጠሽኝ' ነበር ያለኝ። ከስልጠና ስመለስ ህክምናዋን ጨርሳ ወደቤት መግባቷን ሲነግረኝ ልጠይቃት በተደጋጋሚ እቅድ አውጥቼ አውቅ ነበር። አሁን ሳስበው ምናልባት እንዳገኛት እሱ ስላልፈለገ ይሆናል ብቻ ተሳክቶልኝ አያውቅም ነበር።
"ብሩን ከየት አምጥቶ እንዳሳከመኝ ያወቅኩት ቆይቶ ነው። እኔጋ ያለው ስሜት እሱጋም ያለ ይመስለኝ ነበር። ተሽሎኝ ከሀኪም ቤት የወጣሁ ጊዜ ለእኔና ለእሱ ብዬ ብር አጠራቅሜ እንደነበር ስነግረው ከታናሽ እህትነት ውጪ እንደሌላ እንደምንም እንደማያየኝ ነገረኝ። ማግባቱንና የታከምኩበትን ብር አንቺ እንደሰጠሽው ነገረኝ። አላመንኩትም ነበር። ምንም ስሜት ባይኖረው ማግባቱን ለቀናት አይደብቀኝም ነበር ብዬ አሰብኩ።" ብላ ስሜቴን ለማጣራት በሚመስል አየት አድርጋኝ ቀጠለች::
"....ወደላይ ወደታች ብታዪ ወደግራም ወደቀኝም ብትዞሪ አይንሽን የምታሳርፊበት አንድ ነገር ብቻ ኖሮሽ ያውቃል? ሊያውቅ አይችልም!" አለችኝ ዙሪያ ገባችንን እየቃኘች። ማት ባባን እና የሱን ልጆች ጨምሮ ሳሩ ላይ እየተንከባለለ እያጫወታቸው ፣ የማት ሚስት የእማዬን ፀጉር እያበጠረችላት፣ እቤት ውስጥ አባዬና የኔ ልጅ በሆነ ነገር እየተከራከሩ ድምፃቸው ይሰማል። ቀጠለችና
"ልጅነቴ፣ እድገቴ፣ ተስፋዬ፣ ፍቅሬ፣ ቤተሰቤ፣ የወደፊት ትዳሬ ብዬ በልቤ የተሸከምኩት እሱን ብቻ ነበር። ማግባቱን የነገረኝ ቀን ሰማይ ምድሩ ዞረብኝ። እሱ ጭራሽ ከዛ በኋላ ለሳምንት አይኔንም ማየት አልፈለገም። የምኖርበት ምክንያትም ተስፋም አልታይሽ አለኝ። የሆነ ቀን ማታ ራሴን ላጠፋ ሞከርኩ። እድለ ቢስ ነኝ አላልኩሽም? ሞት እንኳን እንደደህና ነገር ራሱን አዋደደብኝ! ለመሞት ይታይሽ? ሰው እንዴት ሞት እንኳን አይሳካለትም? ተረፍኩ!! ተደውሎለት መጣ! "
እሷ እየነገረችኝ ቀኑን በእርግጠኝነት አስታወስኩት። ማታ 3 ሰዓት አካባቢ ስልክ ሲደወልለት ደንግጦ ከተቀመጠበት ሲስፈነጠር። "አብሮኝ የሚሰራው ልጅ ራሱን ሊያጠፋ ሞክሮ ሆስፒታል ነው!" ነበር ያለኝ።
የዛን ቀን ባልደረባዬ የስራ እድገት አጊንቶ እራት ተጋብዘን ሄደን "ስራህ ምንድነው?" ብለውት በዛ ሳቢያ ተጨቃጭቀን ነበር። 'ሁልጊዜ ላንቺ ትንሽ እንደሆንኩ ነው የሚሰማኝ .... ሱፍ ለብሰው ለሚውሉ የስራ ባልደረቦችሽ እንጨት ስፈቀፍቅ ነው የምለው ብዬ አንቺን ላሳፍርሽ አልፈልግም!' ብሎኝ ተናድጃለሁ። ሱፍ ለበሰ የስራ ቱታ ለእኔ ለውጥ እንዳልነበረው ያውቅ ነበር። ሱፍ ለባሽ ከሚላቸው ማናቸውም ለደቂቃ ሀሳቤን ሰርቀውት እንደማያውቁ ያውቃል። ብቸኛ ምርጫዬ እንደሆነ ያውቃል። ብቸኛ በፍቅር የማውቀው ወንድ መሆኑንም ያውቃል።
እስከዛ ቀን ድረስ ሙያውን እንደሚወደው ነበር የማውቀው። የራሱን ፈርኒቸር ቤት ሊከፍት የሚያስፈልጉትን ማሽኖችና ጥቃቅን ወጪዎች መዝግበን አስቀምጠናልኮ! ትምህርቱን ቢጨርስ ደስ ይለው እንደነበር የነገረኝ ቀን እኔ አሁን እየሰራሁ አንተ ተማር እና አንተ ስትጨርስ ደግሞ በተራህ ማስተርሴን ታስተምረኛለህ ብዬው ነበር። ምንም መከፋት ባልነበረው ስሜት ነበር የሚፈልገው ፈርኒቸር ቤቱ ላይ መስራት እንደሆነ የነገረኝ። በእንዲህ ጭንቅላቴ በተሰፋበት ሰዓት ነበር ስልኩ የተደወለው። ሆስፒታል ሊያድር እንደሚችልም ሲነግረኝ ምናልባት እሱም እንደእኔ መጨቃጨቃችን ረብሾት ጊዜውን በዛውም ፈልጎት ይሆናል ብዬ ከማሰብ አልዘለልኩም። አብጠርጥሬ የምጠይቅበት ጥርጣሬ አልነበረኝም።
"እርሱ የሌለበት ህይወት መኖር እንደማልፈልግ ስነግረው 'እሷስ?' ነበር ያለኝ አንቺን 'በህይወቴ ማንም ሰው ያልሰጠኝን ክብርና ፍቅር ነው የሰጠችኝ። በምን ጥፋቷ ልቅጣት?' ነበር ያለኝ። የእውነቴን ነበር። እርሱ ከሌለበት የመኖር እንጥፍጣፊ ፍላጎት አልነበረኝም። ለሊቱን ሙሉ ያደረግሽለትን የሆንሽለትን እየነረኝ ነበር ያደረው። በየቀኑ እንደምንገኛኝ ነግሮኝ ድጋሚ ራስ ማጥፋቱን እንዳልሞክረው ቃል አስገብቶኝ ጠዋት ሄደ።
ያኔ ያላስተዋልኳቸውን እና ባስተውላቸውም ከዛን ቀን እራት ጋር እያያዝኩ ምክንያት የሰጠኋቸውን ለውጦቹ ምክንያታቸው ተገጣጠመልኝ። ከዛ ቀን በኋላ ተነጋግረን የተስማማን የመሰለኝን ልጅ የመውለድ ጉዳይ አንስቶ አላስፈላጊ ብስጭት እየተበሳጨ 'እኔ የሚሰማኝ ስሜት አይገባሽም!' ብሎኛል። 'አንቺ በፍፁም አትረጂኝም' የዛን ሰሞን ዜማው ሆኖ ነበር:: በትንሽ በትልቁ ይነጫነጭ የነበረው ጥሎኝ ለመሄድ ምክንያት እንድሰጠው የሚሰማውን ፀፀት ሊቀንስ መሆኑ ሳይገባኝ ልጅ ስላልሰጠሁት ነው ብዬ አምኜ ነበር ለማርገዝ የወሰንኩት።
በአንድ ጊዜ ቅናትም ጥላቻም ቁጣም እልህም ቁጭትም ..... አንድ ላይ የሚሄዱ ስሜቶች መሆናቸውንም እንጃ ብቻ ውስጤን ሞልተው ፊቴ ላይ ሲንቀለቀሉ እሷ እንኳን አይታዋለች። መበለጥ .....መታለል .....መከዳት ....መሸነፍ...
"ውደጂኝ አልልሽም ግን አትጥዪኝ። እኔ ህይወት ራሷ የቀጣችኝ ሰው ነኝ። እኔን ስለመረጠ እንደበለጥኩሽ ታስቢያለሽ? ያውም እኔ ከምሞትበትና አንቺ ከምታዝኚበት ምርጫ ሰጥቼው? በጥሩነትሽ በልጠሽኛል። ጊዜ አምጥቶ ከነልጄ እጅሽ ላይ ጣለኝ አይደል? ይበልጥ ቅጣቱ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ? አሁንም ማን እንደሆንኩ እያወቅሽ ደግ መሆንሽ? እሱ ይበልጥ ያማል።" ብላኝ ዝም አለች::
"አንዳንዴ የክፋቴ ውጤት ነው ብዬ አስቤ አውቃለሁ:: በመጨረሻ ተደላድዬ እግዜር ታርቆኛል ብዬ መኖር ስጀምር ያ ከይሲ መጣ!! የእግዚአብሄር ቁጣ ካልሆነ በከተማው ከሞላው ሱቅ እኔ ሱቅ ምን ያደርጋል? እድሌ ሲከፋ እንጂ ካልጠፋ ሰዓት አሹ ሊወስደኝ እዛው በቆመበት? .... በአንድ ቦክስ ከግድግዳ ጠርዝ ተጋጭቶ ሰው ሞቶ ያውቃል?? ለኔ ሲሆን የማይገጣጠም ነገር የለም!....... ከዛሬ በኋላ አይኔን ማየት ካልፈለግሽ ከነልጄ ከህይወትሽ እወጣለሁ እመኚኝ አደርገዋለሁ። " ብላኝ እንባዋን እንዳላይባት ዞረች::
"በልብሽ ትንሽዬ ርህራሄ ከተረፈሽ ግን እባክሽ ባባ ከእህቱ ጋር ይጠያየቅ። ለእኔ ብለሽ አልልሽም ለባባ እንዴት እንደምትሳሱለት አይቻለሁ። ይሄን ተስፋውን ይሄን ፍቅር አታሳጪው" ብላኝ መልሴን ሳትጠብቅ ወደውስጥ ገባች።

ከዛ ሁሉ እንደእሳት ከሚንቀለቀል ስሜትጋር ሀዘኔታስ ሲደባለቅ የጤነኛ ሰው ስሜት ነው? ባባ ትምህርቱ እንዳይስተጓጎል በሚል ለትምህርት ቤቱ የሚቀርብ ቦታ ቤት ተፈልጎ እቃዎቿ ተጭነዋል። ሲመሽ ተሰናብታን እና አመስግናን ልትሄድ ስትነሳ ባባ ሁላችንንም ለጤንነት ያልቀረበ ስሜት ውስጥ ከተተን። አንዴ የእህቱን እጅ ይዞ አብራው እንድትሄድ ያለቅሳል። ደግሞ መለስ ብሎ የእናቱን እጅ ይይዝና እንድትቀር ይወተውታል። እላዬ ላይ ተንጠልጥሎ 'መላ በዪኝ!' አይነት ተቁለጨለጨ። እናቱንም እኔንም እህቱንም ማንንም መምረጥ ቸገረው። አባዬ ላለማየት ሳሎኑን ለቆ ወጣ። የነበረኝ ቅጥ አንባሩ የጠፋ ስሜት ላይ ባባ ሊሄድብኝ መሆኑ አተረማመሰኝ:: ማት ሁሉንም ተቆጥቶ
"ምንድነው የማንገናኝ ነገር አደረጋችሁት። የአንድ ታክሲ ርቀት ላይ ናቸውኮ!" ብሎ ሁሉንም አረጋጋ። ለባባ 'ነገ እንገናኛለን! ብለን አባብለነው ሄዱ።
"እውነትሽን ነው? ነገ እንገናኛለን ያልሽው?" አለችኝ ልጄ
"ወንድምሽ አይደል? ልታገኚው በፈለግሽ ሰዓት መሄድ ትችያለሽ! እሱም መምጣት ይችላል።" ስላት ራሴን ሰማሁት። መጥታ አቀፈችኝ። የሚሰማኝን ስሜት ለይቼ እንኳን ሳልረግብ
"አባቴጋ መሄድ እፈልጋለሁ" ብላ ድንጋጤ አከለችልኝ። ድጋሚ አሸናፊን ላየው መዘጋጀቴን እርግጠኛ አልነበርኩም!! የዛን ቀን የማስበው ምን እንደሆነ እንኳን አላውቅም አንዱን ሀሳብ ሳነሳ ሌላውን ስጥል ነጋ! ከቀናት በኋላ ግሩምጋ ደውዬ ሸዋ ሮቢት ሊያደርሰኝ ይችል እንደሆነ ስጠይቀው
"ድሮም ከአማትሽ ጋር ንትርክ ስትጀምሪ ልትጀነጅኚኝ እንዳሰብሽ ገብቶኛል" ብሎ ቀለደብኝ። ከእናቱ ጋር በገንዘቡ ዙሪያ መነጋገራችንን ነግረውታል ማለት ነው።
ሳየው የምናደድ ፣ የምተክን ፣ እንባ የሚያንቀኝ፣ ብዙ ነገር የምለው ነበር የመሰለኝ። እንደዛ አይደለም የተሰማኝ። ዝም ያለ ስሜት! ምንም!ከልጁ ጋር ብቻውን እንዲሆን ትቼው ከግሩም ጋር ርቀን ቆምን።
"አንቺን እስካገኘሁበት ቀን ድረስ እንዳንቺ አይነት ቅን ሰዎች እንደዳይኖሰር ከምድር የጠፉ ነበር የሚመስለኝ። ክፋት፣ ፉክክር፣ ጥሎ ማለፍ ዓለምን በዝቶ እንደልክ ተቆጥሯል። መልካምነት ፣ ለሌላው ቅድሚያ መስጠት፣ መከባበር .....ቂልነት እየመሰለ መጥቷል። ፌቨን የምሬን ነው አንቺ እጅግ መልካምና ቅን ሰው ነሽ። በዚህ ደስ ልትሰኚ ይገባል። ግን ሰውን ከምትወጂው ከፍ አድርገሽ ራስሽን ውደጂ፣ ሌላውን ከምታከብሪው ከፍ አድርገሽ ራስሽን አክብሪው፣ ያኔ አልፎ ሂያጅ የሚሰብረው ልብ አይኖርሽም!" አለኝ ዓይኖቹ ርቀው እነአሸናፊን እያዩ
"አንተም ብትሆን ማለት ነው?"
"ዝግጁ ነኝ እያልሽኝ ነው?"
"አምነሽ ካልሰጠሽ ያክምሽ ያቁስልሽ በምን ታውቂያለሽ?" አላልከኝም? በስሱ ፈገግ አለ። ያልቸኮለ ፈገግታ .......
የምላችሁ ........ጨርሰናል።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
ቁንጅናዋ ብዙ ሰው የሚስማማበት አይነት ነው ። ቆንጆ እንደሆነች ታውቃለች ፤ ግን ቆንጆ
ስትባል ደስ ይላታል።
ሴት ልጅ በየትኛውም እድሜ ቆንጆ መባልን አትጠላም ። ሴት ልጅ መደነቅ ድክመቷ ነው
መሰለኝ። በእርግጥ መደነቅ እና ትክክል መባል የሰው ሁሉ ድክመት ይመስለኛል።
ምንም እንኳን የገላዋ አሰራርም ለአድናቆት እንዲመች አድርጎ ያበጃጃት ቢሆንም
ሴቶች በሚወዷቸው እንደማይጨክኑ ፤ ኤልዳና እኔን እንዳላገኛት መንገድ አለመዝጋቷ
ምስክር ነው ።
እኔ ሞኝ የምባል አይነት ሰው ነኝ መሰለኝ። ለቀልድ እንኳን ሞኝ ስባል አራስ ነብር
የምሆነው ፤ በቃ ክፍ....ት ነው የሚለኝ ።
ሞኝነት ድክመቴ ባይሆን ሞኝ ስባል እስቅ አልነበር ? አሁን ቀጫጫ አይደለሁም ፤ ቀጫጫ
ብባል ግን እስቃለሁ እንጂ አልናደድም ስለዚህ ሞኝ ነኝ ማለት ነው እላለሁ ፤ አንዳንዴ
ደግሞ እንደዚህ ከተመራመርኩ እኮ ሞኝ አይደለሁም እላለሁ
ዘይገርም
አንዳንዴ ሰዎች ጭንቅላቴ ስል ሲሆንባቸው ትኩር ብለው ያዩኛል ። በቂላቂልነቴ save
አድርገውኝ ባይሆን ኖሮ እንዴት እንደዚህ አሰበ ብለው ሲገረሙብኝ አይናቸው ላይ መች
አስተውል ነበር !?
ሰው ድክመቱን ባያሻሽለው እንኳን ጥንጥም ይገባዋል ማለት ነው ፤ ያ ማለት ደግሞ he
might be denying the hard fact deliberately ።
ኤልዳና ጋ ብዙ ቀን እደውላለሁ ፤ ኤልዳና ሲሻት ብቻ ስልኬን ታነሳለች ። ከደወለችልኝ የሆነ
ነገር ፈልጋ ነው ።
ቢሆንም ደስስ ይለኛል
ኤልዳና ከእኔ ጋ ስታወራ አወራሯ ፆታዊ ነገር የለውም ፤ መሽኮርመም ሆነ ደርባባነት
አይታይባትም ፤ ምንም ፆታዊ ፍላጎት ስለሌላት ይሆን ?
አላውቅም !
አግኚኝ ስላት ሀገር እንደምታስተዳድር አይነት ነው ባተሌ መሆኗን የምትነገርኝ። የግል
university እያስተማርኩ ፤ ትልቅ ፕሮጀክት እየመራሁ እኔ እንኳ እንደእሷ ስለመባተል
አላወራም ።
ተሳክቶልኝ ኦር ፈልጋኝ ያገኘችኝ ጊዜ...
ነፃ መሆን አልችልም ፤ አክብጄ ስለማያት ጨዋታ አይመጣልኝም ።
ባገኘውት አጋጣሚ ቀልቧን ለመሳብ እባዝናለሁ ።
በቃ እዛው ከእኔ ጋ እያለች ከሌላ ሰው ጋ ስልክ ታወራለች ። ፊቴ ለምታወራው ወንድ ሲሆን
ደግሞ ደርበብ እሽኩርምም ስትል አስተውላለሁ ፤ሞኝ ስለምመስላት ይሄን የምረዳ
አይመስላትም ወይም ሳይታወቃት በደመ-ነብስ ነው ሁኔታዋ እና አነጋገሯ የሚቀየርባት ።
አንዳንዴ 'ለምንፈልገው ነገር አድራጎታችን ከእውቅናችን ውጪ ይሆን የለ' ።
ትንሽ ለመጫወት እሞክራለሁ ፤ ቀላል ወሬ ታወራልኛለች
ከዛ
የማይመለስ ብር ትበደረኛለች ፤ ከዛ እንቅ አድርጋ ትስመኛለች ደስስስስስ ይለኛል።
ጓደኞቿ ጋ ሆና ካገኘኋት በጣም እንደምወዳት እሷ ደግሞ ከምንም እንደማትቆጥረኝ ፤
ለብቻቸው የነገረቻቸውን በማስረጃ እያጣቀሰች እና እየቀለደችብኝ ታሳየቸዋለች ፤ እነሱ
ደግሞ አምነንሻል ፤ ገብቶናል ለማለት ያሽካካሉ።
አሁን እንደው የሚወደን ሰው ላይ እማኝ አስቀምጦ ማልመጥ ምን የሚሉት ስልጣኔ
ነው?? !!
ኮትህን የት ገዛኸው አለቺኝ አንድ ጓደኛዋ ሽሙጥ እንዳልሆነ እንዳያሳብቅ ፊቷን
እየተቆጣጠረችው
አይን አይዋሽ አይኗ ያስታውቃል ፤ ለበኋላ
የሚሆን ቧልት እያድቦለቦለች ነው
ዝም አልኳት
አሁን ሰው መርጦ እና ወዶ በለበሰው ኮት የለበሰው ሰው ፊት ማላገጥ ትክክል ነው??
ጓደኞቿ እኔ ላይ ያላቸውን ንቀት ወላጇ
የምወዳት ኤልዳና መሆኗን ነጋሪም መስካሪም አያስፈለገኝም
ተሰብስበው ሳገኛቸው ከሚጨንቀኝ ነገሮች አንዱ እጄን የት እንማደርገው ነው ። ኪሴ
ውስጥ እከተዋለሁ ወይ አጣምራለሁ ፤ አልያም የግራ አና የቀኝ ጣቶቼን አቆላልፋለሁ ፤
በእሱ ራሱ ይቀልዳሉ ።
ፍቅር ተአምራዊ መሆኑ ማሳያዬ
ይሄ ሁላ እየገባኝ አለመሸሼ
እኔ ለእሷ ክፉ አይደለሁ ። ከሁሉም ሰው በላይ ስለምወዳት አይደል የተበደረችኝን
እንደረሳሁ ሆኜ ሌላ ቀን እንደገና የማትመልስልኝን ገንዘብ የማበድራት ፤ ለዛውም ላይ ታች
ብዬ የማመጣውን ገንዘቤን !!
መውደዱ የእውነት እንደሆነ የሚታወቅ ሰው ላይ ይሾፋል???
ሰው ላይ መቀለድ አራድነት ነው ???
ስለማታውቀኝ ነው እኮ
ማጣጣል እንደማይጥለኝ ፤ ስንቴ በትግሎቼ እንደወደቅኩ ፤ ወድቄ ሳለሁ ቆሜ
ስለምታገለው እንደማሰላስል !
ለዚህ ነው ይሄ ሁላ ነገሯ እየገባኝ
ጊዜ ሃያል ነው ፤ አይኗ ሲከፈት ሞኝነቴ ጥበብ እንዳለው ትረዳለች ብዬ መጠበቄ።
የድንቁርናዋ ምንጩ አለማስተዋል እንደሆነ የምረዳላት።
ከብልግናዎቿ መሃል መልካምነቷን ለራሴ እንደምነግር አልገባትም ።
ክፉ ቀን ቢመጣባት አብራ ከምታላግጥብኝ ጓደኞቿ የበለጠ እንደምረዳት ፤ ከአጠገቧ
እንደማልጠፋስ አልገባትም ።
ሰው በረከቱ ላይ እንዴት ያላግጣል ? መወደድ በረከት አይደለምን?
ፍቅር የሚወዱንን ብቻ መውደድ አይደለም ።
ለዛ ነው የምወዳት። የቀን ጉዳይ ነው እንጂ ፍቅሬ አንድ ቀን ይጋባባታል ።
ያ አንድ ቀን እንዲመጣ
ትላንት ባልሞከርኩት መንገድ መምጣት አለብኝ ። ለተመሳሳይ አወዳዳቅ ተመሳሳይ
የአተጋገል ስልቶች ምክንያት ናቸው ። ጥበብ ማለት የሚፋለመንን መረዳት ብቻ ሳይሆን
መቅደምም ጭምር ነው። ከትላንት የተሻለ ውጤት መጠበቅ ያለብኝ ትላንት በሄድኩበት
መንገድ ካልመጣሁ ብቻ ነው ።
ማስታወሻ ፦
እጅ መስጠት ውስጥም ደማቅ ድል አለ!!!

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
(ፋራ ነኝ)

በመሊኩ [ MAJNUN ]

ከወሎ ኮምቦልቻ 23 ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ የምትገኘው ደሴ ከተማ ከኢትዮጲያ ቀደምት ከተማዎች ውስጥ ግንባር ቀደም ነች፡፡ ኮምቦልቻም ያው ስሟ እንደ ደሴ ባይገንም ቀደምትነቷ እና ድሙቅነቷ እሙን ነው፡፡ ከጂኦግራፊ ቀረቤታዊ አቀማመጣቸው እና ከማህበራዊ ስሪታቸው ፣ እንዲሁም ከኢኮኖሚ ትስስራቸው አንፃር መንትዮቹ የሚል ቅፅል ስምም ተችሯቸዋል፡፡ ባንድም በሌላም መልኩ ግን የደሴ ስም ከኮምቦልቻ ይልቅ መናኘትን ተጎናፅፏል፡፡ አንዳንዶች ለደሴ ድምቀት እኛ ወሎዬዎች "የወሎ ሀፍረት"!! ብለን ስሙን ልንጠራው የማንሻውን የልጅ ሚካኤል(ራስ አልይ/መሀመድ አልይ) መንበር መቀመጫ መሆኗን እንደ አንድ አመክንዮ ያነሱታል፡፡

ብቻ ከድሮ ጀምሮ ደሴ የወሎ መዲና ነበረች፡፡ ባሁነኛውም የፌደራሊዝም ስረዐት ከወሎ መዲናነቷ ዝንፍ ሳትል እንደ ደመቀች ፣ ተጀብና ተከሽና ፣ አለች፡፡ ወደ ወሬዬ ልመልሳችሁ... ጁመዐ ማለዳ ከኮምቦልቻ ወደ ደሴ መንገድ ትራንስፖርት የሞተር ሳይክል ታርጋ ለማውጣት ማልጄ ወጥቻለሁ፡፡ ያው የደቡብ ወሎ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን ገዘፍ ያሉ መንግስታዊ እና ግለ-ሰባዊ ድርጅቶች መገኛም ነች፡፡ ከተለያዩ የወሎ ክፍለ ሀገሮች ግልጋሎት ለማግኘት ብዙ ሰዎች ስለሚመጡ ጉራው (ወረፋው) እንደ አንቻሮ ገበያ ደመቅቅቅቅቅ ይላል፡፡ በዛ ላይ መመላለስ ከያዝኩኝ ሳምንት ሆኖኛል፡፡ ለዛም ነው የደሴን ብርድ ሳልፈራ ማልጄ የወጣሁት፡፡ ብዙ ሰዉ ከሩቅ ሀገር ስለሚመጣ ላለመቆየት እና ላለመስተጓጎል ሲል ሙስና እየሰጠ ጉዳዩን ያስፈፅማል፡፡ እንደ እኔ አይነቱ ደረቅ አራዳ ደግሞ ሳምንት ታሽቶ ይሸኛል፡፡ ያም ገዱ ካማረ ነው፡፡

አቤት በየመስሪያ ቤቱ ያለ ሙስና እና ዘረፋ!! አሁን አሁንማ የምግቤት ስጋ ቆራጮችም ሳይቀር ሙስና ለምደው ደምበኛ ለይተዋል፡፡ ስጋ መብላትን በረጅም የእቅድ ፕላት ፎርሙ አካቶ በወር አልያም በአመት አንዴ የሚበላን ገሚስ ሀበሻ ሙስና ያልከፈለ እንደሁ አንጆ እና ጣንፊያ ያቀርቡለትና ከአንጆና ጣንፊያው ጋር የስጋ ቆራጩን ስጋ በልቶ ይወጣል፡፡ ብቻ በኛ ሀገር ውስጥ የሙስና እና የዶላር እድገት እንደ ፈረንጅ ልጅ ሆኗል፡፡ ኧረረረ የደሴ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ግን ይለያል፡፡ ደግሞ እኮ የሚገርመው ካንዱ የግድግዳ ጥጋት ከመስሪያ ቤቱ መተዳደሪያ ደንብ ዝርዝር ዝቅ ብሎ "በግርግር ውስጥ ኪስዎን ከሌባ ይጠብቁ" ፣ "ሙስናን በጋራ እንከላከል" ብለው ለጥፈዋል፡፡ ህህህ ቀልዳቸው እኮ አይጠገብም፡፡

አንዱ ሰራተኛ ከሰኞ ጀምሮ ጥርሱን ስሎ ሊበላ ሲያሰባኝ...ሲያሰባኝ ነገ ዛሬ እያለ ይሄው ሳምንቴ መጣ፡፡ በመጨረሻም ምርር ብሎኝ ወደ አለቃው ይግባኝ ብዬ ሄድኩኝ፡፡ አለቃውም ከኔ ሀልጋ ከፍ ከክላሴ ዝቅ ያለ ተሽከርካሪ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ "ምን ልርዳህ"? አለኝ የነፍሰጡር ሆድ የመሰለ ቀፈቱን እያሻሸ፡፡ ካነጋገሩ የወደላይ ሀገር ሰው (ጎጃሜ) ይመስላል፡፡ ኧረ እንደው ጌታዬ እባክዎትን ቢሮ ቁጥር 8 ካሰሩት ጅብ ያድኑኝ፡፡ እእእ ... ማለቴ ቢሮ ቁጥር ስምንት ያለው ባለ ሙያ ከስራ ዲስፕሊን ውጭ የሆነ አላግባብ ክፍያ ካላመጣህ ብሎ እያስተጓጎለኝ ነው አንድ ይበሉልኝ፡፡ አልኩኝ ሙስና ማለት ፈርቼ፡፡ "እህ እህህህ" ብሎ ጉሮሮውን ጠራርጎ ከተገደፈበት ወንበር ቀና አለና እሺ እንግዲህ ችግር የለውም፡፡ ወደዚህ መምጣትህ ጥሩ አድርገሀለል፡፡ አሁኑኑ ባስቸኳይ ቶሎ እንዲሰራለህ አደርጋለሁ፡፡ እንደውም ልደውልለት ብሎ ስልኩን አንስቶ መታ "ለካ ከጅቦች መንጋም እንደዚህ አይነትም ቀና ሰው አለ" ብዬ በእዝነ ህሊናዬ ስብሰለሰል "እህእህህህእ" ብሎ በዳግማዊ ጉሮሮ ጥርጊያ ከሀሳቤ መለሰኝ፡፡ እሺ ይሄው ደውዬለታለሁ፡፡ በቶሎ ይሰራልሀል አለኝ፡፡ ከተቀመጥኩበት ወንበር ተነስቼ ለቀናነቱ አላህ ይስጥልኝ ብዬ አመስግኜ ልወጣ ስል ሰልሶ ጉሮሮውን ጠራረገና ታዳ የደንቡን ውረድ እንጂ አለኝ፡፡ የደንብ? የደንብ? የደንብ ምን ነበር? አቤት??? አልኩኝ ግራ እየተጋባሁ፡፡ ቶሎ እንዲሰራልህ ላደረኩበት የሻሂ አምጣ ብሎ የደንብን ትርጓሜ ፈሰረልኝ፡፡ እህህህ??? የደምብ ማለት ሙስና ነው እንዴ? እዚህም ሙስና??? አልኩኝ ከፊቴ የተቀመጠው መልአክ በቅፅበት ወደ ትልቅ ጅብነት ሲቀየርብኝ ደንግጬ፡፡ ጉድ እኮ ነው!! በር ላይ ያነበብኩት የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች መተዳደሪያ ደንብ ላይ ሙስና የሚል ደንብ አላየሁም፡፡ ወይስ ሙስናም ህገ መንግስቱ ውስጥ ካለተፃፉት ህጎች ውስጥ አንዱ ሆኖ ኖሯል??? ከተኛበት አልጋ ላይ ማለቴ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ተነስቶ "ዉጣ!! የማነው ፋራ" ብሎ አምባረቀብኝ፡፡ ለካ አስር ግዜ ጉሮሮውን ሲጠራርግ የነበረው ይሄ ትልቅ ጅብ ጠቦት አገኘሁ ብሎ ሊበላኝ አስቦ ኖሯል፡፡ ሆሆሆ ሳይመታኝ ተነስቼ ልውጣ ብዬ ሾከክ እያልኩ በገባሁበት በር ወጣሁኝ፡፡ ከግቢ ውጭ ላንድ አፍታ ቆም ብዬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሳስብ ከመንገድ ትራንስፖርት ጀርባ ካለው ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሄጄ ማመልከትን ሁነኛ መፍትሄ ብዬ ዘየድኩኝ፡፡ ወደ... ፀረ ሙስና ኮሚሽን፡፡

ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደርሼ ወደውስጥ ዘልቄ ገባሁ፡፡ ግቢው በር ላይ የፖሊስ ፓትሮል ቁሟል ፣ አልፎ አልፎ ክላሽ የያዙ ፖሊሶች ተገትረዋል፡፡ እነሱን አልፌ ወደ ህንፃው ሳንቃ ስጠጋ ሰራተኞቹ ውጭ ላይ ይተራመሳሉ፡፡ ግራ ገብቶኝ እንደኔ ፋይል ይዞ ግራ የገባውን አንዱን ባለ ጉዳይ ምን እንደተፈጠረ ጠየኩት፡፡ የመስሪያ ቤቱ ሀላፊ በሙስና ወንጀል እጅ ከፍንጅ ተይዞ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየወሰዱት እንደሆነ ነገረኝ፡፡ እርፍፍፍፍፍፍ አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው አለ!! የፀረ ሙስና ኮሚሽን ስራ አስኪያጅ የሙስና ልማት አስኪያጅ ሆኖ ተገኘ፡፡ ጉድ አትሉም!! ሰዐቱ 10:30 ገደማ ደርሷል የደጋማዋ ደሴ ብርድ ከንፋስ ጋር እያፉጫጨ ነው፡፡ ከዛ በኀላ መቆየት አንደ ታይታኒኩ ጄያክ የብርድ ሲሳይ መሆን ነው ብዬ ወደ ወደ ኮምቦልቻ መሄድ ወሰንኩኝ፡፡

የምሽቱ ግር ግር ደሴ ላይ ደርቷል የደሴ ውብ ቀዘባዎች ወ ሸበላዎች ባስፓልቱ ላይ ይገማሸራሉ፡፡ የሸርፍ ተራ ወዝ አደሮች ጥፍንግ ቦንዳ ተሸክመው መንገድድድድድድ እያሉ እየጮሁ ይሮጣሉ፡፡ ወያላው ይጮሀል ፣ የመኪናው ጡሩንባ ያናፋል.... እኔ የሳምንት ልፋት ፣ ብክነት ፣ ቁጭት ፣ ብስጭት አዝሎኝ ወደ መናሀሪያ እራመዳለሁ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር የታክሲውን ሻተር ከፍቶ አንዱ ረዳት ኧኧኧ ቧንቧ ውሀ ነህ? ያለኝ፡፡ አይደለሁም ብዬው አለፍኩ፡፡ ሌላኛው እረዳት ፀጉሩን እየገመደ ኧኧኧ አባት አራዳ ነህ አለኝ፡፡ ዝም ብዬው አለፍኩ፡፡ እኔ ለራሴ ደክሞኛል ምን ይጨቀጭቁኛል ጃል!! ኧኧኧ አራዳ ነህ ብሎ ደግሞ ጠየቀኝ፡፡ " አሁንም ዝም" ሰውዬ ጆሮ የለህም እንዴ? አራዳ ነህ ወይይይይይ??? ያ...ረቢ ኑባሲ!! ሰውዬው የሚፋታኝ ነገር አይደለም፡፡

መለስኩለት............አይ ፋራ ነኝ፡፡


ህህህ አበቃ፡፡


@wegoch
@wegoch
@wegoch
Forwarded from ❀ርብቂ Ribki Photography (Ribka Sisay)
ያ ደግ ከመወለዱም በፊት በፅልመት ነበርን።

ሲወለድም የእልልታችን ድምፅ ሻክሮ ነበር።

ፍንደቃችንም ተቀዛቅዞ። ንጉሳችንም ደነበረ።

ጨቅላዎቻችንን ደጉን ለመጉዳት ሲል ቀጠፈ።

ከግዜያት በኋላ ግን ከደጉ የተሻለ ደስታ አልነበረንም።

ባለፈበት ሁሉ ሳር ቅጠሉ ይቦርቅ ጀመር።

እኛም ስለክብሩ ዳንኪራ ባንረግጥም ስናየው የውስጥ አካላችን ይዘል እና እልልልልልልልል ይል ነበር።

ከተማይቱ በደስታ አቅሏን ስታ ነበር።

ምክንያቱም ደጉን የመሰለ ንጉስ አብሮን ነበርና።

ማንም ሰውም ብቻውን አልነበረም። የሚስቅ እንጂ ከንፈሩን የሚነክስ ሰው አልተገኘብንም።

ፅልመቱም ተገፎልናል።

ስንራመድ እኛን የሚመስል በሄድንበት የሚሄድ በብርሃን የተበጀ የደጉ መልዕክተኛ ይጠብቀናል።

ኦ ደጉ ሆይ ስለተወለድክ አመሰግንሃሁ!

ኦ የደጉ እናት ሆይ እወድሻለሁ !

ኦ የደጉ ተንከባካቢ ሆይ አከብርሃለው!!

.........
የደጉ ጌታችን ልደት መልካም ልብ የምናተርፍበት ይሁንልን!
🤍🤍🤍
......
@ribkiphoto
(ዘመነ ጁንታ በወሎ)

ክፍል 1

ጆሮ የተኩስ እሩምታን ለምዷል ፣ አይን ሬሳ እና ደምን ከቁብ አይቆጥርም ፣ አፍንጫም በየጊዜው የሚሰነፍጠው የባሩድ ሽታ ጋር ተስማምቷል፡፡ከግለሰብ ኪዎስኮች ጀምሮ እስከ መንግስታዊ መስሪያ ቤቶች ሁሉም በየፈርጁ ተበርብረዋል፡፡ ፋብሪካዎች ወድመዋል፡፡ ብቻ ያቺ የወይና ደጋዋ ውብ ኮምቦልቻ እንደ ግንቦት ዛፍ ተራቁታለች፡፡

የወያኔ ጦር (ጁንታ) ወሎን ከተቆጣጠረ በኀላ ከኮሞቦልቻ EDDC (Ethiopia Domestic Distribution Corporation) ዘርፎ የተረፈውን ስንዴና ዘይት ለኮምቦልቻ አቅመ ደካሞች በማከፋፈል ህዝባዊነቱን እያሳየ ነው፡፡ ህህህ አይ ጁንታ!! እርዳታውም ተጠቃሚ የሚያደርገው ሴቶችን እና አቅመ ደካሞችን ብቻ ነው፡፡

በህጉ መሰረት ተረጅ አቅመ ደካማ ሴቶች ከካሜራ እና ከክላሽ ፊት መደዳውን ተኮልኩለዋሉ፡፡ የርዳታው አስተባባሪ ታጋይ ኪሮስ አብረሀ መዝገብ ይዞ ትግረኛ ይሁን አማረኛ በማያስታውቅ ቋንቋ ስማቸውን እየጠራ እርዳታውን እያጋፈረ ነው፡፡ በመሀል አንዳንድ የሙስሊም ስሞችን ሲጠራ ጓያ እንደሰበረው ሰው ይወላከፋል፡፡

ልክ እንደ አብዱ ዛራቅ😜

ከዚህ በታች ስማችሁን የሙጠራችሁ ሰዎች ቶሎ ቶሎ አቤት እያላችሁ ወደዛ እለፉ፡፡ ብሎ ወደ ስንዴ እና ዘይቱ ክምችት ሌባ ጣቱን ቀሰረ፡፡
ወይዞሮ ዘይነባ???
"አቤት"
እለፊ፡፡
ወይዘሮ የዝናሽ???
"አቤት ጌታዬ"
እለፊ፡፡
ቀጠለ.....ወይዞሮ ነፊሳ???
"አቤት" ቀጠን ያለ የወጣት ሴት ድምፅ ነው፡፡ ካቀረቀረበት መዝገብ ቀና ብሎ አያት፡፡ ዋይ!! አንቺ ዎጣት አይደለሽ እንዴ? ምነው ሂደሽ ካንዱ ሱቅ የማትዘርፊ??? በይ አሁን ሳልቶክስብሽ ከዚ ጥፊ!! አለ በ11 ቁጥር ምልክት የተቀነደበ ቅንድቡን ከፍ ዝቅ እያደረገ፡፡
ከዛም ወደ መዝገቡ ተመለሶ..... መጥራቱን ቀጠለ፡፡
ወይዞሮ ፍሬ ወይኒ???
"ዝምምምም" መልስ የለም፡፡ ከንደገና ፊደል እየቆጠረ በሎህሳስ ድምፅ "ፈ...ር...ሒ...ን" ብሎ አስተካክሎ አንብቦ "ዋይ ፈርሂን ነው እንዴ የሚል"..... ወይዞሮ ፈርሂን? ብሎ ተጣራ፡፡
"አቤት አለሁ...አለሁ" ብላ ወደ ዘይት እና ስኳሩ ስታልፍ...ቆይ ቆይ ሙን ያስቾኩልሻል? ቆስ ቦይ እስኪ፡፡
እእእ ስሙሽ እንደ ኮንክሪት ሙሽግ አስቾጋሪ ነው፡፡ ፍሬ ወይኒ ብለሽ የማትቀይሪ ለምድን ነው??? ብሎ ትዕዛዛዊ ምክሩን ሰጠ፡፡ እሺ ጌታዬ እርሰዎ እንዳሉት ይሆናል ብላ መንገዷን ቀጠለች፡፡
እሱም ስም ጥሪውን ቀጠለ...እሺ ወይዞሮ ፏጥማ? ወይዞሮ ፏጥማ?
እድሜያቸው የገፋው እማማ ፋጡማ በሰለለ ድምፃቸው "ለበይክ ጁንታው" አሉ፡፡ የተሰበሰበው ጀማ ግማሹ በድንጋጤ ነፍሱ ባፉ ሹልክ ልትል ደርሳለች፡፡ ከፊሉ ደግሞ በማማ ፋጤ የድንገቴ ቃል የሳቅ ሳግ ተናንቆታል፡፡
ዋይ!! ......ቀና ብሎ አይኑን እያጉረጠረጠ ከፍ ዝቅ አድርጎ አያቸው፡፡ እርሶ ሊረዱ መተው ጁንታ ይላሉ እንዴ???
እንግዲያ ምንዲን ነው የሚባለው እንቶ?? ብለው ጥያቄያዊ መልስ መለሱ፡፡ ዋይ ጁንታ ማለት እኮ ስድብ ነው፡፡ አሁን ብቶኩሱብሁ የማን ያለህ ሊሉ ነው? አለ፡፡ ተግሳፃዊ ቁጣ ጋር፡፡
መገን የኔ ነገር!! በቴሌቢጅን ጁንታ ቲሉ ብሰማ እኮ ነው ጁንታ ማለቴ፡፡ ሲ...ቆይ ታዳ ጁንታ እሚባሉት ማንኞቹ ናቸው አሉ፡፡ አጭር ምርኩዛቸው ላይ አገጫቸውን አስደግፈው ግራ በመጋባት፡፡ ጁንታ ማለትማ እኛ ነን፡፡ ግን እኛ አይደለንም፡፡ እኛ ለነፃነት የምንፋለም ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ነው የምንባል፡፡ በሉ ካሁን በኃላ ጁንታ እንዳይሉ ወደዛ ይለፉ አለ ወደ ስንዴው ድርድር ቀኝ እጁን እያወናጨፈ፡፡ እሺ አፉ በለኝ ጋሽ ጁንታ ብለው ጁንታነትን ጋሼ የሚል ማዕረግ ጨምረው በድጋሜ ጠሩት፡፡ ያኔ እንደ ምጥ ሳቅ እያማጠ የቆየው ጀማ አሽካካ "ሀሀሀሀሀሀሀሀ" ታጋይ ኪሮስም ሳይቀር በእማማ ፋጤ የዋህነት አብሮ ሳቀ፡፡ ሳቁ ጋፕ ሲል መልሶ ፊቱን ቋጠረና መጥራት ጀመረ፡፡
እሺ እንግዲህ...ፀጥታ ይከበር፡፡ እእእ ወይዞሮ ካሚል ሲራጅ??? ወይዞሮ ካሚል ሲራጅ?? "አቤት" ከሰልፈኞቹ መሀል ጎርነን ያለ የወንድ ድምፅ ተሰማ፡፡ ዋይ....እኖዚ ሰዎች ምን ኖክቷቾዋል፡፡ አንተ ዶግሞ እዚህ ሙንድን ነው ሙትሰራ? እኛ ዎንድ ሞች ጠራን? የሴቶች መረሀ ግብር አይደል እንዴ??? አለ እንደ ሀምሌ ደምና ፊቱን አጨፍግጎ፡፡

አቶ ካሚል መለሰ.....ኧረ ጌታዬ እናንተ ከመጣችሁ በኀላ ምን ወንድ አለ??? ጨርሰን ሴት ሁነናል እኮ፡፡

"ሀሀሀሀሀሀሀ" የእድምተኛው ሳቅ ድጋሚ አስተጋባ፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii

#በመሊኩ [ MAJNUN ]
Forwarded from ❀ርብቂ Ribki Photography (Ribka Sisay)
ልጄ ሆይ የእውነት ከምወድህ በላይ አስበልጬ ራሴን የውሸት እወደዋለው።
አሰፍስፈው ለሚጠብቁኝ መካን ጥንዶች በገንዘብ እቀይራቸዋለው። ጥሩ ስለሚንከባከቡክ እና ልብህም ስስ ስለሆነ ቶሎ ችላ ትለኛለህ።
አታስብ መሃል አናትህን መሳም እንደምትወድና ሲደባብሱህ እንቅልፍ እንደሚጥልህ ነግሬልሀለው።
ከእኔ የሆነልህ ይሄው ነው። ይሄንንና ጥሩ ምግብ ንፁህ ልብስ ቆንጆ መኝታም ታገኛለህ።

አደራ ልጄ እንዳየሀቸው ተቀበላቸው። እኔንም እንደ እሩቅ ዘመድ ዘንጋኝ!!
.....
©Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
Forwarded from ❀ርብቂ Ribki Photography (Ribka Sisay)
አደራዬን ከበላው ቆየው! አማቼ ሲያርፉ ልጃቸውን ከእነ ልጇ ተንከባከብ ብለውኝ ነበር።

ሞከርኩ። ግን ከልጆቼ ላስበልጠው አልቻልኩም። እሷንስ እንደሚስት ሾሜያታለው።

አሁን ብበድለውም ብክሰውም ለውጥ አይኖረውም!

የአብራክ ክፋዬ ስላልሆነ ርህራሄ የለኝም!
ወዝ በፊቱ ግጥም ሲል ያንገበግበኝ ጀመር።

እናቱ እሱን እሱን ስትል የእኔን ልጆች ዘንግታለች!

በእጄ ሰበብ ሳይሆን መላ ላበጅለት።
ከተማ እንደደረስን ገብያ መሃል ወስጄ እሰወርበታለው!

ለሳምንት ድምፄን አጠፋና ደውዬ ልጅሽ ጠፋብኝ እርምሽን አውጪ እላታለው!

ትንሽ የሚያሳስበኝ ያን ስትሰማ መነጫነጯ ነው። ለነገሩ ስታኮርፍም ታምራለች!!
......
© Ribka Sisay
.....
@ribkiphoto
ሶፊያ ትባላለች የቀድሞ ፍቅረኛዬ ነበረች። ከተለያየን በጣም ብዙ ጊዜ ሆኖናል። እጅግ ከብዙ ጊዜ በኋላ ተደዋውለን ሻይ እየጠጣን ነው። በጨዋታችን መሃል ድንገት ለምን ግን ያኔ ተውሺኝ አልኳት ። ሳቀች ፤ ስትስቅ አይኗ ይጨፈናል ። ሰላማዊ በሆነ አስተያየት ካለምንም ወቀሳ መልሷን እየጠበኩ እንደነበር የተረዳች መሰለኝ ከሳቋ መልስ "እውነቱን ለመናገር ያኔ መተው ነበረብኝ ፤ ያን ውሳኔ የወሰነችው የድሮዋ ሶፊያ ናት"። አብራሪልኝ አልኳት ከስስ ፈገግታ ጋር ፊቴን አኮስኩሼ "ጭንቅላትህ ምክንያታዊ ሃሳብ አያፈልቅም ነበር ። የማይጥምህን ሃሳብ ፤ ያልወደድከውን አቋም ነፍስህ ተረጋግታ አትሰማም ። አንተ ያልፈለከው ካልሆነ ፤ ነፍስህ ትቅበዘበዛለች ሁሌ ከአንተ የፈለቀ ሃሳብ ትክክለኛ እና አዳኝ ይመስልሃል። Soft dictator ነህ ። አምባገነንነትህ በፍቅር ስለምትሸፋፍነው እና
ያፈጠጠ ስላልሆነ በቀላሉ አይገለጥም ።
ፍቅርህ እጅ መንሻህ ነበር መከራከርያ፤መደራደርያህ፤ማፅናኛህ ፤መፅናኛህ ፍቅር ነበር ። ፍቅር ከእውነት የሚበልጥ ይመስልሃል። አንዳንዴ ፍቅር ፤ አንዳንዴ እውነት እንደየሁኔታው እንደሚበላለጡ አልገባህም ።
በበነነው በተነነው ትቀናለህ ፤ እንዳላየህ የምታልፈው ነገር የለም። ሰው ደሞ ብስለቱ
የሚለካው እንዳላየህ በሚያልፈው እና እያወቀ በሚተወው ልክ ጭምር ነው። ስሜትህን ሆነ አስተውሎትህን አሁንም አሁንም ታንፀባርቃለህ። ከፍተኛ የሆነ Emotional intelligence ይጎልህ ነበር ። በዚህ ሁሉ መሃል አንደ አሁን ብስለት መገለጫ ባይሆን ራሱ በአሁን ማስተዋሌ በጭራሽ አልተውክም ነበር። አየህ ያኔ ሙሉ ሰው ፍለጋ ላይ ነበርኩ። ሙሉ የሚባል ሰው አለመኖሩን ለመረዳት ከብዙ ነፍስ ጋር ተዋሃድኩ ፤ ጉድለት ፤ እንከን ፤ ድክመት መልክ እና ይዘቱን እየቀያየረ ሁሉም ጋር እንዳለ ብዙ ቆይቶ ነው የገባኝ ። ጉድለት ይዞ ምሉዕ ፍለጋ መባተል ያለመብሰል ምልክት ነበር። አለመብሰል ነበር ያዳከረኝ ። ትላንት የገፋሁትን አይነት ማግኘት ቀላል አይደለም ። ሶፊያ እንዲህ አልነበረችም ፤ ጭንቅላቷ ሰልቷል ። እድሜ ይሆን ፤ንባብ ይሆን ፤ ከነፍስ ነፍስ መባተሏ ይሆን ብቻ ሃሳቦቿን የምትገልፅበት መንገድ ጭምር ተቀይሯል ።
ዋነኛ የመለያየት ምክንያት ፍፁም ነፍስ ፍለጋ መባተል ነው። ለድክመቶቻችን ሁሉ ጣት
ቅሰራ እና ማላከክ ፈይዳ የለውም ! አለመብሰል ስንቱን በረከታችንን አሳጣን ።

ቸር ሰንብቱልኝ

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
በጣም "ነበር" ምወዳት


ሰው እንዴት በበአለ ልደቱ በጠዋት ተነስቶ ማልቀስ ይቃጣዋል ። ያውም ወንድ ልጅ ሆኖ ፤ በቃ እንባ እንባ ይለኛል ፤ ልክ አንድ ልጇን እንዳጣች እናት ወገብህ ላይ ነጠላህን አስረህ ፣ ቃላት እንደጉድ እያዥጎደጎድክ እሪሪሪሪሪሪሪሪሪ በል ይለኛል ። ግን ማልቀስ እንዴት ነው? ፣ እንባስ አይንን ከሚያክል ግድብ እንዴት ነው አምልጦ ሚወጣው? ፣

ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም ይባላል ፤ ከልቤ ያለቀስኩበት ጊዜ አስታውሳለው ፣ ከአይኔ እንባ የፈሰሰበትን ጊዜ ግን አላስታውስም ፤ታዲያ እኔ በጨጓራ ነው እንዴ ምኖረው? (ምናልባት ለመጨረሻ ጊዜ ያለቀስኩት ይቺን አለም ስቀላቀላት ሳይሆን አይቀርም)


ያዘንኩባቸው ጊዜያት ግን አሁን ድረስ ሳስታውሳቸው እንዳዲስ ያሳዝኑኛል ፤ ማልቀስ ግን አልችልም ፣ በቃ አልችልም ፤ ውሀው እንደ ደረቀ ዥረት ፣ የኔም የእምባ ቧምቧ ደርቋል ፣ ልቤ በቢላ እንደተወጋ እየደማ እንኳን አይኔ ቅርር እንኳን አይልበትም ፣ ምን አለመታደል ነው ፣ ከአበቦች መሀል አበባ ሆነህ ሳለ እንደ እሾህ መታየት።

ሰው በሙሉ የሀዘኑ መግለጫን እንባ እያደረገ የኔ አይነቱ በነሱ ፊት አረመኔ ድንጋይ ተደርጎ ይወሰዳል። ስንት አዞ ባለበት ያንተ እንባህ ስላሎረደ ብቻ አውሬ ተደርገህ ትቆጠራለህ።

በጣም ነበር ምወዳት ፣


ስለምታምነኝና ስለማምናት ሌሎች ከሚወዷት በላይ እወዳት ነበር። ጓደኝነት በመተማመን ላይ ሲመሰረት ከምድር ከፍ ይላል ፤ መተማመኑ ሲቋረጥ ደግሞ ጓደኝነቱ እንዳይተርፍ ሆኖ ከተሰቀለበት ይከሰከሳል።

የአንድን ሰው እምነት ሰብረህ ከምትጎዳው በላይ ፣ እምነቱን እየጠበክለት ያ ሰው እምነቱን እንደሰበርክበት ሲያስብ የምትጎዳው ጉዳት ይበልጥ ያቆስላል። ከዛ የሚከፋው ደግሞ ዳግመኛ ሌላ ሰው እንዳያምንብህም ፣ እንዲያምንብህም ማድረግ እንዳትችል ያደርግሀል።

በጣም ነበር ምወዳት ፣


"ከልቤ አምንህ ነበር " ነበር ያለችኝ ። የቱ ጋር እንደዋሸዋት አልገባኝም ። እኔን ግን ምን ያክል እንደጎዳችኝ አልገባትም። በ"ነበር " ውስጥ "ከዚ ቡኋላ አይኖርም" የሚል ቃል በውስጡ እንዳለ አልገባትም።
በእርግጥ ላይኖርም ይችላል ምክንያቱም እኔ አሁንም እወዳታለው ግን.....


በጣም ነበር እኮ ምወዳት


"የእውነትህን ስትምል በማነው ምትምለው?" ብላ ጠየቀችኝ
"የማያምነኝ አይመነኝ እንጂ በማንም አልምልም ፣ ግን ላንቺ በእናቴ ሞት እምልልሻለው" ነበር ያልኳት

ለማንም እኮ በእናቴ ምዬ አላውቅም ። ደስ የማይላትን ነገር ላላደርግ 'እናቴ ትሙት' ብዬ ነበር የማልኩላት። እና የትኛው ቃል ከብዶኝ ነው እናቴ እንድትሞት ምፈቅደው?

በፍፁም ቃሌን አላጠፍኩም ፣ ከዛም ብሶ ውሸታም ቀጣፊ እስከሚያስብለኝ ድረስ መካዴን አደለም ሰው ሆኜ እሬሳ ብሆን እንኳን እንዴት አይገባኝም።

በጣም ነበር ምወዳት

"እንዴትም ብንጣላ አኮርፍሽ ይሆናል እንጂ አልለይሽም" ብዬ ቃል ገብቼ ነበር።
ግን ይሄን ቃሌን እንዳልጠብቅ ቃሉን የማይፈፅም ከንቱ ሰው አደረገችኝ ፣ ማነው አላምንህም እየተባለ እታመናለው የሚል?

በሁለት ባላ እንደተወጠረ ገመድ ሆኛለው ፣ አንደኛው ቃሌ አንዱን እንዳፈርስ ይገፋፋኛል ፣ አንደኛው ደሞ ቃሌን እንድጠብቅ ያስገድደኛል ።

መተውም አለመተውም ግዴታ ሲሆን ከምጥ የከፋ ምጥ ይሆናል። ልክ መውለድም አለመውለድም የመጨረሻ ምርጫ ሲሆን ፣ ልክ ጥፍርህን በፒንሳ እየጎተቱ ' ድምፅህን እንዳታሰማ' እንደመባል አይነት ስሜት ላይ ገብቻለው።

በጣም ነበር ምወዳት

ከዚ ቡኋላ አምንሀለው ብላ በእናቷ ብትምልልኝ እንኳን እንደምታምነኝ አላምናትም ፤ መፅሀፍ ቅዱስ ብትመታልኝ እንኳን በፍፁም አላምናትም ፤ ልክ ሳይተማመኑ እንደሚኖሩ ሁለት ሌቦች መኖርን እመርጣለው ፤ ግን በማንም የማይተካ ልቤን ከሷ ውጪ ለማንም አልሰጥም ፣ ይሄን ደሞ ማንም እንዲያምነኝ አልሻም ፤ ብቻ ግን......


በጣም እወዳት ነበር ..........................

ወደፊትም መውደዴን ሳታምነኝ እወዳታለው።

ነገ ሁሉ ዛሬ መሆኑ አይቀርም ፣
ዛሬ ሁሉ ደሞ ትናንት መሆኑ የማይቀር ነገር ነው።

(ቤካ)
@wegoch
@wegoch
@wegoch
Forwarded from ❀ርብቂ Ribki Photography (Ribka Sisay)
የመንፈስ ጭሰት ታውቃለህ? ጨሻለው!

ብዥዥዥ እሽክርክርክር ቅብዥርዥርዥር ቅብጥርጥርጥር ያደርገኛል!

አሁን አንተ ራሱ ታወዛግበኛለህ ስታወራ አትሰማኝም!!
ዝም ስትል ግን ትጮኽብኛለህ!!
....
©Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
-ፅልመት-

ክፍል 1

እንደው ለበደለኩት ሲቀጣኝ እንጂ ካልጠፋ መንገድ በኮሮኮንች ምን ወሰደኝ? እንደው በድፍረት ለሰራሁት ጥፋት ቅምሻ ቅጣት ብሎ እንጂ ለምን በኮብልስቶኑ ታጠፍኩኝ ቀጥታ
መሄድ ስችል ? ድንገት መተጣጠፌ የድካሜ ሰበብ ሆኖኝ ጉሮሮዬን የሚያረሰርስ መጠጥ ፈለኩ በአንዱ እጥፋቴ ቅጽበት ሰዋራ ስፍራ ላይ ያለች ሆቴል አየሁ ወደ ሰዋራዋ ሆቴል ገባሁ
አንዱ ጥግ ቁጭ ከማለቴ ቅፅበት አስተናገጁ ሲወረወር መጣ ቀዝቃዛ በደሌ አዘዝኩ ድንገት የሆቴሉን ድባብ እና ስፋት በዓይኔ ስቃኝ ፤ ስመትር የማቀውን ባለኮፍያ ብራቡሬ ሹራብ የለበሰ ጀርባ አየሁ ሹራቡንም ጀርባውንም አውቀዋለሁ ። ግንባሬን ቁጥር ፤ አይኔን
ትኩር አድርጌ ተመለከትኩ ። ሹራቡን የለበሰችው ልጅ ስታሽካካ ከመስማቴ በፊት ነበር ሚስቴ እንደሆነች ያወኩት ። የሚስቴን ሹራብ ለብሶ እዚህ ሰዋራ ስፍራ የመጣው ማነው ? የሚስቴን ጀርባ የለበሰው ማነው? የሚስቴን ሳቅ አይነትስ የሚያሽካካውስ? አብሯት ያለው ጎረማሳ እያሳቃት ፤ አንገቱ ስር እየወሸቃት ነው ። ሁሉ ነገራቸው ሌላ ነገር እንዳዘለ ያስታውቃል።
አለም ሚዛኗ ተዛባባኝ ፤ ወበቀኝ ፤ ጥሜ ጠፋ ። ግንባሬ ሲወረዛ ታውቆኛል ።ሰውነቴ
ልፍስፍስ አለብኝ ። ሰው ለካ ዱብ'ዳ ሲገጥመው ይሰበራል እንጂ ያዙኝ ልቀቁኝ አይልም ። ወንበሬ ላይ እንዳለሁ እንስ አልኩ ፤ እንደው ኩርምት
የሚስቴን እኔ ራሴ የገዛሁላትን ሹራብ አይቼ ። ስንት ቀን ያሸውትን ፤ የተደገፍኩበትን ፤ከሰውነቴ ጋ የተፋተገውን ጀርባ በቅፅበት ብለየውም አላመንኩም ። ሳቋን የሰማው ጆሮዬን ማመን አልተቻለኝም ። የሆነ ሰው ሹራቧን ፤ ጀርባዋን ሳቋን ተውሷት መሆን አለበት! ስልኬን አውጥቼ "ቤቱሻዬ " ብዬ ሞባይሌ ላይ save ያደረኩትን የሚስቴን ቁጥር ደወልኩበት የሚስቴን ሳቅ፤ ጀርባ ፤ሹራብ የያዘችው ሴት ስልኳ ጠራ ፤ ከቦርሳዋ ስታወጣው እንቅስቃሴዋ ነገረኝ ወይ ገመትኩ ፤ ግን አልተነሳም ። ድብዝዝ አለብኝ ። መላቅጡ የጠፋ ውጅንብር ውስጥ ሰመጥኩ ፤ ተምታታብኝ ፤ እሪሪ ማለት መጮኽ ፈለኩ ግን ደግሞ አቅም አጣሁ እኔ ስልኳ ላይ ከደወልኩላት እሷ እኔ እንደደወልኩ ካወቀች እና ካላነሳች ቀጥሎ ለአስተናጋጁ ምልክት የሰጡት ይመስለኛል ቀልጠፍ እያለ እነሱ ጋ ሲሄድ አየሁት
ገባኝ ካለወትሮዬ በዚህ ሰዓት መደወሌ ቢፈልገኝ ነው ብላ ተለይታው ልትደውልልኝ ነው ። በቃ አስቻኩላው ነው አልኩ ። አስተናጋጁ ተመልሶ መጣ ፤ መልስ ይዞላቸው የመጣ ይመስለኛል።
ተነሱ ፤ ሲነሱ እንዳያዩኝ ፌቴን ወደ ሌላ ቦታ አዞርኩ አላስችል ብሎኝ ስዞር ፤ ይመጣሉ ብዬ በጠበኩት ተቃራኒ ፤ በጀርባ በኩል ገቡ ። ላመል
ያክል ከጎረምሳው ጋ አብራዋ ያለችው ወደ ጀርባውን በአይኖ ገልመጥ አድርጋ ሄደች።
ሌባ ደምቡ ነው ከመኖርያ ስፍራ ርቆ ሰዋራ ስፍራ ይገባል፤ ሹርብ ይለብሳል ጥግ ላይ ጀርባውን ሰጥቶ ይቀማጣል ሲንቀሳቀስ ጀርባውን አያምንም ገልምጥ ያደርጋል ። አዞዞሯ ደመነፍሳዊ ስለነበር አላየቺኝም
አስተናጋጁን ጠራሁት ። አንድ ያልጠጣሁት በደሌ ፊቴ እያለ ሌላ አንድ አምጣልኝ አልኩት ፤ ሊሄድ ሲል በዚህ ጋ መውጫ አለ እንዴ አልኩት ፤ ተያይዘው በገቡበት እጄን እያመላከትኩ ፤ የለም አልጋ ክፍል ብቻ ነው በዚህ ጋ ያለው አለኝ።
ደረቴ ስር ሲሸቀሸቀኝ ተሰማኝ ፤ አጥወለወለኝ ። ብዙ ጥያቄ መጠየቅ ፈልጌ ነበር ። አዘውትረው ይመጣሉ ወይ? ታቃቸዋለህ?? በየ ስንት ግዜ ፤ ስንት ሰዓት ላይ?? ማለት ፈልጌ ነበር አቃተኝ ።
ዝም ብዬ ትኩር ፍዝዝ ብዬ ሳየው ከአፉ እንቅስቃሴ በቀር የሚለውን አልሰማ ስለው ሄደ ።
አለም የምናስበውን እና የሆነብንን ትመስላለች ። አሁን ከሰዓት በፊት የነበረችው አለም ሰላም ነበረች ከመቼው አዘቀዘቀች ። ከመቼው ጤናዬ ታወከ ። ሁሉን ማመን አቃተኝ ፤ የመጨረሻ ብዬ ለአስተናጋጁ በምልክቴ ሂሳብ አልኩት
ሂሳብ ይዞ መጣ እና ድፍን ሁለት መቶ ብር ሰጠሁት ፤ በቶሎ ዘጠና አምስት ብር ይዞ
ተመለሰ ። መልሱን ያዘው አልኩት ። እጅግ አመሰግኗኝ ሊሄድ ሲል ። እንደምንም ራሴን አረጋግቼ ፤ እዛ ከልጅቷ ጋ የተቀመጠው ልጅ ቀጥሮኝ ነበር ፤ እመጣለሁ ብሎኝ ቀረ አልኩት ፤ ዝም ብሎ አየኝ ፤ አዳር ነው እንዴ አልጋ የያዘው አልኩት ፤ አይ አረ ጊዜያዊ ነው አለኝ!!
ፊቴን አዞርኩ ። በዘጠና አምስት ብር ጉርሻ ሚስቴ እንደምትማግጥብኝ አረጋገጠልኝ። በስተመጨረሻ አለማመኔ ድል ተነሳ !
አይኔ የሆነውን ሁሉ ክስተት ሲያስተውል ቆይቶ አለቀሰ። እምባዬን በጉንጬ በኩል
ወረወረው እስከዛሬ ከሷ ጋ እያበረ ከስሜቴ ጋ እየተማከረ የሚወዳት የሚሳሳላት የማይዋሻት አይኔ አለቀሰባት ። ነገዬ ፤ ኑሮዬ ፤እምነቴ ፤ ትዳሬ እጣፈንታዬ ገብቶት አይኔ ብዙ እምባ አመነጨ ።
ባልተከፈተው ቢራ አጠገብ የተከፋ ልቤን አቅፌ ኩርምት እንዳልኩ አንገቴን አቀርቅሬ ድምፅ ሳላወጣ እየተንሰቀሰቅኩ አለቀስኩ ።

ይቀጥላል

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
የመጽሐፍ ውይይት
በ ብሄራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ

መንደሪን መንደሪን
ደራሲ: ምግባር ሲራጅ

@getem
"ድምቀት ወ ፅልመት"



አርብ 'ለት ነበር ፣ 12:00 ሰአት አካባቢ፣ ቀኑ ቀን አልመስል እያለኝ ወደቤቴ ለመሄድ መንገድ ላይ ሳለው አብዶ ይሁን ፣ እያበደ ይሁን ግራ የሚያጋባ ሰው ድንገት በመንገድ ላይ ያገኘኝና ልክ የዘመናት ጓደኛው እንደሆንኩ ያክል ያወራኝ ጀመር።

" አየሀት ያቺን ጀንበር? ....... ፣ ገና እያጎጠጎጠች ያለች ቆንጆ ሴት ትመስላለች ፣ ልክ እንደ አንዲት ሴተኛ አዳሪ ፣ ልክ እንደ አዲስ ፍቅረኛሞች....፣ ግን ፈጣሪ ለምንድነው ይሄን ያክል የምታሳሳ ልጅ ያስመሰላት?............. ግን አንተ ምን ይታይሀል?....... " አለኝ ። እየተከተለኝ ይሁን መንገዳችን ተገጣጥሞ በምታጠፍበት እየታጠፈ ፣ ጀንበሯን አዘቅዝቆ እያየ ይጠይቀኛል።

" እኔ እንኳን ስራ ፈትቼ እሷን የማይበት ጊዜ የለኝም " አልኩት ። እንዲተወኝ ፈልጌ እንጂ ሳላያት ቀርቼ አልነበረም።

" ተፈጥሮ ለማን የተፈጠረ ይመስልሀል ?"

" ያው ለራሱ መሰለኝ " አልኩት ጥያቄው ስላልገባኝ ።
" ተፈጥሮ ሁሉ ለሌላ ጠፈጥሮ ነው የተፈጠረው ፤ ሰው እንኳን ለሌላ ሰው ነው የተፈጠረው " አለኝ አይኑን ከጀንበሯ ሳይነቅል።

"እና ምን ነበር ይታየኛል ያልከኝ" አለኝ ምንም እንዳላልኩት እያወቀ።

" እኔ እንኳን ቆንጆና ደማቅ ጀንበር ናት ምትታየኝ" አልኩት ፣አስተውዬ ለማየትም አልሞከርኩም ምክንያቱም ሰውየው እብድ ይሁን ጤነኛ እርግጠኛ አልነበርኩም።

"አንድጊዜ ቆንጅዬ ልጅ መንገድ ላይ አየሁና መከተል ጀመርኩ" አለኝ ያቺ ቆንጆዋ ልጅ ጀንበሯ አንደሆነች ያክል ወደ ጀንበሯ እያፈጠጠ።

"እሺ......." አልኩት

"ተከተልኳት ተከተልኳት ተከተልኳት....."

"እሺ ከዛስ.." ደገምኩት

"ተከተልኳት ተከተልኳት ተከተልኳት...."
ሳቄ እንደ ትንታ አመለጠኝና ወዲያው ዝም አልኩኝ።

"ተከተልኳት ፣ እንደዚ ቆንጆ ሆና ግን ማንነቷን የሽማግሌ ኪስ ወስጥ አገኘዋለው ብዬ አላሰብኩም ነበር" አለኝ እንደማዘን ብሎ።

"ሌባ ነበረች?"

" ሌባ ህሊናውን ይሸጥ ይሆናል እንጂ አካሉን አይሸጥም ፣ ይቺ ቆንጆ ሰው....ነቷን ሁሉ ነው የሸጠችው ፣ እኔ እሷን መከተሌ ድካም ነው ያተረፈልኝ ፣ አንተም የጀንበሯን ውበት ብቻ ማየትህ የት እንደሚያደርስህ አላውቅም " አለኝና ለትንሽ ጊዜ ዝም አልን። ግን ምን ማለት እንደፈለገ ማወቅ እንዳለብኝ ተሰማኝ።

"አንተ ምንድን ነው ሚታይህ?" አልኩት።

" ታሳዝነኛለች" አለና እንባው እንደቀልድ መውረድ ጀመረ "በጣም ታሳዝነኛለች ፣ ስልጣኑ ቢኖረኝ እንደዚ እንዳማረባት ዘላለም ባቆያት ደስ ይለኛል ፣ ልብ ብለህ እያት ፣ መንገዷን ተመልከት ፣ ቅድም ስንገናኝ የነበረው ውበቷ አሁን የለም ፣ አሁን ያለው ውበቷ ከደቂቃዎች ቡኋላ አታገኘውም ፣ መንገዷም መጨረሻዋም የከፋ ነው " አለና ጣቱን ወደጀንበሯ እየጠቆመ ፣
" አንቺ ጀንበር ተጠንቀቂ ፣ ቀን ወደነበርሽበት ተመለሺ !!" አለና ሳይሰናበተኝ በመጣንበት መንገድ ተመለሰ።

ምን ሊነግረኝ ፈልጎ ነው? ፣ ማንስ ነው የላከው ?፣ ጀንበሯ ማነች? ፣ ቀንስ ምን ነበረች ?፣ አሁንስ ምን ልትሆን ነው? እያልኩኝ እራሴን ስጠይቅ ያቺ ገና እያጎጠጎጠች ያለች ቆንጆ ሴት የምትመስለዋ ፣ ልክ እንደ አንዲት ሴተኛ አዳሪ የምትመስለዋ ፣ ልክ እንደ አዲስ ፍቅረኛሞች የምታስቀና የነበረች ጀንበር አሁን የለችም ፣ ምድሪቱን ጨለማ ወርሶታል ፣ እኔም ከነጥያቄዎቼ ወደ ቤቴ ገባሁ ።

(ቤካ)

@wegoch
@wegoch
@paappii
-ፅልመት-

ክፍል ሁለት

ከቤተልሄም ጋ በጋራ ወደ ቀለስኩት ጎጆ ሄድኩ ።
ሳሉ አምላክ እንዳየቺኝ ሰላም ሰሌ? አለቺኝ ፤ በስሱ ሰላም ሳሉ ብዬ አጉተመተምኩ። ሳሉ እቤት የምታግዘን አጋዣችን ናት። ቤቴ ያ ቅድም የወጣሁበት ቤት አልመስልህ አለኝ ። አስጠላኝ። ሳሉ "ምነው አመመህ እንዴ" አለቺኝ ምነው? ስላት ፊትህ ጥሩ አይደለም አለቺኝ "አዎ አሞኛል" አልኳት ቀና ስል የሰርጋችን ፎቶ ግድግዳ ላይ ተለጥፎ አየሁት ። ትክ ብዬ ስመለከተው ከግድግዳው ላይ አውረደህ ሰባብረው አለኝ 'ማደጋችን የሚለካው የምንፈልገውን ሁሉ ባለማድረግ ነው' ቀጥታ መኝታ ክፍል ሄጄ ተኛው ። እኔ ገብቼ ጋደም ካልኩ አንድ ሰዓት ቆይታ
የድሮ ሚስቴ ገባች መቼም የድሮ ሚስቴ ነች ። የተፋታነው ቅድም ሆቴል ውስጥ ያን ክንውን ካየሁ በኋላ ነው። አልመጣም እንዴ ሰሌ ስትል ሰማኋት ፤ ድምጿ ለካ ያስጠላል ። ነገሩ ከሃዲ ደሞ ምኑ ያምራል ? ትንሽ አሞታል አለቻት ። ምነው ጠዋት ደና አልነበር እያለች ወደ መኝታ ክፍላችን ስትመጣ ኮቴዋ ይሰማል ። እንደ ተኛው መሰልኩ። ህመማችን የሚባባሰው የበሽታዎቻችን ምክንያት እናክምህ ሲሉ ነው።
ወዳጃችን ሲያቆስለን ህመማችን የሚበረታው እንደሚያስብልን ማስመሰሉ ስለማይቀር
ነው። ብርድ ልብስ ውስጥ ተጠቅልዬ ማሰብ ማቆም ያልቻልኩት ነገር ቢኖር ክህደቷን ነው ።
ሰው ከካደው ጋ እንዴት ኑሮን ይገፋዋል ። አለማወቅን የመሰለ ነፃነት የት አለ ?! ዛሬ እዛ
ሰዋራ ሆቴል ባልገኝ መቼ ህይወት ይገለበጥብኝ ነበር??? እስከዛሬ አልፎ አልፎ በኔ ጉትጎታ ብቻ የምንዋሰበው ለካ ውጪ ከማንም ጋ ስለምትጋደም ነው። ለካ እስከዛሬ ለቅሶ ገለመሌ እያለች አምሽታ የምትመጣው የትም ስትሸረሙጥ ነው ! ጭንቅላት አንዴ አይመረዝ አዕምሮ ውስጥ የሚመጣ አንድ መልካም ጥንጥዬ ነገር እንኳን
አይኖርም ። በጣም ሲመሽ ሰሌ ሰሌ እያለች ቀሰቀሰቺኝ ፤ ቀና አልኩ ፊቴን ስታየው ደነገጠች ፤ ድምጿን ጮክ አድርጋ እንዴ ምነው በጣም አመመክ እንዴ ምን ነው?? ዝም ብዬ ትክ ብዬ አየኋት ። ፊትህ ጠቁሯል ፤ አይንህ ብር ብሏል፤ በጣም አልቦሃል ፤ ምን ሆንክ? ሃኪም ቤት እንሂድ
እያለች ብዙ ቀላበደች ። ፊቴ እንደተጨማተረ ፤ በአስለቀሰችው አይኔ ትኩር ብዬ እያየኋት ደህና ነኝ! አልኳት ሁኔታዬን አይታ ይመስለኛል ቃል አልተነፈሰችም !! ፒጃማ ቀይሬ ተመልሼ ተኛው ፤ እንቅልፍ በአይኔ ሳይዞር ፤ በጣም በጠዋት ወደ ስራ ሄድኩኝ ። በዛ ሰሞን አመመህ? ምን ሆነሃል ? ከሳህ የማይለኝ አንድም ወዳጅ ጠፋ ።
የውስጥ ሰላም ሲናጋ ፤ የማይናጋ የሰውነት ክፍል መቼ ይኖራል ። ዘውትር ማታ እቤቴ ስመጣ የማንጠለጥለው አትክልት ፣ ኬክ ፣ ዳቦ እርግፍ አድርጌ ተውኩት ። እንደበፊቱ ልጄን ማጫወት እያንዳንዷን እንቅስቄሴ መጠየቅ አቆምኩ ።
ለካ ሰነፍ ሴት የሞቀ ቤት ታቀዘቅዛለች። ቤተልሄምን አላኮረፍኳትም ፤ ሰው የሚኳረፈው ጭላንጭል ፍቅር ሲኖር ነው። ስታወራኝ
እመልስላታለሁ። ቤተልሄም ምክንያታዊ እንደሆንኩ ስለምታውቅ ዝምታዬን አትንቀውም ።ኮስተር ብዬ ያኮረፍኩበትን ጉዳይ ስናገር ፤ የምዘረዝረው አሳማኝ ምክንያት እንደሚኖር ትላንታችን ምስክር ነው። ምክንያታዊነትህን እወድልሃልሁ ትለኝ ነበር ። እንደምትወደኝ ተጠራጥሬ አላውቅም ነበር አንድ ቀንም !ነፍሴ ተጠይፏታል ። ጎጆ እንደ እምነት አይደለም በአንድ ለሊት አይደረመስም ። ቤቴ ላይ
የማፈሰውን ትኩረት እርግፍ አድርጌ ተውኩት ። ስለወጪ ከሳሉ ጋ ብቻ አወራለሁ። ቤቴ በቶሎ ላለመግባት የድሮ ጓደኞቼን ማሰባሰብ እና መጠጣት ጀመርኩ። አንድ ቀን የያሁት ነገር ኑሮዬን ቀለበሰው ። የነበረኝን ፍቅር ደረመሰው ። ፍቅር እንደዚህ ማያያዣው ስስ ነው??
ስለ አለም የነበረኝ ምልከታ ተዛባ ።
እንዲ እየኖርኩ ሳለ አንድ ቀን ወደ ስራ እየሄድኩ የተሳፈርኩበት ታክሲ አቅጣጫ ስቶ ሲበር ይመጣ ከነበረ ዘመናዊ የቤት መኪና ጋ ተላተመ። ከውስጣዊ ስብራት ሳልጠገን ሌላ ውጫዊ አደጋ
ይቀጥላል...

@getem
@getem
@paappii

#Adhanom Mitiku
የጁመዓን ሲሳይ አያውቁም። ዱዐ በማረግ ፈንታ በየጎዳናው ይቅበዘበዛሉ። ከዛ ቅዳሜ ሲሆን አላህ እኔን አይሰማኝም እያሉ ያማርራሉ።

ያ ረቢ ሳይጠይቁ የሚጠብቁህን ምንድነው ምታደርጋቸው? ከእኛ እኩል ነው የምታያቸው?

......
ጁመዓ ሙባረክ💛
...
©Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
@wegoch
Forwarded from ❀ርብቂ Ribki Photography (Ribka Sisay)
ካራማራ ጫፉን አያይዤ ልስፋው?
ካራማራ አናቱን ሻሽ ልደርብለት?
ካራማራ ልቡን በምን ላርስለት?
....
©Ribka Sisay
....
@ribkiphoto
Forwarded from ❀ርብቂ Ribki Photography (Ribka Sisay)
ለመጨረሻ ጊዜ ያቀፍኩት እዚህ በር ጋር ነበር:(
ያቺ ሴትዮ ስለማትወደኝ ወደ ቤታቸው ገብቼ አላውቅም።
ሰላሳ ሶስት ሳምንት ከሶስት ቀን ሙሉ አልደወለልኝም:(
ስለዚህ ንጋት እዚህ እየመጣው እጠብቀዋለው! እዚህ ስውል ያቀፈኝ ያቀፈኝ ይመስለኛል!
የሳቅነው ያስለቅሰኛል! የተደሰትንበት ያናድደኛል!

ቆይ ተስገብግበን ናፍቆት ብንለማመድስ ኖሮ?
ቆይ የማላውቅበትን ጠብቅሃለው ምን አስባለኝ?
ቆይ ምንአባቱ የማይመጣልኝ?
ቆይ ምን አባቱ የማያቅፈኝ?
ቆይ ምናአባቷ ይቺ ሴትዮ ስታየኝ የምታዝነው?
..........
©Ribka Sisay
..........
@ribkiphoto
-ፅልመት-

ክፍል ሶስት

ከአራት ቀን ራስን መሳት በኋላ አንድ ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ ራሴን አገኘሁት። ጭንቅላቴ የእኔ እንዳልሆነ እስኪሰማኝ ድረስ ህመሙ ከብዶኛል ፤ አንገቴን ላዞር ስሞክር ህመም ተሰማኝ ለካ የአንገት ድጋፍ አጥልቄያለሁ ፤ እግሬ በጀሶ ተጀቡኗል ፤ እንደ ቄስ ጥምጣም የዞረው ፋሻዬ ጭንቅላቴን አልብሶታል። ምን በድዬ ነው አካሌም መንፈሴም አንድ ላይ እስኪጨረምቱ የቆሳሰልኩት። እጅግ ተሰቃየሁ ። ምኔን ላስታም ። ቀና ስል ወንበር ላይ ኩርምት ብላ የተቀመጠች የድሮ ሚስቴን ብቻዋን አያታለሁ። ከስሬ አጠፋም ፤ እዛው ነው የምታድረው ፤ የግሏን ስራ ብትሰራም እኔን ለማስታመም የተወችው ይመስለኛል። አይኔን ስገልጥ አጥቻት አላውቅም ሊጠይቁኝ የሚመጡት ወዳጆቼ እንቀየርልሽ ቢሏት ፤ ዶክተሮቹ ቢመክሯት ፤ የድሮ ሚስቴ
አንገቴን በካራ አለች ፤ ከእዚህ ሆስፒታል እሱ ካልወጣ አልወጣም አለች። ፊት አልሰጣትም ፤ አላዋራትም ። እገላምጣታለሁ እቆጣለሁ ፤ ታለቅሳለች። እነጫነጫለሁ፤ አጉተመትማለሁ ፤ አሽሟጣታለሁ ። በጥቂት ወራት ውስጥ ከሰውነት ተራ ወጣች ማንም ሰው ጥሩ ገቢ ያላት ፤ ፋሽን የምታሳድ ፤ ዛሬ የለበሰችውን ነገ የማትደግም ነበረች ቢባል ግነት ይመስላል። ያለን ነገር ጠቅላላ በነበር ተከበበ ። እኔን ሊጠይቁኝ የሚመጡ ሁሉ ከሰውነት ተራ መውጣቷን እያዩ ዞር ብለው እሷን ገስፀው ፤ አፅናንተው ይሄዳሉ ተቆርቆሪነት በወለደው የወዳጅነት መንፈስ ።
አንድ ቀንም ምግብ ብይ ተጎሳቆልሽ ፤ቤት ሂጂና እደሪ ብያት አላውቅም ፤ በወጉ ስትበላም
ስተኛም አይቻት አላውቅም። የሆነ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነሳ የድሮ ሚስቴን ሳያት ማድያት ጀማምሯታል ። ፀጉሯ ተሰባብሯል ፤ ሽበት ጀማምሯታል ፤ የለበሰችው ቱታ ራሱ ተነጫጭቶል ። ስቆጣት አይኗ እምባ ሲቋጥር ፤ ስታጎርሰኝ በክፉ አይኔ ሳያት ፤ የስሜቴን መቆጣት ስታይ እያለቀሰች ነበር
የምታጎርሰኝ ። ከቀናት መንጎድ በኋላ ኩርምት ካለችበት ቦታ ላይ ሸለብ አርጓት ሳያት ያለፉት የሆስፒታል ቆይታችን ትውስ አለኝ ፤ አሞኝ ሳቃስት እሷ ስትርበተበት ፤ በስሜቴ መኮማተር የወረደው
እንባዋ ፤ ለመንካት እንኳ በራቀ መልኩ ገላዬን በፎጣ ስታብሰው አንድ ባንድ መጣልኝ ። በእዚህ ሁሉ ፊት መነሳት ውስጥ ፤ በእዚህ ሁሉ መነጫነጭ ውስጥ ልጃችን ኤዶም ጋ
እንኳን ልሂድ ብላ ከሆስፒታል ጥላኝ ወጥታ አታውቅም ። የሁለታችንም ቤተሰቦች
ባይኖሩም የቅርብ ጓደኞቼ እንኳን እንደር ሂጂ ቢሏት እሱን ትቼ ነው የምትለው ኤጭ
ፍርጃ ነው ለዛች እምነቴን ለበላችብኝ ። ለዛች አይኔን ላስለቀሰችው፤ ለዛች ልቤን ለሰበረችው ፤ለዛች አንገቴን ላስደፋችው ፤ለዛች ሳቄን ለቀማችው ፤ለዛች ቀልቤን ለነጠቀችው፤ ለዛች ቤቴን ላቀዘቀዘችው የድሮ ሚስቴ። አሳዘነችኝ !! ከስንት ወር በኋላ ቤተልሄም አልኳት ደንግጣ አየችኝ

ይቀጥላል ....

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom mitiku
2024/09/23 06:27:15
Back to Top
HTML Embed Code: