Telegram Web Link
የማለዳቹ ይቺን ስሙማ

''በሸርተቴ ሞራል ሰበራ''

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የተገኘ ፁኹፍ ነዉ።
ፀኀፊ :- ኤፍሬም እንዳለ
የፁኹፉ ድምፅ :- ሚኪያስ ልየዉ @Mykeyliyew

(በንባቡ ላይ ስለተጠቀሰዉ የፀኀፊዉ የስም ስህተት በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለኹ ፀኀፊዉ ''ኤፍሬም ስዩም'' ሳይኾን ''ኤፍሬም እንዳለ'' ነው)።

@Wegoch
@wegoch
@wegoch
የታጋቹ ማስታወሻ
(በእውቀቱ ስዩም)
ከፀሀይ በታች አሮጌ ነገር የለም ፤ ፀሃይ ራሷ በየሰኮንዱ ትታደሳለች፤
ከእንቅልፌ ተነሳሁ፤ ተንጠራራሁና አይኔን ባይበሉባየ ጠራርጌ ከእምብርቴ በታች ያለውን ቃኘሁት፤ አጅሬ ከኔ በፊት ቀድሞኝ ተነስቱዋል ፤ የዛሬው ደግሞ የተለየ ነው፤ እስክንድር ነጋ ንግግር ባደረገ ቁጥር ባንዲራ ይዞ ከጀርባ እሚቆመውን ሰውየ ራሱ እንዲህ አይቆምም ! ጠበቆ ጠብቆ ምንም የተዘጋጀለት ነገር እንደለሌለ ቁርጡን ሲያውቅ ተኛ! ምስኪን!
ያልጋ መውረጃ የለህም ? የሚል አንባቢ አይጠፋም!
ሲጀመር አልጋ ራሱ የለኝም ፤ በርግጥ እንደ ጎማ የሚነፋ ፍራሽ አለኝ ፤ የገዛሁት ሰሞን አንዴ ከተነፋ እስከ ሌሊት ሙሉ ያገለግል ነበር፤ አሁን ቀሳ ከወጣሁ በሗላ ግን ወፈርኩ፤” ወፈርኩ” የሚለው ቃል አነሰ ! ስጋየ ገነፈለ ብል ይሻላል ፤ ሁለት የቁም መስታውቶች ገጣጥሜ ካልሆነ በቀር ሙሉ ሰውነቴን ለማየት እያዳገተኝ ነው፤ ለሶስት ሰአት ያክል ከተኛሁበት ተንፍሶ ምንጣፍ ይሆናል ፤ እንደፈረደብኝ ተነስቼ እንደገና እነፋለሁ፤
ቁርስ መስራት ይጠበቅብኛል? ባለፈው “ አንድ ብርጭቆ ሩዝ በሁለት ብርጭቆ ውሃ ለሃያ ደቂቃ ከቀቀሉት ሁለት ብርጭቆ ሩዝ ያገኛሉ “ የሚል አነበብኩ፤ እንደዛ ከሆነ ለምን በደንብ አላባዛውም ብየ አንድ ብርጭቆ ሩዝ ባራት ብርጭቆ ውሃ ቀቀልኩ፤ ከሃያ ደቂቃ በሗላ ሩዝ ጣል ጣል ያለበት ሙቅ ውሃ ጠጣሁ፤
አንድ ቀን ደግሞ እንቁላል ጠበስኩ፤ከዛ ወደ አፍንጫየ አቅርቤ ባሸተው ምንም መአዛ የለውም፤ ትንሽ ቅመም ነሰነስኩበት፤ ይህም ሆኖ አፍንጫየ ላይ አቅርቤ ስምገው ምንም የለም ፤ ወድያው ሼፍ ዮሀንስ ጋ ደውየ የጠቆመኝ ቅመም ችግር እንዳለበት ነገርኩት ፤ “ ርግጠኛ ነኝ ፌስ ማስክህን ሳታወልቅ ነው ያሸተትከው? “ አለኝ፤ ውነቱን ነው ፤ ፌስማስኬን አድርጌ ከመዋል ማደሬ የተነሳ እንደ ፊት ቡግር ሁሉ ማውጣት ጀምሯል፤
ምግብን ሼፍ ዮሀንስ ይስራት! ሲወርድ ሲወራረድ የመጣው ምግብ ስለደበረው እማይሞክረው አዲስ ነገር የለም፤ ባለፈው ሰይፉ ሾው ላይ ከሞሪንጋ ዱቄት ምን የመሰለ ላዛኛ ሰርቶ አስደምሞኛል፤ ይሄ ልጅ በዚህ አይነት ምርምሩን ከቀጠለ ሳያስበው ክትባቱን ሁሉ ሊያገኘው ይችላል፤
ምግብ ሲነሳ የሆነ ነገር ትዝ አለኝ፤ ይዲዲያ የሚባል ዝነኛ ነቢይ ትዝ አላችሁ ? ሚያዝያ ላይ ኮሮና ይጠፋል ብሎ ተንቢዮ ነበር፤ ከዛ ወረርሽኙ እየባሰበት ሲመጣ ሚያዝያ እንዲራዘምለት ጌታን በፀሎት ጠየቀ ፤ በቀደም ቃለመጠይቅ ላይ ምን ሲል ሰማሁት “ መፅሀፍ ቅዱስን በጣም ከመውደዴ የተነሳ አንዱን ገፅ ቀድጄ በልቼ አውቃለሁ” ፤ እምደንቅ ነው ባክህ! እኔ በዚህ ምስክርነትህ ላይ የታየኝ ነገር ቢኖር ለመፅሀፍ ቅዱስ ያለህን ፍቅር ሳይሆን ለምግብ ያለህን ፍቅር ነው፤ ኪሎህ ራሱ ይሄንን ይመሰክራል፤ ለማንኛውም ክንዳችሁ ላይ የመፅሀፍ ቅዱስ ጥቅስ የተነቀሳችሁ ሰዎች ይሄን ሰውየ ተጠንቀቁት !
ለነገሩ ምግብ ላይ እኔም የዋዛ አደለሁም፤ ይሄው ፤ ገና ከምኝታየ ከመነሳቴ የፍሪጁን በር ከፍቼ ቆሚያለሁ ፤ የሚሳዝን አጭሬ ከተፍ አለልኝ!
አንድ ስሃን ሩዝ
ሁለት ሱካር ድንች
ፍሪጄን የሞላው
ይሄን ሁሉ ሲሳይ፤ ከማን ጋራ ልብላው? ☹️

@wegoch
@wegoch
@paappii
ለምሽታቹ ይቺን ስሙማ

''በሸርተቴ ሞራል ሰበራ''
ክፍል ፪

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የተገኘ ፁኹፍ ነዉ
ፀኀፊ :- ኤፍሬም እንዳለ
የፁኹፉ ድምፅ :- ሚኪያስ ልየዉ @Mykeyliyew


@Wegoch
@wegoch
@wegoch
#የእሳት ላይ ቁጥሮች

  ክፍል - ፲

የወይኑ ፕሮግራም ያለቀ ይመስላል ሁሉም አጣጥሞ ጨረሰ ከብርጭቆአቸው የቀረችውን አልኮል ለወይኑ ማወራረጃ እንድትሆን እስከ መጨረሻው ጭላጭ ሁሉም ይጨልጥ ጀመር
ሻርማይኮች ከወይኑ ፍሬ ያልቀመሰ እንደማይኖር አምነዋል ከወጥ ቤት እስከ ተፈላጊው ነጭ እና ጋርዶቹ ወይኑን ቀምሰዋል  በቀዩ ጨርቅ የተጠቀለለውንም መጽሀፍ ከመሬት የሚወድቅበትን ሰአት እየጠበቁ ነው እንቅስቃሴዎች በረድ አሉ ጭፈራ የለሌለው ሙዚቃ ብቻውን በእኩለ ለሊቱ ያስተጋባል
ምድነው....
 አብዛኛው ሰው እራሱን እየያዘ ብቻውን ያወራ ጀመር 
ሰአቱ ደርሷል.....
አብዛኛው ታዳሚ ጭንቅላቱን እየያዘ ከመሬት ይወድቅ ጀመር ግማሹ በእንብርክኩ እየወደቀ ተንጋሎ ከመሬት ይወድቃል ሻርማይኮች እርስ በእርስ ተያዩ ኢላማቸው ግቡን እየመታ ነው
ዛሬ በዚች ምሽት የብዙ ሚሊዮኖች የመዳን ተስፋ መልስ ያገኛል
ኢትዮጵያውን ምን ያህል ላሰቡበትና ላቀዱት አላማ ጥበባቸውን ማስተዋላቸውን አዋቂነታቸውን እንደሚጠቀሙ በሰባቱ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች አሳይተዋል ሻርማይኮች ከናጋዚ ሞት ተተፍተው ዛሬ ለብዙ መድሀኒት ፈላጊዎች መድሀኒቱን ለመስጠት 11ኛው ሰአት ላይ ቆመዋል
ከኛ ለቃቅመው ዋሻዎቻችን ገዳማትና አድባራቶቻችን በርብረው በሚለቅሙአቸው የጥበብ መፅሀፍት ዛሬ ካሉበት ደረጃ ደርሰዋል በመስረቅ ከኛ በመንጠቅ ከብረዋል ተዝቆ የማያልቅ የሀብት ማማ ላይ ተቀምጠዋል ማስተዋል ጥበብ እውቀት ብልሀት ሁሉን ከደብሮቻችንና ከገዳማቶቻችን ሰርቀው ወስደውብናል መጪውን ሗላውን አሁኑን ጭምር በእኛ አውቀዋል
ዛሬም ከኛ በወሰዱት መፅሀፍ አለምን አዲስ መድሀኒት በትላልቆቹ ላብራቶሪዎቻችን ሰርታናል ብለው ተራ ትርክቶችን ይቀደዱልናል
መፅሀፉን ገልጠው መርምረው እኛ አገኘነው እያሉ ያታልሉናል
ሁሉም ግን በኛ ነው..  ዛሬ አንድ ውሸት መልስ ያገኛል
ፊያሜታና ናትናኤል ከmr issac አይን ላይ ናቸው
ታዳሚው እየተልፈሰፈሰ ከመሬት ተዘርሯል መሬቱ ባማሩ ቆንጆዎች በነጫጭ ሰዎች ከእጆቻቸው ባመለጡት ጠርሙሶች ተሞልተዋል Mr isaac ሰአቱን ጠብቁ ከመሬቱ ተንጋለለ ቀዩ ጨርቅም የወይኑን ፍሬ የወሰደ ይመስል ከመሬት ተዘረጋ
ከወይኑ የገባው እፅ እንቅስቃሴያችንን አደንዝዞ እፁን ከተጠቀሙ  በሗላ ማስተዋላቸውን ያስታል ሁሉም ከሰመመኑ ሲነቃ ምን እንደተከናወነ አያስታውስም
አሁን ከኤንባሲው ቅጥር ከሻርማይኮች ውጪ ቆሞ ሚተነፍስ የለም
ፊያሜታ በፍጥነት ወደ ተንጋለለው ሰውዬ አመራች ብራናውን ለቅመ አድርጋ ወደ አባ አመራች አባ እንባ ቀረሽ ደስታ ከፊታቸው ታየ ጥርሶቻቸውን ከፍተው እጆቻቸውን ዘርግተው ተቀበሏት ሻርማይኮች ሁሉም አንድ ቦታ ተመለከቱ ወደ ተስፋይቱ ወደ ምድረ ገነቲቱ ወደ መፃኢዋ ኢትዮጵያ በሀሳብ ተመሙ
በዚ ብራና ስንት ትውልድ እንደ ሚድን ተመለከቱ ስድስቱም ሰዎች አንድ ላይ ተቃቀፉ ከናጋዚ የሞት ክልል አምልጠው ዛሬ ላይ ሞት ለከበባቸው ሰዎች ሞትን ሲያባርሩ ተመለከቱ ሀዘን ደስታ ናፍቆት ጀብደኝነት ከስሜቶቻቸው መካከል ናቸው
እንዳትንቀሳቀስ...
መተቃቀፉ ሳያልቅ የአንድ ሰው ድምፅ ተሰማ ሻርማይኮች ምን እየሆነ እንደሆነ ማመን አልቻሉም
የያዝከውን ቁጭ አድርገው ወደ አባ እያየ መሳሪያውን ከፊታቸው ደቀነው
ፋታ ሳይሰጣቸው የመጀመሪያውን ቃታ ሳበው አባ ከወደ ደረታቸው ደም ተፈጠረቀ ልክ በወይኑ እንደ ወደቁት እሳቸውም በጥይት ተመተው ወደቁ ፊያሜታ ጩኸቱአን ለቀቀች ኤልያስ ለመጠባበቂያ የያዘውን መሳሪያ አውጥቶ ወደ ተኳሹ ቃታውን ሳበ ወደ ትከሻው ጨረፈው
በፍጥነት መዘናጋቱን ያዩት ሻርማይኮች ምግብ ተደርድሮበት የነበረውን ጠረጴዛ በፊቱ ደፍተው ተከተቱበት
ኤልያስ አባን ከትከሻቸው አቅፎ ከጎኑ ወደ ነበረ ዛፍ አስተኛቸው
ከኤልያስ ጥይት የተረፈው ጋርድ የአቅሙን ተነስቶ የጥይት ዶፍ ወደ ጠረጴዛው ያርከፈክፍ ጀመር
ምድነው ከየት ነው የመጣው ፊያሜታ በአባ መመታት ደንግጣ እንባዋን ታዘራለች
ኤልያስ ሸሚዙን ተልትሎ ለአባ አጥብቆ አሰረላቸው ከደረታቸው የሚወርደውን ደም ሸሚዙ ሊያስቆመው አልቻለም
እጁን ወደ አንገታቸው ሰዶ ከተዘቀዘቁበት ቀና አደረጋቸው አይዞት አባቴ ይጠንክሩ ትንሽ ነው የቀረው ትንሽ
አባ አይኖቻቸው ደም ለብሰዋል የግንባራቸው ደም ስሮች ተገታትረዋል ከአይናቸው የምቶርደው እንባ እየደከሙ እንደመጡ ለኤልያስ ፍንጭ ሰጡት እጆቹን ቀስ አድርጎ ወደ ታች አስተኛቸው
ተኳሹ ተኩሱን አላቆመም ጠረጴዛውን ቦተራርፎታል በቀዳዳዎቹ ትይዩ እነ ፊያሜታ ላይ ያነጣጥር ጀመር  ሁሉም ፈርተዋል ተስፋቸው በአንድ ተልካሻ ነጭ ሲናድ ታያቸው ናትናኤል ለቢንያም መልእክት ይሰጣል ከቢንያም ዘንድ ምንም መልስ የለም
ከተቦተራረፈው ጠረጴዛ አልፋ የመጣች ጥይት ከዮቶር ትከሻ ተሰነቀረች ደሙ ቁሉቁል ከትከሻው ሲወርድ ተመለከቱ ጭንቀት ፍርሀት ነገሰ
ከናጋዚ በሗላ ዛሬም መልአከ ሞት ከቧቸዋል
ፊያሜታ ብራናውን አጥብቃዋለች ከዚ ውጥረት መውጫ የሚሆን ጥበብ ከመፅሀፉ እንዲኖር ተመኘች
የጥይቱ ድምፅ በረደ ዶፉ እስከ ጭራሹ አባራ
 አባ ... ቢንያም ከኤንባሲው ደርሶ ተኳሹን ግንባሩን ብሎ ጣለው
ፀሎቷ የሰመረ መሰላት ናትናኤል ወንድሙን ደግፎ ይዞት ተነሳ
7ቱ ሰዎች ወደ ከዛፉ ስር ተሰበሰቡ አባ ወደ ሞት እየገቡ ነው የናጋዚ የሞት መልአክ ዛሬ አባን አፈፍ አደረጋቸው እያጣጣሩ ከወደ ደረት ኪሳቸው አንድ ብራና አወጡ ይሄን ወረቀት ያዙ
ኤልያስ እንባዎቹ አመለጡት ከአባ ደረት ላይ ተንጠባጠቡ ፊያሜታ አባቴ ሳግ ነገሰባት
 አባ ቀጠሉ....
ወረቀቱ ካርታ ነው ስታቃጥሉት ባዶው ወረቀት በቁጥር የተሞላ መሀሉ ላይ በልዩ ጥበብ የተሳለ ካርታ  ታገኛላችሁ በካርታው ታግዛችሁ ይሄን ብራና ወስዳችሁ  ጥቅም ላይ አውሉት
ትልቁን የመድሀኒት ማምረቻ ተቋም በዚ ካርታ ታግዛችሁ ታገኙታላችሁ ብዙ የባህል ሀኪሞቻችንና ጠቢባን በዛ ከትመዋል ሻርማይክ ብላችሁ ግቡ ፀሀዮች ይቀበሉዋቹሀል ሻርማይክ ማለት ትርጉሙ ፀሀይ ማለት ነው ወደ ሻርማይክ ቤት ግቡ ለኢትዮጵያ እንደ ጀንበሯ አብሩ
               ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ
                  ኀበ እግዚአብሔር
                          አሜን

                       ተፈፀመ
        ብላቴናው በእሳት ገፆች ላይ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
★ቂም የሸፈነው እውነት★★
                  (ሜሪ ፈለቀ)

“መለያየት እፈልጋለሁ፡፡ ፍታኝ?” አልኩት በመኪናው መስኮት አሻግሬ ዓይኖቹን እየሸሸሁ፡፡

“እሺ!!” ነበር መልሱ:: ቢያንስ ‘ለምን?’ ብሎ እንዴት አይጠይቀኝም?

“መች ነው እንዲሆን የምትፈልጊው? አሁን? ነገ? ከሳምንት በኋላ? መቼ?” ቀለል አድርጎ ቀጠለ፡፡ ቀጥዬ የምለው ጠፋኝ፡፡ ለራሴ ምክንያት መስጠት እፈልጋለሁ፡፡ ተናዶ እንዲናገረኝ እሱ ላይ እንከን ማግኘት አጥብቄ እፈልጋለሁ፡፡’ፈታችው’ ከመባል ሌላ ቅጥያ ተጨምሮበት ‘ስላናደዳት ፈታችው’፣ ‘ስለመታት ፈታችው’……… ብቻ ምክንያቱ ከሱ ቢመጣ ደስ ይለኛል፡፡

“ካለቀልን ዛሬም ብንፋታ ደስ ይለኛል፡፡”

“ከዛሬ በኋላ ተፋተናል፡፡ የግድ በህግ መፋታት የለብንም፡፡ እኔን መፍታት አይደል የፈለግሽው? ስለወደድኩሽ እንጂ ማንም ስለፈረመ  እና ምስክር ስለተጠራ አላገባሁሽም፡፡” ብሎኝ ከመኪናው ወረደ እና የኔን በር ከፈተልኝ፡፡ ቤታችን ደጅ ደርሰን ነበር፡፡ ተናደድኩ፡፡

“የንብረት ክፍፍሉ……..” አላስጨረሰኝም፡፡

“የትኛውን ንብረት ነው የምትፈልጊው?” የአጥሩን በር ከፍቶ በእጁ እንድገባ አሳየኝ፡፡

“ድርሻዬን::”

“ህምምምም…….. ቅር ካላለሽ ትንሿን መኪና ልውሰዳት ሌላውን ንብረት አልፈልገውም፡፡ ከዛሬ በኋላ ባልሽ አይደለሁም፡፡ ምንም ንብረትም የለኝም፡፡” ብሎኝ ‘ትንሿ’ ያላት መኪናው ውስጥ ገብቶ ተመልሶ ሄደ፡፡

ምን እንደምፈልግ ግራ ገባኝ፡፡ ካሳሁንን ሳላገባው  በፊት ነበር የምፈታው ቀን የሚናፍቀኝ፡፡ ሳላገባው ፈትቼዋለሁ፡፡ እሱ ያገባኝ የመሰለው ቀን እኔ አግብቼም ፈትቼዋለሁ፡፡ታዲያ ለምን አገባሁት? እሱን አላገባሁትም፡፡ ገንዘቡን እንጂ። ወንዶች ‘ሴት ልጅ ገንዘብ ያለው ወንድ ትወዳለች’ ሲሉ ሳቄ ያመልጠኛል፡፡ ወይ ሰውየው ማርኳታል ወይ ገንዘቡ ማርኳታል፡፡ ለአንዳቸው ቅድሚያ ትሰጣለች፡፡ለገንዘቡ ብላ ከሆነ ገንዘቡን እንጂ እሱን አትወደውም። ገንዘቡ እስካለ ወይም የምትፈልገውን እስክታገኝ ድረስ አለች፡፡ እነሱ ግን ራሳቸውን ሳይሆን ገንዘባቸውን ያቀርቡላታል፡፡ ምክንያቱም የቁስን ያህል ራሳቸውን አያምኑትም፡፡ ስለዚህ ከቁሳቸው ይልቅ ራሳቸውን ተወዳጅ አድርገው ማቅረብ ሲሳናቸው ለገንዘቤ ብላ ነው የወደደችኝ ይላሉ እንጂ ገንዘቤን ነው የወደደችው አይሉም፡፡ ሰውየውን ከወደደችው ለገንዘቡ ብላ፣ ለቁመናው ብላ፣ ለወዙ ብላ…. የሚሉት ቀልድ አይጥመኝም፡፡ በቃ ሰውየውን ነው የወደደችው፡፡

የዛን ቀን ምሽት አልመጣም፡፡ ጠበቅኩት፡፡ እውነቱን እንደሆነ ገባኝ፡፡ ካሳሁን ፈቶኛል፡፡ ሁለተኛው ቀን መሸ ።አልመጣም፡፡ አልደወለም፡፡ ሶስተኛ ቀን ሆነ……… አራተኛ ቀን መጣ… … አስር ቀን ሞላው። አልመጣምም። አልደወለምም። የገባኝ ግን ቢመጣ ደስ እንደሚለኝ ነው፡፡እሱን መፍታት ያስደስተኛል ብዬ ያሰብኩትን ያህል አልነበረም የደስታዬ መጠን፡፡

“አልወደውም፡፡ ከሀብቱ እንጂ ከእርሱ ጉዳይ የለኝም።” ለራሴ ብቻዬን አነበነብኩ። ስልኬን እልፍ ጊዜ ልደውልለት አነሳሁ። እልፍ ጊዜ ተውኩት፡፡ በአስራአንደኛው ቀን ስልኬ ጠራ። እሱ ነበረ። ለምን ደስ አለኝ? አብሬው መኖር የማልፈልገው ሰው ድምፁን መስማቴ እንዴት አስደሰተኝ?

“ደህና አደርሽ ሰብሊ? …… ላግኝሽ?”

“እሺ:: የት እንገናኝ?”

“ስራ ቦታ:: አራት ሰዓት ላይ መጥቼ ወስድሻለሁ፡፡”

ስራ የመግባት ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ቁምሳጥኑን ከፍቼ ሊያቆነጀኝ ይችላል ብዬ ያሰብኩትን ሁሉ ልብስ ሞከርኩ፡፡ ላማልለው? ወይስ ከሱ በመለየቴ አለመከፋቴን ለማሳየት? ለራሴ የምሰጠው ምክንያት ባይኖረኝም በሱ ፊት ቆንጆ ሆኜ መታየት ፈለግኩኝ፡፡ አምስት ዓመት በትዳር አብሬው ስኖር ይሄ ግድ ሰጥቶኝ አያውቅም ነበር። በጥንቃቄ ስዋብ ብዙ ሰዓት ፈጅቼ ደረስኩ፡፡ ተጋብተን ብዙም ሳንቆይ ነበር ካሳሁን እቤት ከምትውዪ ብሎ ለንግድ ተስማሚ የሆነ ቦታ ላይ ትልቅ የሴቶች ፀጉር ቤት የከፈተልኝ ፡፡ በሩ ላይ ሲደርስ የት ይዞኝ ሊሄድ እንደሆነ እያሰብኩ ነበር፡፡ ብዙም ግድ ያልሰጠው ሰላምታ ሰጥቶኝ የመኪናውን በር ከፍቶ አስገባኝ፡፡ በሚከብድ ዝምታ መኪናውን መንዳት ጀመረ፡፡ ላገኘው እንዳልቸኮልኩ፡፡ ተጨነቅኩኝ፡፡

“የት ነው የምንሄደው?” አፌ ይሄን ይበል እንጂ የትም ብንሄድ ግድ አልነበረኝም፡፡

“የምንጨርሰው ጉዳይ አለን፡፡”

ባንክ ቤት በር ጋ ስንደርስ በሁለታችን ስም የነበረውን የባንክ አካውንት ሊያዛውርልኝ መሆኑን ነገረኝ፡፡ በተዘባረቀ ስሜት ውስጥ ሆኜ የሚጠበቅብኝን ፈፀምኩ፡፡ እድሜውን ሙሉ የሰራው ገንዘብ መሆኑን እያወቅኩ ‘አንተስ?’ ብዬ እንኳን አልጠየቅኩትም፡፡ ነገር ዓለሙ ዞረብኝ፡፡ ምንም ሳንነጋገር ፀጉር ቤቱ በር ጋር ደርሰን፡፡በር ሊከፍትልኝ ከመድረሱ ዘልዬ ከመኪናው ወረድኩ፡፡ በሌላ ትህትናው መቁሰል አልፈለኩም፡፡

“የት ነው ያለኸው?” አልኩት

“ቤት እስካገኝ ሆቴል ነው ያረፍኩት::”

“ለጊዜው እኮ እቤት መሆን ትችላህ::”

"በሚቀጥለው ሳምንት በአንዱ ቀን የቤት ባለቤትነቱን ስም አዛውርልሻለሁ:: ሰሞኑን ስራ ስለሚበዛብኝ የምችል አይመስለኝም፡፡” ብሎኝ መኪናው ውስጥ ገብቶ ሄደ፡፡ ራሴ የሚፈነዳ መሰለኝ፡፡የማብድ የማብድ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ወደቤቴ ሄድኩ።

…… አልጨረስንም…

@wegoch
@wegoch
@paappii

#meri_feleke
#የሰኔ መቅሰፍቶች

     ክፍል - ፩

አመት ሊሞላው ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተዋል ቤተሰቡ እየተሰባሰበ ነው ዳር እስከ ዳር ያሉት የቤተሰቡ ሰዎች ከእናትና አባታቸው ቤት ከትመዋል
ቤተሰቡ ውስጥ ትልቅ ፍርሀት ነግሷል ቀን ቀንን እየወለደ ከጭንቆቹ ቀናት ሊደርሱ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተዋል
ቤተሰቡ መሰባሰብ ከጀመረ ሶስት ሳምንታት ተቆጥረዋል አንድ አንድ እያሉ ቤቱን ሞልተውታል
ይህን አመት ካለፉባቸው አመታቶች ውስጥ ልዩ ለማድረግ አስበዋል
ከአመት አመት የሚያጋጥማቸውን የክፉ እጣ ፈንታ ገጠመኝ ይህን አመት አንድ ላይ ለመጋፈጥ አስበዋል
ካለቁም አንድ ላይ ለማለቅ.....
በባለፈው አመት ከቤተሰቦቻቸው አባላት ስድስቱ በከፉው እጣ ፈንታ ተወስደዋል ጥቂት የሚባሉት ከሞት አምልጠዋል
ይህን አመት ደሞ ማን የእጣ ፈንታው ሰለባ እንደሚሆን አይታወቅም
ትናንሾቹ መልአክቶች ቤቱን ደመቅ አድርገውታል ቤተሰቡም ለህፃናቱ ፈርቷል
ምንም በማያውቁትና ባልገባቸው ነገር ተጠቂ እንዲሆኑ አልፈለጉም
ከአመት አመት ብቻ ትልቅ ዱብዳ ከቤተሰቡ ዘንድ ይወርዳል የትም ያለ የቤተሰቡ አካል በእኩል ሰአት በእኩል ቀን በእኩል ደቂቃ አንድ አይነት ነገር ያጋጥመዋል
በዚ አመት ክፉው እጣ ፈንታ ብዙ ሚደክም አይመስልም ሁሉም ቤተሰብ አንድ ቦታ ተሰብስቦለታል
እንዴት እና ለምን እንደሆነ ባይገባቸውም ከአያት ቅድም አያት እየተወራ የተነገራቸው ትልቅ የእርግማን መንፈስ በቤተሰቡ ላይ እንዳለ እና ከልጅ ልጅ እየተላለፈ ብዙ ሰው እንደሚጨርስ ተነግሮቸዋል ምንም ይሁን ምን ትልቅ ዱብዳ ቢሆንም እርግማኑ እያደጉ ያሉ ህፃናትን እንደማይነካ ስለተነገራቸው በትንሹም ቢሆን ተረጋግተዋል
አሁን ወልዶ የሳመ እሱም ተወልዶ ሲሳም ይሄ ነገር እንዳላጋጠመው ተነግሮታል
ካለፉት የቤተሰቡ አባላት በሌሎች ምክንያቶች የሞቱ ሰዎች ጥቂት ናቸው ይህ የእርግማን መንፈስ ቤተሰቡን ጨርሶታል
ይህ አመት አንድ ሆኖ የመጋፈጥ ነው ስንሰበሰብ ፈርቶን ቢቀር ብለው የተመኙት ብዙዎቹ ናቸው
ዛሬ ቤቱ በህፃናቱ ቡረቀና ሳቅ ተሞልቷል ትንሽ ከሀሳባቸው መልስ የሚያደርጋቸው የልጆቹ ሳቅና እከን አልባ ደስታ ነው
እኔ ነኝ ምሞተው እኔጋ ይሆን ያሁኑ አመት እጣ ሚደርሰው
ጭንቅላት በጣሽ ሀሳብ በፍርሀት ውስጥ ሆነው ያስባሉ
ሀሳባቸውን አንድ አርገው እነሱም ስለተሰባሰቡ ትንሽ ፍርሀታቸውን አቅሎላቸዋል
ምን አልባት ከመቶ ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ ይሄ እጣ ለነሱ ብቻ የተፃፈ እንደሆነ አምነዋል
ለምን ......        ቤተሰቡን አንድ የሚያደርግ ጥያቄ
ሰኔ የነሱ የምጥ ወር ነው ሰአቱን ጊዜውን በማያቁበት አንዱ የሰኔ ቀን የእርግማኑ ቃል ይፈፀማል
ሁሌ ለዚ ቤተሰብ ሰኔ እና ሰኞ ይጋጠምበታል
በባለፈው አመት በዛው በሰኔ ወር በእያንዳንዱ ቤተሰብ በእኩል ሰአት በወረደው መብረቅ ስድስት ሰዎች ከቤተሰቡ ተነጥለዋል  
በዚ አመት ደሞ ምን ይወርድ ይሆን....
ግንቦት ሊያልቅ ጥቂት ቀኖች ቀርተዋል ከአያቶቻቸው በተሰጣቸው ምልክት እርግማኑ ሲቀርብ ከአመት አመት የግንቦት ወር ጨረቃ ቀይ ትለብሳለች
ቤተሰቡ ጨረቃን እየጠበቀ ነው ምልክቱ ሲታይ ሁሉም ወደ ፈተና ይገባል
ዛሬ የቤተሰቡ ተወዳጅ ልጆች ፊንሀስና ፊያሜታ ከመሸ ከቤተሰቡ ተቀላቅለዋል በባለፈው አመት ያጡት አባታቸውን ሀዘን ሳይጨርሱ ለዚ አመት የሰኔው መቅሰፍት ደሞ ተዘጋጅተዋል
ማንም የትም ቢሄድ በምድር ላይ እስካለ ድረስ ከዚ ፈተና አያመልጥም ብቸኛው ማምለጫ ከምድር ላይ መጥፋት ነው
ከቤቱ ሚቦርቁት ትናንሽ ህፃናት በትናንሽ እጆቻቸው ከእናቶቻቸው ጋር የሰሩትን እራት ከጠረጴዛው እያቀረቡ
ቤቱ በምግቡ መዓዛ ታውዷል ምን አልባት ይሄ መዓዛ ፍርሀቱን እንደሚቀንስ ተስፋ አድርገዋል.....

      ብላቴናው በእርግማን ገፆች ላይ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የሰኔ መቅሰፍቶች

   ክፍል - ፪

እራቱ ተሰናድቷል ለቤተሰቡ አንድ ጠረጴዛ በይበቃም ህፃናቱ አንድ  ላይ ሊበሉ ተሰብስበዋል
ፀልዩ እሺ መጀመሪያ ፊያሜታ ዛሬ እነሱን በማግኘቷ በጣም ተደስታለች ከና ከመግባቷ ብዙ ነገር እያስረሱአት ነው
አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖል ሽምህ ይቀደስ መንትዝትህ ትምጥ  ፈቀድህ በሸማያት እንዲሁም...
ህፃናቱ በሚኮላተፉ አፋቸው ፀሎታቸውን አዳረሱ
ንፁህ ልብ ንፁህ ደስታ ምንም የማይሽረው ልዩ ፍቅር
ምን አለ እግዚአብሄ ለኚ ህፃናት ብሎ ከዚ መከራ ቢያወጣን እናት እና አባትን በዚ እርግማን ምን ያህል ማጣት እንደሚከብድ ፊያሜታ ታውቃለች
እራቱ አለቀ ....
ህፃናቱ እናትና አባታቸው ጋር ሄደው ተሸጉጠዋል ቤተሰቡ እነሱ ባይኖሩ ምን ሊሆን እንደሚችል ማሰብ ከባድ ነው
ቤተሰቡ በዝምታ ህፃናቱ በቡረቃ ሁለት አለም ሆናዋል
ምሽቱን ግን በሁሉም ዘንድ ዝምታ ነግሱአል ቤተሰቡ በመርገሙ ህፃናቱ ደሞ የቀኑ ውሏቸው አድክሟቸዋል
ምን ያህል ካለነሱ ይበልጥ ጭንቀቱ እንደሚገዝፍ ዛሬ በደንብ ተረዱ
አይ ህፃናት ትናንሽ ትልቅ አለሞች ናቸው የሀዘንን የጨለማን በፍቅር ያለመኖርን መንፈስ አባራው ሚጥሉ ሀዋርያት ናቸው....    ፊንሐስ በአፉ ያልጎመጉማል
አጎቴ ምን ይዘህልኝ ነው ግን የመጣኸው ኤፍራታ የፊንሀስና የፊያሜታ የአክስት ልጅ ናት ፊንሐስ ማለት ስለሚከብዳት ነው አጎቴ የምትለው
አሁን አይነገርም ጠዋት ለሁላችሁም ይሰጣችሁዋል እሺ ኤፊዬ ፊንሐስ አይኑን ከአይኗ ሳይነቅል
ሁሉም ልጆች እሺ አጎቴ ድምፃቸው የሆነ ልዩ ነገር ያመጣል ፍርሀት ይሰብራል
ምሽቱ ደሞ ነግቶ ይሄን ቀን ያሳልፈዋል የጭንቁም ቀን ይቀርባል
ይሄን ምሽት ሳይነጋ እየተኙ እየተነሱ ቢኖሩት ደስታቸው ነው ነግቶ አዲስ ቀን ሳያዩ ሰኔን በዚች ምሽት ቢያሳልፏት የሁሉም ደስታ ነው
ወደ ጭንቁ ቀን ብዙ ወደ ሚያስቡበት ሌሊት ሁሉም ተነሱ ወደ አልጋቸው አመሩ በዚ ሰአት ልጅ ያለው ሰው እድለኛ ነው ከልጁ ጋ እየተጫወተ ሌሊቱን ያጋምሳል
ልጅ የሌለው ከሀሳቡ ከጭንቁ ከፍርሀቱ ጋ እየተጣላ ሌሊቱን በፍርሀት ያድራል
ፊያሜታና ፊንሐስ ወደ ተዘጋጀላቸው መተኛ አመሩ
እህት ካለ ወንድም ወንድምም ካለ እህቱ ማንም የላቸውም
ዛሬም ተደጋግፈው ወደ አልጋቸው አመሩ ፊያሜታ እናቷን ካጣች አመት ሳይሞላት አባቷ ስለተለዩአት ሀዘኑ አጎሳቅሏታል ውበቷ ግን አሁንም እንዳለ ነው
ወንድሟ ፊንሀስ አጠገቧ ባይሆን ኖሮ ምን ሊውጣት እንደሚችል ለአፍታ ማሰብም አፈልግም....
ዛሬ ድካሙ ለነሱ እረፍ ሰቷቸዋል ምንም ሳያስቡ ወደ እንቅልፍ ገቡ
ፍርሀትን አቅፎ .......

     ብላቴናው በእርግማን ገፆች ላይ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
አንድም ለወፍ አንድም ለወንጭፍ !
(ሚካኤል አስጨናቂ )
ምሽቱን በሙሉ የቋመጠለትን ገላ ያለ ከልካይ በእቅፉ ስር አድርጎታል ። በቀዩ የክለብ መብራት እና በሞንታርቦ ድንፋት ከደመቀው ክለብ ውስጥ እንኳን እንደ ሳሌም አይነት የመላዕክት እህት የመሰለች ሴት አይደለችም ስንቱ ጎራዳ ተውቦ ቀልብን ያማልላል ።
ሳሌም ውበቷ ምትሀታዊ ነው ። የሳሌምን ውበት በቅጡ ለመግለፅ የነ በዓሉ ግርማ አይነት የደራሲያን ህብረት በጋራ የሚያዘጋጁት መፅሀፍ ያስፈልጋል ፤ አለ አይደል የአይኖቿን ጉልላትነት በዓሉ ግርማ በ አራት መቶ ገፅ ፅፎት ሲያበቃ ስብሀት ለአብ ደግሞ አፈፍ አድርጎ የሳሌምን ከንፈር በሳሙ ቅፅበት በወንድ ልጅ ልብ ውስጥ እንደ መብረቅ ብልጭ ስለሚሉ አንድ ሺህ አይነት ስሜቶች በአንድ ሺህ ገፅ ከትቦ የሚገልፅበት !
ሄርሞን ደግሞ ለሴት ልጅ ውበት ልቡ ስስ ነው። እዚህ መቶ ሚሊየን አይነት መዓት በየሳምንቱ በሚወራበት ሀገር ውስጥ እየኖርኩኝ ሴቶች ባይኖሩ ኖሮ ምን ይውጠኝ ነበር ? ሲል ያስባል ።
ደባሪ በሆነው የመገናኛ ግርግር ፣ በሺህ የታክሲ ፈስ እና ጩኸት በተከበበው ሜክሲኮ ሰፈር እንዲሁም ኪስ ውስጥ ከሚገባ የገንዘብ በረከት ውጭ ለአይን ደስ የማይል ክርፋት በሚታይበት መርካቶ እየተመላለሰ ነው የሚሰራው ። የሚያየው ነገር ሁሉ ደስ አይለውም ።
ዘወትር የመኪናውን መስኮት ዝቅ አድርጎ አዲስ አበባ ከስሟ ውጭ አበባ ሊያስብላት የሚያበቁ ነገሮች የሉም ብሎ በጥላቻ አይን ሰፈሮቹን ይገላምጣል ። ወዲያው ግልምጫው ላይ እያለ ተረከዝ የሚያሳይ ጠፍጣፋ ቡኒ ጫማ ያደረገች ሙስሊም ሴት ያይና ልቡ አታሞዋን ትደልቃለች ።
በቄንጠኛ ቡኒ ጫማ ጎን አፈትልኮ የሚታይ ጠይም ውብ ተረከዝ ሲያይ መላ ሰውነቱን ይነዝረዋል ። የሴስ አጋንንቶቹ ሄርሞን ያርገበገበውን የወሲብ እሳት የበለጠ እፍ እያሉ ያቀጣጥሉታል ። አጋንንቶቹ ለአቦል ይጠራራሉ ። የወሲብ ቡና ይፈላል ፣ የቅንዝር ፈንዲሻ ይፈነዳል ፣ ተረከዝ ቡና ቁርስ ሆኖ ይቀርባል ። ያኔ አይኑ መንገዱ ላይ በሚርመሰመሱ ሴቶች እግር እና ቂጥ ላይ እየተመላለሰ የከተማውን ክርፋት ይረሳበታል ። በጭኖቹ መሀል ቆሞ ሱሪውን ድንኳን ያሰራው ማገሩ ጥቂት የእንባ ዘለላዎችን ያወርዳል ።
“ሄርሞን ወንድሜ ሆይ ስራህን በጊዜ ጨራርስና አመሻሹ ላይ ዋና ውሰደኝ!” እያለ ይጮህበታል ። ከዛም ቀኑን እያስታመመው ይውልና ምሽት ሲደርስ አንድ ሁለት ለማለት ቦሌ ይሄዳል ። ቀልቡ ወደፈቀደለት መሸታ ቤት ይገባና ሬድ ሌብል ውስኪው ውስጥ በረዶ ጨምሮ ይጎነጫል ።
መጠጥ ሲጀማምር ረጋ ያለ ቤት ውስጥ ይቆይና ትንሽ ሞቅ ሲለው አይኖቹ ይንከራተታሉ ። ያኔ የእመቤት እና የገረድ እቃ ልዩነት ይጠፋበታል ፣ የሙስሊም ሴት እና የክርስትያን ሴት ተረከዝ ይምታታበታል ። ሴቶች ሁሉ ለእሱ ተፈጥረው በዙሪያው የሚበሩ ቢራቢሮዎች ይመስሉታል ። ከሁሉም ሴት ጭን ውስጥ ማዕድን ለማውጣት ፍቃድ የተሰጠው ብቸኛ ሰው አድርጎ ራሱን ይቆጥራል ።
ተረከዝ ባይነት ባይነት !
ጠይም ፣ ቀይ ፣ ቀይ ዳማ
በቡኒ ጫማ ፣ በጥቁር ጫማ
ጭን ባይነት ባይነት !
《ጥቁር ፣ ጠይም ፣ ቀይ ፣ ቀይ ዳማ 》 ሁሉም ለሱ ስምሙ ናቸው ። ሽንቱ እንደመጣበት ሰው እመር ብሎ ይነሳና በክለቡ ጓሮ ሆኖ አይኑ ውስጥ የገባችውን ሴት ጠርቶ ይደራደራታል ።
ልጅቷን ከወደዳት የሚያስቆመው ሀይል የለም ። የቅንዝር አጋንንቶቹ የፈቀዳት ሴትን እንኳን ምድራዊው የሰው ልጅ ሀይል አይደለም የሰማይ መላዕክት የሚነፉት መለከት እንኳ ሊያስቆመው አይችልም ።
የወደዳትን አጋንንቶቹ የፈቀደላት ሴት ቀዳዳ ውስጥ ሲገባ ቀልቡን ስቶ ይውረገረጋል ። በአዕምሮው ጓዳ የሚያውቃቸውን ሴቶች ሁሉ እየሳለ በአንዲቷ ሴት ገላ ዓለም ላይ ያሉትን ሴቶች ሁሉ ያወጣል ።
ከዛም ተልፈስፍሶ አልጋው ላይ ዘፍ እያለ ለቆት ወደነበረው ምድር ይመለሳል !
አጋንንቶቹ አቦል ቡናቸውን ጠጥተው ካበቁ በኋላ እሱን ለመጀመርያው ፀፀት ጥለው ወደ ጎጆዎቻቸው ይሰደዳሉ ።
ያኔ ድሮ በልጅነቱ ቤተክርስትያን ሲመላለስ ከሰማቸው የመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርቶች መሀከል አታመንዝር የሚለውን ትዕዛዝ ቀድሞ ሹክ ያሉት ካህን ፊቱ ድቅን ይላሉ !
አባ መልዓከ ፀሀይ ከበላይ ጣል ያደረጉትን ሸማ እያስተካከሉ …..
“ልጆቼ ከዝሙት ሽሹ ! ዝሙትን ከሌሎች ሀጥያቶች ይልቅ የከፋ የሚያደርገው በራስ ገላ ላይ በእግዚሀር ቤተመቅደስ ላይ የሚደረግ እርኩሰት በመሆኑ ነው ። ሰው መግደል ፣ መስረቅ ፣ መዋሸት የሚባሉ በደሎች ከራስ ገላ ውጭ የሚደረጉ ሀጥያቶች ናቸው ። እነርሱም ያረክሳሉ ፣ ከዝሙት በላይ ግን ሰውነትን የሚያረክስ ሀጥያት የለም ።
ስሙኝ ልጆቼ ከዝሙት ሽሹ ። እናንተን የሚያሰናክል ነገር ባያችሁ ቁጥር አምልጡ ፣ ሩጡ ፣ ጥፉ ….. !”
ሄርሞን ራሱን ካረከሰበት ክፍል ጠፍቶ ሲሮጥ ወደ መሸታ ቤቱ አቅጣጫ ይንደረደራል ። በሩጫው መሀከል ሰረቅ አድርጎ ሲማትር የባንኮኒው መደርደሪያ ላይ በግርማ ሞገስ ተደርድረው ከሚታዩት ኩራተኛ ጠርሙሶች መሀከል አንዱ ጠልፎ ይጥለዋል ።
አረፍ ይላል !
ተጨማሪ መጠጥ ያዛል ። እሱን እየተጎነጨ ራሱን ይወቅሳል ። ሀጥያት በደሉን ያስባል ። ከዝሙት እሳት ፈልቅቆ የሚያወጣውን ሌላ ምትሀተኛ ሀይል መለማመን ይጀምራል ። ፀሎቱን አስኪዶ አሜን ይላል ። ሶስት ጊዜ አሜን ያልተባለ ነገር እንደማይፀና ስለሚሰማው ደግሞ አሜን ይላል ።
ከዛም ፀሎቱን ሊያሳርግ ለሶስተኛው አሜን አ ...... ማለት ሲጀምር እንደ አቦሉ ሁሉ ሁለተኛው ቶና የቅንዝር ቡና እንዳይቀርባቸው የሚፈልጉት አጋንንቶቹ ስስ ልቡን ስለሚያውቁ መረብ ይዘረጉበታል ።
አንድ አይኑን ገለጥ ያደርጋል ። ለሰማይ ለምድር የሚከብድ ውበት ፣ መፅሀፈ ሄኖክ ውስጥ እንዳለው ታሪክ መልዓክትን ካሳቱ የሴት ልጅ ውበቶች መሀከል አፈንግጦ ዛሬ የደረሰ ውበት ላይ አይኑ ይተከላል ።
ሌላ ተረከዝ ፣ ሌላ ዳሌ ፣ ሌላ ጭን ፣ ሌላ ሳቅ ፣ ሌላ አይን ፣ ሌላ ፀጉር ፣ ሌላ ድምፅ ፣ ሌላ መዓዛ ።
እዛው ቆዳውን ያሸልትና አዲስ ማንነት ይፈጥራል። በሌላ የወሲብ ጠኔ ይመታል ፣ በሌላ የሴት ተረከዝ ጣዕም ጉሮሮው ይደርቃል ።
አዲስ ጉጉቱ ፍሬ አፍርቶ ይጎመራል ። ያን ጊዜ አጋንንቶቹ በሳቅ ያውካካሉ ። ሄርሞን በድጋሚ በቁጥጥራቸው ስር ይውላል ።
ጆግናው የአጋንንን ሰራዊት አንባገነኑን ሄርሞን በአንዲት ውብ ተረከዝ ጥይት መትቶ ተቆጣጥሮታል ።
ሄርሞን ወደቀ !
ሄርሞን አለቀ !
ሄርሞን ደቀቀ !
ማልዶ ሲነቃ ሳሌም ስሩ ተኝታለች ። ከዛሬ በፊት ለአጭር ጥሙ አልጋ ክፍል ከመግባት ውጭ ማደር አይወድም ነበር ። ዛሬ ግን አድሯል ። እንደው ቀን ከፍቶበት ፣ ስህተት ሰፍቶበት አድሮ ቢሆን እንኳ በለሊት ከአልጋ ክፍል መውጣት ነው የሚፈልገው ።
ተነሳ !
አብሯት ያደራት ሴት ሂል ጫማ ን አየው ። እንደሌሎቹ ብዙ ሴቶች ድፍን ሸራ ጫማ አድርጋ ስላልነበር ደስ አለችው ።
እሷ ያለችበት ክፍል መዓዛ በኮንዶም ክርፋት አልተበከለም ፣ ጡት ማስያዣ ና ፓንቶቿን አያቸው ።
አልቻለም ዞር አለ ። ሲዞር ከምትሀተኛ ውበት ጋር በአይኑ ተላተመ ።
ይሄን መሳይ ገላ አቅፌ ነው ያደርኩት ? ሲል አሰበና በልቡ ኮራ ።
“ደስ ትላለህ ሄርሞን ” የሚሰማውን ድምፅ አላመነውም ። ሄርሞን ? ጭራሽ ስሜን ነግሬያታለሁ ? ድምፅዋ ደግሞ መረዋ ነው ።
ይህቺ ሴት ማናት ?
“ማን ልበል ?”
“ሃሃሃሃሃሃ ምሽቱን እንደዛ ስሜን እየጠራህ ስታሞካሸኝ አድረህ ማንልበል አልከኝ ?”
“እኔ አንቺን በስምሽ ጠርቼ አሞካሸሁሽ ?”
“ድብን አድርገህ !እንዳንቺ አይነት ሴት አይቼ አላውቅም ምናምን እያልክ ስትለፋደድ አይደል እንዴ ያመሸኸው?”
“በርግጥ ቆንጆ ነሽ ። ”
“ባትልስ ? ምንም የማይወጣልኝ ቆንጆ ነኛ ”
“ግን መልክሽ አዲስ አልሆነብኝም ?”
“ያው እዚህ ስትመላለስ አይተኸኝ ይሆናላ ”
ቀስ ብሎ ፊት ለፊቱ ካየው ወንበር ላይ አረፍ አለ ። ማንን መሰለችኝ ?
አዎ ሰርካለም ራሷ !
ሰርካለምን ትመስላለች ። ሰርካለም አብረው ስምንተኛ ክፍል ሲማሩ የሚያውቃት ልጅ ነበረች። እሷና ሳምራዊት ተወልዶ ባደገባት ጠባብ ከተማ ውስጥ ከሚማሩ የአብዮት ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ የተለዩ ነበሩ ።
ሰርካለም ጠይም ሆና አሳ መሳይ ውብ ነች ። ጠጉሯ ያለምንም ቅጥያ የተንዠረገገ ነው ። በዛ ላይ ሱሪ እንደነውር በሚቆጠርበት ወቅት ላይ ከሳምራዊት እኩል ሱሪ ትለብሳለች ። እንደውም ሸገር ብዙ ጊዜ ኖራ ከመጣችው ሳምራዊት ይልቅ ሰርካለም ሱሪ ያምርባታል ።
ዳሌዋ ያለምንም ከልካይ ይንጎማለላል ።
“አይ የታምራት ልጅ ተበላሸችበት !” የሚሉ የባልቴት ድምፆች ከዚህም ከዛም ይሰማሉ ።
ውበቷ ን እየተመኙ የሚነቅፏት መምህራኖች በግራም በቀኝም በነገር እየጠዘጠዙ ያብጠለጥሏታል ። የሚቀኑባት ሴት ተማሪዎች ቀሚሷን የትም የምትገልብ ሸርሙጣ እያሉ መረን በለቀቀ አፋቸው መረን የለቀቀ ስድብ ይሰድቧታል ።
ግን ሁሉም የማይክዱት አንድ እውነታ ደግሞ አለ ።
ሰርካለም አድጋለች ። እድገቷም ፈጣን ነው ። እሷ በዚህ ሰዓት እንደ ፈለገችው በፈለገችው አቅጣጫ የሚሾሩላት ወንዶች እያሉ እንደሌሎቹ ሴት ልጆች ገመድ መዝለል እየተጫወተች እግሯ አቧራ የሚቅምበት ምክንያት የለም ።
የስንት መጋዘን ባለቤት ሀብታም ነጋዴ ጭራውን እየቆላ እግሯ ስር እየተርመሰመሰ ባለበት ወቅት ላይ ሂሳብ የቤት ስራ መስራት ለምኗ ነው ?
የሀበሻ ተማሪ ትምህርት የሚማረው ለየትኛው የፈጠራ ስራ እራሱን ለማዘጋጀት ነው ? ለመኖር ገንዘብ ለማግኘት ደህና መስሪያቤት ለመቀጠር አይደለምን ? ከዛ ተንቀባሮ ለመኖር ቤተሰብን ለመርዳት ...
ሰርካለም ደግሞ ሁሉንም አሁን መሆን ትችላለች ። ቁንጅናዋ ሁሉን አሸናፊ ነው። እሷን ከሰፈር ውሪ እስከ አስተማሪ
ከችጋራም እስከ ሀብታም ድረስ የሚመኛት አሸን ናቸው ። ሳትማር ፊደል ሳትቆጥር ፣ ለአስተማሪ ሳታሸረግድ ፣ ለሰፈሩ ባልቴት ምላሽ ሳትሰጥ ከሁሉም በላይ መሆን ትችላለች ።
ለዛም በራስ መተማመኗ ጥግ ድረስ ነው ።
ለብዙ ዘመናት ያህል ወንዶች በሷ ስለመጣላታቸው ፣ መምህራን በፍቅሯ ስለመደንዘዛቸው ፣ ሀብታሞች እሷን የነሱ ለማድረግ በገንዘብ መወራረዳቸውን ያውቀዋል ።
ደግሞም የሰርካለም ሀጥያት በጓደኞቿ ዘንድ ምንም ታህል አልነበረችም ። የሰርካለም ብቸኛ ስህተት ከእኛ ቀድማ መደጓ ብቻ ነው ሲል ሄርሞን አሰበ ።
ሰርካለም ዱርዬ የተባለችው ክፍል ስለፎረፈች ፣ ጀላቲ በአደባባይ ስለመጠጠች ፣ ሱሪ ስለለበሰች ፣ ጠጉሯን ስለተተኮሰች ፣ ከፍ ብላ የበቀለች ማሽላ ሆና አንድም ለወፍ አንድም ለወንጭፍ ሆና በእድሏ ስለተፈረጀች ፣ በግድ አብረንሽ እንሂድ ከሚሏት ደረቅ ወንዶች ጋር አብራ መንገድ ስለሄደች እንጂ አሁን ካለው ሄርሞን በላይ በደለኛ ሆና አይደለም ። ብሎ ወደራሱ ተመለከተ !
በዚህ ሳምንት ብቻ ከሀያ ሴቶች ጋር ወቷል ፣ አለቅጥ ጠጥቷል ፣ ቅሟል ፣ አጭሷል ።
ወደ ስራው ኮቱን ለብሶ ሲሄድ ግን ሀገር ምድሩ የተከበሩ ሲል ያሞካሸዋል ።
ሰርካለም የት ሆና ይሆን ? ውጭ ወታ ይሆን ? ሀብታም ሆና ይሆን ? ልጅ ወልዳ ከብዳ ይሆን ?
“ሰርካለም የምትባል አብራኝ የተማረች ልጅ አለች ። የደጀን ከተማ ልጅ ነኝ ”
“እንዴ ሄርሞን ባልሆንክ ?”
ቀና አለ !
“አንቺ ማነሽ ?”
“ሰርካለም። እዚህ መጠሪያዬ ሳሌም ነው ማለትም ማታ እየጠራህ ስታሞካሸው የነበረው ስም ቂ ቂ ቂ !”
ደነገጠ ። ከሁሉም በላይ ያስደነገጠው ነገር ግን ”ያቺ የውቦች ሁሉ ውቧ ሰርካለም እንዴት ያንን በራስ መተማመኗን አጥታ የቡና ቤት ሴት ሆነች የሚለው ጥያቄ ብቻ ነው ። “
ለሊቱን ስታስል ማደሯ ትዝ አለው ። ኮንዶም አለመጠቀሙም ታወሰው ።
አጋንንቶቹ የቅንዝሩን በረካ በፀፀት ፣ መላዕክት በቅስፈት እንዳይደመድሙት ፈራ ።

@wegoch
@wegoch
@paappii
🌙🌙🌙🌙🌙
ዉድ የቻናላችን የእስልምና እምነት ተከታይ ቤተሰቦች እንኳን ለታላቁና ለተከበረው ለረመዳን በአል አደረሳቹ!!!

#ኢድ_ሙባረክ
መልካም በአል እንመኛለን

@wegoch
@wegoch
''ሹሮ በአናት'' እና ''የመሬት ጥበት....''
ክፍል ፩

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የተገኘ ፁኹፍ ነዉ
ፀኀፊ :- ኤፍሬም እንዳለ
የፁኹፉ ድምፅ :- ሚኪያስ ልየዉ @Mykeyliyew


@Wegoch
@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
.
አያ ሙሌ ቁጭ ካለበት ሱቅ የተጋበዛትን ኮካ ኮላ ለባለሱቁ ትቀመጥልኝ ብሎ ይሰጠዋል። ባለሱቁም ኮካኮላዋን ወደ ሳጥኑ ሳይሆን መደርደሪያ ላይ ያስቀምጣታል።

አያ ሙሌ ከአንድ ወር በላይ ቆይቶ ወደዚህች ሱቅ ሲመለስ ባለሱቁ "አያ ሙሌ አስቀምጥልኝ ያልካት ኮካ ኮላ አለች በማለት ከመደርደሪያው ላይ አንስቶ ይሰጠዋል።

አያ ሙሌ ተገርሞ ብቻ ዝም አላለም። እንዲህ ሲል ነበር የልቡን ምኞት ጭምር የተናገረው:— " ለአንተ ነበር ሃገርን አደራ መስጠት "
.
©ሱራፌል አየለ
@wegoch
@wegoch
@wegoch
''ሹሮ በአናት'' እና ''የመሬት ጥበት....''
ክፍል ፪

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የተገኘ ፁኹፍ ነዉ
ፀኀፊ :- ኤፍሬም እንዳለ
የፁኹፉ ድምፅ :- ሚኪያስ ልየዉ @Mykeyliyew


@Wegoch
@wegoch
@wegoch
#የሰኔ መቅሰፍቶች

  ክፍል - ፫

ህፃናቱ ከቤተሰቦቻቸው ቀድመው ተነስተዋል ማታ ቃል የተገባላቸውን ስጦታ ከአጎታቸው ለመቀበል በሩን እያንኳኩ ነው
አጎቴ አጎቴ....
በሩን በትናንሾቹ እጆቻቸው ይመታሉ ጉዞው አድክሟቸው ሿ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ነበሩ ፊያሜታ ድንገት ነቅታ በሩን ከፈተችላቸው አክስታቸው ተራ በተራ እያቀፉ ወደ አጎታቸው አልጋ ወጡ ስላልበቃቸው ግማሾቹ አልጋው ይዘው ቆመዋል
ፊንሀስ ተነስቷል እንዳልሰማ ለጥ አውቆ ሊያስጮኻቸው ነው
አጎቴ አጎቴ ተነስ ተነስ በትናንሽ እጆቻቸው ይነቀንቁታል ፊያሜታ በሩን ድግፍ ብላ በስስት አይን ትመለከታቸዋለች ልጅ የመውለድ ጉጉቷ ከሰሞኑ ጨምሯል ፍቅረኛዋን በሚያሳዝን ሁኔታ ነው የተሰናበተችው በዚ እርግማን ምክንያት እሱን ለዘለአለም ልታጣው እንደምትችል አምናለች ባሁኑ ብተርፍ እንኩዋ ሁሌ በአመት አመት ልቡን እየሰበረች ልታሳዝነው አልፈለገችም ለምን እንደራቀችው እንኳ ምክንያቷን ሳትነግረው የተለየችው አግኝታው ፍቅሯን እስከ ጥግ ገልፃለት ከአይኖቿ ሚወርዱትን እንባዎች መቆጣጠር ሲያቅጣት በቅጡ እንኳ አቅፋ ሳትሰናበተው መምጣቷ ክፉኛ ቆጭቷታል መልኩ ጠረኑ ሁሉ ነገሩ ናፍቋታል እውነቱን አስረድታ ሁሉን ብታጫውተው ሁሉም ጥሩ ሊሆን ይችል እንደ ነበረ ስታስብ ህመሙ ይሰማታ ነበር በጣም እንደሚጎዳ አውቃለች
ድንገት ፊንሀስ የለበሰውን ብርድ ልብስ ገልጦ ሲነሳ እሷም ከሀሳቧ ተመለሰች
ቆይ እናንተ ሰው አታስተኙም እንዴ ህፃናቱን እየተላፋ ያስቃቸው ጀመረ
እሺ አሁን ስጦታችን የት አለ አጎቴ ኤፍራታ ጠየቀች ህፃናቱን ምትመራው እሷ ናት ከሷ ቃል ውጪ ማንም ዝንፍ አይልም ይወዷታል ይፈሯታል አንዳንዴም ይጣሏታል
ቆይ እሺ ጠብቁኝ ላምጣላችሁ ፊንሀስ ከአልጋው ወርዶ ቦርሳውን ወደ አስቀመጠበት አመራ ቦርሳውን ከፍቶ በህፃናቱ ቁጥር ያመጣላቸው የብር መስቀል ይዞላቸው ሄደ surprise መስቀሉን እያሳያቸው
ህፃናቱ በጣም ተደሰቱ መኪና ኳስ ሌሎች መጫወቻዎችን ስላላመጣላቸው ምንም ቅር አልተሰኙበትም
እውነተኛ አዋቂዎች ትልቅ ሰዎች ፊያሜታ የመስቀሉ ነገር አዲስ ቢሆንባትም በነሱ ደስታ ግን ተገርማለች
በሉ እሺ ፊንሀስ ለሁሉም ልጆች አንገታቸውን እያዞረ መስቀሉን አደረገላቸው
እናመሰግናለን አጎቴ ሁሉም እኩል በሉ የተባሉ ይመስል አጎታቸውን ጮክ ብለው አመሰገኑት
አንገታቸው ላይ ያለው መስቀል እያዟዟሩ ተመለከቱት #ፊኮል የሚል ፅሁፍ አገኙበት
እንዴ አጎቴ ፊኮል የሚል ነገር ከመስቀሉ ላይ ምን ያደርጋል ከመካከላቸው አንዷ ልጅ ጠየቀች
ሁሉም ስሙን ለማየት ይበልጥ ያዟዙሩት ጀመሩ
ኑ እስቲ እኔጋ ከአልጋው ወርዶ ወደ መሬት ተቀመጠ ከፊቱ ደረደራቸው
አሁን ልብ ብላችሁ ስሙኝ ሁሌ በምትኖሩባት አለም ብዙ ነገሮች ታገኛላችሁ ብዙ ነገሮችን ታጣላችሁ ልክ ወደ ምድር ስትመጡ መጀመሪያ ምታገኙት ቤተሰባችሁን ሁሌም በምድር የእናንተ የመጀመሪያ ስጦታ ቤተሰቦቻችሁ ናቸው ግን ደሞ ሁሌም በዚች ምድር እስከ ዘለአለም አብሯችሁ ሚኖር ነገር ላታገኙ ትችላላችሁ ቤተሰቦቻችሁም ድንገች ትተዋችሁ ሊሄዱ ይችላሉ እዩን እስቲ እኔና ፊያሜታን ከኔ እና ከሷ በቀር ለእኛ ማንም የለንም  እናታችንን አባታችንንም አተናል ይሄ የምድር ህግ ነው ሁሉም ጊዜው ሲደርስ ያልፋል ይሄዳል በተለያየ ምክንያት ሊሆን ይችላል እንጂ
ነገር ግን ሁሌም ማታጡትና ከእናንተ እርቆ የማይሄድ ሁሌ የሚጠብቃችሁ አንድ ነገር አለ እሱም አባታችን እግዚአብሄር ነው አያችሁ እናንተን ለቤተሰቦቻችሁ እንደ ስጦታ ይሰጣችሉዋል እናንተም ከነሱ የቤተሰብ ስጦታ ትሰጣላችሁ ፍቅር ደግነት መልካምነት ሁሉንም በእነሱ ታገኛላችሁ ለቤተሰቦቻችሁ ፍቅር መስጠት ደግሞ እናንተ ምክንያት ትሆናላችሁ ማለት ነው
አያችሁ እግዚአብሄር ድንገት ከእናንተ ነጥሎ ቤተሰቦቻችሁን ቢወስድባችሁ ነገር ግን ቤተሰቦቻችሁን ለእናንተ የሰጣችሁ አምላክ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር አለ ማለት ነው ስለዚህ መከፋት ማዘን ማልቀስ የለባችሁም ሁሌም ቀና ብላችሁ የሰማዩ አባቴ አመሰግንሃለሁ እሺ ልትሉት ይገባል
በመስቀላችሁ ላይ ያለው ፅሁፍ #ፊኮል ይላል ፊኮል ማለት ንግግር አፈ ቃል ትእዛዝ ማለት ነው
ፊኮል ማለት በተዘዋዋሪው እግዚአብሄር ከእናንተ ጋር ነው ማለት ነው ማለት ነው
ሁሌም አዝናችሁ ዝቅ ስትሉ መስቀላችሁን እዩ ፊኮል ሚለውን ስታነቡ ያኔ እግዚአብሄር ከእናንተ ጋር እነደሆነ ታስባላችሁ ማለት ነው ለኔ አሁን እህቴ እናንተ እና መቼም የማይለኝ የሰማዩ አባቴ ከእኔ ጋር አለ ስለዚህ ምን እንለዋለን
የሰማዩ አባቴ አመሰግንሃለሁ እሺ አስቲ አንዴ በሉት
የሰማዩ አባቴ አመሰግንሃለሁ እሺ ህፃናቱ ደስ በሚል ድምፃቸው አመሰገኑ
እርግማኑን ስለ ፈራ ወላጆቻቸውን ድንገት ቢያጡ እንኳ ብዙ እንዳያዝኑ የተጠቀመበት መንገድ ነው
የእሱንና የእህቱን እጣ በህፃናቱ ላይ እንዲያድር አልፈለገም
በሉ ተነሱ ቁርስ እንብላ እንጂ ህፃናቱ መስቀሎቻቸውን ለወላጆቻቸው ሊያሳዩ ተፈትልከው ወጡ
ፊንሐስ በእጁ የቀረችውን አንድ መስቀል ለፊያሜታ አሰረላት
ፍርሀቱ ዘልቆ  ተሰማት......

ይቀጥላል....
ብላቴናው በእርግማን ገፆች ላይ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
.
........ሁለት ጋብሮቮ ሾፌሮች ጠባብ ድልድይ ላይ ስለተገናኙ አንደኛው መኪናውን ወደኀላ አንቀሳቅሶ ሌላውን ማሳለፍ ሊኖርበት ሆነ። ግን ወደኀላ በመንቀሳቀስ ነዳጅ ማቃጠልን ሁለቱም አልፈቀዱም።

ስለዚህም አንደኛው ቮፌር "አሁን ቁርጡን ሲያውቅ ያሳልፈኝ የለ?" ብሎ ጋዜጣውን ዘርግቶ ማንበብ ጀመረ።

ይኸኔ ሁለተኛው ሾፌር ከመኪናው ወጣና ኮፈኑ ላይ ተንጋሎ ፀሐይ እየሞቀ " የኔ ወንድም ጋዜጣውን አንብበህ ስትጨርስ ታውሰኛለህ?" አለው ይባላል።

በነገራችን ላይ ጋቭሮቦች በአለማችን የሚገኙ ቋጣሪ የሆኑ የሰው ፍጡሮች ናቸው። ከቋጣሪነታቸው የተነሳ በምሽት መፅሀፍ ሲያነቡ አንዱን ገፅ ጨርሰው ወደሌላው ገፅ ሲሻገሩ መብራት እንዳይቆጥር አጥፍተው ነው ሚገልፁት ይባላል።😂
@wegoch
@wegoch
#የሰኔ መቅሰፍቶች

  ክፍል - ፬

ቀኑ ቀኑን እየወለደ የእርግማኑ ወርም ሊገባ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተዋል ፍርሀቱን የለመዱት ቢመስልም የለመዱት ፍርሀት ሌላ ፍርሀት እየወለደ ያስፈራቸዋል
ትንናትም ዛሬም ነገም የቤቱ ልዩ አለሞች ህፃናቱ ናቸው ከፊንሀስና ከፊያሜታ ጋ በጣም ተላምደዋል ምኝታ ቤቱ ወደ ሳሎን ተቀይሮ በሚነጠፈው ትልቅ ፍራሽ ሁሉም አንድ ላይ ይተኛሉ
እፍንፍን ጭንቅንቅ ሲሉ ፍርሀቱ በትንሹም ቢሆን ይቀላቸዋል ሁሉም በአንድነት የሞቀ ጨዋታ ውስጥ ይገባሉ ምንም እንዳልተፈጠረ ሀሴት ይሰማቸዋል
ዛሬም በምሽቱ ሰብሰብ ብለው የተፈላውን ሻይ እየተጎነጩ ብርዱን ከኩባያው በሚወጣው ሙቀት በእጃቸው እየሳቡ የፊንሀስን ጣፈፋጭና ደስ የሚሉ ታሪኮችንና የመጽሐፍ ቅዱስ ወንጌሎችን ይሰማሉ
ህፃናቱ እሰከ ልባቸው ዘልቀው ያዳምጡታል ሁሉን እና እያንዳንዷነን ነገር በፅሞና ይከታተሉታል
ወላጆቹም አብረው ከታሪኮቹ ጋር ይተማሉ ቤቱ በፊንሀስ ሞቅ በህፃናቱ ደመቅ ብሏል
ዛሬም አሰፍስፈው እየጠበቁት ነው ፊንሀስ ዛሬ የሱን ጭንቀት አስወግዶ የነሱንም ጭንቀት ከላያቸው ላይ ለማጥፋት ወስኗል
ልጀምር አይደል አላቸው ያዘጋጀላቸውን መፅሀፍ ቅዱስ እያደላቸው አዎ አጎቴ ሁሉም በአንድ ድምፅ
እሺ ዛሬ ምነግራችሁ በህይወታችን ውስጥ ጭንቀት ስለ ተባለ አደገኛ ነገር ነው
መጽሀፍ ቅዱስ ላይ የተጨነቁ ሰዎች ምን ምን አድርገዋል የሚለውን እናያለን
ግን በመጀመሪያ እናንተ ለምን ትጨነቃላችሁ ህፃናቱን በአይኖቹ እየቃኘ ጠየቃቸው
እኔ ማሚ ካመማት እጨነቃለሁ እኔ ደሞ ትምህርት ቤት ዝቅተኛ ውጤጥ ሳመጣ አባዬ እንዳይቆጣኝ እጨነቃለሁ እኔ ደሞ ካመመኝ እጨነቃለሁ ሁሉም ህፃናት ጭንቀቶቻቸው ከየት እንደሚመጡ ነገሩት
ወላጆች ደሞ በአፋቸው ነግረው ባያስረዱትም ይሄ እርግማን የሚባል ነገር በነሱ ጭንቅላት ውስጥ ትልቅ ቦታ እንዳለው በውስጣቸው ያነበንባሉ
እሺ እስቲ እግዚአብሄር የልቤ ስላለው ስለ ዳዊት ልንገራቼሁ እናንተም ትናንሽ መላእክት የእግዚአብሔር የልቡ ሰዎች ናችሁ እሺ ...
እሺ አጎቴ ህፃናቱ በአንድ ድምፅ
ንጉሥ ዳዊት “ልቤ በየዕለቱ በሐዘን እየተደቆሰ፣ በጭንቀት ተውጬ የምኖረው እስከ መቼ ነውሲል በመዝሙር 13:2 ፅፏል ህፃናቱ በወላጆቻቸው ታግዘው ምዕራፉን ገልጠው አነበቡት
 ታድያ ዳዊት ይህን ሁኔታ እንዲቋቋም የረዳው ምንድን ነው ብለን መጠየቅ አለብን እናንተም ልክ እንደ ዳዊት ሲጨንቃችሁ ምን ማድረግ አለብን ልትሉ ይገባል
ታድያ ዳዊት በጸሎት አማካኝነት የልቡን ለአምላክ ያፈሰሰ ከመሆኑም ሌላ በአምላክ ታማኝ ፍቅር ሙሉ በሙሉ ይተማመን ነበር አያችሁ ዳዊት በጭንቀቱ በፍርሀቱ ጊዜ ሁሌም በአምላኩ ጠባቂነት እና ገደብ የሌለው ፍቅር ይተማመን ስለ ነበረ ጭንቀቱ በሱ አካል ላይ ሀይል እንዳይኖረው ያደርጋል
ሌላው በዳዊት መዝሙር 13:5፤ 62:8 አምላክም የከበደንን ነገር በእሱ ላይ እንድንጥል ጋብዞናል ይላል ዳዊት የጨነቀውን የከበደውን ሁሉ በአምላኩ ላይ ይጥል ነበር ማለት ነው ክንዱ ያልቻለውን መከራ በአምላኩ ረዳትነት ያልፈው ነበር ማለት ነው እናንተም ፍርሀታችሁን ጭንቀታችሁን ለአምላካችሁ መስጠት ለሱ መንገር ነው አለባችሁ ማለት ነው ምክንያቱም ሁሌም ለልጆቹ የሚያስብ አባት ስላለ
መከራና ጭንቀት ከእኛ ፊት ቢቆሙም ሁሌ በአምላክ ረዳትነት ማለፍ እንደምንችል ንጉስ  ዳዊት ይነግረናል
ህፃናቱ ልባቸው ተሞላ ሚነገራቸውን ነገር ሁሉ ይረዱታል
ቁጭ ብለው ፊንሀስን ሚሰሙት ሌሎቹ ሰዎች የሆነ ነገር ገሸሽ ሲልላቸው ታወቀ
ፍርሀቱ በአምላክ ይወገዳል..... እርግማኑስ

                  ይቀጥላል..
    ብላቴናው በእርግማን ገፆች ላይ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
#ስለ_ፎቶ
(በእውቀቱ ስዩም)
(ክፍል አንድ)
.
.
ልጅ እያለሁ ፎቶ ብርቅ ነበር ፤ ከእናቴ ጋራ የሆነ ግብዣ እሄዳለሁ፤ የቤት እመቤቲቱ ቡናው እስኪፈላ ከግድግዳው ላይ መስኮት የሚያህል ባለፍሬም ፎቶ መስቀያ አውርዳ በዳንቴል ወልወል አድርጋ ትጋብዘናለች:: በፎቶው ውስጥ ሚስት ጥበብ ቀሚስ ለብሳ ፤ገብረክርስቶስ ጫማ አድርጋ ቁጢጥ ብላ ትታያለች ፤ ባል ሱፉን ግጥም አድርጎ አጠገቧ ቆሞ ይታያል ፤ በሰሌዳው ውስጥ ያለውን ብዙ ቦታ የሚቆጣጠረው የባልና ሚስቱ ፎቶ ነው ፤ ቴምብር የሚያካክሉ የልጆች ፎቶዎች ፍሬሙን ተጠግተው ጣል ጣል ይደረጋሉ ፤ አንዳንዴ እናቴና ጋባዧ ሳያዩኝ መስታውቱን ከፍቼ እበረብራለሁ ፤ ያልተዋጣላቸው ፎቶዎች ከጀርባ ተደብቀው አገኛለሁ፤ በጊዜው ዴሊት ማድረግ እሚባል ነገር ስላልነበረ ያለሽ አማራጭ የከሸፉ ፎቶዎችሽን ሰብስቦ መደበቅ ነው፤ አስራሁለተኛ ክፍል ስደርስ የፎቶ አልበም መጣ፤ ግን በጊዜው የነበሩት አልበሞች ከአምሳ ገፆች በላይ አልነበራቸውም ፤ ከዚያ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሆነው ቦታ፤ ያገለገለ የሰርግ ጥሪ ካርድ ፤ የከሸፈ ሎተሪ እና የመፅሄት ቅዳጅ ይቀመጥበታል ፤የፎቶ አልበም ሲቀርብልን የምናየው በታላቅ ተመስጦ እንደነበር ትዝ ይለኛል ፤ ያኔ የጎረቤት ፎቶ በምናይበት ጥሞና ዛሬ ፊልም የምናይ አይመስለኝም ፤ እያንዳንዱ ፎቶ ደግሞ የራሱ ታሪክ ነበረው፤፤ በከተማችን የነበረው ብቸኛ ፎቶ ቤት እነማይ ፎቶ ቤት ይባላል ፤ የስቱዲዮዋ ባክግራውንድ ሁሌም የዘንባባ ዛፍ ነው፤ ካሜራው የቅየሳ መሳርያ ይመስላል፤ ከጎኑና ከጎኑ ሁለት ትልልቅ ባለ ባርኔጣ አምፕሎች ያጅቡታል፤ አንዱ አምፖል ብቻ የሚለቀው ጨረር ድፍን ጎጃምን ራት ሊያበላ ይችላል፤ ሲመስለኝ ከተማው መብራት ሃይል የለህዝቡ የሚያከፋፍለው ከነማይ ፎቶ ቤት የተረፈውን መብራት ሳይሆን አይቀርም ፤ በጊዜው “ ፊትዎትን በሳሙና በመታጠብ አይንዎን ከትራኮማ ይጠብቁ” የሚል መፈክር በሬድዮ ይነገር ነበር፤ የእነማይ ፎቶ ቤት አምፖል ባጨናበሰው አይን፤ ትራኮማ ተጠያቂ መሆኑ ያሳዝነኛል፤ ብዙ ጊዜ የተነሳነው ፎቶ ለመድረስ በትንሹ አምስት ቀን ይፈጃል፤ ጉጉታችን አይጣል ነበር:: በተለይ ሴቶች የቀጠሮ ቀናቸው እስኪደርስ ድረስ እየተቁነጠነጡ ፎቱዋቸውን ቢያንስ ሁለቴ በህልማቸው ያዩታል፤ ሲኒማ ወደ ከተማው ከመግባቱ በፊት ቅዳሜ ከሰአትን የምናሳልፈው እነማይ ፎቶ ቤት በር ላይ የተለጠፉትን የሳምንቱን ፎቶዎች በማየት ነበር ፤ አልፎሂያጁ የከተማዋ ቆንጆ ሴት የተነሳችውን ፎቶ ከብቦ እያየ “ እዩዋትማ!! እመብርሃንንኮ ነው እምትመስል ” እያለ ያደንቃል ”፤ አንዳንዱ ጎረምሳ በማየትና በማድነቅ ብቻ አይወሰንም፤ ፤ ለፎቶ አንሽው ጉርሻ ሰጥቶ የቆንጆይቱን ፎቶ አጥቦ እንዲሸጥላት ያግባባዋል፤ ከዚያ ፎቶዋን በኪሱ ይዞ በከተማው በመዞር 'ገርሌኮ ' ናት እያለ ጉራውን ይነሰንሳል ፤ ማርክ ዙከርበርግ የሰው ፎቶን Share የማድረግ ሀሳብ የወሰደው ከነማይ ፎቶ ቤት ይሆን
.
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#የሰኔ መቅሰፍቶች

  ክፍል - ፭

ፍርሀቱ የቀነሰ ይመስላል ውጥረት ቀንሶ ጭንቀቱንም ለማስወገድ እየሞከሩ ነው ፊንሀስ ትልቅ ነገር በቤተሰቡ ላይ እየሰራ ነው ደረቁ ሳቅ ወደ ለዛ ተሸጋግሯል ህፃናቱ ብሶባቸዋል ቤቱን ደስታ በደስታ እያደረጉት ነው አሁን አሁን እርግማን የተባለ ነገር እየተረሳ ይመስላል በእስከዛሬው የቤተሰቡ ታሪክ እንዲህ ያለ መሰባሰብና ደስታ ታይቶ አይታወቅም እርግማኑ ብዙ አስከፊ ጎኖች ቢኖሩትም ቤተሰቡን አሰባስቦ አንድ ስላደረገ ደስ አሰኝቷቸዋል
በህፃናቱ የማያልቅ ደስታ ወላጆቻቸው ሀሴት ያደርጋሉ ምንም ነገር ላለማሰብና ሁሉን ነገር ለመርሳት እየሞከሩ ነው እርግማኑንም ቢሆን በአንድነት ለማለፍ ተዘጋጅተዋል ወይ አምላክ እራርቶ የህፃናቱ ሳቅ እንዳይቀየር ሲል ይሄን አመት እንዲዘላቸው እየተማፀኑ ነው
ዛሬ ቤቱ ሞቅ ብሏል ምሽቱ ደመቅ ብሏል የህፃናቱ ጨዋታ ብርዱን አስረስቷቸዋል አካባቢያቸው ላይ ምንም ነገር የለም ከእናት እና ከአባታቸው የወረሱት የተንጣለለው መሬት ላይ ያሉባት መካከለኛ ቤት ተሰርታለች አልፎ አልፎ ከሚታዩት ደሳሳ ጎጆዎች በቀር ቀና ሲሉ ሰፊው ሰማይ ዝቅ ሲሉ ቢሄዱበት የማያልቅ ሰፊ መሬት ነው የሚታያቸው
ፍርሀቱን የጨመረባቸው አንዱ ነገርም ይሄ ብቸኝነታቸው ሳይሆን አልቀረም
በምሽቱም አለፍ አለፍ እያሉ ከሚሰሙት የውሾች ድምፅ በቀር ሌላ ምንም የለም ጨዋታው ደርቷል ሳቁ ጦፋል ልዩ ምሽት ሆኖላቸዋል
ህፃናቱ ይዘምራሉ ይታገላሉ በሚኮላተፉት ትናንሽ አፋቸው ተሰምተው የማይታወቁ አስቂኝ ተረቶችን ያወራሉ ቤቱ በነሱና በፊንሀስ አማካኝነት ነፍሰ ተዘርቶበታል ዛሬም አንድ ነገር ሊናገር ድምፁን ጠረግ ጠረግ አደረገ  ውብ ነገሮችን ለማግኘት ፈልጋችሁ ታውቃላችሁ ልጆችዬ የነገዋንስ ፀሀይ ጀንበሯን ጮራዋን ለማየት ተመኝታችሁ ታውቃላችሁ
ሁሌም የሆነ ነገርን ለማግኘት በፈለግን ቁጥር ብዙ ፈተናዎች ከኛ ጋር ይጋጠማሉ ተስፋ ሳንቆርጥ ሁሉን ፈተና ከተጋፋን የወደድነውን ነገር ከማየት የሚያግደን የለም በጨለማው ሰአት የጨረቃን ብርሀን የናፈቀ እስክትወጣ ድረስ ብርዱን ቁሩን ጨለማውን ተቋቁሞ መጠበቅ አለበት
 ውብ ነገሮችን ለማግኘት ሰው ፍርሃቱን አልፎ መሄድ አለበት፤ በምንፈግልጋቸው ነገሮችና በእኛ መካከል የቆመው ትልቁ ግድግዳ ካለማውቅ የሚመነጨው ፍርሃት ነው
ፍርሀታችንን ሁሌም የምናጠፋው ለምን እንፈራለን ብለን መጠየቅ የጀመርን ሰአት ነው
ሁሌም ላሰባችሁት ላለማችሁት ለወደዳችሁት ነገር ወደ ፊት ብቻ
ህፃናቱ እጆቻቸውን ከፍ አርገው ወደ ፊት ሌላ ሳቅ
ፊንሀስ በሩን ከፍቶ ወጣ ቅድም ስለ ብርሀኗ ሲያወራላት የነበረችው ጨረቃ ዛሬ መልኳ ጠፍቶ ደም ለብሳለች
ደሟ ጨረቃ ለዚ ቤተሰብ ትልቅ ምልክት ናት የጭንቁ ቀን መቀራቡን ማብሰሪያ ምልክት
ያየውን ወደ ቤቱ ገብቶ አንሾካሾከ ሙቀቱ በብርዱ ተተካ ሳቁም ጠፍቶ የበፊቱ የቤተሰቡ መልክ ተመለስ
ጨረቃዋ ነገ ወደ ቀድሞ መልኳ ትመለሳለች
ቤተሰቡስ.....

ይቀጥላል...
     ብላቴናው በእርግማን ገፆች ላይ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ትዝታየ በፎቶ ዙርያ
(የመጨረሻው ክፍል)
( በእውቀቱ ስዩም)
.
በልጅነቴ ትዝ ከሚሉኝ መፈክሮች አንዱ “ ያልሰራ አይብላ” የሚል ነው፤ ስራ ብሄራዊ ሀይማኖት ሆኖ ነበር፤ ይሄ ደግሞ በጊዜው ፎቶ አነሳስ ላይ ሳይቀር ይንፀባረቃል ፤ አንድ ሰው ፎቶ ሲነሳ የሆነ ሰርቶ ማሳያ ነገር ፎቶው ውስጥ ማካተት ነበረበት፤ የቤት እመቤት ከሆነች ጥጥ እየፈተለች ወይም ምስር እየለቀመች ትነሳለች፤ ገበሬ ከሆነ የማሽላ እሸት አንጠልጥሎ ፤ የእንጨት መሰንጠቂያ ያለው ወጣት ደግሞ የሰራውን ቁምሳጥን ተሸክሞ ይነሳል ፤ አንድ ቀን ከአባቴ ጋር ፖሊስ ጎረቤታችን ቤት ሄድን:: በቤቱ ግድግዳ ላይ አራት ሰዎች ጎን ለጎን ቆመው የሚታዩበት ትልቅ ባለፍሬም የፎቶ መስታወት ተሰቅሏል:: “ ሽጉጥ ታጥቀህ የቆምከው አንተ ነህ ፤ቀሪዎች ወንድሞችህ ናቸው ልበል ?” ሲል ጠየቀ አባየ፤
“ አይደሉም! “ አለ ሰውየው” ይሄኛው ለመጀመርያ ጊዜ እጄ ላይ የወደቀው ሌባ ሲሆን እኒህ ደሞ ምስክሮች ናቸው ” በጊዜው ሰርቶ ማሳያም ሆነ ሰሮ ማሳያ የሌለን ልጆች ግን እጃችንን አንከፍርረን እንነሳለን፤ ከፎቶ መነሳት ውስጥ በጣም ከባዱ የእጅ ማስቀመጫ ማግኘት ነበር ፤ በተለይ ትምርት ቤት ውስጥ በቡድን በቡድን ስንነሳ- የነበረብን አበሳ- አይነሳ ! እጅህን ብድግ አድርገህ አጠገብህ የቆመቺው ልጅ ተከሻ ላይ ስታስቀምጠው አመናጭቃ ትወረውርብሃለች ፤ እጆችህን በወገብህ ላይ ብታስቀምጥ" ምነው ጠላ የቀጠነባት ኮማሪት መሰልህ" ይልሀል ፎቶ አንሺው፤ አሳርፍ በሚባለው ፈሊጥ ቆመህ ብትዘጋጅ “ እጅህ ቁርጭምጭሚትህ ላይ ደረሰኮ ፤ የጭላዳ ዝርያ አለብህ? ብሎ ያሸማቅቅሀል፤ እጅህን አገጭህ ስር ብታስደግፈው “ አቡሽ! አለሎውን እስክትወረውረው በጉጉት እየጠበቅንህ ነው” ብሎ ያላግጥብሀል፤ ያለህ አማራጭ እጅህን ኪስህ ውስጥ መክተት ነው፤ችግሩ እኛ የደሃ ልጆች የምንለብሰው ሱሪ ኪስ አልነበረውም፤ “ ሽልንግና ፀባይ ካለህ ከኮሌታህ ላይ ቀንሼ ኪስ ልስፋልህ እችላለሁ” ብሎኝ ነበር የመንደራችን መኪና ሰፊ፤ እኔ ደግሞ ከሁለቱ አንዱ አልነበረኝም፤አንዳንዴ ከስማርት ስልክ በፊት የነበረውን ህይወት ስታስቡት ይገርማል፤ እንደዛሬ ካሜራ በኪሳችን ይዘን ከመዞራችን በፊት ከምናደንቃቸው ዝነኞች ጋር ፎቶ የምንነሳው እንዴት ነበር? ፤ ሙሉቀን መለሰ ዝንጥ ብሎ ስታዲየም አካባቢ ሲናፈስ ታገኝዋለሽ እንበል ፤
“ ወይኔ ሙሌ እንዴት እኮ እንደማደንቅህ”
“ አመሰግናለሁ የኔ ቆንጆ"
“ ካላስቸገርኩህ ፒያሳ ፎቶ ቤት ሄደን ለማስታወሻ የሚሆን ፎቶ እንነሳ?”
ሙሉቀን መለሰ ዘፈኑን ትቶ ዘማሪ የሆነው እንዲህ አይነት ውጣ ውረድ አጋጥሞት ይመስለኛል፤ በነገራችን ላይ ፤በአዲሳባ ከተማ ውስጥ የመጀመርያውን ፎቶ ቤት የከፈተው የማንኩሳ ሰው ነው ፤ መቼም አታምኑኝም፤ ግን አንዴ ጀምሬዋለሁና ልቀጥል ፤ ጎሹ ይባላል፤ ማንኩሴው ከመላው ምስራቅ አፍሪካ የመጀመርያው የካሜራ ጥበብ ባለቤት እንዴት ሆነ እሚለውን አንድ ቀን እተርከዋለሁ :: አዲስአበባ ውስጥ አንድ አርመን የቡልዶዘርና የአውቶብስ ቅልቅል የሚመስል ባቡር ሰርቶ ነበር :: በምርቃቱ ላይ ተገኝቶ ባቡሩን አምስት ፎቶ እንዲያነሳው ለጎሹ ጥሪ ቀረበለት! ጎሹነት ጥሪውን ተቀብሎ አዲሳባ ሲገባ በጊዜው የነበሩት ከንቲባ ሃያ ጊዜ መድፍ አስተኩሰው ተቀበሉት፤ብቻ ስራውን ለመስራት ቀላል ሆኖ አላገኘውም፤ የከተማው ህዝብ በካሜራው ውስጥ ለመግባት ካለው ጉጉት የተነሳ ግልብጥ ብሎ ባቡሩ ጀርባ ላይ ወጣ ፤ ከዚያስ? ትሉኝ ይሆናል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አካባቢው “ሰባራ ባቡር "ተብሎ ይጠራል፤

@wegoch
@wegoch
Forwarded from Mykey (Mikiyas Liyew Tadesse)
እንደምን አደራቹ?

በአካባቢያችን ላይ እንዲኹም በእንቅስቃሴዎቻችን መኻከል ምናገኛቸዉ ''መስማት የተሳናቸዉ'' ሰዎች ምን ያህል ሊነግሩን 'ሚፈልጒትን ነገር እንረዳቸኋለን?

መልካም ቀን!
ግንቦት/ 2012
ሚኪያስ ልየው/Mikiyas Liyew


@Mykeyonthestreet
2024/09/25 04:27:40
Back to Top
HTML Embed Code: