Telegram Web Link
#ወግ_ብቻ

ወንጀለኛው
(ካህሊል ጂብራን)

፨፨፨

አንድ በርሀብ የተጎዳ፣ ፈርጣማ ሰውነት ያለው ወጣት በእግረኛ መንገድ ላይ ተቀምጦ እጆቹን በመዘርጋት ረሃብና ሃፍረት እየሸነቆጡት በሚያሳዝን ዜማ ይለምናል። ምሽት ላይ ከናፍሮቹ እና ጉሮሮው ደረቁበት። እጁ ግን እንደሆዱ ባዶ ነበር። ከተቀመጠበት ተነስቶ ከከተማ ወጣና በአንድ የዛፍ ጥላ ስር ተቀምጦ በምሬት ያነባ ጀመር። ከዚያም ረሃብ ውስጡን እየሞረሞረው ግራ የተጋቡ አይኖቹን ወደ ሰማይ ላካቸውና እንዲህ አለ፤ <<ጌታዬ ሆይ፣ ወደ አንድ ሃብታም ሄጄ ስራ እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት። እሱ ግን ቡትቶዬን አይቶ ፊቱን አዞረብኝ። የአንድ ትምህርት ቤት በር አንኳኳሁ፣ ግን ባዶ እጄን ነበርና ችላ ተባልኩ። ቁራሽ ዳቦ የሚያስገኝልን የትኛውንም አይነት ስረ ሞከርኩ፣ ይሄ ሁሉ ግን ከንቱ ነበር። ተስፋ በመቁረጥ እንዲመፀውቱኝ ለመንኩ፣ መፅዋቾቹ ግን ተመለከቱኝና <ጠንካራና ሰነፍ ነው፤ መለመን አልነበረበትም> አሉኝ... <<ጌታዬ ሆይ፣ እናቴ የወለደችኝ በአንተ ፍቃድ ነው። አሁን መጨረሻው ከመድረሱ በፊት ምድር ወደ አንተ እንድመለስ ፈቅዳልኛለች።>>



ይሄን ጊዜ ፊቱ ተለዋወጠ። ብድግ አለና አይኖቹን በቁርጠኝነት አጉረጠረጣቸው። ከአንዱ የዛፍ ቅርንጫፍ ወፍራም አርጩሜ ቆርጦ ወደ ከተማዋ በመቀሰር ጮኾ ተናገረ። <<ያለኝን ድምፅ ሁሉ አጠራቅሜ ዳቦ ስጡኝ ብያችሁ ነበር። እናንተ ግን ችላ አላችሁኝ። አሁን በጉልበቴ አገኘዋለሁ! በፍቅር እና በርህራሄ ስም ለምኜያችኋለሁ፤ ስብዕና ግን ዋጋ አልነበረውም። አሁን በርኩስ መንፈስ ስም አገኘዋለሁ!>>
ዓመታት ሲያልፉ ወጣቱ ዘራፊ፣ ነፍሰ-ገዳይ እና የነፍስ አጥፊ ሆነ፣ የተቃወሙትን ሁሉ ያጠፋል፤ ጉልበቱን በመጠቀም ብዙ ሃብት ሰበሰበ። ከግብረ-አበሮቹ አድናቆትን አገኘ፣ በሌሎች ሌቦች ተከበረ፣ በህዝቡ ዘንድ ደግሞ ተፈሪ ሆነ።



ሃብቱና በጉልበቱ ያገኘው ተፈሪነቱ፣ አሚሩ የከተማዋ ባለስልጣን አድርጎ እንዲሾመው አበቃው- ብልህነት የጎደላቸው አገረ-ገዢዎች አሳዛኝ ሥራ። ከዚያ በኋላ ስርቆት ህጋዊ ስራ ሆነ፤ ጭቆና በስልጣን ይደገፍ ጀመር፤ ደካሞችን ማጥፋት የተለመደ ተግባር ሆነ እናም ዙፋኖች ይፈሩና ይከበሩ ጀመር።
#ስለዚህ ስግብግብነት ነካ ያደረገው ስብዕና አይናፋሮችን ወንጀለኛ፣ ሰላማዊ ሰዎችን ደግሞ ነፍሰ-ገዳይ ያደርጋል፤ ስግብግብነት የጎበኘው ስብዕና ያድግና መልሶ ስብዕናን አንድ ሺ እጥፍ ጊዜ ያጠፋዋል!

፨፨፨

ምንጭ ፦ እንባ እና ሳቅ(Tears and Laughter)
ደራሲ ፦ ካህሊል ጂብራን
ትርጉም ፦ ተስፋሁን ምትኩ

...ዋጋ የነሱት(ያሳጡት)ነገር ዋጋ ያስከፍላል...!
@wegoch
@wegoch
@wegoch
የጥላቻ ንግግርን በጋራ እንከላከል።

Oromiffa Version:

https://forms.gle/AWq3CWKwKQqvpNoV9

Amharic Version :

https://forms.gle/oMa2WHCrENvFdL3R9

English Version:

https://forms.gle/ZzJ3Kmzafu1S7o479

Thank you for your support!
''የባለቅኔው ኑዛዜ''
ክፍል ፪
ፋሲካ ከበደ እንደፃፈው
አቅራቢ @Mykey21

@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
#የደሜ ዜመኞች

   ክፍል - ፯
  ቀጥያለሁ......

አይነጋ የለ እንደ መንፈቅ የረዘመብኝ ሌሊት ነግቶልኛል
በአይነ ህሊናዬ ስስለው የነበረውን ነገር ከፊያዬ ጋ ለማድረግ ጓጉቻለሁ
ዛሬ ለኔ የፍቅር ቀን ነው
አንድ ነገር አብዝተን በጓጓንለት ቁጥር ላሰብነው ሁኔታ ማድረግ የምንፈልጋቸው ነገሮች ይበዛሉ
እኔም በላፈልኝ ሌሊት ውስጥ አይደለም በአንድ ቀን በሳምንታት እድሜ አድርገን ማንጨርሳቸውን ነገር ሳብሰለስልና ስመኝ ነበር ........ ፍቅር ነዋ ነገሩ
እሷ ያለችበት አለም ይሁን እንጂ የትም እደርሳለሁ
ተመስገን...
ፈጣሪ ምወደውን ቀዝቀዝ ያለ አየር በቅዝቃዜው ወላጆች በደመና ልኮልኛል
መሬቱንም ለማረስረስ ካፊያ ይጥል ጀምሯል
ዝናብ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ሚሰሙን ነጎድጓዶች አሉ
በኔም ስሜት ነጎድጓዱን በተሰመኝ ትላልቅ ስሜቶች ወክዬዋለሁ ዝናቡም ቀስ እያለ ይመጣ ይሆናል ልቤን ዘንባ በፍቅሯ ካረሰረሰችልኝ
ወጣ አልኩና የፍቅሯ ዝናብ የልቤን ሀገር እንዲያረሰረስልኝ ተማፀንኩ
ፊቴን ቀና አድርጌ ሌት ያልተኛውን አይኔን በዝናብ ኣራስኩት
ጠብታዎቹ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ወደ ውስጤ ሲያስገቡ ተሰማኝ
በጠብታው ምት ውስጥ ከዝናቡ በፊት ካፊያ ነው ሚመጣው
ፊያም ባትዘንብልኝ እያካፋችልኝ በመሆኑ ተመስገን አልኩኝ
ወደ ፊያ ተፈተለኩ.....
እጇን ከደረቷ ከታ ኩምሽሽ ብላ ቆማለች ዝናቡ ፀጉሯን አርጥቦ በለበሰችው ጃኬት ይንፎለፎላል
ጉርዷም በስብሷል
እዛ እረጅም ፀጉር ላይ ዝናቡ የሙጢኝ ብሏል የብዙ ኮረዶችን ፀጉር ያረጠበው ዝናብ በፊያ ፀጉር ላይ በማረፉ ደስ ሳይለው አይቀርም
ሌላ እኮ ናት ልጅቷ
ከፀጉሯ እየተንሸራተቱ በሚወድቁት ጠብታዎች የረጠበው ግንባሯን ጠጋ ብዬ ሳምኩት
አሙቀኝ ብላ አቀፈቺኝ ስላስጠበኩአት ተናዳ እኔን ለማርጠብ ፈልጋ ነው
ከላይ ብትቀዘቅዝም ከውስጡአ ሚወጣው ሙቀት አንገቴን ፈጀው
የያዝኩትን ጥላ ዘረጋሁት
እጆቻችንን አጥብቀን አቆላለፍናቸው ....
የሷን ባላውቅም የደም ዝውውሯ እስኪሰማኝ እጄን አጥብቃ ይዛኛለች ...        ፍቅር ነዋ
ወደ ትንሿ ቤቴ መክነፍ ጀመርን
እንግዳዋ በሬን በራሷ እጅ ከፍታ ገባች
ባላሰብኩት ፍጥነት ጃኬቷን እስከ ጉርዷ አውልቃ ከፍሬሼ ገብታ በብርድ ልብሱ ተጠቀለለች
ቤቴን ዙሪያዋን እየቃኘችው ነው
ጨለምለም ካለችው ቤቴ ቤት ለእንቦሳ ሳትል ዘው ብላ ገብታለች
ደማቋ ብርሀኔ ከፍራሼ ውስጥ ገብታ ቤቴን አብርታልኛለች
ቤቴን ስትቃኝ እኔም በተራዬ የብርሀኗ ምንጭ ከየትኛው ውበቷ ላይ እንዳለ ስቃኛት ነበር
አትገባም እንዴ አለቺኝ
እኔም በራሴ ቤት ና ግባ ተብዬ በመግባቴ ደስ ብሎኛል
ለፀጉሯ ሚድረቂያ ፎጣና እረዘም ያለ ሹራብ ሳቀብላት እጄን ጎተት አርጋ ከጀርባዋ እንድሆን አዘዘቺኝ
እኔም ጉብ አልኩባት
በብርድ ልብስ በሞቀው አየር ውስጥ እግሬን ወደ ውስጥ ሰደርኩት
እግሯ እግሮቼን ሲነኩት ቅዝቃዜዋ ጣቶቼን አስደነገጡአቸው
ወገቧ ከሆዴ ጋ የሙጢኝ ተጣብቋል
ከላይ ከለበሰችው ሸሚዝና ከውስጥ ሱሪዋ በቀር ምንም የለም
እኔም ወደ ትእዛዟ ገባሁ...
ፀጉሯን በፎጣው ማድረቅ ጀመርኩ ዳሌዋ ጋ ሊደረስ ትንሽ የቀረው ፀጉሯን አፍተለትለው ገባሁ
ፎጣው በዝናቡ ውሀ ይደርቃል እኔም ማላውቀው ነገር ትንፋሼን ያደረቅው ጀምሯል
የቀዘቀዘ ሞቃት ሆነቺብኝ እዛው መሞቅ ጀመረች
እኔም በአንገቶቿ ስር ጭምር እየገባሁ ፀጉሯን እየያወጣሁ ተያያዝኩት
በዙ ነገሮች የልቤን ምት ጨመሩት
እግሮቻችን ተጠባብቀዋል
ዳሌዋ ከወገቤ በታች የሙጥኝ ተጣብቋል እጆቼ በሳሱ ገላዉቿ ላይ ስልጣን አጊተዋል
ቤቴ ወሬ ናፈቃት ምትሰማው የሁለት ሰዎች ፈጣን ትንፋሾችን ነው
ከወገቤ በታች ጭንቀት ወጠረ
ፀጉሯ እስኪበቃው ደረቀ ወደዛ ወረወርኩት  ለስ
እጆቼን መሰስ አድርጌ ከጀርባዋ ላይ ጣልኩት ጀርባዋ ሙቅ ነው ለስላሳ መዳፎቼ ትልግ ግዳጅ ላይ ናቸወቀ
ኋላዋ አስፈራኝ እኔም ፈራሁ ጀርባዋ ከበደኝ ለሆነ ፈተና ዝምታዋ እንደመጣ ገባኝ
አልቻልኩም እናንተዬ በጣም የበዛ ደም እየፈሰሰኝ ነው አሁን ላይ ትንሽ ዜማ ላጫውትላችሁ
            ውብ አለም የሌለሽ እንደው ይጨንቀኛል
            ይህ ፍቅርሽ ስንቴ ገሎ ስንቴ አድኖኛል
                              ጎሳዬ ነው ትንሽ ፋታ እንውሰድ እንጂ
አዎ በገሎ ማዳን ውስጥ ነው ብዙ ሞቶች ከብዙ ድህነቶች ጋ ትግል የሚያደርጉት
መተ ተብዬ ዛሬም እየኖርኩ ነው አሁንም ተመልሼ መሞቴ አይቀርም ግን ከእንግዲህ ከሞቴ ሚያስነሳኝ ሰው ስለሌለ በዛው መቅረቴ ነው
አዳኜ እሷ ስለነበረች ከእንግዲህ ሞት እንጂ መዳን በኔ ዘንድ የለም        ስቃይ ብቻ
       
                   እመለሳለሁ......
           ብላቴናው በደም ቀለም

@wegoch
@wegoch
@wegoch
''የባለቅኔው ኑዛዜ''
ክፍል ፫
ፋሲካ ከበደ እንደፃፈው

@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
Forwarded from Mykey (Mikiyas Liyew Mykey)
ረመዳን ከሪም!
@Mykeyonthestreet
#ወግ_ብቻ
.
እንደ አውሮፓዊያን የዘመን ቀመር በ 1926 አንድ ታዋቂ የሩሲያ ደራሲ በድብርትና በሐዘን
ስሜት በመሰቃየቱ ህክምና ለማግኘት ወደ ስነ ልቦና ሐኪም ጎራ አለ።
.
.
ከምርመራው በኋላ
የሐዘን ስሜት የሚያጭሩ ተረቶችን ከማንበብ ታቅቦ በምትኩ ደስታና ሳቅ የሚፈጥሩትን
እንዲያነብ ሐኪሙ መከረው። እንዲያውም አስቂኝ የሆኑትን የሚኻኤል ዞሼንኮን (Mikhail
Zoshchenko) ድርሰቶች ቢያነብ በጤናው ላይ አመርቂ ለውጥ እንደሚያመጣ አበክሮ
አስረዳው።
.
ግና ደራሲው የሰጠው መልስ ሐኪሙን በድንጋጤ እንዲዋጥ አደረገው-
«ሚኻኤል ዞሼንኮ ማለት እኔ ነኝ» ብሎ።
.
.
አሜሪካዊው ጸሐፊ አልበርት ሐበርድ
«ለሌሎች የመጽናኛ እና የደስታ ስሜት ፈንጣቂ የሆኑ ብቁ ሰዎች ብዙ ጊዜ ራሳቸውን
ለማጽናናት ሳይቻላቸው ይቀራሉ» ይለናል። ራስህ የፈጠርከው መድሃኒት ለሌሎች ፍቱን
ሆኖ ያንተን በሽታ ለማርከስ ሲሰንፍ እንደማለት ነው።
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ፍም በሆነ ገላ ቤቴን ባበራው ውበት መካከል ውስጥ ነኝ
ለትንሽ ደቂቃዎች በጋለ ገላ ታስሬ ነበረ ፈተና ይሁን እውነተኛ ስሜት ምንም አላወኩም ፈተና ከሆነ እንዳለፍኩት እርግጠኛ ነኝ
ደሞም ፈተና ነው.....
ከውብ ፀጉሯ ብድግ ብዬ ጀርባዋን እየሳሳሁለት ትቼው ተነሳሁ ትናንት የገባሁት ቃል የጋለው ገላዬን አቀዝቅዞልኛል
ንዝረቴን አቁሞልኛል       ቃል ነዋ
ለእግሯ የሚሆን ካልሲ ላመጣላት ወደ ውስጥ ገባሁ
ባለችበት አገኘሁዋት ምን እናድርግ አለቺኝ ያመጣሁላትን እየተቀበለቺኝ
ቤቴ ድምፅ ሰማች ከችኩል ትንፋሾች ነፍስ ያለው ቃል ሰማች
አራበሽም አልኩአት ብድግ ብላ እኔ ነኝ እንደውም ሰርቼ ማበላህ አለቺኝ
ሙያዋ ሊፈተን መሆኑ ነው እንግዲህ
አስቀድሜ ቤቴን ሙሉ ስላደረኳት ምንም ይጎድላል ያልኩት ነገር የለም
አንድም ነገር ሳረዳት ሁሉንም እያንጎዳጎደች አውጥታ አዘጋጀች
እዚ ቤት ምትኖር ሌላ ሴት አለች እንዴ ብላ ጎሸም አደረገቺኝ
በል እንጀራ ገዘተህ ና እሺ ሚሰራውን በምን ልንበላው ነው አለቺኝ
እኔም ፈጠን ብዬ ወጥቼ ሁለት እንጀራ ከሰፈሩ ገዝቼ መጣሁ
እውነትም ፍጥነቷ ወሬ ላይ ብቻ እንዳሎነ ተረዳሁ ከመቼ ከትፋ ከመቼ ምን ብላ ሽንኩርቱን አቁላልታ ቲማቲሙን ስትጨምር ደረስኩባት
ምን እንደምትሰራ ያወኩት የባልትናውን ሽሮ ስትጨምር ሳያት ነው
ወፍራምና እረዥሙ ሹራቤ ለሷ የተሰራ ይመስል ውበቱ ጨምሯል
ያደረኩት ጸጉሯ ግርማውን ተላብሷል
የኔ እመቤት ቤቴን ማሞቅ ላይ ነች ጉድ ጉድ ስትል በቃ ሀሴቴ ከፍ አለ ሚስቴ እንድትሆን ተመኘሁዋት
ግን ቤቴ መተሽ ሽሮ ሰርተሽ ነው ምታበዪኝ አልኩአት ወደ እሷ ጠጋ እያልኩኝ
ማቀፍ ስለፈለኩ ነው ወሬውን ጣል ያደረኩት
ይው ስጋው እንዳያልቅብህ ብዬ እኮ ነው አለቺኝ መቼም ወሬዋ አይጣል ነው
እኔም በከፈተችልኝ መንገድ ገባ አልኩና ቅድም ትቼው የሄድኩት ጀርባ ተመልሼ ተጠመጠምኩበት
ወገቧን በእቅፌ አስገባሁት
ቆይ ላቅምስህ ብላ በማማሰያው ቀንጥባ ሰጠችኝ በአንገቷ ስር እርመሰመሰው ገባሁ ከንፈሮቼ እረጠቡ
አንገቷን ቀና አድርግ ጥርሷን ነክሳ ፈገግ አለች
መዞር ስለፈለገች እኔም ፈቀድኩላት
እጇቹአን አንገቴ ላይ እንደ ማህተም አጥብቃ አሰረቻቸው ወገቧን ይበልጥ ወደ እኔ አስጠጋሁት
ግንባሮቻችን አገጣጠምናቸው ከናፍርቷ ቀያይ ናቸው ዳር ዳሩ ላይ ጠቆር ያለው መስመር የበሰለ ኢንጆሪ አስመስሏቸዋል
ኢንጆሪን መተው ከባድ ነው ባህታዊ እንኳን ከባእቱ የሚያስት ውበት ከፊቴ ድቅን ብሏል
አይኖቼን ከይኖቿ ነቅይ ወደ ከንፈሯ በድጋሚ ጣልኩት ከንፈሬን አስከተልኩት
ደስ የሚል .......
ከተጣበቅንበት ያላቀቀን የሽሮዋ ተክ ተክ የሚል ድምፅ
ደረሰ አለቺኝ ደግማ ከንፈሬን እየሳመቺኝ
ሁሉንም አዘጋጅተን ወደ ገበታችን ቀረብን
ነጭ ወይን ከፈትኩኝ ለክብሯ ብዬ
ሽሮ በወይን አለቺኝ
ወደ ጂፓሴ ጠጋ ብዬ  የጥልዬን ክፉ አይንካሽ ሚለውን ዜማ ከፈትኩት
ጠጋ አልኩና የልቤን በዜማው አልኩአት
የመጀመሪያውን ጉርሻ ከአፌ ላከችለኝ ብርጭቆቻችንን አገጫጨናቸው
ለፍቅር ....
ከትዝታዬ ተመልሻለሁ ያልጨረስኩላችሁን የጥልዬን ዜማ ፋታ እንውሰድበት
                      የልቤን ልንገርሽ
                     ሳልደብቅ ገልጬ
                    በጣም እወድሻለሁ ከሂወቴ አብልጬ
                   መከራና ስቃይ ግድ የለም ይቆየኝ
                   እግዜር በጥበቡ ካንቺ ብቻ አይለየኝ
አዎ አሁንም መከራና ስቃይ በኔ ላይ ቢፈራረቁም ግድ የለም ይቆዩኝ ስሜቱ ቢከብድም አንቺን ከማገኝሽ ከትዝታሽ ይኸው የማገኝሽ እስኪመስለኝ በትዝታሽ ውስጥ ነኝ የኔ እመቤት
             
                     እመለሳለሁ......
                ብላቴናው በደም ቀለም
@wegoch
@wegoch
@wegoch
''የባለቅኔው ኑዛዜ''
ክፍል ፬
ፋሲካ ከበደ እንደፃፈው

@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
#ሱዳን__ገባ_አሉ__ማ__ኮሮና

ኮሮና "ጠቃልዬ ሱዳን ገብቻለሁ" አለ አሉ።......የኔ ሀሳብ አይደለም (አትኮሳተሩብኝ) አሉ ነው። ....አንድ ጠበል ቦታ ሰይጣን የያዘው አንድ ሰው አባ በመስቀል ግንባሩን ብለው "ማን ነህ አንተ?" ሲሉት "ኮሮና" አለ አሉ። ልብ አድርጉልኝ እኔም የሰማሁትን ነው ኃላ አብርሃም አለ ብላችሁ ትዝብታችሁን እኔ ላይ እንዳትጥሉ ......ከዚያ በኃላማ ሰው ሁሉ መላ አካላቱ ጆሮ ሆኖ ወደ ፀበል ቤቱ አተኮረ አሉ (አሉ ነው ልብ አርጉልኝ)......አባ ቀጠሉ "ምንድን ነው አላማህ?"አሉት አሉ በጆክ የያዙትን ፀበል አንዴ ካከናነቡት በኃላ እሱም እየተንቀጠቀጠ "ያው ህዝቡን መጨረስ ነዋ አዋቂ አልል ህፃን አልል......."አባ ይሄኔ አላስጨረሱትም በመስቀል አናቱንና አንድ ጆክ ፀበል ደረገሙበት እየተብረከረከ "ጥንቃቄያችሁስ አይረባም ነበር በፀሎታችሁ አቃጠላችሁኝ እንጂ" አለ አሉ አባም "የት አባክ አንተ ከይሲ......እሸኝሀለው ዛሬማ አንላቀቃትም" አሉት አሉ......ይሄኔ ውጪ ያለው ምእመን ሳኒታይዘር ነሽ አልኮል ነሽ አውጥቶ እጁን ተቀባባ አሉ.......አሁን ትወጣለህ አትወጣም እያሉ በመስቀል ሲደበድቡት በፀበል ሲጠምቁት ብዙ ካስቸገረ ኃላ "ሱዳን ገብቻለሁ በቃ" አለ አሉ።ህዝቡ ደስ አለው ጥቂቶች እንደውም ሳኒታይዘር ፣አልኮል የያዙበትን እቃ እንደ ኳስ ወደ ላይ አጉነው እየመቱ ሲያሽቀነጥሩት ታይተዋል አሉ....(አሉ ነው ግን)......ገሚሱም ተቃቅፎ በእንባና ሳቅ ፊቱ ተጥለቅልቆ ታይቷል አሉ.......ሰው እኮ ግርም ይላል ከፈጣሪ ደጃፍ ሄዶ የሰይጣንን ቃል ሰምቶ ይቦርቃል፤ኮሮና ህዝቡን ሊያዘናጋ ይሆን ወይስ እውነት ሱዳን ገባ እንጃለት........እና እላችኃለው ይሄንን ወሬ የሰማሁት ከእናቴ ነው ....ከቤት ስትወጣ እንደ አልቃይዳ ተሸፋፍና በፊት ጭንብል ላይ ነጠላዋን በነጠላዋ ላይ እጇን አድርጋ (ቫይረሱ እጇን ፈልቅቆ የሚገባ ነበር የመሰላት....ጥንቃቄ ላይ እኮ እሳት ነች) ....ነበር ።ስትመለስ ግልጥልጥ ብላ ፈገግ ብላ መጣች። እማ የእጅ ውሀ ላቅርብልሽ ስላት "ተወው ባክህ...ኤዲያ" አለች በማን አለብኝነት ኮራ ብላ.....እንዴ ምን ተገኘ እማ ስላት "ኮሬና ተጠቃሎ ሱዳን ገባ አቡዬ ...የኢትዮጵያ አምላክ መች ጥሎን ይጥለንና..." .......ግራ ገብቶኝ እንዴት? ማን ነው ያለው? ስላት "ፀበል ቦታ አስለፍልፈው ወደ ሱዳን ሸኙት" አለችኝ። ምን አልሽኝ እማ? የት ፀበል ቦታ ነው? "ኧረ ምኑን አውኩት የት ደብር እንደሆነ ብቻ አሉ ነው "ብላኝ እርፍ.......ይሄኔ ነው መሸሽ...ደስታም ጥርጣሬም ለሁለት ሰንጥረውኝ አለ አይደል የጭንቀት ፈገግታ ፈገግ አልኩ.....

አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
@wegoch
@wegoch
@paappii
#የደሜ ዜመኞች
     
    ክፍል - ፱
   ቀጥያለሁ......

ቤቴ በውብ ንግስት ጣፋጭ በሆነች ሽሮ ከምርጥ ወይን ጋር ከምሰማው ጥዑም ዜማ ጋ ሌላ ሆነናለች
የሁሉም መሰረት ደሞ እሷ ናት
ባማሩ እጆች የተሰራውን ምግብ በወይኑ እያወራረድን በውብ ዜማ ተመስጠን በልተን ጨረሰን
ዛሬ ሁሉም ነገር ደስታ ብቻ ነው
ከትዝታዬ መለስ ልበል አንዴ ብቻ ስሙኝ አደራ እንዳታዝኑብኝ      እሺ
ባሰብኩት ሁኔታ በጣም ህመሜ ብሶብኛል ይህን ምፅፍላችሁ ቃሌ ድምፅ ሆኑአችሁ እንድትሰሙኝ ብቻ ሳይሆን ወደ ትዝታዬ ለመመለስ የማደረግው ፍቱኑ መዳኒቴም ጭምር ነበር
ከአፍንጫዬ ሚወጣው የደም ጠብታ ዛሬ መልሱን አገኘ አባቴ ሀዘኑን እንኳ ሊደብቅ አልተቻለውም
ፊት ለፊቴ ተንበርክኮ ከተራመዱ ብዙ ጊዜ የሆናቸውን እግሮቼን በእንባው አራሳቸው
እንባው መዳኒት ሆኖኝ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ከጉልበቴ ስር ባነሳው ምንኛ ሀሴት ባደረኩ
ላተርፍህ ብችል.... ሊጨርሰው አልቻለም ነፍሴን ልስጥህ... በሀዘን ሳግ ሆኖ እንባ እየቀደመው ምንም ሊያወራኝ አልቻለም
የኔ አባት አለኝ በእንባው የራሳቸውን ጉልበቶቼን ይዞ
ያ አዝማሪ ጀግና የስንኞች አባት ስንት ዜማ ባንቆረቆረበት ልሳኑ አፉ ለኔ እንዲህ ቃል ሲያጥረው ማየት ምንኛ ህመም ነው
ለስቃይ የፈጠረኝ ሰው.....
ልጅህ የደም መርጋት በሽታ አለበት ብለውታል ሲመስለኝ ምሄድበትንም ቀን አያይዘው ሳይነግሩት አልቀሩም
ማንባት የለመደው አይኔ ዛሬ ሲቃ በሌለው ድምፅ ዘለላውን ብቻ ዱብዱብ ያደርገው ጀምሯል
ለምን እንደማለቅስ አላውቅም ምን አልባት ለአባቴ ስል ይሆናል እንጂማ እኔ ወደ ማርፍበት አለም ልጓዝ ነው ከዚ ካለሁበት ከስቃይ ምድር ለቅቄ
አድሎኝና ብዙ ጊዜ ኖሮኝ ከዚ በባሰ ስቃይ ውስጥ ሆኜ እንኩዋ ውብ ትዝታዎቼን ብነግራችሁ ምንኛ ደስ ባለኝ ነበረ
ግን በቃ ምን አባቴ ላድርግ......
ግን ምነግራቹ ነገር አለኝ
ዛሬ ይሄን ምፅፍላችሁ በደም ቀለም ብቻ አይደለም
በደምና በእንባ ዘለላዎቼ እየጠቀስኩ ነው ማጫውታችሁ
እንባዬ ለአባቴ ነው ደሜ ደሞ ለፊያዬ
ደሞ አልፈራሁም
ስሞት እኮ ለዘላለማዊ ህይወቴ ውልደቴን እያበሰርኩ ነው
አልቅሼ ነው የመጣሁት አልቅሼ ነው ምሄደው ለዛም ነው እንባዬ
ደሞ እጅግ ደስ ብሎኛል ወደ እሷ እየሄድኩ ነዋ እዚ በትዝታ ከምዋትት እዛ በፍቅር መላእክት እርዳታ ብፈልጋት ይሻለኛል
መንገዱ ላይ ነኝ አዎ መንገድ ላይ ነኝ
ሞት እንደ ንፋስ ሽው ሲል እየተሰማኝ ነው መልአከ ሞት ለቀም ሊያደርገኝ አሰፍስፎ ቆሙአል
እኔም ከሱ እጅ ለመግባት እየዳዳሁ ነው ወደ እሷ ለመጓዝ
ውልብ ትልብኝ ገባች እኮ እናንተዬ
አረ እስቅላችሁ ጀመር   አለም ነው
እዛ እንገናኝ እንጂ እናንተ ሳመጡ ሰራግችን አይደገሰም በእውነት ስላችሁ
ሀዘን ደስታ ስቃይ ምን አይነት ስሜት ነው እናንተዬ
እዚ የጀመርኩትን ውብ ትዝታዎቼን እዛው ስትመጡ ከእሷ ጋ እንጨርስላቹሀለን
መቼም ከዛ አይቀር
ለመጨረሻ ጊዜ ሁለት ዜማዎችን አጫውታላቹሀለሁ
አንደኛውን አሁኑኑ ሁለተኛውን እሷን ፍለጋ ልሄድ ስለሆነ የዛን ሰአት አካፍላቹሀለሁ
ስወለድ አባቴ 15 አዝማሪ አምጥቶ ድል ባለ ዜማ ነው የተቀበለኝ ሲዜምልኝ እንደመጣው እያዜምኩ ነው ምሄደው
ስሞት አዝማሪዎች ባይኖሩም
በምከፍተው ዜማ አዝያሚው ሲያዜም እኔ እና መልአከ ሞት እዝማቹን እየተቀበልን ጉዞአችንን እንቀጥላለን
ኋላ ሳታመሰግነን እንዳትሉኝ ደሞ በጣም እወዳቹሀለሁ
ሰማይ ቤት አባቴ በጣም ስለሚናፍቀኝ እዛ ለማገኛቸው አዳዲስ ጓደኞቼ ደሞ የሱን ትዝታ ከመላእክት በምዋሰው ብዕር አወጋቸዋለሁ
ልዩነቱ እዛ ምንም ስቃይ የለም
በጸአዳ ባጌጠ ደስታ ውስጥ ሆኜ ነው አባቴን እና እናንተን ምጠብቀው
ግን
ይሄ የደሜ ዜማ ነው ባማሩ ትዝታዎች በስቃይ ምፅፈው
         አልፈራሁም ደሞ ማርያምን
 ዜማውን ተጋበዙልኝ
                   ልምጣ ወይ ልቅር ምን ይሻለኛል
                  ከፍቅርሽ ሚያስጥል ማን ዘንድ ይገኛል
                  ስለት አለብኝ ከርቤ እና እጣና
                  ለመተያየት እንዲያበቃን
       ማ ዘንድ ይደር ሄዶ ጎኔ ሰው አልሆንም ካላንቺ እኔ
                                ቴዲ ነፍሴን ስሙልኝ አቦ
አዎ ማድርበት ምሸሸግበት ጥግ አጥቻለሁ ሁሉም አንቺን በማጣቴ የሆነ ነው
ልምጣ ወይስ ልቅር እያልኩ ስባዝን ይኸው በጊዜው እራሱ ከተፍ ብሎልኛል
ፀሎቴም ተሰምቶ ስለቴን እዛው ለመላእክት እሰጣለሁ ካንቺ ላገናኘኝ ፈጣሪ እንዲሰጡልኝ

                 ሊፈፀም ሰአቱ ደርሷል
                        እቀጥላለሁ....
          ብላቴናው በእንባ ዘለላ ከደም ቀለምጋ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
...የሂትለር ሀዘኔታ...(የሂትለር ያልሆነ እውነተኛ ታሪክ)
አልጋዬን ሳነጥፍ፣ቤቴን ለማስዋብ ከዳር እስከ ዳር የወጠርኩትን የአረንጓዴ፣ቀይ ጥቁር እና ነጭ ቀለማት ህብር የሆነ ማዳበሪያ ተገን አድርጋ በነፃነት ማገሬ ላይ የምትራመድ አይጥ ከሀሳቤ አናጠበችኝ።ተወርውሬ እስከ ማዳበሪያዬ አነቅኳት።እስከ ዛሬ የበደለችኝ ትዝ አለኝ።ጫማዎቼ፣ልብሶቼ፣ምግቤ፣ሌላም ብዙ ነገሮቼ፤የአጄን የማነቅ ሀይል በእጥፍ ጨመርኩባት።ስትፍጨረጨር ተሰማኝ።ስቃይዋ ሀዘኔታን በውስጤ ዘራብኝ።አይጣዊ መብቶችዋ ትዝ አሉኝ።ለሰከንዶች ሃይማኖተኛ ሆንኩ።ነፍስ እያጠፋሁ እንደሆነ ታወሰኝ።እጄ ከእዚህ ሊበረታ አልቻለም።ለቀቅኳት።የራሴ ህይወት ይልቅ አሳሰበኝ።ሳልፍጨረጨር እየሞትኩ እንደሆነ ገባኝ።በራሴ እጆች።ቀናት እየጠፉብኝ እድሜዬ እየሮጠ ዛሬ የኖርኩትን ነገ እየደገምኩ፣ልጅ ነኝ ጊዜ አለኝ እያልኩ አርጅቼ ልሞት ነው።አይጧን አስታወስኳት ስለቃት ያልተገራ እና ያልፈቀደችውን ጉዞ ነበር ያጀረገችው።ካገኘችው ጋር እየተላተመች ወደ ታችችችች።ለጊዜው ራሴን ከተጠያቂነት ለማፅዳት እስትንፋሷን ለማረጋገጥ ስላልደፈርኩ ደፋር ለሆነ አካል እድሉን ሰጠሁ።ማለቴ ለድመታችን።

@wegoch
@wegoch
@wegoch
''የባለቅኔው ኑዛዜ''
ክፍል ፭
ፋሲካ ከበደ እንደፃፈው

@Wegoch
@Wegoch
@Wehoch
ምርቃትዋን ከ ''ባለቅኔው ኑዛዜ'' መፅሐፍ ላይ
አቅራቢ @Mykey21

@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
#ወግ_ብቻ
.
#ድኻ_ወርቅ_አይግዛ› በዳንኤል ክብረት

‹ድኻ ወርቅ አይግዛ ከገዛም ይጥፋበት› ይላሉ የምንዳዬ እናት አባዬ፡፡ ‹ምነው አባዬ ድኻ በመከራ የገዛውን ወርቅ እንዴት ይጥፋበት ይላሉ› ብለን ሞገትናቸው፡፡ ‹እይውልህ እኛ ሠፈር አራት ኪሎ አዲሴ የሚሏት አንዲት ጎረቤታችን ነበረች፡፡ ቁርስ፣ ምሳና እራት የተዘበራረቁባት፡፡ ለነገሩ ላለው ነው እንጂ ለሌለው ሰው ምግብ ስሙ ያው ምግብ ብቻ ነው፡፡ ምግብ - ቁርስ፣ ምሳ እራት የሚሆነው በሰዓቱ ስታገኘው ነው፡፡ በሰዓቱ ካላገኘኸው ያው ምግብ ብቻ ነው፡፡ ከድንጋይ ትፈልቅቀው፣ ከሳጥን ትስረቀው ሳናውቅ አንድ ቀን በድንገት አራት ኪሎ ወርቅ ቤት ሄዳ ወርቅ ገዛች ተብሎ ተወራ፡፡ የቡና ሴቶች ‹ግማሽ ግራም ወርቅ ገዝታ በከረጢት ቋጥራ አስቀመጠችው› ብለው ያሽሟጥጧታል፡፡

የገዛች ለት ምሽት እኛ ቤት ቡና ተጠርታ መጣችልህ፡፡ ሴቱ ሁሉ ግጥም ብሏል፡፡ ተርብ ተርቦቹ ደግሞ የዛን ቀን አንድም ሳይቀሩ ተለቃቅመው መጥተውልሃል፡፡ ገና ወደቤት ስትገባ ከሁላችን ለይታ ‹ወይዘሮ የወርቅ ውኃ ደኅና አመሹ› አትልልህም፡፡ አሁን በእርሷ ቤት ወርቅ መግዛቷን ልትነግረን እኮ ነው፡፡ ተያየንና ‹ኡኡቴ› ብልን ዝም አልን፡፡ ገና ከጠፈር ወንበሩ ላይ ሳትደላደል ‹እኔኮ በዚህ ዘመን ድኻ እንዴት ይኖራል፤ እኛስ እሺ› ብላ አረፈችው፡፡ ‹እናንተ እነማን ናችሁ› አለቻት እቴኑ በዓይኗ ቂጥ እያየቻት፡፡ ከምንም ሳትቆጥራት ‹ኧረ እንዴው ተውኝማ፣ ወርቅ እንደዚህ ሰማይ ይንካ› አለች ቆሎውን እየዘገነች፡፡ ‹እኛ ወርቅ ዘመን እንጂ ወርቅ ምን ያደርግልናል› አሏት እማማ ትጓደድ፡፡ ላምሮት ተናደደችና ‹ምን ዳር ዳር ትያለሽ፣ ወርቅ ገዝተሻል› አለችና አፈረጠችው፡፡ ሴቱ ሁሉ አንድ ጊዜ ቤቱን በሁካታ ሞላው፡፡ መቼም እርሷ አፍርጠው ናት፡፡

ሳቃችንን ሳንጨርስ ‹ቆይ ቆይ እስኪ› አለች አዲሴ ጆሮዋን እንደ አንቴና ሰቅላ፡፡ መቼም ከአራት ኪሎ ሠፈር ጯሂና አስጯሂ አይጠፋም ብለን ጸጥ አልን፡፡ አራት ኪሎ ጠብና ዕርቅ የተለመደ ነው፡፡ ተደባዳቢና ገላጋይ በየተራ ነው፡፡ ዛሬ ትደባደባለህ፣ ነገ ደግሞ በተራህ ገላጋይ ትሆናለህ፡፡ ሁላችን ኮንዶሚኒየም ላይ እንደተሰቀለ ዲሽ ጆሮአችንን አከታትለን ብንሰቅልም የመንገደኛ ተረብ ብቻ ነው የምንሰማው፡፡ አዲሴ ተነሣችና ሳንዱቁ ላይ በልብስ ተሸፍኖ የተቀመጠውን ራዲዮ እስከ አንጀቱ ድምጹን ለቀቀችው፡፡ አበደች እንዴ ብለን በግራ ዓይናችን ገላመጥናት፡፡

‹ዛሬ በዋለው የዓለም ገበያ› ይላል ራዲዮኑ፡፡ እርሷ እዚያው እንደተለጠፈች ናት፡፡ እዚህ አራት ኪሎ ያለው የጉልት ገበያ የሚናፍቃት ሴትዮ የዓለም ገበያ ምን ሊያደርግላት ነው ብለን ሳቅን፡፡ ለወትሮው በዱቤ የሰጧት እንዳያንቋት ገበ ድርሽ አትልም ነበር ነበር፡፡ እንዲያውም እማማ ትጓደድ ‹አዲሴኮ ገበያ ብቻ ሳይሆን ገበያው የሚባል ሰውም ትፈራለች› እያሉ ይተርቧት ነበር፡፡ ራዲዮው ‹ዛሬ በዓለም ገበያ ወርቅ በካራት ይህን ያህል ተሽጧል› ሲል ‹እንዴው በደኅና ጊዜ ባልገዛ ይቆጨኝ ነበር፡፡ ለካስ ሰው ልጁን ወርቁ፣ ወርቂቱ፣ ወርቄ፣ ወርቅ አገኘሁ፣ ወርቅ አለማሁ፣ ጥሩ ወርቅ፣ አመለ ወርቅ እያለ የሚጠራው ወርቅ እየተወደደበት ነው› አለችና የግራ እጅ መዳፏን በቀኝ አራት ጣቶቿ ደበደበችው፡፡

ከዚያ በኋላ አዲሴን ማን ይቻላት፡፡ ከሱቅ በዱቤ ዕቃ ስትወስድ እንደ ድሮው መለመን፣ መለማመጥ ቀረ፡፡ ‹ማነህ ባለ ሱቅ፣ እስኪ አንድ አምስት ኪሎ ስኳር አምጣ› ትለዋለች፡፡ ‹እንዴ እማማ አዲሴ፣ በኋላ ባይከፍሉኝስ፤ ያለፈውን በመከራ አይደል እንዴ የከፈሉኝ› ሲሏት ‹ያለፈው አለፈ፣ በቃ እናንተ ሰው ይቀየራል ብላችሁ አታስቡም፤ አምጣ ባክህ፣ ቢበዛ ወርቄን ሽጬ እከፍልሃለሁ› ትላቸዋለች፡፡ ኧረ እንዲያውም አንድ ቀን አንድ ቄስ በዚያ ሲያልፉ ጠራቻቸውና ‹ዛሬ ሲያቃዠኝ አድሯል ይርጩኝ› ትላቸዋለች፡፡ ‹የክርስትና ስምሽ ማነው› ይሏታል ‹እኅተ ወርቅ› ትላቸዋለች፡፡ ቄሱ ደንግጠው ‹እኅተ ማርያም› ማለትዎ ነው› ይሏታል፡፡ ቀኝ እጇን ወደ ጎን እያውለበለበች ‹እርሱ የነዛ የነዛ ስም ነው› አለቻቸው፡፡ ‹ታድያ እኅተ ወርቅ፣ አይ፣ ያልተማረ ሰው ሰጥቶዎት እንዳይሆን› ይላሉ ያልገባቸው ቄስ፡፡ ‹ይኼው ነው አባቴ፣ካልተረዱት ይተውት› አለቻቸው፡፡

ድሮ አዲሴ ቀበሌ መሄድ አትወድም ነበር፡፡ ‹እነርሱ መዋጮ ብቻ ነው ሥራቸው› ትላለች፡፡ ወርቅ በገዛች ሰሞን ‹ምነው ስብሰባ በተጠራ፣ ልክ ልካቸውን ነበር የምነግራቸው› ማለት አበዛች፡፡ በልኳ ለብሳ የማታውቅ ሴትዮ ድንገት ተነሥታ ልክ ልክ ነጋሪ ሆችልህ፡፡ የስብሰባው አጀንዳ ‹ሴቶች በልማት ይሳተፉ› የሚል ነው፡፡ አዲሴ ተነሣችና ‹ለሴቶች ዕድገት ወሳኙ ወርቅ ነው፡፡ እኛ ሴቶች ከወንዶች እኩል እንድንሆን ወርቅ ያስፈልገናል› ስትል አንዷ ‹ታዲያ እንደ መሠረት ደፋር አትሮጭም፣ ማን ከለከለሽ› ብላ አሳቀችባት፡፡ ‹የሴቶችን ችግር ለመፍታት ስብሰባ ሳይሆን ሴቶች ወርቅ የሚገዙበት መንገድ መመቻቸት አለበት› ብላ ስትቀመጥ ሰብሳቢዋ ምናልባት መልስ ቢሰጡ ብላ ነው መሰለኝ ለወይዘሮ ወርቅ ያንጥፉ ዕድል ሰጠቻቸው፡፡ ሊያነጥፉላት ነው፡፡

‹ድኻ ወርቅ አይግዛ፣ ከገዛም ይጥፋበት› ትል ነበር አያቴ፡፡ ወ/ሮ አዲሴ ትናንት ግማሽ ግራም ወርቅ ስለገዛሽ ወሬሽ ሁሉ ምነው ወርቅ ብቻ ሆነሳ› ሲሉ ሁሉም የኮረኮሩት ያህል በሳቅ ፈነዳ፡፡ ‹ባለፈው እዚህ ሠፈራችን ያለ ጎረምሳ መጽሐፍ አሳተመ ተብሎ ደስ አለን፡፡ ምንም ቢሆን ያሳደግነው ልጅ ነው ብለን፡፡ እሱ ግን ፊደል የፈጠረ እንጂ መጽሐፍ ያሳተመ አልመሰለውም፡፡ ቡና ልንጠጣ ቤታቸው ስንሄድ የዛሬው የቡና ቁርስ የኔ ግጥም ነው ብሎ ግጥም ሊያነብልን ጀመረ፡፡ ምነው ሸዋ! ሐዲስ ዓለማየሁም እንዲህ አላደረጉ፡፡ ደግሞኮ
አራት ኪሎ ኪሎ
አራት ኪሎ ኪሎ
የድንጋይ አሎሎ› የሚል ግጥምኮ ነው፡፡› ሰብሳቢዋማ ከጠረጴዛው መነሣት እስኪቸግራት ተደፍታ ነው የሳቀችው፡፡ ያው ወ/ሮ ወርቅ ያንጥፉ ከሳቅክላቸው ማንጠፍ ነው፡፡ ‹ይባስ ብሎ ቀበሌ አዳራሽ ልጆቹን ሰብስቦ ‹ታዋቂው ደራሲ› የሚል ፖስተር ለጥፎ ልምድ አካፍላለሁ ይላቸዋል፡፡ ‹እርሟን ጠምቃ፣ ሰጠች ጠልቃ› አሉ፡፡
አንበሳ ተኝቶ ፍየል ዘለለችው
ንቆ ቢያሳልፋት ሞኝ አደረገችው› አለ የሀገሬ ሰው፡፡ በብጥሌ ወረቀት አላሳተምንም እንጂ ስንት ግጥም ነበረንኮ፡፡
መቶ ታምሳ ዜማ የሚሰማብሽ
ድኻ ባለጠጋ የማይጠፋብሽ
ፀሐይ እንደ እንግሊዝ የማይጠልቅብሽ
የሁሉ እኩል ሀገር አራት ኪሎ ነሽ› ብሎ እንደመግጠም ‹አራት ኪሎ ኪሎ፣ የድንጋይ አሎሎ› ብሎ አሎሎ የሚያህል ግጥም የጻፈን ልጅ ልምድ አካፍላቸው ማለት በአሎሎ ደብድባቸው እንደ ማለት ነው፡፡› ሳቅና ጭብጨባ አጀባቸው፡፡
@wegoch
👇 ቀጣዩን ክፍል ከዚህ በታች ያንብቡ 👇
👆 የቀደመውን ከዚህ በላይ ያንብቡ 👆

ድኻ ወርቅ አያግኝ ማለት ይኼ ነው፡፡ አሁን እኛን የቸገረን እንዲህ እንደ አዲሴ የሚባርቅባቸው ድኾች ናቸው፡፡ ሥልጣን አይቶ ለማያውቀው ሥልጣን ትሰጡትና ይባርቅበታል፡፡ የቢሮውን መኪና በሠፈራችን እያፈጠነ ካላሳየን ሞቶ ይገኛል፡፡ በታክሲ ሲሰቃይ ለከረመ ሰው ቪ ኤይት መኪና መስጠት በውኃ ጥም ለከረመ ሰው ቅቤ አቅልጦ እንደማጠጣት ነው፡፡ ሁለቱም ጤና አይሆናቸውም፡፡ አበሉ፣ ስብሰባው፣ ግብዣው፣ ፊርማው፣ ብርቅ ይሆንበታል፡፡ ቀበሌውና ክፍለ ከተማው የግል ንብረቱ ይመስለዋል፡፡ እኛም አሽከሮቹ እንመስለዋለን፡፡ የተሾመ ሰሞን ብርቅ ስለሚሆንበት ያገኘውን ገንዘብና መሬት ይጠበጥበዋል፡፡ ያልራሰ መሬት ማለትኮ ነው፡፡ ምን ውኃ ይመጥነዋል፡፡ ‹አይቶ አያውቅ ዳቦ ፍሪዳው ነው› ይባላል፡፡ አንድ ስብሰባ ላይ አንዲት እንግሊዝኛ የሰማ ዕለት እኛን ሰብስቦ እርሷን ካልተናገረ ይሞታል፡፡ ውጭ ሀገር ሄዶ አንዲት ነገር ካየ፣ ብርቅ ስለምትሆንበት ‹ቻይና ሳለሁ፣ ኮርያ ሳለሁ› እያለ መከራ ያሳየናል፡፡ ድኻ ወርቅ አይግዛ የተባለውኮ ለዚህ ነው፡፡

አላያችሁም እንዴ በድንገት ሀብታም የሆነን ሰው፡፡ ሳይነግራችሁ ታውቁታላችሁኮ፡፡ የውሻ ማሠሪያ የሚያህል የአንገት ወርቅ፣ ክብደት መለኪያ የሚሆን የእጅ ሰዓት፣ የሚታይ ከናቴራ፣ ከከናቴራው ላይ አዲስ ሸሚዝ፣ በሸሚዙ ላይ አዲስ ሹራብ፣ በሹራቡ ላይ አዲስ ኮት፣ በኮቱ ላይ አዲስ የውጭ ካፖርት፣ በካፖርቱ ላይ ስካርፕ ደርቦ ታዩታላችሁ፡፡ ይህን ስታዩ ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ› በሉና ሽሹ፡፡ መኪና ከገዛማ አይጣልባችሁ፡፡ በግራ እጁ መሪ ይዞ፣ ወንበሩን ወደ ኋላ ስቦ፣ ልጥጥ እያለ፣ የአስፓልት ውኃ እየረጨባችሁ ያልፋል፡፡

እና አዲሴ ተይን እባክሽ፣ አንቺ ዛሬ ወርቅ ስትገዥ የችግራችን ሁሉ መፍቻ ወርቅ መሰለሽ፡፡ የክፉ ሐኪም ምክር አትምከሪን፡፡ ክፉ ሐኪም ሥጋው የገጠጠ በሽተኛ በቀበሌ ደብዳቤ በነጻ እየታከመ እያየ ከምግብ በፊትና ከምግብ በኋላ ሦስት ጊዜ የሚዋጥ መድኃኒት ያዛል፡፡ ይህ ማለትኮ ሰውዬውን አትድንም ተስፋ ቁረጥ ማለቱ ነው፡፡ መድኃኒቱንስ በነጻ አገኘ፡፡ ምግቡን ማን ይሰጠዋል? አሁን ያስቸገሩን እንዳንቺ ያሉት ናቸው፡፡ ሲበሉ የበላን፣ ቤት ሲሠሩ የሠራን፣ አበል ሲከፈላቸው የተከፈለን፣ ሲሾሙ የተሾምን፣ የእነርሱ ችግር ሲፈታ የእኛ የተፈታ የሚመስላቸው የአእምሮ ድኾች፡፡ ድኃ ወርቅ አይግዛ ከገዛም ይጥፋበት የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ ወርቁ ጠፍቶባቸው ከሥልጣን ሲወርዱ፣ ከሀብት ሲናዱ ምን እንደሚመስሉ አይተናቸዋላ፡፡
ሞቅ አድርገን አጨበጨብንላቸው፡፡ ራሷ ሰብሳቢያችን አጨበጨበች፡፡ እኔም ከእርሷ ወስጄ ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ ከገዛም ይጥፋበት› እላለሁ፡፡
አሉኝ የምንዳየ እናት አባዬ፡፡
@wegoch
@wegoch
@wegoch
ምክር እስከመቃብር
(ከኣልፎ ሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ)
(በእውቀቱ ሥዩም)
.
እንደምነሽ ሸገር
እንደምነሽ ሸገር
የቤት ኣከራየ የጋሽ ጣሰው ኣገር
እየመጣሁ ነው፡፡ወደ ኣዲስ ኣበባ እየመጣሁ ነው፡፡እናቶች
ኣባቶች ልጆች ኦርጅናሎች ሰልቫጆች! እኔ ሳልመጣ ውጊያውን
እንዳትጀምሩት ኣደራ፡፡ ኣጭርና ጣፋጭ ይሁን እንጂ
በማንኛውም ትግል ላይ ለመሳተፍ ዝገጁ ነኝ፡፡የጥይት መከላከያ
ቆብ ሹራብና ሱሪ እንዲሁም ፈንጅ የማይበትነው ጫማ
ከተሰጠኝ ኣንድ ሻለቃ እመራለሁ፡፡ኣነሰ ከተባለ ኣንዲት ኮረብታ
እቆጣጠራለሁ፡፡ በጦር ምህንድስና ላይ እሳተፋለሁ፡፡ ባሩድ
ኣገነፋለሁ፡፡ የታንክ ጎማ እነፋለሁ፡፡በሰላሙ ቀን ለሞባይል፤
በቀውጢው ቀን ለሽጉጥ ማስቀመጫ የሚሆን ሰገባ እሰፋለሁ፡፡
ይሄም ኣላዋጣ ካለ የኤፍሬም ይሳቅን ቡድን የሚፎካከር
ኣስታራቂ ቡድን ኣቋቁሜ” ኣንተም ተው ኣንተም ተው፤
ያስታረቅሁበትን ኪሴ ውስጥ ክተተው” የሚል ኣገልግሎት
እሰጣለሁ፡፡ቃሌ ነው፡፡የተናገርኩት ከሚጠፋ በቅርቡ የገዛሁት
ጋላክሲ ሙባይል ይጥፋ(በዝች ንግግር ውስጥ የተደበቀ ጉራ
እንዳለ እናንተ ሳትሉኝ ኣውቀዋለሁ)
ገና ለገና ካሜሪካ ሊመጣነው በማለት ማጅራቴን ለመመታት
እያሟሟቃችሁ ያላችሁ ዱርየዎች እንዲሁም ከዱላ የተረፈች
ማጅራቴን በማሸት ትርፍ ለማጋበስ የተሰናዳችሁ ወጌሻዎች
ተስፋ ቁረጡ ፡፡ ቤሳቢስትን የለኝም፡፡(ማጅራት መምታት ሲነሳ
ፋሲል ደመወዝ ትዝ ኣለኝ፡፡እንኳን እግዜር ማረህ ልለው ብደውል
ከዲሲ በርሮ ኣትላንታ እንደገባ ነገረኝ፡፡ለኮንሰርት ይሁን
ለስልታዊ ማፈግፈግ ኣልነገረኝም፡፡ ወይ ኣበሳ!እኛ
ኢትዮጵያውያንኮ ምስኪን ነን ፤ ኣገር በቀል- ዱላ ሸሽተን ስንሄድ
የውጭ ኣገር ዱላ ይጠብቀናል፡፡
ኣሜሪካ ሁለት ወር ስቆይ ያተረፍኩት ነገር ቢኖር ግብዣና ምክር
ነው፡፡ዲታው ቢራ ጋብዞ ወደ ኣገርቤት ይዣት የምመለስ ቦርጭ
ያወጣልኛል፡፡ቺስታው ቦርጬ እንዴት እንደምቀንስ ይመክረኛል፡፡
ኣሜሪካ ፍሪሽ የሆነ ሰው ኑሮው ምክር እስከመቃብር ነው፡፡
ከኢትዮጵያ ወደ ኣሜሪካ ገንዘብ የተላከለት የመጀመርያው ሰው
ሳልሆን እቀራለሁ?
ለምሳሌ ጺም ለመቆረጥ ኣስር ዶላር መከስከስ ነበረብኝ፡፡
ፈርዶብኝ ኣሜሪካ ስገባ ጺሜ ያለወትሮው ቶሎቶሎ ማደግ
ጀመረ፡፡ኣዲኣበባ እያለሁ ጺም ኣልነበረኝም፡፡እንዲያውም” ይሄ
ልጅ ጺሚ የሚባል ነገር የለውም ስልብ ነው እንዴ?” የሚል
ኣሜት በመንደራችን ይናፈስ ነበር፡፡ስልብ ኣለመሆኔን ለማሳየት
ኣንድ ሁለት ቀን መንገድ ዳር ሸንቻለሁ፡፡
እንደልማዴ ከቀናኝ የሚጋብዘኝ ከፈረደብኝ የሚመክረኝ ኣላጣም
በማለት Fenton መንገድ ላይ ወደሚገኝ ያበሻ ምግብ ቤት
ጎራ ኣልኩ፡፡ ኣንዱ መድረክ ላይ የሱዳን ዘፈን ይዘፍናል፡፡
ከተስተናጋጆች ውስጥ ኣንድም የሚያዳምጠው የለም፡፡ሁሉም
ሙባይሉ ላይ ኣቀርቅሯል፡፡የታደለው ከፍቅረኛው በቫይበር
የተላከለትን የክንፈር ምስል እያየ በደስታ ይዋኛል ፡፡
ያልታደለው”የትምርት ቤት ክፍያ እየደረሰብኝ ስለሆነ ቶሎ
ላክልኝ እንጅ”የሚል ካገር ቤት የተላከ መልክት እያነበበ
ተክዟል፡፡ ሌላው ግድግዳው ላይ በተንጠለጠለው ቲቪ ላይ
የሚተላለፈውን ያሜሪካ እግርኳስ እየተመለከተ ምድር ጠቦታል፡፡
ያሜሪካ እግርኳስ ቢሏችሁ እንደ ዋናው እግርኳስ እንዳይ
መስላችሁ፡፡ ኣንዱ ጠብደል ጥቁር ሙልሙል ኳስ ይዞ
ይሮጣል፡፡ሌላው ኣሳድዶ ይደርስበትና ዘርጥጦ ይጥለዋል፡፡ ለኔ
ይህ ጨዋታ ሳይሆን ህጋዊ እውቅና ያለው ኣምባጓሮ ነው፡፡
በዚህ መሃል ዘፋኙ “ከ እኔ ጋ ናችሁ?” እያለ ኣስሬ ቢጣራም
ማንም ተጉዳይ ኣልጣፈውም፡፡ ልምምድ ላይ ያለ ይመስል
ለራሱ ዘፍኖ ወረደ ፡፡ስላሳዘነኝ ባንኮኒውን እንደመቋሚያ ተደግፌ
በጥሞና ኣዳመጥሁት፡፡ድምጹ ከዛፍ ላይ ኣምፖል ያረግፋል፡፡
ቢሆንም ዘፈኑን ኣለቅጥ ያስረዝመዋል፡፡የሱን የሱዳን ዘፈን ታግሶ
መጨረስ ሱዳንን በእግር እንደማቋረጥ ነው፡፡
ጥግ ላይ ክበበው ገዳ ተቀምጧል፡፡ ወንበር ስቤ ኣጠገቡ
ተሰየምሁ፡፡ ራት ይጋብዘኛል ብየ ስጠብቅ ከራት ጋር የተያያዘ
ገጠመኝ ጋበዘኝ፡፡
ክበበው ገዳ ጎረምሳ እያለ የለቅሶ ቤት እራት ኣያመልጠው
ነበር፡፡ እንድያውም እንዲያባላኝ እያለ ቃሪያ በኪሱ ይዞ መዞር
ጀምሮ ነበር፡፡ ኣንድ ለቅሶ ላይ ታድያ እራት ሲቀርብ ክበበው
ከቤቱ ይዞት የመጣውን ቃርያ ከኪሱ ኣውጥቶ ኮርሸም ሲያደርግ
የተመለከተ የሰፈር ልጅ ወደ ኣስተናጋጆች እያጨበጨበ “እዚህ
ጋ ቃርያ ኣልደረሰኝም” ብሎ ጮከ፡፡
ኣለፍ ብሎ፤ የጃንሆይ ኣምባሳደር ዘውዴ ረታና ያሬድ ጥበቡ
ቁጭ ብለዋል፡፡ያሬድ ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ ሲሆን
ዘውዴ የተንቀጠቀጠው ተራራ ነው፡፡ኣሁን ዲማሚቱና ተራራውም
ባንድ ጠረጴዛ ዙርያ ተቀምው ሳያቸው ገረመኝ፡፡
ከማጅራቴ ኣካባቢ “ልትጽፍ ነው የመጣህ ኣይደል”የሚል
ሹክሽክታ ሰማሁ፡፡ወይንሸት ናት፡፡ ባለፈው ኣመት ከባህል
ቡድናችን ጋር ስትመጣ ኮከብ ድምጻዊ ነበረች፡፡ኣሁን እዚሁ
ቀርታ ኮከብ ኣስተናጋጅ ሆናለች፡፡ኣፍንጫዋ ላይ የወርቅ ቡግር
የመሰለ ሎቲ ለጥፋለች፡፡እዚህ ኣገር ሴቶች ሎቲ
የሚያንጠለጥሉት ጆሮኣቸው ላይ ሳይሆን ኣፍንጫቸው ላይ ነው፡፡
ስለወይንሸት በሌላ ምእራፍ እተርካለሁ፡፡
በሩ ኣጠገብ ተኬን ኣየሁት፡፡ ተኬ በደርግ ዘመን ካይሮ ላይ
ከጠፋው የብሄራዊ ቡድናችን ገንዘብ- ያዥ ነበር፡፡ኢትዮጵያ
ከግብጽ ጋር ባደረገችው በግጥምያ ዋዜማ ላይ በረኛውን
ጨምሮ ብዙ ተጫዋቾች ስለኮበለሉ እሱ የበረኛውን ቦታ ተክቶ
ተሰልፏል፡፡ ከተቃራኒ ቡድን የተለጋች ኳስ ወደእሱ ኣቅጣጫ
ስትመጣ በገንዘብ ቆጠራው ለምዶበት ጣቱን በምላሱ እያጣቀሰ
ሲርበደበድ ፤ ኣስራ ሰባት ጎል ገበቶበታል፡፡ (ምንጭ፡
የይድነቃቸው ተሰማ ሪፖርት)ተኬ ጉዳዩ ሲነሳበት
ያማርራል፤“ይሄ ውለታ ቢስ ህዝብ የገባብኝን ኣስራ ሰባት ጎል
እንጂ ያዳንሁትን ሰባት መቶ ጎል ኣላሰበልኝም” ይላል፡፡ካገሩ
ወጥቶ መቅረት ኣሳብ ፈጽሞ ኣልነበረውም፡፡ይሁን እንጅ ይህን
ሽንፈት ይዞ ጓድ መንግስቱ ፊት መቆም የሚያመጣውን ነገር
ኣስቦ በዛው” ነካው“፡፡
ኣሁን በሩ ኣጠገብ ቁጭ ብሎ ”ብሉ ሙን“ ቢራ ይጠጣል፡፡
የቢራ ጠርሙሱን በጥርሱ ከፍቶ ቆርኪውን ጠረጴዛ ልይ ተፋው፡፡
ቢራ መክፈቻ ቢቀርብለትም ተጠቅሞበት ኣያውቅም፡፡እግዜር
መንጋጋን የፈጠረው ሲርብህ ኣጥንት እንድትቆረጥምበት
ሲጠማህ የቢራ ጠርሙስ እንድትከፍትበት ነው ይላል፡፡

@wegoch
@wegoch
#ቅንድል_ዲጂታል_መፅሔት
አለምን በስጋት እየናጠ ስላለው COVID-19 በስፍት የተዳሰሰበት ፣ ሀገሪኛ ወጎች ፣ የስነ ልቦና ግኝቶች ፣ የቅን ተምሳሌት እንግዶች ፣ የጥበብ ቱሩፍት ፣ አጃኢብ ያስባሉ የአለም ድንቅ ትዕይንቶች እና ዕልፍ ገፆች በወጣት ፀሀፊዎች ከልብ ተቃኝተውበታል፡፡

#ያንብቡትና_ያትርፉበት!

#ቅፅ-2 #ቁጥር-1👇👇


@kendelM
@kendelM
ቅንድል_ዲጂታል_መፅሔት_ቅፅ_2_|_Kendel_edited10.pdf
6 MB
ቅንድል ዲጂታል መፅሔት
#ቅፅ-2 #ቁጥር-1

#አዲስ ይዘት፣
#ልዩ አቀራረብ
#ሚያሸልሙ_ጥያቄዎች_የተካተቱበት



💵ፓኬጅ ከገዙ 60 ሳንቲም ብቻ💵

ቅን ፣ ምክንያታዊ እና ሀገር ወዳድ ትውልድ ለኢትዮጵያ !!!
@KendelM
@KendelM
#የደሜ ዜመኞች

ክፍል - ፲
ቀጥያለሁ...
(የሞቴ መምጣት ደርሳለችና የፍቅሬን ንሰሀ ስሙልኝ)
ቀጥያለሁ.....

የፍቅሬ ሀገር ድንበር ስለሌለው መሰረትና አጥር ሳይከልለው ወደ አርያም ሊፈረጥጥነው
ተጠርቷላ
መልአከ ምትም ከፊቴ ተገትሮ ና እንጂ  እየጠበቀችህ ብሎ እጁን ዘርግቶልኛል
እኔም ከእጁ ለመግባት ቸኩያለሁ ግን ንሰሀዬን ልነግራችሁ ወደድኩኝ
                    ማ ዘንድ ይደር
                   ሰው አሳዝኖ ሰው ላይሆን ነገር
                   ምን አስጀመረው የማይሆን ነገር
                   ልቤ አንቺን ትቶ ከማን ዘንድ ይደር
                  ልማልልሽ ወይ በቶ መስቀሌ
                  ከራሴ ጋር ነው ብጣላሽ ጥሌ
ትዝ ይለኛል የፊያሜታዬ ልደት ሰኔ 19 ነበር ምን አድርጌ እንደማከብርላት ግራ ግብት ብሎኝ ነበር ብዙ ጊዜ ፈጣን ትሁን እንጂ ፀጥታ ነፍሱአ ነው ልደቷን እኔ እና እሷ ብቻ እንድናከብረው ፈለኩኝ በምቶደው በፀጥታ አለም ውስጥ ሆነን
ትምህርቱ ሊያልቅ የ1 ሳምንት ጊዜ ብቻ ነበር የቀረው እናም ሁሉም ነገር መለየት መለየት ብቻ ነው ሚሸተው
የኛም ቢዝነስ ከምላችሁ በላይ አድጓል ግን በዛው ልክ ማላውቃቸው ሰዎች ቢዝነሴን እንድተውና ከስራቸው ገለል እንድል እየነገሩኝ ነበር
አልሰማም ብያለሁ እኔም
ሰኔ 18 ላይ ነኝ ነገ የንግስቴ የውልደቷ ቀን ነው ማንንም ሳላማክር ሁሉን ነገር በራሴ ለማድረግ ወስኛለሁ
ገና በጠዋቱ ፊያዬ እየሮጠች መታ ከእቅፌ ውስጥ ገባች ጊዮርጊስ ሄጄ ፀሎት አድርጌ መጣሁ አለቺኝ ምን ታየሽ ባክሽ አልኩአት ትናንሽ አይኖቹአን አንስታ ገላመጠቸኝ
ሁሌ ሳናዳት እንዲህ ነው ምታደርገው   
ይሄን ደሞ ላንተ ብላ ከወደ አንገቷ እጆቹአን አስገባች የሚያምር ቶ መስቀል ወደ አንገቴ አስጠጋችልኝ እንዳይጠፋብኝ አስሬው እኮ ነው አለቺኝ
መስቀሉን ስማ አሰረቺልኝ መቼም ላልየህ ቃሌ ነው የኔ አባት ቃሏ ሰርስሮኝ ወደ ውስጤ ዘለቀ
እንባ ቀረሽ ስሜት ውስጥ ገብታ እኔንም ይዛኝ ዘለቀች
ዛሬ ስሜቷ ሁሉ ዝብርቅርቅ ሆኑአል
ሁሌ ወደ ምንቀምጥባት ቦታ ወስጄ አወራት ጀመር
ትዝ ይለኛል ይሄን ዜማ ከሰጠችኝ መስቀል ጋር አያይዤ እዘፍንላት ጀመር
                  ልቤ አንቺን ትቶ ከማዘንድ ይደር
                  ልማልልሽ ወይ በ ቶ መስቀሌ
                 ከራሴ ጋር ነው ብጣላሽ ጥሌ
የሰጠችኝን መስቀል እየዳበሰች ከእቅፌ ውስጥ ገብታለች
ደሞ ነገ የንግስቴ ልደት ነው
ሁሌ ደስ ሲለኝ በደስታዬ ሀይል ዳመናውን ማዘው ይመስል ዛሬም ስሜቴን ተረድቶ በነጎድጓዱ መጣው ይለኝ ጀምሯል
ካፊያ ከሰማዩ ሲጀምር ይዣት ልነሳ ተነሳሁ  አይሆንም አለቺኝ ምወደው ዝናብ ከላይ ከእቅፌ ስር ደሞ ንግስቴ ተኝታለች
በእቅፌ ስር ነች ቶ መስቀሌን በጣቶቿ እየዳሰሰች በትንፋሿ አንገቴን ታሞቀው ጀምራለች
ምን ቁር ምን ብርድ ምን ዶፍ አሁን በኔ ላይ ስሜት አያመጡም የሷ ትንሽ ትንፋሽ የልቤን እሳት ይለኩሰዋል
ያ ውብ ፀጉር በዝናቡ ጠብታዎች ውበቱ ጨምሯል ጠብታዎቹ ቁጭ ቁጭ ብለው ለፀጉሯ ማጌጫ የተቀመጡ ጌጦች መስለዋል ሁሉ ነገራች በስብሷል ዝንቡ ክፉኛ ቢያረጥበንም በፍቅር እቅፍ ውስጥ ሙቅ ቤት ሰርተናል
ፈራሁ አለቺኝ ዝም ብለሽ እቀፊኝ አልኩአት      ለካ
እንባዋን ከዝናቡ ጠብታውች እጋ እኩል እያፈሰሰቸቻው ነው
ስቅ ሲላት ሳግ ወደ ላይ ስሜቷን ሲያወጣው እኔም ማልቀሷን አወኩኝ
ምድነው የሆነሽቢኝ ፈራሁ ፈራሁ ብቻ ነው መልሷ
ከፊቴ የማላውቃቸው ሁለት ልጆች ኢስኮ ታች ሜዳ ላይ በጣም ተፈልገሀል አሉኝ መጣሁ አልኳቸው ከሁኔታቸው የግዴት ትዕዛዝ ነው ሚመስለው
ደርሼ ልምጣ አልኩአት አትሂድ አለቺኝ አሁን ነው ምመለሰው ብላትም እባክህ ሆነ መማፀኑአ ተነሺ እሺ አብረን ሄደን እንመለሳለን አልኩአት
ዛሬ ከበስተጀርባዬ ሚቆም ማንም ሰው አልነበረም ሚከተለኝ ህዝብ ዛሬ ከኋላዬ የለም አጆቹአን ይዤ አለሜን እያስከተለኩኝ ወረድኩ
በጨቀየው ሜዳ ወደ 12 የሚጠጉ ልጆች ተሰብስው ቆመዋል በዛ ዝናብ እኔን ቀመው እየጠበቁ ነው አንድማ ማውቀው ፊት የለም
እኔ ከጨቀየው መሬት አለሜን አስከትዬ ጭቃው እየዛኩ ወደ ነሱ ተጠጋው ፎቁ ላይ ያለው ተማሪ ከሜዳው ሚደረገውን ድርጊት ተገርሞ ይመለከታል እጇን አጥብቄ ይዤዋለሁ
ድንገት ከወደ ጭንቅላቴ ከፍ ያለ ምት ተሰማኝ እጆቹአን ለቅቄ ከመሬት ወደኩኝ ጩኸቷ ከጆሮዬ ያቃጭላል ሰውነቴ ብዙ ምቶችን እያስተናገደ ነው ዝናቡ ከላይ የነሱ ቡጢ ከሰውነቴ ይወርድ ጀመረ ኢስኮ እያለች የነበረችው ፊያዬ ዋይ ዋይታዋ ቀነሰብኝ ድምጿ ከጆሮዬ ሲጠፋ የተማሪው ጩኸት ሲያስተጋባ ተሰማኝ ዱላው እየቀነሰ ዝናቡ ሀይሉን ጨምሯል
ደም የሞሏው ፊቴ በዝናቡ እየታጠበ ይነፃ ጀመር ከምንም በላይ የጭንቅላቴ ህመም አይሎብኛል አይኔን ከሜዳው ላይ ጥዬ ብዥታዬን አጠራ ጀመር እሷን መፈለግ ጀመርኩ
ከፊቴ ውድቅ ብላለች ያ ውብ ገላ ከጨቀየው ሜዳ ላይ ተንጋሎ ወድቋል
በተሰባበሩት እጆቼ አይኔን እጠርግ ገባሁ እየዳሁ አጠገቧ ደረስኩ ቅድም ስዳብሰው የነበረው ፀጉር በጭቃ ተለውሷል
በእጆቿ ሆዶአን ይዛዋላች አሁንም ይበልጥ ተጠጋሁዋት
ከዝናቡ አልፍ አንድ ዘለላ እንባ ከአይኗ ስትፈስ አየሁ
 ሆዷ ደም ለብሷል ሆድ እቃዋ ተገልብጧል
ኢ ኢ ኢ ስስስኮ አለቺኝ ምድነው እናቴ እጆቼ ግንባሮቿ ላይ ጣልኩት
ቶሎ እንድትመጣ እሺ አባቴ አለቺኝ በደም እጇ ከአንገቴ የተንጠለጠለውን የሰጠችን መስቀል በደም ለወሰቻቸው
ተማሪው ሜዳው ላይ ደርሷል ወዴት እንደምመጣ ባላቅም እሺ እንኩአን ሳልላት አፋፍሰው ወሰዱአት
እኔም በተማሪዎቹ ድጋፍ ተነስቼ እከተላት ጀመረ በታክሲ ተጭኜ ዝም ብዬ መጓዝ ጀመርኩ የተማሪዎቹን የለቅሶና የሀዘን ድምፅ እየሰማሁ ከአንድ ሆስፒታል ደጃፍ ደረስኩ
በነሱ ድጋፍ ከውስጥ ዘለኩ የት እንዳስገቡአት እንጃ ብቻ ሁለት ነርሶች ወደ እኔ መጡ ሊወስዱኝ ፈለጉ አይሆንም አልኩኝ  ቶሎ ና እሺ ቶሎ ና የመጨረሻ ድምጿ ከጆሮዬ ያስተጋባል ቃናዋ በህሊናዬ ያንሻብብ ጀመር
ነርሶቹ እንደያዙኝ እሪታና ጩኸት ሲበዛ የአለሜ ቃና በድምፃቸው ተዋጠ ነርሶቹ በሰሙት ጩኸት ለቀቁኝ
ሞታለች የሚል ድምፅ ስሰማ እኔም ሌላ ምት ወደ ጭንቅላቴ ሲመጣ ታወቀኝ ከመሬት ወደኩ ጭንቅላቴ ሲከፈል የጎን አጥንቴ ሲደቅ ተሰማኝ
እናንተዬ ልቤ እየቀነሰችብኝ ትንፋሽ እያጠረኝ ነው እጆቼ ንዝረታቸው ጨምሮ ምፅፈው ሁሉ እየተደለዘ ነው እፍን ምልስ እፍን ምልስ
ሞቷን ስነግራችሁ እኔም ልሄድ ነው መሰለኝ
ደሜ ወረቄትን ሸፍኖታል ድምፅ አልባው እንባዬ እየወረደ ነው ልሄድ ነው በቃ ልሄድ ነው ልቤ እየያዘገመች ነው እጆቼም ዝለውብኛል
እይኔ መስለምለም ጀምሯል ብዥ ብዥ ሆኖብኝ መስመሬን እየሳትኩ ነው ምፅፈው
ከዚ ወዲ ፋታ ለመውሰድ ብዬ ዜማ ስለማላጫውትላችሁ እቺን ብቻ ስሙልኝ እሺ ወደ እኔ ቶሎ ኑ እሺ እናንተም እዛ ስንገናኝ ብዙ ነገር ነው ማጫውታችሁ
መልአከ ሞት መጨረሴን አውቋል መሰል ቀኝ እጄን ለቀም አድርጎ ይዞኛል
በግማሽ ሞት እና በግማሽ ሂወት ውስጥ ነኝ
በግራው አይኔ ካለሁበት አለም ወጥቼ አዲስ ነገርች እያየሁ ነው
በቀኜ ደሞ በደም የተጨማለቀውን ገፄን
እቺን ስሙልኝ አደራ ቶሎ ኑ በሷ ቃል ነው እኔም ምሰናበታችሁ
ዜማዋ ልትጀምር ነው
          የት ነው የምትኖሪው ያለሽበት ቦታ
           ምንኛ ሀያል ነው ይህ ያንቺ ትዝታ
          ደቂቃዎች ሴኮንድ እንዴት ልለይሽ
                 የትዝታዬ ምንጭ ውሀ
            ውሀ ጥሜ ነ
2024/09/25 10:26:03
Back to Top
HTML Embed Code: