Telegram Web Link
ፎቶ በመላክ ሦዕል ለማሳል።
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 order ማድረግ ይቻላል።

@seiloch
@seiloch
የአማልፊዋ ወጣት
Written by መሐመድ ኢድሪስ

ከኡማ ጋር አስር ሰአት ላይ ቀጠሮ ነበረኝ። እዛው እስዋ የምትማርበት ኮሌጅ
አጠገብ ያለ ፌርማታ ጋ ነበር የተቀጣጠርነው፡፡ ዘወትር ወደምንሄድበት
መናፈሻ፣ በዘጠኝ ቁጥር አውቶብስ ለመሄድ ነው ያሰብነው፡፡ ወርቃማ
ፀጉርዋንና ውብ ሰማያዊ አይኖችዋን ለማየት ከመጓጓቴ የተነሳ ዘጠኝ ሰአት
ተኩል ነበር የደረስኩት። ቦታው ጭር ያለ ሲሆን ብዙ የመኪና ግርግር
አይታይበትም፡፡ በምስራቅ ሳንላጀሮ፣ በደቡብ ኮንካ ዲማሬኒ፣ በሰሜን
ምስራቅ ራቬሎ ማናሮ የሚያዋስናት አማልፊ ኮስት፤ በሎሚ እርሻዎቿም
ትታወቃለች፡፡ ከኡማ ጋር ከተዋወቅን ዘጠኝ አመታት ቢያልፉም፣ የፍቅር
ግንኙነት
የጀመርነው ግን ከአንድ አመት በፊት ነበር፡፡ ያን ቢጫ ቱታዋን ለብሳ ስፖርት
ስትሰራ ነበር ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋት፡፡ አንድ ሸበቶ ፀጉር ያላቸው በደንብ
የለበሱና ከዘራ የያዙ አዛውንት መጥተው አጠገቤ ተቀመጡ፡፡ ዕድሚያቸው
በግምት ወደ ስድሳ አምስት ይጠጋል። ነጭ ሙሉ ሱፍ፣ ከቡናማ ሸሚዝ ጋር
አስማምተው ለብሰዋል፡፡ ወርቃማ ህብር ያለው ቢራቢሮ ከረቫት አስረው፣
ነጭ ባርኔጣ ደፍተዋል፡፡ ጫማቸው በደንብ የተወለወለ ሲሆን የሥነ ፅሑፍ
ተማሪ በመሆኔ ሰውየው ሰብአዊ ፍጡር ብቻ ሳይሆኑ ገፀ ባህሪ ጭምር
መስለው ታዩኝ፡፡
ምን ዓይነት ገፀ ባህሪ ይሆኑ፡፡ በጣም ሃብታምና የተካበደ ሳይሆን ቀለል ያለ
አኗኗር የሚመሩ፡፡ እንዲህ ዓይነት አለባበስ ለብሶ አውቶቡስ የሚጠብቅ
ሰው አይቼ ስለማላውቅ ነው፣ ስለሳቸው እንዲያ የገመትኩት፡፡
“ሶስት ቁጥር አውቶቡስ አልፋለች?” ሲሉ ጠየቁኝ፡፡
“ከመጣሁ ጀምሮ አላለፈችም” መለስኩኝ፡፡
“ከመጣህ ስንት ጊዜ ሆነህ?”
“ወደ ሃያ ደቂቃ ገደማ” በጥያቄው እየተገረምኩኝ፡፡
“ሶስት ቁጥርን ነው የምትጠብቀው?”
“አይ እኔ እንኳን ዘጠኝ ቁጥር ነው የምጠብቀው”
ሁለታችንም ዝም ብለን ተቀመጥን፡፡ ያጋጣሚ ነገር ሆነና፣ ወዲያው ዘጠኝ
ቁጥር አውቶቡስ መጣችና ፌርማታው አጠገብ ቆመች፡፡ ሰውየው ዞር ብለው
አዩኝና፤ “መጣችልህ” አሉኝ፡፡ አዛውንቱ ያልገባቸው ነገር አለ፡፡ እኔ ኡማን
ሳልይዝ አልሄድም፡፡
“አይ ትለፈኝ” አልኩኝ፤ በመጠኑ አፈር እያልኩኝ፡፡
በሩን ዘግቶ ሄደ፡፡
“እንግዳ ነገር ነው” አሉ፡፡
“አይ የምጠብቀው ሰው ስላለ ነው” አልኩኝ ፍርጥም ብዬ፡፡
“ሴት ናት?” ፈገግ አሉ፡፡
“እ…አዎ” እያመነታሁ፡፡
“እንግዲያማ እንዳንተ አይነት ጀግና ወጣት፣ እንዴት መንገድ ፌርማታ ላይ
ሊጠብቅ ይችላል?”
እኔ ስለ ሰውየው ስገምት፣ ሰውየው ግን ስለኔ ማወቃቸው ገረመኝ፡፡
“አያስደንቅም፡፡ ሁላችንም ያለፍንበት ነው፡፡ ወጣት ወንዶች---ማለት እንዳንተ
አይነት ተማሪ፣ የገንዘብ ችግር ሊኖርበት ስለሚችል፣ ፍቅረኛውን ፌርማታ
ጋ ቢቀጥር አያስገርምም”
እዚህ ላይ እንኳ ተሳስተዋል፡፡ ባይበዛም የተወሰኑ ሺ ሊሬዎች ይዤ ነበር፡፡
“ቀድመህ መገኘትህ ትክክል አድርገሃል፡፡ በምንም መንገድ ሴትዋን ማጣት
የለብህም፡፡ አንዴ ካጣሃት እንደገና ለማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው” አሉኝ፡፡
“እንዴት?”
“እኔ ላይ ስለደረሰብኝ ነው፡፡ እንደምታውቀው አማልፊ በሎሚ እርሻዎችዋ
ትታወቃለች፡፡ እና ወሲብ የጀመርኩት በአስራ ስድስት አመቴ ነበር፤ አስራ
ዘጠኝ አመት ከሞላት የጎረቤት ልጅ ጋር፡፡ መጀመሪያ እንደ ጓደኛ ነበር
የምንተያየው፡፡ አንድ ቀን ቤቷ ስሄድ ቤተሰቦችዋ ሁሉ እቤት አልነበሩም፡፡”
አሉና ጭልጥ ብለው በሃሳብ ተጓዙ፡፡
“ከዚያስ?” ጠየቅኩኝ፤ቀጣዩን ለመስማት እየጓጓሁ።
እንደመባነን አሉና፤ “ና አንድ ነገር ላሳይህ አለችና፣ ከመደርደርያው ላይ አንድ
ግማሽ የደረሰ የጂን ጠርሙስ አንስታ፣ ሁለት ብርጭቆ ላይ ቀዳች፡፡
ከዚያም ሁለት ትልልቅ አረንጓዴ የሎሚ ፍሬዎችን ቆርጣ ከጨመቀችበት
በኋላ ብርጭቆዋንና ብርጭቆዬን አጋጨች፡፡ ጠጣሁት፡፡ ትንሽ ቆይቶ
ሰውነቴን ሁሉ
ሲነዝረኝ ተሰማኝ፡፡ ከት ብላ ሳቀችና እንደገና ብርጭቆዎቻችን ሞላችና
አሁንም ሎሚ ቆርጣ ከጨመቀች በኋላ እንደገና አብረን ጨለጥነው፡፡ ከዚያ
በኋላ
ራሴን ያገኘሁት የሷ አልጋ ላይ ነበር፤ ሁለታችንም እርቃናችንን ሆነን፡፡ እንደዚያ
አይነት ወሲብ በመላው አለም ተደርጎ የሚያውቅ አይመስለኝም--”
ብለው ትካዜ ውስጥ ገቡ፡፡
“እባክዎትን አያቋርጡ” ለመንኳቸው፡፡
“እንደነገርኩህ ዋናው ነገር ሴትዋን ማጣት የለብህም፡፡ በፍቅር ከነፍን፡፡
ሁልጊዜ ከወሲብ በፊት ጂን በሎሚ መጠጣት አይቀሬ ሆነ፡፡ በሁለተኛው
አመት ኔፕልስ ኮሌጅ መግባት ነበረብኝ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለሶስት አመት
መለያየት የግድ ነበር፡፡ ከሶስት አመታት በኋላ እኔ የአስራ ዘጠኝ አመት፣ እሷ
የሃያ ሁለት ዓመት ጎረምሶች ሳለን፣ ኔፕልስ መጣችና ተገናኘን፡፡ የደረሰችው
በእኩለ ሌሊት ስለሆነ ሱቆችም ሱፐር ማርኬቶችም ዝግ ነበሩ፡፡ አንድ ክፍት
ግሮሰሪ ብቻ ነበር፡፡ ለረዥም ሰዓት ተቃቅፈን ከተሳሳምን በኋላ ልጋብዛት ወደ
ግሮሰሪው አመራን፡፡ የሚበላ ነገር ቀማምሰን፣ ጂን በሎሚ አዘዝን፡፡
“ጂን ቢኖርም ሎሚ ግን እንደሌለ አስተናጋጅዋ ነገረችን፡፡ ጂኑ ተቀዳና
ቀመስኩት፡፡ አጥወለወለኝ። እሷንም ሳያት ፊትዋ ኮሶ መስሏል፡፡ ሁለታችንም
ተግባባን፡፡ መጣሁ አልኩና ወጣሁ፡፡ ወዴት ነህ ብላ አልጠየቀችኝም፡፡
ምክንያቱም የት እንደምሄድ ታውቃለች፡፡ ክፍት ሱቅ ፍለጋ ማሰስ ጀመርኩ፤
ሁሉም ዝግ ነበር፡፡ ከሩቅ አንድ የበራ መብራት አየሁ። ልቤ እየመታ በፈጣን
እርምጃ መራመድ ጀመርኩ። ወደ መብራቱ እየቀረብኩ ነው፡፡ ስደርስ የሱቁ
በር ከውጭ በትላልቅ የሰረገላ ቁልፎች ተከርችሟል፡፡ ከዚያ ሱቅ ውጭ
ከተማው ሁሉ ኦና ሆኖ ጭር ብሎ ነበር። እንኳን ክፍት ቤት ሊኖር ቀርቶ የሰው
ዘር የለም። በፍርግርጉ የብረት መዝጊያ በመስተዋቱ ውስጥ የሱቁ
ሸቀጣሸቀጦች ሁሉ ይታዩኛል፡፡ የወተት ተዋፅኦ፣ ልኳንዳው፣ ለስላሳ መጠጡ፣
አልኮሉ፣ ፍራፍሬው---ከሁሉም በላይ ግን በግምት ሁለት ሳጥን የሚሆን
ትኩስ ትላልቅ አረንጓዴ ሎሚዎች---” አሉና ፈዘው ቀሩ፡፡
በመገረም አፌን ከፍቼ ቀርቻለሁ፤ “ከዚያስ?” አልኩኝ፤ በደከመ ድምፅ፡፡
“ሎሚዎቹን እያየሁ ፈዝዤ ቀረሁ፤ በሎሚዎቹ ውስጥ ግን እሷን ነበር
የማየው፡፡ አይኔ እንባ አቅርሮ እዛው እንደተገተርኩ ሁለት ፖሊሶች መጡ፡፡
“ምን ታረጋለህ?” ጠየቁኝ፡፡
“ሎሚ ልገዛ ነበር” መለስኩ፡፡
“ተዘግቷል! ቀጥል!”
እያዘንኩ ተመለስኩ፡፡ ግሮሰሪው ውስጥ ቁጭ ብላ ነበር፡፡ ምንም ሳንነጋገር
አንገታችንን ደፍተን ወደ ማደርያችን ሄድን፡፡ በነጋታው ጠዋት የማይታለፍ
የስራ ቀጠሮ ስለነበራት አማልፊ መመለስ ነበረባት፡፡ ምንም ፍቅርም
ወሲብም ሳንሰራ እንቅልፍ በአይናችን ሳይዞር ነጋ፡፡ ጠዋት ላይ ሸለብ
አደረገኝ፡፡ ስነቃ አልጋው ላይ የለችም፡፡ ኮሞዲኖው ላይ ግን አንድ ወረቀት
ነበር፡፡ ነገሮች ሲመቻቹ እመጣለሁ፡፡ ጠብቀኝ ይላል፡፡ የኮሌጁ ትምህርት ብዙ
ስላልተሳካልኝ ወደ ንግድ ገባሁ፡፡ አንድ ሱቅ ተከራየሁ፡፡ እቃ ስሞላ
የመጀመሪያው ዋናው ነገር ግን ሎሚ ነበር፡፡ ሱቁ እየተስፋፋ መጣ፡፡ ትርፉ
በጣም እየጨመረ
ስለመጣ፣ አሉ ከተባሉ የሎሚ ገበሬዎች እየወሰድኩ ሎሚ አከፋፋይ ሆንኩኝ፡፡
አማልፊ መጣሁና ብዙ ሄክታር መሬት የሎሚ እርሻ. አለማሁ። … እዚሁ
አማልፊ የሎሚ የታሸገ መጠጥ ፋብሪካ የከፍትኩት በዚያን ጊዜ ነበር…”
ሶስት ቁጥር አውቶብስ መጥታ ፌርማታው አጠገብ ቆመች፡፡
“ልጄ አደረቅኩህ ሰላም ዋል፡፡” አሉና ፈጠን ብለው ወደ አውቶቡሱ ውስጥ
ገቡ፡፡ የታሪኩን መጨረሻ ለማወቅ ተከትያቸው ወደ አውቶቡሱ ልገባ
ስል፤“ቻዎ …” አለችኝ ኡማ፤ ዞር ብዬ ሳያት ጉርድ ቀሚስ ለብሳ፣ ሎሚ
እየመጠጠች ነበ
ር፡፡
አንዴ እሷን፣ አንዴ ሽማግሌውን አፈራርቄ ተመለከትኩ፡፡ ፈገግ ብለው እያዩኝ
ጣታቸውን እሷ ላይ ቀሰሩ፡፡ “ዋናው ነገር ሴትዋን ማጣት የለብህም” እያሉ
እንደሆነ ገባኝ፡፡
እኔና ኡማ ፌርማታው ጋ ተቀምጠን ዘጠኝ ቁጥርን ስንጠብቅ፣ አዛውንቱ
የሎሚ ከበርቴ ለመሆን ያደረሳቸውን ጉዳይ እያሰብኩ ነበር፡፡ እንዲያ
ተዘጋጅተው
ግን ያቺ የሚጠብቋት ሴት መጥታላቸው ይሆን? አልኩ፡፡---

ሸጋዋ!! የኔዋ ቅዳሜ!!💚💛


@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ጃምቦ ከሞት ተነስቷል !
(አሌክስ አብረሃም)

አንድ ቀን በጧቱ አንድ የሰፈራችን ህጻን ልጅ በራችንን አንኳኳና <<አቡቹ ጃምቦ በፍጥነት
እፈልግሃለሁ ይልሃል ብሎ ተፈተለከ>> ቤተሰቡ ተጨነቀ ! እኔም ንስሃ ገብቸ ከቤቴ
ወጣሁ ! ጃምቦ መንደር ያንቀጠቀጠ ዱርየ ነው! ገና አጠገባችሁ ሲቆምና የገደል ስባሪ
የሚያህል ሰውነቱ ጥላ ሲያርፍባችሁ ሰማይ ምድሩ ይጨልምባቹሃል! ጃምቦ ጋር ተጣላሁ
ብሎ ፖሊስ መጥራት ጃምቦን መሳሪያ ማስታጠቅ ነው! እውነቴን ነው ፖሊሶቹን ጠረቃቅሞ
መሳሪያቸውን ከመቀማት የማይመለስ ጠረንገሎ ! እና ጃምቦ ጠራኝ ወገኖቸ !
እግሬ እርስ በርስ እየተጋጨብኝ እንደምንም ሁልጊዜ የሚቀመጥበት ድድ ማስጫ ስደርስ
እንዲህ ሆነ ! በዛ እድሜ ግጥም ስነጽሁፍ ምናምን እንደምሞካክር ሰምቶ ኑሮ መዓዛ
ለምትባል ታች ሰፈር ለምትኖር አባቷ መቶ አለቃ ለሆኑ ልጅ የፍቅር ደብዳቤ ጻፍ ብሎ
አዘዘኝ ሰኔና ሰኞ ሲገጥም ጥበብና ጃምቦ እኩል ይጠራሉ ! እስክርቢቶና ወረቀቴን አዘጋጅቸ
የሚለውን መጻፍ ጀመርኩ <<አንችን ካየሁሽ ጀምሮ ጸሃይ በመሬት ዙሪያ እንደምትዞር
ዞረብኝ >> በልና ጻፍ አለኝ <<ጃምቦ ጸሃይ አትዞርምኮ መሬት ናት በጸሃይ ዙሪያ
የምትሽከርከረው>> ብየ በትህትና የአምስተኛ ክፍል የጅኦግራፊ ተሞክሮየን አካፈልኩ !
ወዲያው ግን የሆነ ነገር ጓ ካለ በኋላ ጸሃይም መሬትም ደመናም እኔ ራሴም በጃምቦ ዙሪያ
መሽከርከር ጀመርን ከዛን ቀን ጀምሮ ጀኦግራፊ የሚባል ትምህርትና የፍቅር ደብዳቤ
አስጠላኝ !
እንደዛ የጃንቦን ኩርኩም ተቋቁሜ የጻፍኩትን የፍቅር ደብዳቤ ለመዓዛ እንድሰጥ ራሴን
ላከኝ! ወይ ጣጣ ይታያችሁ የመዓዛ አባት ጡረታ ከወጡ ጀምሮ ዋና ስራቸው በረንዳ ላይ
ተቀምጠው ሽፍታ ገድለው መንግስት የሸለማቸውን ማካሮቭ ሽጉጥ እየወለወሉ ስድስት
ቆንጆ ሴት ልጆቻቸውን መጠበቅ ነው! ከፊት እሳት ከኋላ እሳት ይሁን ዱርየ ከሚገለኝ
አገራቸውን አገልግለው ጡረታ የወጡ መቶ አለቃ ይግደሉኝ ሞቱም ስም አለው ብየ
የግቢያቸውን በር አንኳኳሁ ! በሩ ድንገት ተከፍቶ በጣም ቆንጆዋ የመዓዛ ታናሽ እህት ሳራ
<<አቡቹ በጧቱ ከየት ተገኝህ>> አለችኝ ! ቀጥላም መዓዛን መፈለጌን ስነግራት አባቷ ጋር
ዘመድ ጥየቃ መሄዳቸውን ነገረችኝ !
ጃምቦ ታዲያ መልሱን ስነግረው ትንሽ አሰበና ደብዳቤውን ከጀ ነጥቆ ከፋፍቶ ትንሽ
ካነበበው በኋላ <<መዓዛ>> የሚለውን ስም እየሰረዝክ ሳራ በሚል ተካው>> አለኝ !
ተካሁት ! ሂድና ለሳራ ጃምቦ ነው በለህ ስጣት አለኝ ! ሂጀ ሰጠኋት ! ሳራና ጃምቦ ጓደኛ ሆኑ
ጃምቦ ምን ይሳነዋል!
የሆነ ጊዜ ታዲያ <<ጃምቦ ጌታን ተቀበለ >> የሚባል ወሬ በሰፈሩ ተወራ ! በቃ ቢሰድቡት
አይመልስ ቢመቱት መልሶ አይማታ ተባለ ! እውነትም አንድ ቀን ሳምሶን የሚባል ልጅ የድሮ
ቂሙን ሊወጣ ጃምቦን እፊቴ በጥፊ ሲያጮለው ጃምቦ <<ጌታ ይባርክህ እኔ ከፉን በክፉ
አልመልስም ለዚህ አለም ነገር ሙቻለሁ >> ብሎ አለፈ ! ጃምቦ እውነትም ሞተ ተባለ !
ማመን አልቻልኩም! በቃ የሰፈሩ ልጅ ሁሉ ጃምቦን የጉልበቱ መፈተኛ አደረገው አንዱ
በርግጫ አንዱ በቦክስ ! እኔ ራሱ መሞከር አማረኝ ! አንድ ቀን ግን እንዲህ ሆነ ጃምቦ
ወደቸርች ሊሄድ ሲጣደፍ የሰፈር ጎረምሶች ፊቱ ቆሙና አላሳልፍ አሉት ! ጭራሽ የያዘውን
መጽሃፍ ቅዱስ ቀምተው መሬት ላይ ከመጣል አልፈው ያ ሳምሶን እንደለመደው ጃምቦን
ሊጠረቅመው ጥፊ ሰነዘረ፣ ግን ምን ዋጋ አለው የጃምቦ መዳፍ ድነት እንደዥንጥላ
ተዘርግቶ የሳምሶንን መዳፍ አፈፍ አድርጎ እጁ እስኪንቋቋ ጠመዘዘና ሁሉም እየሰማ
ባስገምጋሚ ድምጹ እንዲህ አለ << የጠበኝነት መንፈሴ እንጅ ጡንቻየ አልሞተም እሺ? >>
ወዲያው ጎረምሳው ሁሉ ግማሹ አጥር እየዘለለ ግማሹ መንገድ እያሳበረ ወደየመንደሩ
እግሬ አውጭኝ አለ . . .
<<ጃምቦ ከሞት ተነስቷል>>
<<ጃምቦ ከሞት ተነስቷል>> ከሚል ጩኽት ጋር !
እና ምን ለማለት ነው ? አገራችን ላይ የማሰር የመግደል የማፈንና የማሰቃየት መንፈስ
ለሰላም ለፍቅር ሲባል አሸለበ እንጂ አልሞተም ! በውሃ ቀጠነ እዚህና እዛ አጉል የተዳፈነ
ጉልበት እንፈታተን የምትሉ አቅመቢስ በጥባጮች ሁሉ የጦርነት መንፈስ እንጂ ራስንና
አገርን የመከላከል አቅም አልሞተምና እባካችሁ ስርዓት !!

መልካም የረፍት ቀን!!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ስሜ G እባላለሁ ስም መጥፎ ጎን ሊኖረው ይችላል በማለት ነው ግን በውስጥ መስመር ችግር የለውም የአፋልጉኝ ጥሪ ነው ።
ተወለድክ የተባልኩበት አገር መተማ ወይም ሸዲ ይባላል ስሙን እንጅ አገሩን በውን አላውቅም የኔ እናት ና አባቴ ለስራ የትውልድ አገራቸውን ለቀው ስራ ፍለጋ በተሰደዱበት ወቅት የእግዚአብሔር ፍቃድ ሆነና እኔን እድለቢሱን ልጃቸውን ወልዱ ግን ተስማምተው ተፋቅረው ትድረው ከወለዱኝ በሁላ ምክንያቱን ባልታወቀ ፀብ ተጣልተው ገና ቦርቄ ስልጨርስ እናቴ በሰው አስመጥታ ሰርቃ ወደ ጎንደር ይዛኝ ጠፋች 3 አመት ከሰው ቤት ተቀጥራ እዳሳደገችኝ ከዛም አሁን ወዳለሁበት አገር አመጣችኝ አባቴን ስላት ያኔ ልጅ እያለሁ ከአእምሮዬ በላይ የሆነ መልስ ትሰጠኝ ነበረች ከዛም አልፎ ብር ስትዚ። ስራ መስራት አለበህ ስትለኝ ያቅሜን እየሰራሁ ት.ት አቋረጥኩ ሀሳቤ ሁሉ ገንዘብ ለይ ሆነ ግን ሊሳካ አልቸለልኝም በዙ ለፋሁ የለ ወክቱ እዴት ይምጣ ገንዘብ እሷ አያደርገውም አያገኝም ዝም ይለኛል ይረሳዋል ትል ነበር ግን የናት ሞት ና የትን ድንጋይ እየቆየ ይቆረቁራል አይደል ሚባለው አሁን አባቴ በጣም ናፍቆኛል 19 አመት ያለ አባት ቆይቻለው እናቴ የተለያየ ምክንያት ታቀርባለች ግን የአባቴን ናፍቆት ግን አላስታገሰልኝም ይበልጥ ሳድግ ናፈቀኝ አሁን ክፉና ደጉን ለይቸ አወኩ አሁን ሶሻል ሚዲያም እደዚህ አይነትም በጎ ጎን አለው ብዬ ከስንት አመታት ደብቄ የያዝኩትን ሚስጢር በተዘበራረቀ ሀሳብ ሁኜ ትንሽ ለማለት ነው የመፃፉም ልምድ የለኝም ፍሬ ሀሳቡን ለማጋራት እንጅ ለማንኛውም እናቴ ፈንታ ጌታቸው ትባላለች እዚህ መጥታም አንድ ሰው አገባች አሁን 1ወንድም 1 እህት ወልዳለች 15 አመት ምናምን እየሆናቸው ነው ከተጋብ..................... የኔ ጉዳይ አንድም ቀን አስጨንቆት አያውቅም እጀራ አባቴ። አባቴ በለጠም የኔን እናት ከማግባቱ በፊት ከሌላ ወልዶ እደነበር ከውስጧ የልጠፋ እውነታ ነው ከዛ ውጭ አንድም ነገር የምታቀው ነገር የለም እናቴ እደ አባትም እናትም ሁና አሳድጋኛለች ቢሆንም እሷ ዘላለም አብራኝ እደማትሆን እና የፈጣሪ ነገር እሷን ይዞብኝ ከሄደ
ከዛ በሁላ ቤተሰብ ባገኝ ጣእም የለውም ለማንኛውም እናንተ በተቻላችሁ መጠን ቤተሰቤን እዳገኝ እርዱኝ

Call 0942329852

ለሌሎች በማስተላለፍ የወንድማችንን
ነፍስ እናስደስት።

@getem
@getem
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

#አድዋ

### የዓድዋ ድልና ዳግማዊ ምኒልክ ###

የዓድዋ ድል ያለ መሪዉ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ፈፅሞ ማሰብ አይቻልም ። በእሳቸው የአመራር ብቃት፣ስልትና አርቆ አስተዋይነት የመጣ ነዉና።
....
ከየት ተማሩት?
.
ፕ/ር ጌታቸዉ ኃይሌ "የአፄ ምኒልክ የአመራር ስልትና የአድዋ ድል" በሚለዉ ፅሁፋቸዉ እንዲህ ይላሉ :-

"የምኒልክ አርቆ አስተዋይነት ከምን እንደመጣ ገና ብዙ ጥናት ያስፈልገዋል። ትልቁ ምክንያት ግን በመቅደላ የአፄ ቴዎድሮስ እስረኛ በነበሩበት ጊዜ ከሀገር ሊቃውንትና ከውጭ ሀገር እስረኞች ጋር መጎልመስ ሳይሆን አይቀርም። የአፄ ቴዎድሮስ ጭካኔ ሽንፈትን እንዳስከተለ ስላዩ፥ ተቀናቃኞቻቸውንም በፍቅር አሸነፏቸው። የቅኝ ገዢዎችን ተንኮልና ዲፕሎማሲ አይተው በዘዴያቸው መቷቸው።" ይላሉ።
.....
* የአስተዳደር  ጥበብ

አፄ ምኒልክ የአስተዳደር ጥበባቸዉና ነገሮችን የሚመለከቱበት መንገድ እጅግ ብልህነት የተሞላበት ነበር። ሀገራችን ኢትዮጵያ ከእርሳቸዉ ቀድማ  እንደ አፄ ቴዎድሮስና እንደ አፄ ዮሐንስ ያሉ ታላላቅ ነገሥታት አግኝታ የነበረ ቢሆንም እንደ ምኒልክ ግን ጀግንነትን፥  ሃይማኖታዊነትን፥ ብልሃተኝነትን በአንድ ላይ አጣምሮ የያዘ አልነበረም። ታዲያ ይህ የአስተዳደር ብልሃታቸዉ ከሹመት አሰጣጥ ጀምሮ እንደነበር አለቃ አፅሜ እንዲህ ፅፈዋል:-

"አፄ ምኒልክ ዘውድ የደፉ ዕለት ከንጉሥ ሥልጣን ሰገድ ሱስንዮስ ጀምሮ የተሠራውን ሠላሳ አምስት ሹመት ለጦር አበጋዞቻቸው ሰጡ። አፄ ዮሐንስም እንደባህሉ አድርገዋል። ሹመቱን የሰጡት ግን ለትግራይ ተወላጆች ብቻ ነበር። አፄ ምኒልክ ግን ከሌላ አካባቢ ለመጡት ጭምር እንጂ ለሸዌዎች ብቻ አልነበረም።"

አስተዋይነትና ስልት

አፄ ምኒልክ በጣም አስተዋይና ስልት አዋቂም ናቸዉ። በዚህ ስልት አዋቂነታቸዉ ነዉ  ጣሊያንን ከራሱ በገዙት ጠመንጃና መድፍ ዓድዋ ላይ ጉድ የሰሩት። ይህንን ስልት አዋቂነታቸዉን ቀድሞ የአፄ ቴዎድሮስ እስረኛ ሆነው ሳለ ከመቅደላ ካመለጡበት  ጊዜ ጀምሮ ከአፄ ዮሐንስ ጋር ሊያደርጉት የነበረውን ውጊያ በወቅቱ ያላቸውን አቅም አይተው ከንጉሡ ጋር  በአማላጅ የታረቁበት መንገድ ላይ መመልከት እንችላለን ። በተጨማሪም  ሸዋ ሲገቡ ግዛቱ ይገባኛል በሚል ሹም ተይዛ ደረሱ። እሱን በጥቂት ሠራዊት ማሸነፍ ትልቅ ዕውቀት ያስፈልግ ነበርና ማድረጋቸውም እንዲሁ የምኒልክን አስተዋይነት አጉልቶ የሚያሳይ ነዉ ።


ሌላኛዉ የአፄ ምኒልክ ጊዜዉን የዋጀ ስልት አዋቂነት ማሳያ አፄ ዮሐንስ በንዴት በሱዳን ደርቡሾች ላይ ሲዘምቱ፥ አፄ ምኒልክ ከደርቡሾች ጋር በእንግሊዞች ላይ የጋራ ግምባር መፍጠራቸው ነዉ። በወቅቱ እንግሊዞች ሪር አድሚራል ሂወትን ልከው አፄ ዮሐንስን እንደቀለዱባቸው፥ ሬነል ሮድን ልከው አፄ ምኒልክን ሊቀልዱባቸው ቢሞክሩ አልተሳካላቸውም። በአንፃሩ አምባሳደር ሬነል ሮድ አፄ ምኒልክ እንደቀለዱበት ያወቀው ወደመጣበት ከተመለሰ በኋላ ነው። ግን እዚያው ባለበት ጊዜ የውል ውይይት ሳይጀምሩ ከማን ጋር እንደሚዋዋል በምልክት ሲያስጠነቅቁት፥ "ጣሊያን ምጽዋን እንድትይዝ ለምን ጋበዛችኋት?" አሉት። ሲሰማ ክው አለ። ምንም ከማያውቅ የዋህ ሰው ጋር የሚነጋገር መስሎት ነበር። የመጣው ኢትዮጵያ ከሱዳን ደርቡሾች ጋር እንዳትስማማ ቃል እንዲገቡለት ነበር። የማይከበር ቃል ያለው እንግሊዝ አገር ብቻ መስሎታል። "ግዴለህም፥ ደርቡሾች የሃይማኖታችን ጠላቶች ናቸው። እኛ እንደናንተ ክርስቲያኖች ነን" ሲሉትና በሰማው ሲደሰት፥ የደርቡሽ መልእክተኞች ከጓዳ ሆነው ይስቁ ነበር። እንግሊዝና ፈረንሳይ በኮሎኒ ሽሚያ ጊዜ በማህላቸው ግጭት እንዳይነሣ ሁለቱ ሀገሮች መስማማታቸውን ንጉሡ ስለሚያውቁ፥ የሱዳኖቹ መልእክተኞች ከመመለሳቸው በፊት የሰጧቸው ምክር፥ "በምሥራቅ (ከግብጽ) እንግሊዞች ሲመጡባችሁ፥ የፈረንሳይ ባንዲራ ሰቅላችሁ ጠብቋቸው። በምዕራብ (በፋሹዳ) ፈረንሳዮቹ ሲመጡባችሁ የእንግሊዝ ባንዲራ እያውለበለባችሁ ተቀበሏቸው" የሚል ነበር።

ታዲያ የተንኮታኮተችውን ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ ሌሎቹ ሲሳናቸው አፄ ምኒልክን የቀናቸውም በዚሁ  በዘዴኛነታቸው ነው።
.
ይቀጥላል....

#የጥቁር_ህዝብ_ኩራት
#ዓድዋ_123
#የኢትዮጵያውያን_ድል
#VictoryofAdwa
#Ethiopia

@wegoch
@wegoch
@kinchebchabi
ከንፈርሽ ያምራል ማለት ልሳምሽ ማለት ይሆን?
ስማ የላኩልህን የጓደኝነት ጥያቄ ቶሎ ባትመልስ ኖሮ እሰርዘው ነበር ግን እንኳን
ተቀበልከኝ። እኔም እኮ ቆንጆ ሴቶችን የመግፋት ስነልቦና የለኝም ....ቢሆንም ተርፈሀል።
ያው የምትፅፋቸው ነገሮች ያዝናኑኛል አንዳንዶቹ አይገቡኝም...አንዳንዶቹማ እኔንም
አይገቡኝም ግን አብረን ለመረዳት እንሞክራለን ያው አብረን ስል ለማቅረብ እየሞከርኩ
እንደሆነ ይታወቅልኝ።አንድ ቀን እኮ በአካል ከአንድ ወዳጄጋ አንድ ቴብል ላይ ቁጭ ብላ
እጄን ጨብጣለች እኔ ቡና ስጠጣ እሷ ምን እንደጠጣች እኔንጃ ከንፈሯን እንጂ የያዘችውን
አላየሁም ነበር አሁን ስጠይቃት እሷም አታውቀውም እኔን እያየች ነበር ይሆን? የዛኔ
ዝምተኛ ትመስል ነበር እኮ ...ከማከብረው ሰው አጠገብ ነበር የተቀመጠችው ለዛ ነው
ዝምታዬ የታያት እኔኮ ዝም የምለው በእንቅልፍ ልቤ ነው እሱም ስላልተቀረፀ ነው።
ያቺ ጓደኛህስ የት
ሄደች? አብረን አይደለንም እንጂ አለች አልኳት በምን ተለያያቹ?ሴት መንከባከብ
አትችልም በሚል ተልካሻ ምክንያት አልኳት።ምን አለቺኝ መሰለሽ በፍቅር እንጂ በፍልስፍና
አይኖርም። ብትረዳው እኮ ፍልስፍና ውስጥ ብዙ ፍቅር አለ ቆይ ግን
ያልገባን፣ያልተረዳነው፣ያልደረስንበት ነገር ሁሉ ፍልስፍና ነው? በአንዳንድ ሴቶች ፍቅር
መስጠት ማለት አንድ ቺብስ አንስተሽ ካቻብ አስነክተሽ ማጉረስ ይሄ ነው እንክብካቤ? በሯ
ላይ ያደረስሻትን ልጅ በሰላም ገባሽ ወይ ማለት ነው እንክብካቤ? ቤታቸው ምሽግ ነው
እንዴ? ማነች ደሞ እቺ አሁን የምታወራላት ለምትሉ በሚቀጥለው ቻፕተር ታገኟታላቹ።

ሰላም እደሩልኝ!!💚💛❤️

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ቀይ ለባሾቹ……

ዛሬ ከቢሮዬ አርፍጄ ነበር የወጣሁት ። በጠዋት መግባት ነው እንጂ ሊሳካልኝ
ያልቻለው አምሽቶ መስራት ልምዴ ነው። ዛሬ ግን ብቻዬን አላመሸሁም ነበር
ያለልምዷ ፀሃፊዬም አምሽታለች። ለወትሮ መውጫ ሰአቷን ለደቂቃ እንኳን
አሳልፋ አታውቅም ከሰራተኛ ሁሉ ፈጥና የምትወጣው እሷ ናት ፣ የኋላ የኋላ
ስሰማ ባል ተብየው ሁሌ ሰአቷን ጠብቆ በር ላይ እንደሚጠብቃት ሰማሁ። ዛሬ
ግን አምሽታ ሳያት ተጣልተው መሰለኝ ። በዛ ላይ በጣም አምሮባታል…….ከላይ
ያረገቻት ቀይ ቢጢሌ ቀያይ ጡቶቿን አንሳፈዋቸዋል…..ወንድ ልጅ መቼም እውር
ካልሆነ በቀር ምንም አይነት ጠንካራ እና ግትር ቢሆን እንኳን አይኖቹን መግታት
አይችልም ። ዛሬ ግን ለምን እንደሆነ ባለውቅም ተለየችብኝ አዘውትራ ነጭ ልብስ
ስለምትለብስ ነው መሰለኝ ዛሬ ቀይልብስ አድርጋ ሳያት ልዩ ሆነችብኝ። ከስር
ያረገችውም ቀይ መሆኑን ያቅኩት ከወንበሯ ተነስታ ስትቆም ነበር . የወገቧ
ቅጥነት እና የዳሌዋ ስፋት ቀይ በቀይ ሆነው ልክ እንደ ኤድስ ሪቫን ተቆላልፈዋል.
ሰአቱ ይበልጥ እየመሸ ነው ። እኔ የራሴ ቢሮዬ ውስጥ ተቀምጫለው ….ቀጥሎ
ካለው ቢሮ ፀሃፊዬ ብቻዋን ተቀምጣለች ….ስራ አንዳልስቆያት እርግጠኛ ነኝ…
ከባሏ ብትጣላ ነው ያመሸችው ስል ገመትኩኝ…ደሞ ሴቶች ከባሎቻቸው ጋር
ሲጣሉ ለምን መዘነጥ እንደሚወዱ አላውቅም በእነሱ ቤት ማስቀናታቸው ነው
…..ፀሃፊዬም ዛሬ ባሏን ለማስቀናት ከመዘነጧ አልፎ ሌላ ቦታ እንዳመሸች አርጋ
ባሏን ለማቃጠል ቢሮዋ ተቀምጣለች….ሃሳቤን ሰረቀችው…..ቢሮዬን አልፌ
ቢሮዋ ስደርስ መስታወት ይዛ ፊቷን ስትመለከት አገኘኋት ሳታስበው ስለገባሁባት
ደነገጠች….ፈገግ ስል እሷም የእፍረት የሚመስል ፈገግታ አሳየችኝ….ይመስለኛል
ከመልኳ ጋር በእልህ እያወራች ነበር። አይ ሴት በመልካቸው ሲመኩ እኮ ….መልክ
ለፈረስም አልጠቀማትም አለች አያቴ.

“ዛሬ ስራ በዛ እንዴ?” አልኳት ጠረንቤዛዋ ላይ እየተቀመጥኩኝ
“አይ ስራ እንኳን አልበዛም ትንሽ ማምሸት ፈልጌ ነው” አለችኝ ቀይ የተቀቡት
ከንፈሮቿ የጥርሷን ንጣት አጉልተውታል …..ዛሬ ባጠቃላይ ቀይ ሆና ተውባለች
“በሰላም ነው ? ሌላ ቀን ከሁሉ ቀድመሽ የምትወጪው አንቺነሽ፣ እንደውም
እንዳወጣጥሽ አገባብሽ ቢያምር ኖሮ እስካሁን የሁላችንም አለቃ በሆንሽ ነበር”
ስላት ሳቀች ዛሬ ምንድን ነው? አሳሳቁዋ እንኳን ተለየብኝ ለነገሩ ከዚህ በፊት
ብዙም ንግግር አልነበረንም …..ስለዚህ አስተውዬ አይቻት ስለማላውቅ ይሆናል.
“ማን ነው ያለው?”
“ሁሉም የቢሮ ሰው ያማሻል……ዛሬ ግን እኔም ገርሞኛል…ሁሌ ብቻዬን
ስለማመሽ” አልኳት
“ሁሌ ለምን ታመሻለህ?”

“በጊዜ ቤት መግባት አልወድም በጊዜም መጠጥ ቤት መሄድም አልወድም…..
ግዴታ ከሁለት አንዱ ጋር ነው የምሄደው ፣ ሁለቱም ደግሞ በጊዜ የሚኬድባቸው
አይደሉም …….. የግድ ማምሸት አለብኝ”
ሳቀች እሷ ግን ዛሬ ያለወትሮዋ ለምን እንዳመሸች ጠየቅኳት መልሷን ለመስማት
ጓጉቻለው ያቃጠላት ባሏን ለመበቀል እንደሆነ ስትነግረኝ በቃ አይዞሽ ትንሽ ዘና
በይ ብዬ ይዣት ለመውጣት አሰብኩኝ…..እሾህን በሾህ አይደል።መለሷ ግን
ለምን እንደሆነ አላውቅም አስደነገጠኝ
“ዛሬ እኮ ቫለንታይንስ ዴይ ነው……ከጓደኛዬ ጋር ማታ ነው ቀጠሮዋችን….ስለዚህ
ቤት አምሽቼ ከምወጣ እዚሁ አምሽቼ ላግኘው ብዬ ነው” አለችኝ። ለካ የእኛ
ሙሽሪት ቀይ በቀይ የተበሰው ለቫለንታይን ቀን መሆኑ ነው……ፀሃፍዬን ውጪ
የማግኘት አላማው ኖሮኝ ባያውቅም ዛሬ ግን ሳላስበው …..የሆነ ነገር ተሰምቶኝ
ነበር…..ለነገሩ ግልብ ስሜት እንደሆነ ጥርጥር የለኝም….ምክንያቱም ከዚህ በኋላ
ለሴት የምሰጠው እንጥፍጣፊ ስሜት የለኝም.
ጠረንጴዛዋ ላይ እንደተቀመጥኩኝ ስልክ ተደወለላት
“ደረስክ ….በቃ መጣሁ…መጣሁ” ብላ ስልኩን ዘጋችው
“በቃ መሄዴ ነው …አንተ ብዙ ትቆያለህ?” አለችኝ
“አይ ……ትንሽ” አለኳት……ከሄደች በሁላ ቢሮዬ ገብቼ በመስኮት
ተመለከትኳት……ቀዩዋ ሙሽራ አስፋልቱን ተሻግራ መኪና ውስጥ ስትገባ
አየሁዋት……ተሳሳሙ

ዛሬ ቫለንታይን ቀን ነው ማለት ነው?…..አልኩኝ አይምሮዬ ፍቅር ነክ የሆኑ ነገሮችን
ሁሉ እየረሳ መጥታል….ከመስኮቱ ሳልንቀሳቀስ….ሁለት ጥንዶች የአስፓልቱን
ጠርዝ ይዘው ሲጓዙ ተመለከትኳቸው….ሴቲቱ ቀይ ለብሳለች……..አሃ ቫለንታይን!!!

ብዙም ሳልቆይ ቢሮዬን ለቅቄ ወጣሁኝ……ሀሳቤ ሲናወጥ ተሰማኝ…..የቀበርኩትን
ጉድ ሁሉ ቀይ ለባሾቹ ቆፈሩብኝ….ህመም ለቀቁብኝ…..ወደማዘወትረው መጠጥ
ቤት ስደርስ……ሁሉ ተለዋውጦ ጠበቀኝ
በየጠረቤዛው ቀያይ አበቦች ተቀምጠዋል…ጥንዶች ይበዛሉ….ቤቱ አንደሌላው
ጊዜ ሞቅ ሞቅ ያለ ሙዚቃ አልተከፈተበትም….ቀዝቃዛ
ዘፈኖች….ይከታተላሉ….ቢራዬን አዘዤ ዙሪያዬን ማስተዋል ጀመርኩኝ……ብዙ ቀይ
ለባሾች ቤቱን ሞልተዋል…..ጥንዶቹ ሁሉ እንደድራማ ሰሪ እንቅስቃሴያቸው
በጥንቃቄ ነበር…..እጆቻቸውን ሲያቆላልፉ…መልሰው ሲላቀቁ….ስደባበሱ…
ሲነጋገሩ …..እየተጠባበቁ ሲሳሳቁ….ሳቄ መጣ….እነባዬም ሳቄን ተከትሎ መጣ…
ቀይ ለባሾቹ ዛሬ ቁስሌን ቀሰቀሱብኝ….ቀይ ነገር ጠላሁኝ ….ቀይ ሽብር ሁሉ ትዝ
አለኝ…ለእኔ ሃዘኑ የዛን ያህል ነውና.

ሳልፈልግ በግድ ሰብለን አስታወስኳት……ገንዤ ከቀበርኩበት በግድ ቆፍሬ
አወጣሁዋት……..በፍርድ ቀን ማስታወስ ሲገባኝ በፍቅር ቀን
አስታወስኳት…….ሰው ሁለቴ ሶስቴ አፈቀርኩኝ ሲል ይገርመኛል…..ልብ እንዴት
ከአንድ ጊዜ ባለይ ለሰው ይሰጣል? እየተቆራረሰ? እየተሸራረፈ? እንዴት ሁለቴ
ይፈቀራል…..የሌላውን ባላውቅም እኔን ግን አቅቶኛል…..ከድታኝ ለሄደችው ልቤን
ሰጥቻለው….መልሼ ስላልተቀበልኳት…ከዚህ በሁዋላ የምሰጠው ምንም የለኝም.
መጠጥ ቤቱ እየቆየ በቀይ ለባሾች ሞላ……ዘፈኑ እየቀዘቀዘ በሄደ ቁጥር ከኔ በቀር
ሁሉም በትዝታ እና በፍቅር ይግላል….እኔ ግን በረዶ እየሆንኩ ስመጣ ተሰማኝ…
በላይ በላዩ የምጨልጠው ቢራ ግን እየቆየ ያቀልጠኝ ጀመር.
እንደ ፍቅር እራስን ከፍ የሚያደርጉበት ነገር የለም…..ሁሉም ሰው ሲያፈቅር
እንደሱ ማንም ያፈቀረ አይመስለውም…እንደሱ ስለፍቅር የተጎዳ…ስለፍቅር ብዙ
ብዙ ነገር የሆነ ማንም እንደሌለ በርግጠኝነት ይወራረዳል….እኔም እኔ ሰብለን
እንዳፈቀርኳት…እኔ ስለፍቅር ሁን የተባልኩትን እንደሆንኩት ማንም የለም ብዬ
እወዳደራለው…ከፊቴ ያሉትም ሁሉም ቢጠየቁ ይሄኔ እንደነሱ ያፈቀረ ያለ
አይመስላቸውም ። አይምሮዬ ሲደማ ተሰማኝ….እንደ ቀይ ለባሾቹ….ቫለንታይንን
በቀይ ለማክበር ተገደድኩኝ ቀይ ለብሼ ሳይሆን አልቅሼ…አይኖቼን አቅልቼ……
የበይ ተመልካች ሆኜ….ዙራዬን ከከበቡኝ ቀይለባሽ ውቦች ጋር….ብቻዬን
ተከዝኩኝ…..ሰብለም ይሄኔ ከባለተረኛው ጋር ቀይ ለብሳ ቫለንታይንን እያከበረች
ይሆናል……እሷ ምን አልባት የምትሰጠው ልብ ይኖራታል ፣ ምክንያቱም……ከኔ
ጋር እያለች ለኔ አልሰጠችኝም…..አላፈቀረችኝም……ስለዚህ የማፍቀር እድሉ
አላት…..እኔ ግን እሷን ብቻ አፍቅሬአለው በቃኝ!

ልክ ነው ሃዘንም እንደ ደም ቀይ ነው….ፍቅርም እንደ ፅጌሬዳ ቀይ ነው….ሁለቱም
በቀይ ይከበራሉ…..በቀይ ይመሰላሉ
ሞቅ ሳይለኝ አይቀርም…… አስተናጋጁ ቢራ ሊጨምርልኝ መጣ…..ጠርሙሱ
እየከፈተ ፈገግ ሲል….ቀይ ድዱ ፍንትው ብሎ ታየኝ…..ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ
አይቼው ባውቅም ቀይ ድዱን አስተውዬው አላውቅም. ከት ብዬ ሳቅኩኝ
“ወገኛ አንተም እንደ ቀይ ለባሾቹ…….ቫለንታየንን በቀይ ማክበርህ ነው?” ብዬ
ለብቻዬ ሳቅኩኝ…..አስተናጋጁ ይከፋብኝ አይከፋብኝ አላውቅም። ሌሊቱ እየነጋ
ነው…..ሰው ሁሉ ተደስቷል እኔ ግን
ሳልሰክር አልቀርም ……ቫለንታየንን እንደ ጉድ
አከበርነው አልኩኝ…..ዝሆኗ እና ጉንዳኗን አሰብኳቸው
ዝሆንን እና ጉንዳን ድልድይ ሲሻገሩ ድልድዩ ይነቃነቃል አሉ….ከዛ ጉንዳኗ
“ነቀነቅነው” አለች አሉ። እንደምንም……ግን አከበርናት….እስኪነጋ ጨፈርን
….አለቀሰን….ተከዘን…አይ ቫለንታይን….እንደ ለቅሶ በጥቁር መከበር የነበረበትን
በአል በቀይ አጨማለቁት!!!!ቀይ ለባሾቹ…

((( ሚስጥር )))💚💛❤️


@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ረባሿን ሴትዮ አገኘኋት!
«ዘውድአለም ታደሠ»
እንዴት አመሸህ ህዝቤ? ፒስ ነህ ወይ? እኔ ሳይቸግረኝ ኮንዶሚኒየም ግራውንዱን ተከራይቼ መከራዬን እየበላሁ ነው። ኮንዶሚኒየም መኖር መከራው ብዙ ነው። ረብሻና ጩኸቱ አይጣል! በተለይ ምን እንዳዩ እንጃ የብሎኩ አሮጊቶች ጌሾ ሚወቅጡት፣ ስንዴ ሚያበጥሩት፣ በረበሬ ሚደልዙት፣ ሰው ሚያሙት ሁሉ እኔ በር ላይ ተቀምጠው ነው!
ዛሬ በግዜ ገብቼ ገና አረፍ ከማለቴ የሆነ ነገር
«ግው ግው ግው» ሲል ደንግጬ ተነሳሁና ድምፁን አዳምጥ ጀመር ... «ግው ፣ ግው ፣ ግም ፣ ግው» ይላል። አረ ይሄ ነገር ምንሼ ነው? አልኩ ደንግጬ ።
ግው! ግው! ግው! ሲል መሬቱ ራሱ ይንቀጠቀጥ ጀመር ... ደጄ ላይ ዳይኖሰር ዱብ ዱብ የሚል ሁሉ መስሎኝ ነበር። (አቤት ግነት)
ቀስስ ብዬ መጋረጃዬን ገልጬ ሳይ ሁለት አሮጊቶች በትልቅ ሙቀጫ የሆነ ነገር ይወቅጣሉ! እቺን ይወዳል ቶኪቻው!
በደምፍላት በሩን በርግጄ ስወጣ የፊት ጥርሳቸው የወለቀ ኮሳሳ አሮጊት
«ጎሽ ጎረምሳው ና ወዲህ» ብለው የያዙትን ግድንግድ የእንጨት ዘነዘና አቀበሉኝ። መቼም የቄራን ልጅ ሼም ነው የገደለው ዘነዘናውን ተቀብዬ አንድ ሀገር ሚጥሚጣ ወቅጬ ዘነዘናውን ላስቀምጥ ስል ሌላኛዋ አሮጊት
«እቺን ሳትጨርስማ ንቅንቅ የለም!» አሉኝ ቆፍጠን ብለው ሌላ ማዳበሪያ እየጠቆሙኝ። አረ ያሮጊት ጉልቤ!
ወፈር ስል ተንቀሳቃሽ ወፍጮ አረጉኝ እንዴ ሰዎቹ? እያልኩ በሆዴ ሳልወድ በግዴ መውቀጥ ጀመርኩ። አሁን ቆይ አንድ ማዳበሪያ ሚጥሚጣ ምን ይሰራላቸዋል በናታችሁ? ወይስ እኔን አስፈግተው ለልኳንዳ ቤቶች እያዞሩ ሊያከፋፍሉት ነው? መቼም ዘንድሮ ሁሉም ነጋዴ ሆኗል። የመሸጥ ዘመን ነው! ሁሉም ሻጭ ሆኖ ገዥ የጠፋበት ዘመን! ... (ኢየሱስኮ በዚህ ዘመን ተወልዶ ቢሆን በጨርቅ እንደተጠቀለለ ተሽጦ ነበር)
ለነገሩ አለም ራሷ በተለይ አፍሪካ ትልቅ ጉሊት ሆናለች! ሁሉም እጁ ላይ የገባውን ነገር ይዞ ለመሸጥ ገበያ ይወጣል! አፍሪካውያን እጃቸው ከገባ በኋላ ጨክነው ለገበያ የማያቀርቡት ብቸኛ ነገር ...... ስልጣን ብቻ ነው!
እናማ .... እንደምንም ሙሉ ማዳበሪያ ሚጥሚጣ ወቅጬ ጨርሼ አሮጊቶቹ ይመርቁኛል ብዬ ስጠብቅ ወላቃዋ የድሮ አራዳ «እንግዲህ በተመሳሳይ ፕሮግራም እንገናኛለን» ብለው ፈገግ አሉ። ወይ ዘመን ደሞ «በተመሳሳይ ፕሮግራም እንገናኝ» የሚል ምርቃት አመጡብን? .. አረ እቺ ኮንዶሚኒየም ወዴት እየሄደች ነው? ብዬ ወደቤት ገብቼ አረፍ አልኩና እነዚያ የማይሞቱትን አክተሮች ለማየት ቃና ልከፍት ሬሞቴን ሳነሳ እቺ ለሊት ተነስታ ቡና እየወቀጠች ምትረብሸው አንደኛ ፍሎር ላይ ያለችው ረባሿ ሴትዮ ትዝ ስትለኝ ዛሬም እንደልማዷ እኩለለሊት ተነስታ ቡና በመውቀጥ ብሎኩን ከማናጋቷ በፊት ቤቷ ሄጄ ማስጠንቀቅ እንዳለብኝ ወሰንኩ።
አዎ በጣም መሮኛል! ጎበዝ! እስከመቼ ነው በገዛ ቤታችን (ይቅርታ በኪራይ ቤታችን ለማለት ነው) እየተረበሽን የምንኖረው?
ዘራፍ!! ወንድ ልጅ ቆረጠ! አላርፍ ካለች በያዘችው ዘነዘና ..... (አረ የሰይጣን ጆሮ ይደፈን) ..... ብቻ ዛሬ አስቁሚያት በሰላም መተኛት አለብኝ። ብዬ ተንደርድሬ ወደቤቷ በመሄድ በሯን በሃይል አንኳኳሁ!
ወዲያው በሩ ቀስስ ብሎ ተከፈተና .... አንዲት ውብ ልጅ ብቅ አለች!! የተመሰቃቀለው ጥቁርና ረዥዥም ፀጉሯ ከእንቅልፏ እንደነቃች ይናገራል። ሰማያዊና ትንንሽ አይኖቿ ግምባሯ ላይ የተተከሉ የሰማይ ቁራጮች ይመስላሉ! ቻፒስቲክ ያልነካቸው በምራቅ የረጠቡ ከንፈሮቿ ልብን ቀጥ ያደርጋሉ። አፍንጫዋ ከንፈሮቿን የሚጠብቅ ቀጥ ብሎ የቆመ ዘብ ይመስላል ..... ዝቅ ብዬ እግሮቿን አየኋቸው።
ቀለም ያልነካቸው የጣቶቿ ጥፍሮች ፣ የጣቶቿ ርዝማኔ ፣ (አሁን በዚህ እግር በካልቾ ቢመታ ቅር የሚለው ሰው ይኖራል?) .... በዚያ ላይ ጠረኗ .... በምን አቅሟ ነው ይሄ ሁሉ ውበት የተሸከመችው በናታችሁ?
ቆይ!! ምናባቴ ፈልጌ ነበር የመጣሁት? አዎ ያቺን ረባሽ ሴትዮ ፍለጋ! ግን ብስጭቴ የት እንደገባ እንጃለቱ የሰሞኑ የሃይለስላሴን ሃውልት መስዬ በዝምታ ስቃኛት ....
«ፈልገኸኝ ነው ወንድሜ?» አለችኝ።
ብዙ ሰው «ወንድሜ» ብሎኛል። እንደዛሬ ግን ቃሉ ማርኮኝ አያውቅም። ወይ ድምፅ!! አሁን ይሄ ድምፅ እዚህ ቆሽቋሻ ኮንዶሚኒየም ውስጥ ይኖራል ቢሉ ማን ያምናል? ድምጿ ጆሮ ጋር ሳይደርስ ቀጥታ የሚያርፈው ልብ ላይ ነው!! ይሄን ድምፅ ነበር ዳውንሎድ አርጎ እየሰሙ ለሽሽ ማለት!
እንደምንም ቀልቤን ሰበሰብኩና
«እዚህ ቤት ለሊት እየተነሳች ቡና ምትወቅጥ ሴት አለች?» አልኳት።
ደንገጥ ብላ
«እኔ ነኝ ቡና ምወቅጠው ረበሽኩህ እንዴ?» አለችኝ።
ያልጠበቅሁት ነገር ቢገጥመኝም ቆፍጠን ብዬ እንዲህ አልኩ ...
«ታዲያ ቡና ጠጡ አይባልም እንዴ?»😂😂😂
@wegoch
@wegoch
@kaleab_1888
“የታጠፉት ገፆች”
Written by ሌሊሣ ግርማ
fo


…. ለእሱ እውነት ያለው አየር ላይ ነው፡፡ አየሩን እንጂ በቴሌቪዥን
የሚቀርበውን አየር ትንበያ ፈፅሞ አያምንም፡፡… ሰዎች በአንደበታቸው
የሚናገሩት መቶ ፐርሰንት ውሸት እንደሆነ ያውቃል፡፡ በአንደበታቸው ሲጎርሩ
ፊታቸውን በጥሞና ያጠናል፡፡ አይን አይናቸውን። እንደ አይን ሀኪም፡፡…
ተረማምደው ደረስን ከሚሉበት የበለጠ አረማመዳቸውን ያነባል፡፡ እውነት
እንዳላቸው ይገባዋል፡፡ እውነታቸው ግን የሚናገሩት ላይ አይደለም ያለው፡፡
ወይንም ለሰው ብለው ከቤታቸው ተለማምደው ይዘው አደባባይ ላይ
በሚወጡት አኳሃናቸው ላይ አይደለም፡፡
እውነታቸው ያለው ራሳቸውን ለጥቂትም ቅፅበት በሚረሱበት ጊዜ ነው፡፡
አንዳንድ ጊዜ ድብን ያለ እንቅልፍ ጥሏቸውም መተወን የሚቀጥሉ አሉ፡፡
በጉራ የሚያንኮራፉ፡፡ እሱ ሰዎችን ማንበብ ይችላል። ያነበበውን ግን
አይነግራቸውም፡፡ ከነገራቸው፤ ይደነግጣሉ፡፡ ግራ ይጋባሉ፡፡ ይቆጣሉ፡፡
ስለዚህ አይነግራቸውም፡፡ እያነበባቸው ይመሰጣል፡፡ እንደ መፅሐፍ፡፡
መፅሐፍትንም የሚያነበው እንደ ሰዎች ነው፡፡ በመስመሩ መሀል፡፡ ፀሐፊው
መናገር ከፈለገው ጀርባ ያለው ንግግሩን፡፡ አንባቢን ለመስበክ ሲጥር፣ ጥረቱ
ከምን እንደመነጨ ይገባዋል፡፡… መፅሐፉን በጣም መሸጥ የፈለገ…መፈለጉን
አይገልፅም፡፡ እሱ ግን እንዳይገለፅ በጥንቃቄ የተደበቀውን ያነባል፡፡
ሰዎች የማያምንበትን የፃፈ ፀሐፊን፣ በሙሉ እምነት ተመስጠው ሲያነቡ
አንዳንዴ ያጋጥሙታል። ሌላ ጊዜ ደግሞ መፅሐፍ በመፃፉ በራሱ ለመገረም
ድርሰት ያበረከተን ሰው ስራ፣ በራሳቸው የማንበብ አቅም ለመደመም መፅሐፍ
ሲያገላብጡ ያገኛል፡፡ ሁለት ተዋናዮች ሲናበቡ፡፡ እሱ ሁለቱንም በቀረቡበት
ዋጋ አይቀበላቸውም፤ ይመነዝራቸዋል፡፡ በቃ ይሄ “ሆቢው” ነው፡፡ የሰውን
እውነተኛ ማንነት ማንበብ፡፡
አንዳንድ ጊዜ እንዲያውም ሰዎቹም አያስፈልጉትም። ሰዎቹ የተጠቀሙበትን
እቃ በማስተዋል እውነተኛ ገፃቸው ይነበብለታል፡፡ መኪናቸውን፣ ቤታቸውን…
አንዳንድ ጊዜ የቤት ሰራተኞቻቸውን አይቶ ቀጣሪዎቹን ያነባል፡፡… ደግሞ
“ንባቤ በጣም ትክክለኛ ነው” ብሎ ነው የሚያስበው፡፡ ግምቱን ተጨባጭ
መረጃ ነው የሚያደርገው፡፡ ግን ተጨባጭ መረጃ ማለት ጋዜጣ ወይም
የዘንድሮው የሬዲዮ ዜና ከሆነ…ምናልባት አንድ ፊቱን ግምቱ ሳይሻል
አይቀርም፡፡
* * *
እና ብዙ አስመሳዮች ይገጥሙታል፡፡ ወይን ጠጅ እዘው፣ ሻማ አስለኩሰው
በአደባባይ የግጥም መፅሐፍ የሚያነቡ አይነቶች፡፡… የሚያነቡት የግጥም
መፅሐፍ ምን እንደሆነ አሻግሮ ይመለከትና… እየተወኑ ያለው ዘውግ
ይገባዋል፡፡ ጎመን የግጥም መፅሐፍን እንደ ጮማ በወይን ለማወራረድ
ሲታገሉ እሱ ተሻግሮ ተቀምጦ ያስተውላቸዋል፡፡… ተውኔቱን የሚያካሂዱት
ተመልካችን ለመሳብ ቢሆንም እሱ ግን ተራ ተመልካች አይደለም።
የተተወነውን ሁሉ አያምንም፡፡ “ሮማንቲክ” ትዕይንት ለመፍጠር ሲጥሩ…
“ቧልታይ” ይሆናሉ፡፡ መሆናቸውን ግን አያውቁትም፡፡ ሻማው ቀልጦ
እስኪያልቅ ችክ ብለው ከማይረባው መፅሐፍ ጋር መታገላቸውን ይቀጥላሉ፡፡..
መምሰል እና መሆን አንድ እና ያው ሆነው አያገኝም፡፡ “ዓለም ትያትር ናት”
ተዋናዮቹ ግን በደንብ መተወን አይችሉም፡፡ ማስመሰላቸውን ወደ መሆን
ደረጃ ማስጠጋት ያቅታቸዋል፡፡ የራሳቸውን መኪና ሲነዱ ሰርቀው ነው
የሚመስሉት፡፡ ይንቀዠቀዣሉ፡፡… ፊታቸው እንኳን በውስጡ እድሜ ልካቸውን
የኖሩበት አይመስልም፡፡…መጀመሪያ፤ ፊታቸውን እንዳይቆጣ በሰላምታ
ማለስለስ ያስፈልጋል፡፡… ሰላምታ በቀን አስር ጊዜ ካልተሰጣቸው ፊት ሰርቀው
መልበሳቸው የተነቃባቸው ይመስላቸዋል፡፡ የተነቃ ሲመስላቸው ተንኮለኛ
ይሆናሉ፡፡
…እሱ ራሱን መመልከት ነው እንጂ የማይችልበት…እነሱን ጠርጥሮ ማየት
ተክኖበታል፡፡ ብዙዎቹ ከስልካቸው ጋር ነው የሚጫወቱት፡፡ ወይም ከስልካቸው
ጋር ነው ሲጨንቃቸው የሚያወሩት፡፡… ከስልክ ጋር የሚጫወቱት ጥልቀት
አይገኝባቸውም፡፡ እሱ መፅሐፍ የሚያነቡትን ማንበብ ያስደስተዋል፡፡
ተመስጧቸውን በማጥናት የሚተውኑት ተውኔትን ጥልቀት መለካት ይችላል፡፡
… በመሰረቱ ነገር አለሙ በሙሉ ተውኔት ቢሆንም አንዳንዶቹ ግን በቀላሉ
አያስነቁም….፡፡ አተዋወናቸው ከልብ የመነጨ ይመስላል፡፡ እስኪያስነቁ ድረስ
እሱ ያስተውላቸዋል፡፡
* * *
…እችኛዋ ሰሞኑን እዚህ ካፌ ያገኛት ናት፡፡…. ምንም ጥያቄ አልነበረውም፤ገና
ዓይኑን እንዳሳረፈባት የተለየች መሆኑዋን አወቀ፡፡ ልዩ መሆኗ ብቻ ሳይሆን ደስ
አለችው፡፡… የካፌው በረንዳ ላይ ሆና ነው ቡና የምታዘው፡፡ በወረቀት
የተለበዱ መፅሐፍት ጠረጴዛዋ ላይ ከክርኗ ሳይርቁ ይቀመጣሉ፡፡ መፅሐፍቱን
በሰው ፊት አታነባቸውም፡፡ ግን እሱ እንደምታነባቸው አውቋል፡፡… የሚያነብ
ሰው እና የሚነበብ መፅሐፍ ያውቃል፡፡… ብዙ ጊዜ መፅሐፍ የሚሸፍን ሰው፣
የንባብ አሻራውን መደበቅ የሚፈልግ ነው፡፡… እቺ እንዲህ ናት። መነፅር
አድርጋለች፡፡ የአይን ነው፡፡ የፋሽን አይደለም። ጭንቅላቷ ከዳሌዋ ጎላ ይላል፡፡
ጎላ ማለቱን በፍሪዝ ፀጉሯ ውስጥ ደብቃዋለች፡፡ ቀለበት አላደረገችም…ግን
ባል ያደከማት ወይንም ያዳከመች መሆኗ ሰውነቷ እንደ ድመት ዘና ብሎ
ወንበሩ ላይ የሚቀመጥበት መንገድ ይገልፀዋል፡፡… ወይ አንዱን አባራ ሌላ
ከማጥመዷ በፊት እረፍት እየወሰደች ነው፡፡… ተነስታ ከመሄዷ በፊት አንድ
ሲጋራ ታጨሳለች፡፡… የተመልካችን ትኩረት ለመሳብ ወይ የራሷን ብስጭት
ለመግለፅ አይደለም፡፡ በቃ ማጨስ ስለፈለገች ነው፡፡ አንገቷ ላይ እንደ ሻሽ
የመሰለ ባለ ብዙ ጠቃጠቆ ሻርፕ ታደርጋለች፡፡ “ለማንም ጉዳዬ አይደለም”
የሚል ተውኔትን ለማንፀባረቅ ፈፅሞ አትሞክርም፡፡ እሱ ግን ለማንም ጉዳዩዋ
እንዳልሆነ እርግጠኛ ሆኗል፡፡
በዛ ሰዓት ያንኑ ካፌ እሱም ማዘውተር ጀመረ፡፡ ስለወደዳት ሊሆን ይችላል፡፡
ወይንም ተውኔቷ አዲስ ስለሆነበት…ብቻ ነገም ደግማ እስክትመጣ ቀደም
ብሎ ደርሶ ይጠብቃታል፡፡… ምናልባት መኖሪያ ሰፈሯ እዛው አካባቢ ይሆናል
ብሎ እየጠረጠረ ይጠብቃታል፡፡ ሰዓት አታዛንፍም፡፡ ሶስት ሰዓት ላይ እዛ
በረንዳ ላይ ናት፡፡ መፅሐፍ ከክርኗ አጠገብ ይቀመጣል፡፡ ቡናውን ቀስ ብላ
ትጠጣለች፡፡
….ቀስ እያለ አጠገቧ ያለው ወንበር ላይ መቀመጥ ጀመረ፡፡ እጆቿን
ያስተውላል፡፡ እጅ ብዙ ነገር ይናገራል። በእንክብካቤ ነው ያደገችው፡፡ ምንም
አይነት ስራ ሰርታ አታውቅም፡፡ ኮምፒውተር ላይ በጣም ፈጣን የሚመስሉ
ረጃጅም ጣቶች ነው ያሏት፡፡… ሊያናግራት ሞክሮ ያውቃል፡፡ አጭር መልስ
ሰጥታው ያለ ሰዓቷ ለመሄድ ተነሳች፡፡ ከዛ በኋላ ጎኗ ላለመቀመጥ ማለ፡፡
ፈራት፡፡
በመስመር መሀል ሊያነባት አልቻለም፡፡ ተሰቃየ። የሆነ ማስተር ፒስ ነገር
ሆነችበት፡፡ ጠረኗ እንደ ልጅነት ትዝታ እየመጣ ማታ ይረብሸዋል፡፡… የካፌውን
አስተናጋጆች ስለ ማንነቷ ጠይቆ አጥጋቢ መልስ አላገኘም፡፡… አድራሻዋን
ማወቅ አልፈለገም፡፡ አድራሻ ምንም አያደርግለትም፡፡ የምታነበውን መፅሐፍ
ብትሰጠው በደንብ ያውቃት ነበር፡፡ እሷን ከማንበብ የምታነበውን መፅሐፍ
ማንበብ ይቀላል፡፡
…ከብዙ ክትትል በኋላ አንድ ቀን በጋዜጣ- ያልተለበደ መፅሐፍ ይዛ መጣች፡፡
የአማርኛ መጽሐፍ። ትንሽ ሳትቸኩል አትቀርም የዛን ቀን፡፡ የቡናዋን ከፍላ
ሲጋራዋን በጥድፊያ አጭሳ ተነሳች፡፡…ወጣች፤ አልተመለሰችም፡፡ ጠረጴዛው
ላይ የተወችውን መፅሐፍ፣ እሱ ተሸጉጦ ከሚያስተውልበት ተንደርድሮ
አነሳው፡፡… እንደ ሌባ በጉያው ሸጉጦት፣ ከዛ አካባቢ ተሰወረ፡፡
ሌላ ስፍራ ሄዶ ይገላልጠው ጀመር፡፡ መፅሐፉ የበዕውቀቱ ስዩም “ስብሰብ
ግጥሞች” ናቸው፡፡… መፅሐፉ ላይ ያለውን ግጥ
ም ሳይሆን የመፅሐፍ
ባለቤቲቷን አሻራ ለማንበብ ገፆቹን በጥንቃቄ ያገላብጥ ጀመር፡፡
በመግቢያው ገፅ ላይ “T” የሚል አንድ ፊደል ሰፍሯል፡፡…የእሷ ስም መሆን
አለበት ብሎ አሰበ፡፡…ወይ “ፅጌ”… “ፀደኒያ”… ፀሐይ እንኳን አትሆንም፡፡ በቃ
“ፀ” ብዬ ልያዛት አለ፡፡
እያንዳንዱን ገፅ በጥሞና መመርመር ጀመረ። አንዳንዶቹ ግጥሞች ያሉበት
ገፅ ጆሮው ታጥፏል፡፡ ለምሳሌ ገፅ አስራ ስምንት፣ “ሞኝ ፍቅር” የሚለው፡፡
“ለሱ
ሰው ብቻ አይደለችም
ጠፈር ናት ባካሏ
መሬት ናት በነፍሷ
ዕድሜ ልኩን ቢሮጥ
አያመልጥም ከሷ፡፡”
ይላል ግጥሙ፡፡ ፌመኒስት ናት ብሎ አሰበ፡፡ ወይንም ጥሏት የሄደው ወንድ
ተመልሶ መጥቶ መለመኑ አይቀርም ብላ አስባ ይሆናል…እያለ ገፆቹን ማጥናት
ቀጠለ፡፡ ሌላ የታጠፈ ገፅ አገኘ- “ይድረስ ለአድርባይ ጓዴ” ይላል የግጥሙ
አርዕስት፡፡
“እየለየ ጊዜ ቦታ እየመረጠ
እስስታማ መልክህ ገፅኽ ተለወጠ
አህያ እንዳልነበርክ በሰርዶዎች መሀል
አህዮች ሲበዙ ዛሬ ጅብ ሆነሀል”
ይኼም ያው ጥሏት የሄደው ሰውዬ የበደላትን የሚገልፅ ግጥም መሰለው፡፡
የሆነ አህያ ሰው ጋር ነው ፍቅር ይዟት የነበረው፡፡ ግን ፍቅሩ ወጥቶላታል፡፡ ለዛ
ነው “አድርባይ ጓዴ” ብላ የጠራችው፡፡…የታጠፉት ገፆች የተወሰኑ ናቸው፡፡..
እየመረጠ፣ በከፍተኛ ጥሞና ማንበቡን ቀጠለ፡፡ የግጥም መፅሐፉን ከዚህ
በፊት አንብቦታል፡፡ አሁን ግን እያነበበ ያለው እሷን ነው፡፡ “ፀ”ን፡፡ የእሷን
ደብዳቤ ነው በግጥሞቹ ውስጥ ተፅፈው ያገኛቸው፡፡
ቀጥሎ “የባይተዋር ገድል” የሚለው መልዕክቷን አነበበው፡፡ ገፁን በደንብ
አድርጋ ነው ያጠፈችው፡፡ ምን ያህል ባይተዋር ሆና እንደተሰቃየች ወለል ብሎ
ታየው። እንደዛ በረንዳ ላይ ተቀምጣ እያያት የሰበሰው ምስል ሁሉ በዚህ
ግጥም ውስጥ መልሶ መጣበት፡፡ የግጥሙ የመጨረሻው ስንኞች በጥቁር
ቀለም ተሰምሮባቸዋል፡፡
“…በሌሊት ወፍ ምትክ፣ ክንፍ ያወጣ ሌሊት፣ ጎጆህን ሲዞረው
መረሳት የሚሉት፣ የኑሮ ገባር ወንዝ፣ አልጋህን ሲገምሰው
“መንሳፈፉስ ይቅር፣ መስጠም ያቅተዋል ሰው” ሲያሰኝህ እድልህ
ያኔ ይጀመራል፣ የባይተዋር ገድልህ”
…የእሷን ድምፅ አንዴ ብቻ ነው የጠየቃትን አልባሌ ጥያቄ ስትመልስለት
ያዳመጠው፡፡ አንድ ጊዜ ብቻ፡፡ ያችኑ ትዝታውን ተጠቅሞ ግጥሙን
ሲያነብ፣በህሊናው የእሷ ድምፅ ነበር በለቅሶ ዜማ የሚንሾካሾክበት፡፡…
ህመሟ ቁልጭ ብሎ ታየው፡፡ እንባው እንደ ሳግ ጉሮሮው ላይ መጥቶ
ተጠራቀመበት፡፡… ሳያስበው አንድ ነገር ተገለፀለት፤ እቺን ልጅ ከገባችበት
ሀዘን ለማውጣት ከነገ ጀምሮ እንደሚጥር፡፡ “ይኼ ተውኔት አይደለም” አለ
ለራሱ፡፡ ይኼ እውነተኛ የሰው ነብስ ሀዘን ነው፡፡ እደርስላታለሁ…፡፡ ብሎ
በሀይል ማለ፡፡
የመጨረሻው የታጠፈ ገፅ ላይ ያለውን ግጥም፣ እንባ ብዥ ባደረገው አይኑ፣
ጉሮሮው ላይ ያለውን ሳግ ለመዋጥ እየታገለ አነበበው፡፡ “ምንቸት እና ጋን”
ይላል አርዕስቱ፡፡
“ይኑሩ እንጂ ባ’ገር
በቀዬ በሰፈር
ኩሬ ሙሉ ውኃ፣ ምድጃ ሙሉ ሻይ
ዳውላ ሙሉ አፈር
የምንቸቶች ስፍር መች በጋን ይለካል
ጋኖች እንኳን ቢያልቁ ሌላ አፈር ይቦካል፡፡”
በገፁ ላይ ጠብ ያለውን እንባ ሲጠርግ፣ የድል አድራጊነት መንፈስ እየዋጠው
ነበር፡፡ ያ አህያ ባሏ ጥሏት ቢሄድ…ሌላ አፈር ይቦካል፡፡ እኔ እሱን እተካዋለሁ፡፡
እንደኔ የሚረዳት የለም፡፡ እንደኔ እሷን ማንበብ የሚችል የለም፡፡…ድንገት
እርግጠኛ ሆነ- እቺ ሴት “ፐ”… “ፀ” የእሱ እጣ ፋንታ መሆንዋን አመነ፡፡
ቀኑ እንዴት እንዳለፈ አያውቀውም፡፡ ግጥሞቹን ከገጣሚው በላይ ተረዳቸው፡፡
የሚረዳቸው ደግሞ በእሷ አንፃር እያደረገ ሲተረጉማቸው ነው፡፡ ገፃቸው
የታጠፉትን ብቻ ሳይሆን ያልታጠፉትንም… ልክ እንደ እሷ ደብዳቤ እያሰባጠረ
አነበባቸው፡፡
በተከታዩ ቀን ካፌው ገና ሳይከፈት ቀድሞ ተገኘ። እሷ በሰዓቷ መጣች፡፡ ግን
ብቻዋን አልነበረችም። ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ ጠና ያለ ሰውዬ ጋር ነው
የመጣችው፡፡ አጎቷ ለመሆን እድሜው ትንሽ ያጥራል፤ ግን እኩያዋ
ለመሆንም ይበዛል፡፡ ጥጥ እራስ ነገር ነው፡፡
እሱ… አዘጋጅቶ የመጣው ዲስኩር ጠፋበት። ሽማግሌው ሰውዬ ከየት
መጥቶ ህልሙ መሀል እንደገባበት አላወቀም፡፡… በስንት መከራ ኪሱ ውስጥ
የሸጎጣትን የግጥም መፅሐፍ በቀስታ አውጥቶ ወደ “T” አቅጣጫ ሰደደው፡፡
…የእጅ አዘረጋጉ ሊኮረኩራት እንደከጀለ አይነት ከተሸማቀቀች በኋላ…
መፅሐፉን ስታየው…ስትለየው ድንገት ፈገግ አለች፡፡
“ትላንት እዚህ ጥዬው ሄጄ ነው?” ብላ ጠየቀችው፤ ግልፅ በሆነ የዋህ
አንደበት፡፡
“አዎ” አላት እሱ፡፡
“…መፅሐፌን ብትጥይው ኖሮ አልለቅሽም ነበር” አለ አጎትየው፡፡ እና ጠጋ
ብሎ “አሁን ሳሚኝና መፅሐፌን ስጭኝ…” አላት፡፡
ሳመችው፡፡ አጎትየው ፍቅረኛዋ ሆነ፤ ሲሳም፡፡
“የግጥሙን መፅሐፍ እሱ ነው የሚወደው…እንኳን አልጠፋ…አይለቀኝም
ነበር፡፡” አለች፤ ወደ እሱ ዞር ብላ እንደ ማስረዳት፡፡ ከዛ ወደ አጎቷ ተመለሰች፡፡
እሱ ምንም ሳይናገር ከጎናቸው ተነስቶ ሌላ ቦታ ቀየረ። መሄዱን ልብ
አላሉም፡፡ … የሆነ ጥግ ተወሽቆ ሁለቱ ሲዳሩ፣ እሱ ብቻ ማየት የሚችለውን
ጥናት ማድረግ ቀጠለ፡፡ በመስመር መሀል ማንበቡን፡፡ መስመሮቹ ግን ብዥ
ብለው ያበጡ ሰንበሮች ይሆኑበታል፡፡…ቢሆኑም ማንበቡን አያቋርጥም፡፡

የኔዋ💚ሸጋዋ💛ቅዳሜ❤️!!!!

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ሰለም ሰላም እንደምን አላችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን እህቶቸ እና ወንድሞቸ
፨ ፈለገ ጥበባት የሚል የቴለግራም ግሩፕ አለ አላማው የተደበቁ የኢትዮጵያን ማንነቶች፤ የአበው የአባቶቻችን የእውቀት ልቅህና ከውቂያኖስ የጠለቀ እወቀትና ሚስጥር፤ ተሰምተው እና ታይተው የማይታወቁ የተሰወሩ ገዳማትን፤ የኢትዮጵያን የትላት ድብቅ ና ሚስጥራዊ ማንነቷ የወደፋት እጣ ፈንታዋን የሚያትቱ ገዳማት ብቻ ላይ የሚገኙ የአበው የትነቢት መፅሀፍትን እነ ፥መፅሀፍ ሔኖክን እነ እራእየ ሳቤላ፥ መፅህፈ አክሲማሮስን፥ ፍካሬ እየሱስን የመሳሰሉ ፥ስለ ሀገራችን ምን ምን ሚስጥራትን ይተነብያሉ? አለም የሚመካባቸው ታላላቅ ስራወች ምንጫቸው ሰርቀው የወሰዶቸው የእኛው የብራ መፃህፍቶች አንደሆኑ በመረጃ አንመለከታለን ..ይህን እና የመሳሰሉትን በሰፊው እናያለን፡፡ ይህ ግሩፕ ማንኛውም ሀይማኖትን ፣ ዘርን ፣ ብሄርን አይከለክልም አላማውም ኢትዮጵያዊነትን ማስተዋውቅ ነው ፤ለሁም ክፍት ነው በሉ አሁን ወደ ዚህ ግሩፕ ለመቀላቀል ታች ያለውን ተጭነው ጆይን ያድርጉ::
👇👇👇👇👇👇
@Wegoch
@felegetibebat
@felegetibebat
ጓሳና ድንግል ያለአንድ ቀን
አይበቅል

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ገበሬ አንዲት ክፉ ሚስት ነበረችው፡፡ በእርሻ
ሲደክም ውሎ ሲመጣ፤
“ና ወጥ ስራና ራቴን አብላኝ”
“ና እግሬን እጠበኝ” ትለዋለች፡፡
ሌላ ቀን ደግሞ፤
“ወገቤን አሞኛል ና እሸኝ” ትለዋለች፡፡
ደሞ ሌላ ጊዜ፤
“ና፤ እግሬን እጠበኝ”
“ና በቅባት እሸኝና አስተኛኝ!” ትለዋለች፡፡
እንዲህ ቁም ስቅሉን ስታሳየው ከርማ፣ የአምላክ ፈቃዱ ሆኖ ከዚህ ዓለም
በሞት ተለየች፡፡
ከሞተች በኋላ ብዙ ጊዜ በብቸኝነት መኖሩን ያስተዋሉ ሰፈርተኞች መክረው
ዘክረው፤ ሌላ ሚስት እንዲያገባ አደረጉት፡፡
አዲሲቱ ሚስት ደግሞ የመጨረሻ ደግ፣ አስተዋይ ሆነችለት፡፡
ጠዋት ከአልጋው ሳይነሳ ቆንጆ ቁርስ ሰርታ እዛው ባፍ-ባፉ አጉርሳው፤ ማታም
ከእርሻ ሲመለስ እግሩን አጥባ ወገቡን በቅባት አሽታ፣ ራቱን አጉርሳው
አቅፋው ትተኛለች፡፡
ይሄኔ ይህ ባል፤ እንዲህ ብሎ ፀለየ ይባላል፡-
“አምላኬ ሆይ፤ ስላደረክልኝ ሁሉ ምስጋና ይግባህ! አንድ ውለታ
እንድትውልልኝ እጠይቅሃለሁ፡፡ ይኸውም ከዚች የተሻለች የምትመጣ ከሆነ
እባክህ እቺንም ግደልልኝ!”
***
ዱሮ፤ ዱሮ ዱሮ፤
“ጉዟችን ረዥም
ትግላችን መራራ” ይባል ነበር፡፡
አንድ የደርግ ካድሬ አገሩን ሲያምስ ሲያተራምስ ከርሞ ተረኛ ታካሚ ሆኖ ራሱ
ታሰረ፡፡ ከዚያ ሲደጋግመው የኖረውን ያንን መፈክር መጠየቅና መቃወም
ጀመረ፡-
“ትግላችን መራራ፣ ጉዟችን ረዥም” ብሎ ነገር ምንድን ነው? መራራ ከሆነ
አጠር ይበል፣ ረዥም ከሆነ ጣፈጥ ይበል፡፡ ለምንድን ነው ለህዝባችን ደግ
የማንመኘው” አለ። ካልተቀጡ የማይማሩ አያሌ ካድሬዎች ስናፈራ ኖረናል፡፡
ዞሮ ዞሮ ቤት ያፈራቸው ናቸው!
ዛሬም ሊቀጥል እንደሚችል ጭንቅላትን ይዞ ማሰብ አይጠይቅም፡፡ ዋናው
ከሆነውና ከሚሆነው መማር ነው!
“ምንኛ ታድሏል የሰነፍ አዕምሮ
እንኳን መማር ቀርቶ ፊደል ሳያጠና
ሁሉንም ያወቀ ይመስለዋልና
አሁን የት ይገኛል ቢፈልጉ ዞሮ
መስማት ከማይፈልግ የባሰ ደንቆሮ”
ብለዋል ከበደ ሚካኤል፡፡ መስማት ካቃተን ለውጥ አናመጣም፤ ዕውነት
ለመናገር ለውጥን ከልብ ካላሰብነው አገር አንለውጥም፡፡ መቼም! መቼም!
መቼም!
የመከላከያን መዋቅርና አስተሳሰብ፣ መለወጥ፣ ስለደ ህንነት ያለንን ግንዛቤ
ማሻሻል፣ አገርን ከማዳን አኳያ መታደጊያችን ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የንቃተ
ህሊናችን መበልፀግ እጅግ ወሳኝ ነው፡፡ እነዚህን የአገር ህልውናዎች
በጤናማ መንገድ አለመንከባከብ ቆይቶ ያስከፍለናል፡፡ ወታደራዊና
ደህንነታዊውን ኃይል በጤናማ ዐይን ካላየን፣ እንዲሁም የምንመኛትን
ኢትዮጵያ ለመገንባት ካልተዘጋጀን፣ እንደ ልማዳችን ይረፍድብናል፡፡ “ባለበት
ሃይ!” የምንባለው ለዚህ ነው!
አንዳንድ ዕድሎች አይደገሙም፡፡ አጋጣሚዎችን ቀልጠፍና መጠቅ ብለን
ካልተጠቀምንባቸው ያመልጡናል፡፡ አንዴ ከጠፉ የማይመለሱ ብዙ ናቸውና
ይሄንን ቀን አንጣው!
Girl, if you want to
Prove that you are a virgin
Don’t forget, that
you’ll never prove it again!
ድንግልናሽን ማረጋገጥ ከፈለግሽ ደግመሽ እንደማታረጋግጪው እወቂ፤
እንደማለት ነው፡፡ “ጓሳና ድንግል ያለአንድ ቀን አይበቅል” ማለት ይሄ ነው!!

(( ነብይ መኮንን ))💚💛

ምንጭ:-አዲስ አድማስ ጋዜጣ ( የካቲት 9/06/2011 )

ሸጋ የረፍት ቀን!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ግራዚያኒ እነዚህን ህዝቦች ሲጨፈጭፋቸው...አንተ ኦሮሞ ነህ፣አማራ ነህ ፣ትግሬ ነህ ጉራጌ ነህ ብሎ ወይም ዘርን ለይቶ አይደለም። አንተ የኢትዮጵያ ህዝብ ብሎ እንጂ። ( ዘረኞች ይሄንን እውነታ እንዴት መረዳት አቃታቸው .? )

አገር በቀልድ እንዳልተገነባች ማሳያ በቂ ነው እነዚህ ሰዎች የሞቱት በዘራቸው ሳይሆን ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው !!!

ክብር ለሰማዕታት !!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ለሞተልህ ያልቆምክ አንተ ለማን ልትሞት? ኢትዮጵያዊነት ነጻነትና መስዋእትነት ነው።
አንገታችን የተቃናው፣ ልባችን የኮራው በሞቱልን ሰማእት ነው። ኢትዮጵያን አትግፋ፥ እሷን
ገፊ የስሪቷ አሻራ ጣይ የሚያኮሰምነው፣ ማቅናት ያልቻለ እብቅና ቅንቅን ነው!!

💚💛

@wegoch
@wegoch
የካቲት 12 ግን ታስቦ መዋሉ ብቻ በቂው ነው ትላላችሁ???

አስተያየታቹን ከነ ምክንያታቹ ብታደርሱን ደስ ደስ ይለናል....

ክብር ለሰማዕታት !!💚💛

@balmbaras
@Gebriel_19
Audio
የካቲት 12
በ ሀይማኖት ግርማ

ከ ጳውሎስ ኞኞ 'የኢትዮጵያ እና የኢጣልያ ጦርነት'.


@getem
@wegoch
2024/09/28 17:27:11
Back to Top
HTML Embed Code: