Telegram Web Link
ዩናይትድ ተጫዋቹን ሊሸጥ ነው !

ማንችስተር ዩናይትድ ፈረንሳዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ዊሊ ካምብዋላ ለስፔኑ ክለብ ቪያሪያል ለመሸጥ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።

ቪያሪያል ተጨዋቹን በ10 ሚልዮን ዩሮ ለመግዛት ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ከስምምነት መድረሳቸው ተነግሯል።

ተጨዋቹ በቀጣይ የህክምና ምርመራውን በማድረግ ቪያሪያልን በይፋ ለመቀላቀል ቀጠሮ እንደተያዘለት ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አስቶን ቪላ አማዱ ኦናናን ሊያስፈርም ነው ! በአሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ የሚመራው አስቶን ቪላ ቤልጂየማዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች አማዱ እናና ከኤቨርተን ለማስፈረም መቃረባቸው ተነግሯል። የ 22ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጫዋች አማዱ ኦናና በአስቶን ቪላ ቤት የረጅም ጊዜ ኮንትራት ለመፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊው ክለብ አስቶን ቪላ አማዱ ኦናናን በ50 ሚልዮን…
ጃሬድ ብራንዝዌት ኤቨርተንን ላይለቅ ይችላል !

የመርሲሳይዱ ክለብ ኤቨርተን አማካይ አማዱ ኦናና ወደ አስቶን ቪላ ማምራት በማንችስተር ዩናይትድ የሚፈለገውን ጃሬድ ብራንዝዌት ዝውውር ሊያስቀረው እንደሚችል ተገልጿል።

አማዱ ኦናን በ50 ሚልዮን ፓውንድ ለአስቶን ቪላ ለመሸጥ የተቃረበው ኤቨርተን ከፍተኛ የዝውውር ሒሳብ ካልቀረበላቸው ጃሬድ ብራንዝዌትን በዚህ ክረምት ላይሸጡት እንደሚችሉ ተነግሯል።

ቀያዮቹ ሴጣኖች ለ 21ዓመቱ ተከላካይ ጃሬድ ብራንዝዌት 50 ሚልዮን ፓውንድ የሚደርስ ሒሳብ አቅርበው በኤቨርተን ውድቅ እንደሆነባቸው ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
Photo
“ ለወጣቶች ልምዴን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ “ ናኒ

በመቻል ስፖርት ክለብ ምስርታ ላይ ለመገኘት ግበዣ ቀርቦለት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ሉዊስ ናኒ በመምጣቱ በጣም ደስተኛ መሆኑን ገልጿል።

" ኢትዮጵያ በመምጣቴ በጣም ደስተኛ ነኝ " ያለው ሉዊስ ናኒ " ኢትዮጵያን ባህሏን ሕዝቧን ማወቅ እፈልጋለሁ ፣ በመቻል ስፖርት ክለብ የምስረታ በዓል እንድገኝ ግብዣ ሲቀርብልኝ በደስታ ነው የተቀበልኩት " ሲልም ተናግሯል።

ግብዣው ኢትዮጵያን ለማየት እና ለመጎብኘት ዕድል እንደሚፈጥርለት የገለፀው የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋች ሉዊስ ናኒ " ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ እግር ኳስ ስፖርተኞችን ለማውጣት ወጣቶችን እና አካዳሚ ላይ መሥራት ይገባል።

በቀጣይ ለወጣቶች ልምዴን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ ለዛም ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት“። በማለት ተናግሯል።

ምንጭ - ኢዜአ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🇪🇹 ዋናው ስፖርት 🤝

✍🏾 ታላቅ ስምምነት ከ #ዋናው! ✍🏾

#ቅርብ ቀን ይጠብቁን...

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
ከተመረጡ ባንኮች ወደ M-PESA ገንዘብ በማስተላልፍ በቀላሉ ክፍያዎችን እንፈፅም ፤ እስከ 50 ብር ተመላሽ ስጦታ እናግኝ።

M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!

🔗የM-PESAን ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom  #FurtherAheadTogether
“ ሳካ እንዴት እንደሚጫወት አውቃለሁ “ ኩኩሬላ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን የመስመር ተጨዋች ማርክ ኩኩሬላ በነገ ምሽቱ የፍፃሜ ጨዋታ ቡካዩ ሳካን ሜዳ ላይ ምቾት ለማሳጣት እንደሚሞክር በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" ቡካዩ ሳካ እንዴት እንደሚጫወት አውቃለሁ " የሚለው ኩኩሬላ ስለ እሱ ቪድዮች መመልከት አይጠበቅብኝም ምክንያቱም ሁሉንም የአርሰናል ጨዋታዎች ተመልክቻቸዋለሁ ብሏል።

ከሳካ ጋር መጫወት ከባድ መሆኑን የገለፀው ተጨዋቹ " ነገርግን ይህ ፈተና ያስደስተኛል የመጀመሪያ አላማዬ እሱን ሜዳ ላይ ምቾት ማሳጣት ነው " በማለት ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" እንግሊዝ የብሔራዊ ቡድን ሪያል ማድሪድ ነች " ዋትኪንስ

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጨዋች ኦሊ ዋትኪንስ በአሁን ሰዓት የሶስቱን አናብስት ማሸነፍ አስቸጋሪ መሆኑን በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" እንግሊዝ ማለት የብሔራዊ ቡድን ሪያል ማድሪድ ነች " የሚለው ኦሊ ዋትኪንስ " ሁኔታው ተመሳሳይ እንደሆነ ያሳያል እኛን ማሸነፍ በጣም አስቸጋሪ ነው እኛ ለማሸነፍ አንድ የግብ እድል በቂያችን ነው በማለት ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ማይኖ ነገ ግብ እንደሚያገባ ይሰማኛል " ሩኒ

የቀድሞ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች ዋይን ሩኒ ኮቢ ማይኖ በነገው የአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ለቡድኑ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተናግሯል።

“ ኮቢ ማይኖ በነገው ጨዋታ ግብ እንደሚያስቆጥር እና በእንግሊዝ ውስጥ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ይሰማኛል “ የሚለው ዋይን ሩኒ እሱ በጥቂት አመታት ከአለም ምርጥ ተጨዋቾች አንዱ ይሆናል ብሏል።

“ ቤሊንግሀም ፣ ላሚን ያማል ፣ ኒኮ ዊሊያምስ እና ፎደን በአጥቂ ስፍራ ነው የሚጫወቱት ኮቢ ማይኖ ትልቅ ዲሲፕሊን እና የጨዋታውን ጥልቅ ግንዛቤ የሚጠይቅ ቦታ ነው የሚጫወተው “ ሩኒ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" እንግሊዝ ሻምፒዮን የምትሆንበት ጊዜ አሁን ነው " ዴክላን ራይስ

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዴክላን ራይስ ቡድናቸው የአውሮፓ ዋንጫው ሻምፒዮን የሚሆንበት ጊዜ አሁን መሆኑን በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" ከብሔራዊ ቡድን ጋር በተከታታይ ለሁለተኛ ጊዜ ለፍፃሜ የመድረስ አጋጣሚ አይገኝም " የሚለው ዴክላን ራይስ ከባለፈው ፍፃሜ ተምረናል ነገ ማሸነፍ ነው ፍላጎታችን ሲል ተደምጧል።

ስፔን ሮድሪ ብቻ ሳይሆን ጥሩ አማካዮች መያዟን የገለፀው ዴክላን ራይስ " እንግሊዝ የአውሮፓ ዋንጫውን የምታሸንፍበት ጊዜ አሁን ነው " በማለት ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Spain - England
Argentina - Colombia
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from HEY Online Market
•PlayStation 5, 73,000 Birr
•Playstaion 5 Slim, 78,000 Birr

•PlayStation 4 Slim, 35,000 Birr
•PlayStation 4 Pro, 43,000 Birr

•Playstaion portal, 35,000 Birr
•Meta Quest 2, 55,000 Birr
•Meta Quest 3, 83,000 Birr

Contact
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
" አላማችንን ለማሳካት ጥሩ እድል አግኝተናል " ሳውዝጌት

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት ቡድናቸው በምሽቱ ጨዋታ ተደራጅቶ እንደ ቡድን እንዲጫወት ከጨዋታው በፊት በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል።

አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት ምን አሉ ?

- " ለማሳካት ያሰብነውን አላማችንን ለማሳካት ጥሩ እድል አግኝተናል ስለፍፃሜው ለተጨዋቾቹ ብዙ መናገር አያስፈልግም ለፍፃሜ ተጨማሪ ማነሳሻ ነገር አያስፈልገውም።

- ዛሬ ጥሩ እንቅስቃሴ አድርገን ማሸነፍ እንፈልጋለን አስደሳች ታሪክ ይሆናል ዋንጫው በእጃችን ነው ያለው ህልማችንን ለማሳካት አንድ ጨዋታ ነው የሚቀረን።

- የስፔን ብሔራዊ ቡድን ኳስን ተቆጣጥሮ በጥሩ ሁኔታ የሚያጠቃ ቡድን ነው በደንብ ተደራጅተን መጫወት አለብን በመጨረሻው ጨዋታ ጥሩ ኳስ ተቆጣጥረናል።"ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ዋንጫውን ማሸነፍ እንፈልጋለን " ሉዊስ ዴ ላፉንቴ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላፉንቴ ቡድናቸው በአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ መድረሱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ከምሽቱ ጨዋታ በፊት በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።

" እዚህ ባደረግነው ነገር ደስተኛ ነኝ በአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ መድረስ በእግርኳስ ትልቅ ስኬት ነው " ያሉት አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላፉንቴ ጨዋታውን አሸንፈን ዋንጫውን መውሰድ እንፈልጋለን ብለዋል።

" ከባድ ጨዋታ ይሆናል ብዬ እጠብቃለሁ ምክንያቱም ሁለቱም ጥሩ ቡድኖች ናቸው ፣ ጥሩ ጊዜ ላይ ነን የፍፃሜ እንደመሆኑ ተመጣጣኝ ጨዋታ እንመለከታለን።" ሉዊስ ዴ ላፉንቴ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
“ ጀርመን ውስጥ የኬንን የዋንጫ ጥማት አስቀጥያለሁ “ ዳኒ ኦልሞ የስፔን ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዳኒ ኦልሞ ሀሪ ኬን ዋንጫ እንዳያሸንፍ የማድረግ ስራውን ገና አለማጠናቀቁን በሰጠው አስተያየት ተናግሯል። " ጀርመን ውስጥ የዋንጫ እርግማኑን ሊያጠፋ የተቃረበውን ሀሪ ኬን አስቁሜው አስቀጥዬለታሁ " የሚለው ዳኒ ኦሎም " አሁንም ስራዬ ገና አልተጠናቀቀም " ሲል ተናግሯል። ባለፈው አመት…
" የመጀመሪያ ዋንጫዬን ለማሸነፍ ሁሉንም መስዋዕትነት እከፍላለሁ " ኬን

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጨዋች ሀሪ ኬን የመጀመሪያ የቡድን ዋንጫውን ለማሸነፍ ዛሬ ምሽት ሁሉም መስዋዕትነት ለመክፈል መዘጋጀቱን ገልጿል።

" የቡድን ዋንጫ አለማሸነፌ የሚደበቅ ሚስጥር " አይደለም የሚለው ሀሪ ኬን " አመታት በተቆጠሩ ቁጥር ይህንን የመቀየር ጉጉቴ እየጨመረ ነው ዛሬ የመጀመሪያ ዋንጫዬን አሸንፌ ምርጡን ምሽት ለማሳለፍ ሁሉንም ዋጋ እከፍላለሁ " ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#CopaAmerica2024

በአሜሪካ አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የዘንድሮው የ2024 የኮፓ አሜሪካ ውድድር ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ ሌሊት 9:00 በአርጀንቲና እና ኮሎምቢያ መካከል ይደረጋል።

ትላንት በተደረገ የደረጃ ጨዋታ ዩራጓይ ካናዳን በመለያ ምት በማሸነፍ የውድድሩን ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ ማጠናቀቅ ችለዋል።

የኮፓ አሜሪካ ፍፃሜ ጨዋታን ብራዚላዊው የ 44ዓመት ዳኛ ራፋኤል ክላውስ በመሐል ዳኝነት እንደሚመሩት ይፋ ተደርጓል።

በሀርድ ሮክ ስታዲየም ለሚደረገው የፍፃሜ ጨዋታ የቀረቡ የስታዲየም መግቢያ ትኬቶች ሙሉ ተሸጠው መጠናቀቃቸው ተገልጿል።

በኮፓ አሜሪካ ፍፃሜ ጨዋታ እረፍት ሰዓት ኮሎምቢያዊቷ አርቲስት ሻኪራ ስራዎቿን በማቅረብ ውድድሩን እንደምታደምቅ ይጠበቃል።

የውድድሩን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች ደረጃ አርጀንቲናዊው የፊት መስመር አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ በአራት ግቦች እየመራው ይገኛል።

የኮፓ አሜሪካ አሸናፊዎች ስንት ያገኛሉ ?

- የዋንጫው አሸናፊ :- 16 ሚልዮን ዶላር

- የፍፃሜ ተፋላሚ :- 7 ሚልዮን ዶላር

- 3ኛ ደረጃ :- 5 ሚልዮን ዶላር

- 4ኛ ደረጃ :- 4 ሚልዮን ዶላር የሚሸለሙ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ወጣት ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ጠየቀ ! አማራጭ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም በእንቅስቃሴ ላይ የሚገኘው አርሰናል የአያክሱን እንግሊዛዊ ወጣት ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ ለማስፈረም የዝውውር ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል። ባለ ጥሩ ተሰጥኦ ባለቤት መሆኑ የተነገረው የ 18ዓመቱ ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ በአያክስ ያለው ውል በ2025 የሚጠናቀቅ ሲሆን መድፈኞቹን መቀላቀል ይፈልጋል ተብሏል። መድፈኞቹ ከቀናት…
አርሰናል ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ተስማማ !

ግብ ጠባቂ ለማስፈረም በእንቅስቃሴ ላይ የሚገኘው አርሰናል እንግሊዛዊውን ወጣት ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ ለማስፈረም ከአያክስ ጋር ከስምምነት መድረሳቸው ተነግሯል።

ባለ ጥሩ ተሰጥኦ ባለቤት መሆኑ የተነገረው የ 18ዓመቱ ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ በአርሰናል ቤት የአራት አመት ኮንትራት ለመፈረም ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል።

መድፈኞቹ እንግሊዛዊውን ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድን በአንድ ሚልዮን ዩሮ ለማስፈረም መስማማታቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
#CopaAmerica2024 በአሜሪካ አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የዘንድሮው የ2024 የኮፓ አሜሪካ ውድድር ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ ሌሊት 9:00 በአርጀንቲና እና ኮሎምቢያ መካከል ይደረጋል። ትላንት በተደረገ የደረጃ ጨዋታ ዩራጓይ ካናዳን በመለያ ምት በማሸነፍ የውድድሩን ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ ማጠናቀቅ ችለዋል። የኮፓ አሜሪካ ፍፃሜ ጨዋታን ብራዚላዊው የ 44ዓመት ዳኛ ራፋኤል ክላውስ በመሐል ዳኝነት…
የኮፓ አሜሪካ ፍፃሜን የሚመሩት ዳኛ ማን ናቸው ?

የኮፓ አሜሪካ ፍፃሜ ጨዋታን ብራዚላዊው የ 44ዓመት ዳኛ ራፋኤል ክላውስ በመሐል ዳኝነት እንዲመሩት ተመርጠዋል።

ዋና ዳኛው የኮሎምቢያ ብሔራዊ ቡድን ከሁለት አመታት በፊት ለመጨረሻ ጊዜ በአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ሲሸነፍ ጨዋታውን መርተው ነበር።

የኮሎምቢያ ብሔራዊ ቡድን ለመጨረሻ ጊዜ የተሸነፈው ከሁለት አመታት በፊት ከአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ጋር ባደረጉት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ነበር።

የኮሎምቢያ ብሔራዊ ቡድን ያለፉትን ሀያ ሰባት ጨዋታዎች ያልተሸነፉ ሲሆን ሀያ አንዱን ጨዋታዎች በአሸናፊነት መወጣት ችለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🎁 #በፍፃሜው ይገምቱ፣ #ይሸለሙ!

🏆  በዛሬው ምሽት የ2024 አውሮፓ ዋንጫ የፍፃሜ ፍልሚያ ማን አሸንፎ ዋንጫውን ያነሳል?

🇪🇸 ስፔን ወይስ እንግሊዝ 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿

💬 ግምትዎን
#በገፃችን ኮሜንት ላይ ብቻ ያስቀምጡልን!

⚠️ የውድድሩ ህጎች፦
👉🏾 የፍፃሜውን አሸናፊ ሀገር እስከ የግብ መጠኑ #በትክክል ቀድመው የሚገምቱ #3 ተከታታዮቻችን የዋናውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማልያዎች ይሸለማሉ።
👉🏾 የዋናውን ማህበራዊ ገፆች መከተል፣ መወዳጀትና ማጋራት አይዘንጉ።
👉🏾 የተስተካከሉና ተደጋጋሚ መልሶች በፍፁም ተቀባይነት የላቸውም።
👉🏾 አንድ ተሳታፊ ከሁለት ጊዜ በላይ አይሸለምም፡፡

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
TIKVAH-SPORT
ጆሽዋ ዚርክዜ ለዩናይትድ ፊርማውን አኖረ ! ኔዘርላንዳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ የሚያደርገውን ዝውውር  ለማጠናቀቅ ያደረገውን የህክምና ምርመራ ማጠናቀቁ ተገልጿል። ተጨዋቹ አሁን ላይ በማንችስተር ዩናይትድ ቤት ለአንድ ተጨማሪ አመት የማራዘም አማራጭ ያካተተ የአምስት አመት ኮንትራቱን መፈረሙ ተገልጿል። ማንችስተር ዩናይትድ በቀጣይ የተጫዋቹን ዝውውር ይፋ…
ማንችስተር ዩናይትድ በይፋ ተጨዋች አስፈረመ !

ማንችስተር ዩናይትድ ኔዘርላንዳዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ኔዘርላንዳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ በማንችስተር ዩናይትድ ቤት እስከ 2029 የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረም ችሏል።

በአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ የሚመራው ማንችስተር ዩናይትድ ለተጨዋቹ ዝውውር 42.5 ሚልዮን ዩሮ መክፈላቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዕለታዊ ከሳፋሪኮም ወደ ቴሌ የሚያስደውለን የድምፅ ጥቅል በመግዛት በእጥፍ የድምጽ ደቂቃዎች በሽ በሽ እያልን እንደዋወል!
0️⃣7️⃣👉🏼0️⃣9️⃣ ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.
mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን
https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
2024/10/01 13:26:19
Back to Top
HTML Embed Code: