Telegram Web Link
" ከእኛ የሚበልጥ ቡድን የለም " ሉዊስ ዴ ላፉንቴ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላፉንቴ በአሁን ሰዓት ከስፔን የሚበልጥ ቡድን እንደሌለ ከምሽቱ የጣልያን ጨዋታ በኋላ በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።

በድሉ መደሰታቸውን የገለፁት አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላፉንቴ " በተጨዋቾቼ በጣም ኮርቻለሁ በመላ ሀገሪቱ ደስታን አንግሰዋል ፣ ያለኝ በጣም ጥሩው ነገር ተጨዋቾቹን በደንብ አውቃቸዋለሁ " ብለዋል።

አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላፉንቴ ቀጥለውም በአሁን ሰዓት ከስፔን ብሔራዊ ቡድን የበለጠ ቡድን አለ ብለው እንደማያምኑ ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኒኮ ዊሊያምስ ወደ ባርሴሎና ?

የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ስፔናዊውን የአትሌቲክ ቢልባኦ የፊት መስመር ተጨዋች ኒኮ ዊሊያምስ የማስፈረም ፍላጎት እንዳላቸው ተገልጿል።

ባርሴሎና በቀጣይ ለማስፈረም የሚፈልገውን አቅም ያለው ወጣት እና ወደፊት ታላቅ ተጨዋች መሆን የሚችል የክንፍ አጥቂ መስፈርት ኒኮ ዊሊያምስ እንደሚያሟላ ተነግሯል።

ይሁን እንጂ ባርሴሎና ኒኮ ዊልያምስን ለማስፈረም በቀጣይ ያለባቸውን የፋይናንስ ችግር ማስተካከል እንዲሁም ተጨዋች መሸጥ ሊጠበቅባቸው እንደሚችል ተገልጿል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል እና ቼልሲ በበኩላቸው ኒኮ ዊሊያምስን ለማስፈረም በዝርዝር ውስጥ የያዙ ክለቦች መሆናቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሮቤርቶ ባጅዮ ጥቃት እንደደረሰበት ተገለጸ !

የቀድሞ ጣልያናዊ ታሪካዊ ተጨዋች ሮቤርቶ ባጅዮ ትላንት ምሽት በመኖሪያ ቤቱ የጣልያን እና ስፔንን ጨዋታ በመመልከት ላይ እያለ ጥቃት እንደደረሰበት ተገልጿል።

የቀድሞ ተጨዋቹ በመኖሪያ ቤቱ ከቤተሰቡ ጋር ጨዋታውን በመመልከት ላይ እያለ አምስት የሚደርሱ መሳሪያ የታጠቁ ዘራፊዎች ሰብረው ሲገቡ ለመከላከል ሲሞክር ጥቃት እንዳደረሱበት ተነግሯል።

ሮቤርቶ ባጅዮ ዘራፊዎቹን ለማስቆም ሲሞክር ጭንቅላቱ ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ተከትሎ ወደ ሆስፒታል ማምራቱ ተገልጿል።

ዘራፊዎቹ መላው ቤተሰቡን በአንድ ክፍል ውስጥ በመቆለፍ ጌጣጌጥ እና ገንዘብ ይዘው መሄዳቸው ተጠቁሟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
Samsung Galaxy S22 Ultra
256 GB - 67,000 ETB
512 GB - 78,000 ETB

Samsung Galaxy S23 Ultra
256 GB - 92,000 ETB
512 GB - 109,000 ETB

Samsung Galaxy S24 Ultra
256 GB - 109,000 ETB
512 GB - 124,000 ETB

Exchange Available
🏍️ Free Delivery

Contact us :
0925927457 @eBRO4
@Heyonlinemarket
Forwarded from WANAW SPORT
📢 ፈጣን እና አስተማማኝ አቅርቦት ከ #ዋናው!

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 09011382830910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ይዘዙን።

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
ዌልስ ከአሰልጣኟ ጋር ተለያየች !

ለአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ሳያልፍ የቀረው የዌልስ ብሔራዊ ቡድን ከዋና አሰልጣኙ ሮበርት ፔጅ ጋር መለያየታቸው ይፋ ተደርጓል።

አሰልጣኝ ሮበርት ፔጅ የዌልስ ብሔራዊ ቡድንን በአሰልጣኝነት እየመሩ ከሰልሳ አራት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታሩ አለም ዋንጫ ውድድር ማሳተፋቸው ይታወሳል።

የዌልስ ብሔራዊ ቡድን በአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ ጥሎ ማለፍ በፖላንድ በመለያ ምት ተሸንፎ ለውድድሩ ማለፍ ሳይችል መቅረቱ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ምባፔ ለኔዘርላንድ ጨዋታ ላይደርስ ይችላል ! ትላንት ምሽት በአፍንጫው ላይ ከባድ ጉዳት ያጋጠመው ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ለአርቡ የኔዘርላንድ ጨዋታ ላይደርስ እንደሚችል ተገልጿል። ፈረንሳይ ከፖላንድ ጋር በምታደርገው የአውሮፓ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ኪሊያን ምባፔ የመድረስ እድል እንደሚኖረው ተዘግቧል። ኪሊያን ምባፔ በጉዳቱ ምክንያት በቀሪ የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር…
" ምባፔ በኔዘርላንድ ጨዋታ ሊሳተፍ ይችላል " ዴሻምፕ

የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ  ኪሊያን ምባፔ በዛሬ ምሽቱ የኔዘርላንድ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ ይሳተፋል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ልምምዱን በጥሩ ሁኔታ እንደሰራ የገለፁት አሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ " በምሽቱ የኔዘርላንድ ጨዋታ ይሳተፋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን " ሲሉ ተናግረዋል።

ከቀናት በፊት አፍንጫው ላይ ጉዳት ያጋጠመው ኪሊያን ምባፔ ወደ ሜዳ የሚመለስ ከሆነ ተመሳሳይ ቀለም ያለው የፊት ጭምብል አድርጎ እንደሚጫወት ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

10:00 ስሎቫኪያ ከ ዩክሬን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
17 '

ስሎቫኪያ 1 - 0 ዩክሬን

ሽራንዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#እረፍት

ስሎቫኪያ 1 - 0 ዩክሬን

ሽራንዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባሕር ዳር ከተማ ድል አድርገዋል

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሀያ ስምንተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባሕር ዳር ከተማ ከአዳማ ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ2 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

የጣና ሞገዶቹን የማሸነፊያ ግቦች የአብስራ ተስፋዬ ፣ ወንድወሰን በለጠ እና ፍቅሩ አለማየሁ በራሱ ግብ ላይ አስቆጥረዋል።

የአዳማ ከተማን የመሪነት ግቦች ዮሴፍ ታረቀኝ እና ኤሊያስ ለገሰ ማስቆጠር ችለዋል።

የሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ምን ይመስላል ? 

3️⃣ ባሕር ዳር ከተማ :- 49 ነጥብ

5️⃣ አዳማ ከተማ :- 44 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?

- ሀዋሳ ከተማ ከ ባሕር ዳር ከተማ

- አዳማ ከተማ ከ መቻል

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
54 ' ስሎቫኪያ 1 - 1 ዩክሬን

ሽራንዝ ሻፓሬንኮ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
80 ' ስሎቫኪያ 1 - 2 ዩክሬን

ሽራንዝ        ሻፓሬንኮ
ያሬምቹክ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
🔥 የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታዎች በድምቀት ቀጥለዋል!

ዛሬ ምሽት፡

⚽️ Netherlands vs France ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት | 10፡00 PM በSS Football 225 ጎጆ ፓኬጅ በSS Euro2024 222 በሜዳ  ፓኬጅ

🤔ዋንጫው የማን ነው? የእርሶን አስተያየት ያጋሩን                        

በጀርመን የሚደረጉትን ደማቅ ጨዋታዎች በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች በወር ከ350 ብር ከጎጆ ፓኬጅ ጀምሮ ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#Euro2024onDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
ዩክሬን ወሳኝ ድል አሳክታለች !

በአውሮፓ ዋንጫ ውድድር የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ የዩክሬን ብሔራዊ ቡድን ከስሎቫኪያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

ለዩክሬን ብሔራዊ ቡድን የማሸነፊያ ግቦችን ሻፓሬንኮ እና ያሬምቹክ ሲያስቆጥሩ ለስሎቫኪያ ብሔራዊ ቡድን ኢቫን ሽራንዝ ከመረብ አሳርፏል።

ሮማን ያሬምቹክ በሶስት ግቦች በአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ላይ ብዙ ግብ ማስቆጠር የቻለ ቀዳሚው ዩክሬናዊ ተጨዋች መሆን ችሏል።

ኢቫን ሽራንዝ በሁለት ተከታታይ የአውሮፓ ዋንጫ ውድድሮች ላይ ግብ ማስቆጠር የቻለ የመጀመሪያው ስሎቫኪያዊ ተጨዋች መሆን ችሏል።

ወቅታዊ የምድብ ደረጃ ምን ይመስላል ?

1️⃣ ሮማንያ :- 3 ነጥብ

2️⃣ ዩክሬን :- 3 ነጥብ

3️⃣ ስሎቫኪያ :- 3 ነጥብ

4️⃣ ቤልጂየም :- ምንም ነጥብ

በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ እሮብ ስሎቫኪያ ከሮማንያ እንዲሁም ዩክሬን ከቤልጅየም ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

1:00 ፖላንድ ከ ኦስትሪያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

የፖላንድ ብሔራዊ ቡድን በኔዘርላንድ ከተሸነፈበት የመጀመሪያ ጨዋታ የአራት ተጨዋቾች ለውጥ በማድረግ ወደ ሜዳ የሚገቡ ይሆናል።

የኦስትሪያ ብሔራዊ ቡድን በበኩሉ በፈረንሳይ ከደረሰበት ሽንፈት የሶስት ተጨዋቾች ለውጥ አድርገው ወደ ሜዳ ይገባሉ።

የኦስትሪያ አሰልጣኝ ራልፍ ራኚክ በራሱ ላይ ግብ ያስቆጠረውን ዎበር ጨምሮ በፈረንሳይ ጨዋታ በመሐል ተከላካይነት የተጠቀሟቸውን ሁለት ተከላካዮች ተጠባባቂ አድርገዋል።

የፊት መስመር ተጨዋቹ ማርኮ አርናቶቪች በበኩሉ ሚሼል ግሪጎራሽን በመተካት በቋሚ አሰላለፍ ተካቷል።

የፖላንድ ወሳኝ ተጨዋች ሮበርት ሌዋንዶውስኪ በምሽቱ ጨዋታም በጉዳቱ ምክንያት ለብሔራዊ ቡድኑ በቋሚ አሰላለፍ ገብቶ ግልጋሎት አይሰጥም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
10 ' ፖላንድ 0 - 1 ኦስትሪያ

ትራውነር

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/09/29 14:16:25
Back to Top
HTML Embed Code: