Telegram Web Link
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from HEY Online Market
iPhone 16 Promax
iPhone 16 Pro
iPhone 16 Plus
iPhone 16
Available Now!

0925927457 @eBRO4
0953964175 @heymobile
@heyonlinemarket
የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች !

10:00 ፋሲል ከነማ ከ ስሑል ሽረ

1:00 ባሕር ዳር ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና

3:45 ኒውካስል ከ ዌምበልደን ( ሊግ ካፕ )

4:00 አርሰናል ከ ፒኤስጂ

4:00 ስሎቫን ብራቲስላቫ ከ ማንችስተር ሲቲ

4:00 ባርሴሎና ከ ያንግ ቦይስ

4:00 ባየር ሌቨርኩሰን ከ ኤሲ ሚላን

4:00 ዶርትመንድ ከ ሴልቲክ

4:00 ኢንተር ሚላን ከ ሬድ ስታር ቤልግሬድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ አርሰናል ከአውሮፓ ምርጥ ቡድኖች አንዱ ነው “ ኤንሪኬ

የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የዛሬ ምሽት ተጋጣሚያቸው አርሰናል ከአውሮፓ ምርጥ ቡድኖች አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

“ አርሰናል በአሁኑ ሰዓት ከአውሮፓ ምርጥ ቡድኖች አንዱ ነው ኳስ ሲቆጣጠሩም ከኳስ ውጪም በትልቅ ደረጃ መሆናቸውን መመልከት ይቻላል “ ሲሉ አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ተናግረዋል።

አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪክ አክለውም አርሰናል በትልቅ ደረጃ የሚጠቀስ ጠንካራ የተከላካይ ክፍል እንዳለው ገልፀዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የዋልያዎቹ ተጋጣሚ ስብስቧን አሳውቃለች !

የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታዋን ከኢትዮጵያ ጋር የምታደርገው ጊኒ ስብስቧን ይፋ አድርጋለች።

በቅርቡ ብሔራዊ ቡድኑን የተረከቡት አሰልጣኝ ሚሼል ዱሱዬር የሴልታ ቪጎውን አማካይ ኢላክስ ሞሪባ ለቡድኑ ጥሪ ሳያቀርቡለት ቀርተዋል።

የኢትዮጵያ እና ጊኒ ጨዋታዎች :-

ጥቅምት 2/2017 ዓ.ም እና

ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም በአይቮሪኮስት አቢጃን ስታድ ደ ኢቢምፔ ስታዲየም ይደረጋል።

ሙሉ የቡድን ስብስቡ ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አንድሬስ ኢኔስታ ጫማውን ሊሰቅል ነው !

ስፔናዊው የቀድሞ የባርሴሎና ታሪካዊ የመሐል ሜዳ ተጨዋች አንድሬስ ኢኔስታ በ 40ዓመቱ ጫማውን መስቀሉን በይፋ ሊያሳውቅ መሆኑ ተገልጿል።

አንድሬስ ኢኔስታ በእግርኳስ ህይወቱ 1016 ጨዋታዎችን ሲያደርግ 107 ጎሎች አስቆጥሮ 191 ለግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።

አንድሬስ ኢኔስታ በእግርኳስ ህይወቱ ምን አሳካ ?

9️⃣ የላሊጋ ዋንጫ

7️⃣ ሱፐር ኮፓ

6️⃣ ኮፓ ዴላሬ

4️⃣ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ

3️⃣ የአለም ክለቦች ዋንጫ ፣ ዩኤፋ ሱፐር ካፕ

2️⃣ አውሮፓ ዋንጫ

1️⃣ የአለም ዋንጫ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የላሊጋ የወሩ ምርጥ አሰልጣኝ ታውቋል !

የስፔን ላሊጋ የ 2024/25 የውድድር ዘመን የወርሀ መስከረም የወሩ ምርጥ አሰልጣኝ ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት የአትሌቲክ ቢልባኦው ዋና አሰልጣኝ ኤርኔስቶ ቫልቬርዴ የስፔን ላሊጋ የወርሀ መስከረም የወሩ ምርጥ አሰልጣኝ በመሆን መመረጥ ችለዋል።

አሰልጣኝ ኤርኔስቶ ቫልቬርዴ አትሌቲክ ቢልባኦን እየመሩ በወሩ ካደረጓቸው አራት ጨዋታዎች ሶስቱን ሲያሸንፉ በአንዱ አቻ ተለያይተዋል።

አትሌቲክ ቢልባኦ በሊጉ በአስራ አራት ነጥቦች አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባርሴሎና ተጨዋቹ ወደ ሜዳ ይመለሳል !

የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፍራንክ ዲ ዮንግ ከረጅም ጊዜ ጉዳት በማገገም ወደ ሜዳ እንደሚመለስ ተገልጿል።

ባርሴሎና ዛሬ ከያንግ ቦይስ ጋር ለሚያደርገው የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ፍራንክ ዲ ዮንግን በስብስቡ ማካተቱ ይፋ ተደርጓል።

ኔዘርላንዳዊው አማካይ ፍራንክ ዲ ዮንግ ለመጨረሻ ጊዜ ለባርሴሎና የተጫወተው ከአምስት ወራት በፊት እንደነበር ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሊቨርፑል ተጨዋቾቹ ልምምድ አልሰሩም !

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል የፊት መስመር ተጨዋች ዲያጎ ጆታ በዛሬው ዕለት የቡድን ልምምድ አለመስራቱ ተገልጿል።

በተጨማሪም ጣልያናዊው የፊት መስመር ተጨዋች ፌዴሪኮ ኬሳ በቡድኑ ልምምድ ላይ ሳይሳተፍ መቅረቱ ተዘግቧል።

በሌላ በኩል ህመም አጋጥሞት የነበረው ዳርዊን ኑኔዝ እና አንዲ ሮበርትሰን በክለቡ መደበኛ ልምምድ ላይ መሳተፋቸው ተገልጿል።

ሊቨርፑል በነገው እለት በአንፊልድ ስታዲየም ከቦሎኛ ጋር የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሁለተኛ ጨዋታውን ያደርጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ከ 100 ሚልዮን ዩሮ በላይ ይገባኛል “ ኦሲሜን

ናይጄሪያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ቪክቶር ኦሲሜን ለእሱ እየተጠየቀ የሚገኘው የዝውውር ሒሳብ የሚገባው መሆኑን ገልጿል።

በራሱ ብቃት እና ችሎታ እንደሚተማመን የሚገልጸው ቪክቶር ኦሲሜን “ ከ 100 ሚልዮን ዩሮ በላይ የዝውውር ሒሳብ ቢወጣብኝ ይገባኛል “ ብሏል።

በዘመናዊ እግርኳስ ውስጥ እንደ እሱ አይነት የአጨዋወት ባህሪ እና ስኬት ያላቸው ተጨዋቾች ጥቂት ብቻ መሆናቸውን ኦሲሜን አክሎ ገልጿል።

ስሙ በታላላቅ ክለቦች ጋር ሲያያዝ የቆየው ቪክቶር ኦሲሜን በተጠናቀቀው የዝውውር መስኮት መጨረሻ ቀን በውሰት ጋላታሳራይን መቀላቀሉ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ቴንሀግ ሁልጊዜም ሊባረር ሲል ያሸንፋል “ ኤቭራ

የቀድሞ የቀያይ ሴጣኖቹ ተጨዋች ፓትሪስ ኤቭራ አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ የመሰናበት አደጋ አላቸው የሚባሉ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ልምድ እንዳላቸው ተናግሯል።

አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ በቀጣይ ከፖርቶ እና አስቶን ቪላ ጋር የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች የወደፊት ቆይታቸውን ሊወስኑ እንደሚችሉ እየተነገረ ይገኛል።

“ ሁልጊዜም ኤሪክ ቴንሀግ እነዚህን ጨዋታዎች ካላሸነፈ ይሰናበታል ብለን ስናስብ ሁሉንም ያሸንፋቸዋል በዚህ ፍራቻ የለኝም “ ሲል ኤቭራ ተናግሯል።

ፓትሪስ ኤቭራ አያይዞም አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ የክለቡ ባለቤቶች " INEOS " ድጋፍ አላቸው ብሎ እንደሚያስብ ገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሀሪ ኬን ልምምድ ሰርቷል !

እንግሊዛዊው የባየር ሙኒክ የፊት መስመር ተጨዋች ሀሪ ኬን በቡድኑ መደበኛ ልምምድ መሳተፉ ተገልጿል።

ሀሪ ኬን ከቀናት በፊት ባየር ሙኒክ ከባየር ሌቨርኩሰን ጋር አቻ በተለያዩበት የሊግ ጨዋታ መጠነኛ ጉዳት አስተናግዶ ነበር።

ይህንንም ተከትሎ ባየር ሙኒክ ነገ ምሽት ቪላ ፓርክ ላይ ከአስቶን ቪላ ጋር በሚያደርገው የሻምፒየንስ ላግ ጨዋታ እንደሚደርስ ይጠበቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ሊቨርፑል ተጨዋቾቹ ልምምድ አልሰሩም ! የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል የፊት መስመር ተጨዋች ዲያጎ ጆታ በዛሬው ዕለት የቡድን ልምምድ አለመስራቱ ተገልጿል። በተጨማሪም ጣልያናዊው የፊት መስመር ተጨዋች ፌዴሪኮ ኬሳ በቡድኑ ልምምድ ላይ ሳይሳተፍ መቅረቱ ተዘግቧል። በሌላ በኩል ህመም አጋጥሞት የነበረው ዳርዊን ኑኔዝ እና አንዲ ሮበርትሰን በክለቡ መደበኛ ልምምድ ላይ መሳተፋቸው ተገልጿል። ሊቨርፑል…
ሊቨርፑል የተጫዋቹን ግልጋሎት አያገኝም !

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል የፊት መስመር ተጨዋች ፌዴሪኮ ኬሳ ጉዳት እንዳጋጠመው አሰልጣኝ አርኔ ስሎት አረጋግጠዋል።

ተጨዋቹ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ሊቨርፑል ነገ ከቦሎኛ ከሚያደርገው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ውጪ መሆኑ ተገልጿል።

ፌዴሪኮ ኬሳ ሊቨርፑል ቅዳሜ ከክሪስታል ፓላስ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል አሰልጣኙ ጠቁመዋል።

ፖርቹጋላዊው የፊት መስመር ተጨዋች ዲያጎ ጆታ በበኩሉ ለነገው የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EthPL

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የ 2017 የውድድር ዘመን ሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ ከስሑል ሽረ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 0ለ0 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ ስሑል ሽረ :- 5 ነጥብ

3️⃣ ፋሲል ከነማ :- 5 ነጥብ

ቀጣይ መርሐ ግብራቸው ምን ይመስላል ?

እሁድ ⏩️  ድሬዳዋ ከተማ ከ ስሑል ሽረ

ሰኞ ፋሲል ከነማ ከ አዳማ ከተማ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
⚡️ #ከዋናው ይዘዙ፣ በስጦታ ይንበሽበሹ! ⚡️

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ8289 ወይም በስልክ ቁጥሮቻችን በመደወል፤ እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WanawSportBot ይዘዙን።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
የዩናይትድ የወሩ ምርጥ ተጨዋች ማን ይሆናል

በአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ የሚመሩት ማንችስተር ዩናይትዶች የወርሀ መስከረም የወሩ ምርጥ ተጨዋች #ሶስት እጩዎችን ይፋ አድርገዋል።

በዚህም መሰረት :-

ክርስቲያን ኤሪክሰን

አሌሀንድሮ ጋርናቾ

አንድሬ ኦናና የመስከረም ወር የማንችስተር ዩናይትድ ምርጥ ተጨዋች እጩ ሆነው መቅረብ ችለዋል።

የወሩ ምርጥ ተጨዋች ማን ይሆናል

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጣልያናዊው ዳኛ ከስራቸው ታገዱ !

ጣልያናዊው ዳኛ ፋቢዮ ማሬስካ የጣሊያን ሴርያ ጨዋታዎችን ለአንድ ወር እንዳይዳኙ መታገዳቸው ተገልጿል።

ዋና ዳኛው በቅርቡ የኩዌት ፕርሚየር ሊግ ጨዋታ በመሩበት ወቅት ተጨዋች አስፈራርተዋል በሚል ቅሬታ እንደቀረበባቸው ተገልጿል።

ቅሬታ አቅራቢው ተጨዋች ዋና ዳኛው " በቀጣይ ስንገናኝ እገልሀለሁ " ብሎ አስፈራርቶኛል በሚል ቅሬታ ማቅረቡ ተነግሯል።

የ 43ዓመቱ ዳኛ ፋቢዮ ማሬስካ በተጨማሪም ዛሬ ምሽት አራተኛ ዳኛ ሆነው ሊመሩ ከነበረው የፒኤስቪ እና ስፖርቲንግ ሊስበን ጨዋታ በሌላ ዳኛ መተካታቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኪሊያን ምባፔ ከጉዳቱ አገግሟል !

ፈረንሳዊው የሪያል ማድሪድ የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ካጋጠመው ጉዳት ማገገሙን አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ አረጋግጠዋል።

ከተጠበቀው ጊዜ ቀደም ብሎ ከጉዳቱ ያገገመው ኪሊያን ምባፔ ዛሬ ልምምዱን እንደሚሰራ አሰልጣኙ ገልጸዋል።

ሎስ ብላንኮዎቹ ነገ ከሊል ጋር በሚያደርጉት የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ኪሊያን ምባፔ መሰለፉን አይተው እንደሚወስኑ አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ከአርሰናል ጋር ሻምፒየንስ ሊግ ካሸነፍኩ ለእኔ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል “ ካይ ሀቨርትዝ

የመድፈኞቹ የፊት መስመር ተጨዋች ካይ ሀቨርትዝ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ከአርሰናል ጋር የሚያሸንፍ ከሆነ የበለጠ እንደሚያስደስተው ገልጿል።

“ ሻምፒየንስ ሊግ ማሸነፍ በጣም አስደሳች ነው ነገርግን ከአርሰናል ጋር ማሸነፍ ከቻልኩ የበለጠ አስደሳች ይሆናል ለእኔ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል “ ሲል ካይ ሀቨርትዝ ተናግሯል።

ጀርመናዊው የፊት መስመር ተጨዋች ካይ ሀቨርትዝ ከዚህ በፊት ከቼልሲ ጋር የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ማሳካቱ ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የብሩኖ ፈርናንዴዝ ቀይ ካርድ ተሻረ !

ፖርቹጋላዊው የቀያይ ሴጣኖቹ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ብሩኖ ፈርናንዴዝ ከቀናት በፊት በቶተንሀም ጨዋታ የተመለከተው ቀይ ካርድ እንደተሻረለት ተገልጿል።

ማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋቹ የተመለከተውን ቀይ ካርድ በመቃወም ይግባኝ ጠይቀው እንደነበር ተገልጿል።

ይህንንም ተከትሎ ብሩኖ ፈርናንዴዝ በቀጣይ የሊግ መርሐ ግብሮች ለማንችስተር ዩናይትድ ግልጋሎት መስጠት እንደሚችል ይፋ ተደርጓል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/02 00:25:36
Back to Top
HTML Embed Code: