Telegram Web Link
TIKVAH-SPORT
ሮድሪ ከውድድር አመቱ ውጪ ሆነ ! ስፔናዊው የማንችስተር ሲቲ አማካይ ሮድሪ በቅርቡ ባጋጠመው ከባድ ጉዳት ምክንያት ከውድድር አመቱ ውጪ መሆኑን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አረጋግጠዋል። ተጨዋቹ ባለፈው ሳምንት ማንችስተር ሲቲ ከአርሰናል ባደረገው ጨዋታ “ ACL “ ጉዳት እንዳጋጠመው ይታወቃል። የሮድሪ ጉዳት “ በጣም አስከፊ እና ከባድ ነው በዚህ አመት አንመለከተውም “ሲሉ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ…
“ ወደ ፍልሚያ ለመሄድ መዘጋጀት አለብን “ ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በቀጣይ በቡድናቸው ሮድሪን መተካት የሚችል አማራጭ እንዳላቸው ገልፀዋል።

ፔፕ ጋርዲዮላ ከተናገሯቸው ሌሎች አስተያየቶች መካከል :-

- " ኒውካስል ከጠንካራ እና አስቸጋሪ ቡድኖች አንዱ ነው በተለይ በሜዳው ወደ ትልቅ ፍልሚያ ለመሄድ መዘጋጀት አለብን።

- የምናሸንፍ ከሆነ ያለ ሮድሪ መፎካከር እንችላለን ማለት ነው የማናሸንፍ ከሆነ ግን ሮድሪ ስላጎደለን ነው።

- በሮድሪ ቦታ ሪኮ ሌዊስ እና ማቲኦ ኮቫቺች እንጠቀማለን ኢልካይ ጉንዶጋንም መጫወት ይችላል ጆን ስቶንስ እና አካንጂም መጫወት ይችላሉ አማራጭ አለን።

- ለሮድሪ ተተኪ በጥር ማስፈረም የሚያስፈልገን ከሆነ እንነጋገርበታለን ገና ለዛ ብዙ ጊዜ አለን።" ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from WANAW SPORT
📞 8289 📞

ወደ ዋናው የጥሪ ማዕከል በቀላሉ ይደውሉ፣ #ትዕዛዝዎን ያድርሱን!

📞 8289 📞

Instagram | Facebook | TikTok

🏅ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
“ የሮናልዶ መፈረም መልበሻ ቤቱ ላይ ተፅዕኖ ያሳደረ ይመስለኛል “ ሶልሻየር

የቀድሞው የቀያይ ሴጣኖቹ አሰልጣኝ ኦሌ ገነር ሶልሻየር ከአመታት በፊት ሮናልዶን ማስፈረማቸው መልበሻ ቤቱ ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።

“ ምናልባት ሌሎች ተጨዋቾች ሮናልዶ ሲመጣ ያን ያህል እንደማያስፈልጉ ተሰምቷቸው ነበር " ያሉት ሶልሻየር “ ምክንያቱም እሱ ከአለም ምርጥ ኮከቦች አንዱ ነበር “ ብለዋል

“ ሮናልዶ ጥሩ ስራ ሰርቶ ነበር በዛ አመቱ ሀያ አራት ጎል አስቆጥሮ የቡድኑ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኗል ነገርግን ከአስር ሳምንት በኋላ እኔ ስራዬን አጣሁ “ ሲሉ ሶልሻየር ተናግረዋል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ምናልባት በማንችስተር ሲቲ ሀላንድ እያደረገ ከሚገኘው የበለጠ ማድረግ ይችል ነበር የሚል እምነት እንዳላቸው አሰልጣኝ ሶልሻየር ጨምረው ገልጸዋል።

አሰልጣኙ አክለውም “ የክርስቲያኖ ሮናልዶ መፈረም ሙሉ መልበሻ ቤቱ ላይ ተፅዕኖ ያደረገ ይመስለኛል “ ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ፈረሰኞቹ የመጀመሪያ ድላቸውን አሳክተዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የፈረሰኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ፍፁም ጥላሁን እና አማኑኤል ኤርቦ ከመረብ ሲያሳርፉ ለወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ኪሩቤል ወንድሙ አስቆጥሯል።

ቀጣይ መርሐግብር ምን ይመስላል ?

ሰኞ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ መቐለ 70 እንደርታ

ሐሙስ ⏩️ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ከ ሲዳማ ቡና

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አል ነስር ድል አድርጓል !

በሰዑዲ ዓረቢያ ሊግ የአምስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አል ነስር ከአል ዌህዳ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የአል ነስርን የማሸነፊያ ግቦች አንሄሎ ጋብሬል እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ በሰባ ግቦች ለአል ናስር ብዙ ግብ ያስቆጠረ በታሪክ አራተኛው ተጨዋች መሆን ችሏል።

ፖርቹጋላዊው ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ በእግርኳስ ህይወቱ 903 ኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2ኛ. አል ነስር :- 11 ነጥብ
14ኛ. አል ዌህዳ :- 4 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታቸው ምን ይመስላል ?

ቅዳሜ አል ነስር ከ አል ኦሮባህ

ሐሙስ - አል ዌህዳ አል ፋይሀ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/09/27 17:21:17
Back to Top
HTML Embed Code: