Telegram Web Link
“ ራያ ዝግጁ መሆኑን ለማወቅ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገናል “ ሚኬል አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቤን ዋይት እና ጁሪየን ቲምበር ልምምድ መስራታቸውን እና ለጨዋታ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አሰልጣኙ አያይዘውም አዲስ ፈራሚያቸው ሚኬል ሜሪኖ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል ጠቁመዋል።

ግብ ጠባቂው ዴቪድ ራያ በበኩሉ “ በጥሩ ጤንነት ላይ መሆን አለመሆኑን ለማወቅ ተጨማሪ 24 ሰዓት መጠበቅ አለብን “ ሲሉ ሚኬል አርቴታ ተናግረዋል።

በነገው የሌስተር ሲቲ ጨዋታ ዴቪድ ራያ መድረስ አለመድረሱን ነገ አይተው እንደሚወስኑ ሚኬል አርቴታ ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ሮድሪ ከባድ ጉዳት አጋጥሞታል ! ስፔናዊው አማካይ ሮድሪ በሳምንቱ መጨረሻ ከአርሰናል በነበረው ጨዋታ ያጋጠመው ጉዳት የ “ ACL “ ጉዳት መሆኑን ማንችስተር ሲቲ በይፋ አረጋግጧል። ተጨዋቹ በቀኝ ጉልበቱ ላይ ጉዳቱ እንዳጋጠመው የገለፀው ክለቡ ለተሻለ የህክምና ምርመራ ስፔን እንደሚገኝም አስታውቋል። ሮድሪ በቀጣይ ለምን ያህል ጊዜ ከሜዳ እንደሚርቅ ለማወቅ የህክምና ምርመራዎች መቀጠላቸውን ክለቡ…
ሮድሪ ከውድድር አመቱ ውጪ ሆነ !

ስፔናዊው የማንችስተር ሲቲ አማካይ ሮድሪ በቅርቡ ባጋጠመው ከባድ ጉዳት ምክንያት ከውድድር አመቱ ውጪ መሆኑን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አረጋግጠዋል።

ተጨዋቹ ባለፈው ሳምንት ማንችስተር ሲቲ ከአርሰናል ባደረገው ጨዋታ “ ACL “ ጉዳት እንዳጋጠመው ይታወቃል።

የሮድሪ ጉዳት “ በጣም አስከፊ እና ከባድ ነው በዚህ አመት አንመለከተውም “ሲሉ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በይፋ አሳውቀዋል።

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አያይዘውም ኬቨን ዴብሮይን ከነገው የኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታ ውጪ መሆኑን ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ለማሸነፍ ልክ ነው ያልኩትን አድርጌያለሁ “ አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው ነገ ከሌስተር ሲቲ ጋር ከሚያደርገው ጨዋታ በፊት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ምን አሉ ?

- “ በማንችስተር ሲቲ ጨዋታ ለመፎካከር እና ጨዋታውን ለማሸነፍ ልክ ነው ብዬ ያሰብኩትን አድርጌያለሁ።

- ስለ ቡድኑ ብዙ ጥሩ አስተያየቶችን ስምቻለሁ በመጨረሻው ጨዋታ ባደረግነው ነገር ትችቶች ካሉ ከዚህ ቡድን ስለሚጠበቀው ነገር ይነግረናል።

- ቶሚያሱ ዛሬ በነበረን ልምምድ በከፊል ተሳትፏል በጥሩ ሁኔታ እየተሻሻለ ይገኛል።

- በነበረን አጨዋወት ምክንያት ዩቲዩብ ላይ መተቸት አልፈልግም ግንቦት ላይ የሆነ ነገር ስለማሸንፍ እዛ መሆን እፈልጋለሁ።“ ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ሮድሪ ከውድድር አመቱ ውጪ ሆነ ! ስፔናዊው የማንችስተር ሲቲ አማካይ ሮድሪ በቅርቡ ባጋጠመው ከባድ ጉዳት ምክንያት ከውድድር አመቱ ውጪ መሆኑን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አረጋግጠዋል። ተጨዋቹ ባለፈው ሳምንት ማንችስተር ሲቲ ከአርሰናል ባደረገው ጨዋታ “ ACL “ ጉዳት እንዳጋጠመው ይታወቃል። የሮድሪ ጉዳት “ በጣም አስከፊ እና ከባድ ነው በዚህ አመት አንመለከተውም “ሲሉ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ…
“ ወደ ፍልሚያ ለመሄድ መዘጋጀት አለብን “ ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በቀጣይ በቡድናቸው ሮድሪን መተካት የሚችል አማራጭ እንዳላቸው ገልፀዋል።

ፔፕ ጋርዲዮላ ከተናገሯቸው ሌሎች አስተያየቶች መካከል :-

- " ኒውካስል ከጠንካራ እና አስቸጋሪ ቡድኖች አንዱ ነው በተለይ በሜዳው ወደ ትልቅ ፍልሚያ ለመሄድ መዘጋጀት አለብን።

- የምናሸንፍ ከሆነ ያለ ሮድሪ መፎካከር እንችላለን ማለት ነው የማናሸንፍ ከሆነ ግን ሮድሪ ስላጎደለን ነው።

- በሮድሪ ቦታ ሪኮ ሌዊስ እና ማቲኦ ኮቫቺች እንጠቀማለን ኢልካይ ጉንዶጋንም መጫወት ይችላል ጆን ስቶንስ እና አካንጂም መጫወት ይችላሉ አማራጭ አለን።

- ለሮድሪ ተተኪ በጥር ማስፈረም የሚያስፈልገን ከሆነ እንነጋገርበታለን ገና ለዛ ብዙ ጊዜ አለን።" ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from WANAW SPORT
📞 8289 📞

ወደ ዋናው የጥሪ ማዕከል በቀላሉ ይደውሉ፣ #ትዕዛዝዎን ያድርሱን!

📞 8289 📞

Instagram | Facebook | TikTok

🏅ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
“ የሮናልዶ መፈረም መልበሻ ቤቱ ላይ ተፅዕኖ ያሳደረ ይመስለኛል “ ሶልሻየር

የቀድሞው የቀያይ ሴጣኖቹ አሰልጣኝ ኦሌ ገነር ሶልሻየር ከአመታት በፊት ሮናልዶን ማስፈረማቸው መልበሻ ቤቱ ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።

“ ምናልባት ሌሎች ተጨዋቾች ሮናልዶ ሲመጣ ያን ያህል እንደማያስፈልጉ ተሰምቷቸው ነበር " ያሉት ሶልሻየር “ ምክንያቱም እሱ ከአለም ምርጥ ኮከቦች አንዱ ነበር “ ብለዋል

“ ሮናልዶ ጥሩ ስራ ሰርቶ ነበር በዛ አመቱ ሀያ አራት ጎል አስቆጥሮ የቡድኑ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኗል ነገርግን ከአስር ሳምንት በኋላ እኔ ስራዬን አጣሁ “ ሲሉ ሶልሻየር ተናግረዋል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ምናልባት በማንችስተር ሲቲ ሀላንድ እያደረገ ከሚገኘው የበለጠ ማድረግ ይችል ነበር የሚል እምነት እንዳላቸው አሰልጣኝ ሶልሻየር ጨምረው ገልጸዋል።

አሰልጣኙ አክለውም “ የክርስቲያኖ ሮናልዶ መፈረም ሙሉ መልበሻ ቤቱ ላይ ተፅዕኖ ያደረገ ይመስለኛል “ ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ፈረሰኞቹ የመጀመሪያ ድላቸውን አሳክተዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የፈረሰኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ፍፁም ጥላሁን እና አማኑኤል ኤርቦ ከመረብ ሲያሳርፉ ለወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ኪሩቤል ወንድሙ አስቆጥሯል።

ቀጣይ መርሐግብር ምን ይመስላል ?

ሰኞ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ መቐለ 70 እንደርታ

ሐሙስ ⏩️ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ከ ሲዳማ ቡና

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አል ነስር ድል አድርጓል !

በሰዑዲ ዓረቢያ ሊግ የአምስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አል ነስር ከአል ዌህዳ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የአል ነስርን የማሸነፊያ ግቦች አንሄሎ ጋብሬል እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ በሰባ ግቦች ለአል ናስር ብዙ ግብ ያስቆጠረ በታሪክ አራተኛው የውጪ ሀገር ተጨዋች መሆን ችሏል።

ፖርቹጋላዊው ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ በእግርኳስ ህይወቱ 903 ኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ኛ. አል ነስር :- 11 ነጥብ
1️⃣4️⃣ኛ. አል ዌህዳ :- 4 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታቸው ምን ይመስላል ?

ቅዳሜ አል ነስር ከ አል ኦሮባህ

ሐሙስ አል ዌህዳ አል ፋይሀ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አዳማ ከተማ ድል አድርጓል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አዳማ ከተማ ከባሕር ዳር ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የአዳማ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ስንታየሁ መንግሥቱ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ባሕር ዳር ከተማ የመጀመሪያ ሽንፈቱን ሲያስተናግድ አዳማ ከተማ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል።

ቀጣይ መርሐግብር ምን ይመስላል ?

ማክሰኞ ወልቂጤ ከተማ ከ አዳማ ከተማ

ማክሰኞ ⏩️  ባሕር ዳር ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#SaudiLeague 🇸🇦

በሰዑዲ ዓረቢያ ሊግ የአምስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አል ኢትሐድ አል ካሊጅን 4ለ1 ሲያሸንፍ አል አህሊ በአል ቃዲሲያ 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።

የአል ኢትሀድን የማሸነፊያ ግቦች ካሪም ቤንዜማ ፣ ጋምዲ ፣ ስቴቨን ቤርግዊን እና ሁሴም ኡራ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

የአል ቃዲሲያን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ፔር ኤምሪክ ኦባምያንግ ማስቆጠር ችሏል።

ፈረንሳዊው የፊት መስመር አጥቂ ካሪም ቤንዜማ በውድድር ዘመኑ ስድስተኛ የሊግ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።

በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ስንተኛ ናቸው ?

1️⃣ኛ አል ኢትሀድ :- 12 ነጥብ
4️⃣ኛ አል ቃዲሲያ :- 10 ነጥብ
7️⃣ኛ አል አህሊ :- 7 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታቸው ምን ይመስላል ?

ሐሙስ ⏩️ አል አክዱድ ከ አል ኢትሀድ

ቅዳሜ ⏩️ አል አህሊ ከ አል ሂላል

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኤሲ ሚላን ድል አድርጓል !

በጣልያን ሴርያ የስድስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኤሲ ሚላን ከሊቼ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የኤሲ ሚላንን የማሸነፊያ ግቦች አልቫሮ ሞራታ ፣ ቲኦ ሄርናንዴዝ እና ክርስቲያን ፑልሲች ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

የሊግ ደረጃቸው ?

2️⃣ኛ ኤሲ ሚላን :- 11 ነጥብ
1️⃣7️⃣ኛ ሊቼ :- 5 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታቸው ምን ይመስላል ?

እሁድ ፊዮሬንቲና ከ ኤሲ ሚላን

ቅዳሜ ዩዲኔዜ ከ ሊቼ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Forwarded from HEY Online Market
iPhone 16 Promax
iPhone 16 Pro
iPhone 16 Plus
iPhone 16
Available Now!

0925927457 @eBRO4
0953964175 @heymobile
@heyonlinemarket
የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች !

8:30 ኒውካስል ከ ማንችስተር ሲቲ

10:00 መቻል ከ ሲዳማ ቡና

10:00 ዩድኒዜ ከ ኢንተር ሚላን

11:00 አርሰናል ከ ሌስተር ሲቲ

11:00 ቼልሲ ከ ብራይተን

1:00 ድሬዳዋ ከተማ ከ ወላይታ ድቻ

1:00 ጂኖኣ ከ ጁቬንቱስ

1:30 ባየር ሙኒክ ከ ባየር ሌቨርኩሰን

1:30 ዎልቭስ ከ ሊቨርፑል

4:00 ኦሳሱና ከ ባርሴሎና

🔴 የ የዛሬው የይግምቱ ሽልማታችን የማንችስተር ሲቲ ፣ አርሰናል ፣ ቼልሲ ፣ ሊቨርፑል እና ባርሴሎና ጨዋታዎች ናቸው።

🔴 የዛሬ አምስት ሽልማቶቻችን 7:00 ፣ 9:30 ፣ 9:40 ፣ 12:00 ፣ 3:00 ሰዓት ላይ ወደ ቤተሰቦቻችን የሚደርሱ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቼልሲ ተጨዋቾቹ ባይጫወቱም ስታዲየም እንዲገኙ ጠይቋል !

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ የክለቡ ተጨዋቾች ቡድኑ በሜዳው የሚያደርጋቸውን ጨዋታዎች እንዲታደም ማሳሰባቸው ተገልጿል።

አሰልጣኙ ተጨዋቾቹ በጨዋታው የቡድን ስብስብ ውስጥ ባይካተቱም እንኳን በሜዳው ሲጫወት ግዴታ ስታዲየም በመገኘት እንዲያበረታቱ መንገራቸው ተዘግቧል።

ሰማያዊዎቹ በሳምንቱ አጋማሽ ባሮውን በሊግ ካፕ ሲያሸንፉ ኮል ፓልመርን ጨምሮ ለጨዋታው ያልተመረጡ ተጨዋቾች ስታምፎርድ ብሪጅ መገኘታቸው ይታወሳል።

አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ውሳኔያቸው የቡድኑን መንፈስ ለማሳደግ አስፈላጊ ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
“ ስለ ሲቲ ሁሉም መረጃ አለኝ “ ሚኬል አርቴታ የአርሰናሉ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የማንችስተር ሲቲ ተጨዋቾች ስለ ቡድናቸው የአጨዋወት ዘይቤ የሰጡት አስተያየት አግባብ አይደለም ስለ እነሱም አውቃለሁ ብለዋል። “ እኔ ማንችስተር ሲቲ ውስጥ አራት አመታት አሳልፌያለሁ ከእነሱ በፊት እዛ ነበርኩ ስለዚህ እመኑኝ ስለ እነሱ ሁሉም መረጃ አለኝ “ ሲሉ ሚኬል አርቴታ ገልፀዋል። “ ኢትሀድ ላይ ባደረግነው…
“ አርቴታ ለተናገረው ነገር ማብራሪያ መስጠት አለበት “ ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ  አሰልጣኝ ሜኬል አርቴታ ከቀናት በፊት የተናገሩትን “ ግልጽ ማድረግ አለባቸው “ ሲሉ አሳስብዋል።

ሚኬል አርቴታ ከቀናት በፊት በሲቲ ጨዋታ በተከተሉት አጨዋወት ምክንያት ለቀረበባቸው ትችት ምላሽ ሲሰጡ “ ሲቲ በነበርኩበት አራት አመት ስለ እነሱ ሁሉንም መረጃ አውቃለሁ “ ብለው ነበር።

“ በቀጣይ አርቴታ ነገሩን የበለጠ ግልጽ ማድረግ አለበት “ ያሉት ፔፕ ጋርዲዮላ “ እዚህ በነበረበት ሰዓት ሁሉንም ነገር አውቃለሁ ሲል ምን ለማለት እንደፈለገ በግልጽ ያብራራ ብለዋል።

“ ምክንያቱም ንግግሩ በሂደት ላይ ካለው 115 ክስ ጋር ሊገናኝ ይችላል ፤ ምናልባት ስለዛ የሚያውቀው ሊኖር ይችላል አላውቅም “ ሲሉ ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ከሲቲ ያለንን ርቀት ለማጥበብ እንሞክራለን “ አርኔ ስሎት

የሊቨርፑሉ ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት በቀጣይ ቡድናቸው የሚሰጠው ግምት ከፍም ይበል ይነስ ክለቡ ባለፈው አመት ካሳካው ነጥብ ለማሻሻል እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

“ ሊቨርፑል ዋንጫ የማንሳት እድሉ ከፍ ወይም ዝቅ ተደርጎ ይነገር አይመለከተኝም ባለፉት ሁለት አመታት ሲቲ ከእኛ በላይ 31 ነጥቦች ሰብስቧል ያንን ክፍተት ለማጥበብ እንሞክራለን “ ሲሉ አርኔ ስሎት ተናግረዋል።

የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ውስጥ ቀላል ጨዋታ እንደሌለ ብዙ አሰልጣኞች ሲናገሩ ሰምቼ ነበር እውነት መሆኑን አረጋግጫለሁ ሲሉ አርኔ ስሎት ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ አርሰናል ቤቴ ነው “ ካይ ሀቨርትዝ

ጀርመናዊው የመድፈኞቹ የፊት መስመር ተጨዋች ካይ ሀቨርትዝ በአርሰናል ቤት ደስተኛ መሆኑን ገልጿል።

“ እዚህ ምቾት ተሰምቶኛል አርሰናል ቤቴ ነው በየቀኑ እዚህ መሆኔን እወደዋለሁ “ ሲል ካይ ሀቨርትዝ በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

ከተቀናቃኝ ቡድን በመሄዱ እና ትልቅ ክፍያ በማግኘቱ በእሱ ላይ ጥርጣሬ ቢቀርብ እንደማይገርመው የገለፀው ካይ ሀቨርትዝ " ነገርግን እኔ አቅሜን አውቀዋለሁ በራሱ አምናለሁ “ ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/01 07:39:01
Back to Top
HTML Embed Code: