Telegram Web Link
ቶተንሀም ድል አድርጓል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሀም ከካራባህ ጋር ያደረገውን የዩሮፓ ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታ 3ለ0 በሆነ ውጤ ማሸነፍ ችሏል።

የቶተንሀምን የማሸነፊያ ግቦች ብሬናን ጆንሰን ፣ ፓፔ ሳር እና ዶምኒክ ሶላንኬ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ቶተንሀም በጨዋታው ገና በስምንተኛው ደቂቃ ተከላካያቸው ራዱ ድራጉሲን በቀይ ካርድ መውጣቱን ተከትሎ በአስር ተጨዋቾች ጨዋታውን ለመጨረስ ተገደዋል።

በሌላ ጨዋታ ሮማ ከስፔኑ ክለብ አትሌቲክ ቢልባኦ ጋር ያደረገውን የዩሮፓ ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቋል።

የሌሎች የዩሮፓ ሊግ ጨዋታዎች ውጤት ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
iPhone 16 Promax
iPhone 16 Pro
iPhone 16 Plus
iPhone 16
Available Now!

0925927457 @eBRO4
0953964175 @heymobile
@heyonlinemarket
⚽️አጓጊው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስድስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች!

👉 ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ለመከታተል ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!

👉 የዲኤስቲቪን ዲኮደር በ1,199 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!

መልካም የመስቀል በዓል!
ጁቬንቱስ ግብ ያልተቆጠረበት ክለብ ሆኗል !

የሴርያው ክለብ ጁቬንቱስ ከአምስቱ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ባደረጋቸው የሊግ መርሐ ግብሮች ምንም ግብ ያላስተናገደ ብቸኛው ክለብ መሆኑ ተገልጿል።

ጁቬንቱስ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ባደረጋቸው አምስት የጣልያን ሴርያ ጨዋታዎች ምንም ግብ ሳይቆጠርበት መውጣት ችሏል።

ጁቬንቱስ ሶስቱን የሴርያ ጨዋታዎች ምንም ግብ ሳያስቆጥር በአቻ ውጤት ሲያጠናቅቅ ሁለቱን በማሸነፍ በዘጠኝ ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ከጠበቅኩት በላይ ነው ያገኘሁት “ ሚኬል አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድኑን ወጣት አማካይ ኢታን ንዋኔሪ ከጠበቁት በላይ ሆኖ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

አርሰናል ቦልተንን ባሸነፈበት ጨዋታ ግብ ማስቆጠር የቻለው ኢታን ንዋኔሪ “ የዋናው ቡድን አካል ነው በቀጣይ የጨዋታ ጊዜ ያገኛል “ ሲሉ ሚኬል አርቴታ ተናግረዋል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አክለውም የ 17ዓመቱ እንግሊዛዊ አማካይ ኢታን ንዋኔሪን ከጠበቁት በላይ ሆኖ እንዳገኙት ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EthPL 🇪🇹

በ 2017 የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ስሑል ሽረ ከሀዋሳ ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የስሑል ሽረን ግብ ፋሲል አስማማው ከመረብ ማሳረፍ ሲችል መሐመድ ሱሌይማን በመጨረሻ ደቂቃ በራሱ ላይ ያስቆጠረው ግብ ሀዋሳ ከተማን አቻ አድርጓል።

ከአመታት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የተመለሱት ስሑል ሽረዎች ከመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች አራት ነጥቦች በመሰብሰብ በግብ ክፍያ በልጠው የሊጉ መሪ መሆን ችለዋል።

ቀጣይ መርሐግብር ምን ይመስላል ?

ማክሰኞ ፋሲል ከነማ ከ ስሁል ሽረ

እሮብ ⏩️ ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኒውካስል የተጫዋቹን ግልጋሎት ላያገኝ ይችላል !

ኒውካስል ዩናይትድ ነገ ከማንችስተር ሲቲ ጋር በሚያደርገው የሊግ ጨዋታ የአሌክሳንደር አይሳክን ግልጋሎት ላያገኝ እንደሚችል አሰልጣኝ ኤዲ ሀው ገልጸዋል።

“ አይሳክ አሁንም ጣቱ ላይ የጉዳት ስሜት አለው ለማንችስተር ሲቲ ጨዋታ መድረሱ አጠራጣሪ ነው ሳምንቱን ሙሉ ልምምድ አልሰራም “ ሲሉ አሰልጣኝ ኤዲ ሀው ተናግረዋል።

ኒውካስል ዩናይትድ ነገ 8:30 በሴንት ጄምስ ፓርክ ስታዲየም ከማንችስተር ሲቲ ጋር ተጠባቂ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ካላፊዮሪን ሴርያ ውስጥ ማቆየት አለመቻላችን ያሳዝናል “ የጁቬንቱስ ሀላፊ

የጣልያኑ ክለብ ጁቬንቱስ ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ጊንቶሊ አርሰናልን የተቀላቀለው ሪካርዶ ካላፊዮሪ ሴርያ ውስጥ አለመቆየቱ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል።

“ ካላፊዮሪን ሴርያ ውስጥ ማቆየት አለመቻላችን በጣም ያሳዝናል “ ሲሉ የገለፁት ስፖርቲንግ ዳይሬክተሩ “  የእሱ መልቀቅ ለእኛ ለምንፈልገው ክለቦች ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ለሊጉ መጥፎ ነው “ ብለዋል።

መድፈኞቹ ሪካርዶ ካላፊዮሪን 38 ሚልዮን ፓውንድ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ከቦሎኛ ማስፈረማቸው አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሊቨርፑል ግብ ጠባቂው ወደ ሜዳ ይመለሳል !

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር ልምምድ መስራቱን አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ገልጸዋል።

“ አሊሰን ልምምድ ሰርቷል ለጨዋታ ብቁ ነው ብለን እናስባለን እሱን በድጋሜ በማግኘታችን ደስተኞች ነን “ ሲሉ አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ተናግረዋል።

ብራዚላዊው ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር በጉዳት ምክንያት ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ለሊቨርፑል ግልጋሎት እንዳልሰጠ ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባርሴሎና ከዩኤፋ ቅጣት ተጥሎባቸዋል !

የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ከሞናኮ በነበረ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ደጋፊዎቹ የዘረኝነት ባህሪ አሳይተዋል በሚል ከአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ቅጣት እንደተጣለባቸው ተገልጿል።

በዚህም መሰረት ባርሴሎና በቀጣይ ከሜዳው ውጪ ለሚያደርገው አንድ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ትኬቶች እንዳይሸጥ እና 10,000 ዩሮ ቅጣት እንደተጣለበት ተነግሯል።

ይህንንም ተከትሎ ባርሴሎና በቀጣይ ከሜዳው ውጪ ከሬድ ስታር ቤልግሬድ ጋር የሚያደርገውን የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ያለ ተጓዥ ደጋፊ ለማድረግ ይገደዳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ኒውካስል የተጫዋቹን ውል ማራዘም ይፈልጋል ! ኒውካስል ዩናይትድ የእንግሊዛዊውን የፊት መስመር ተጨዋች አንቶኒ ጎርደን ኮንትራት ማራዘም እንደሚፈልጉ ተገልጿል። በአሰልጣኝ ኤዲ ሀው የሚመራው ኒውካስል ዩናይትድ አንቶኒ ጎርደን ከእረፍት ሲመለስ ኮንትራቱን ለማራዘም ንግግር ለመጀመር ማሰባቸው ተነግሯል። ኒውካስል ዩናይትድ ተጨዋቹ በመጀመሪያ አመቱ በክለቡ ላሳየው ጥሩ ብቃት መሸለም እንደሚፈልጉ ተዘግቧል።…
ኒውካስል የተጫዋቹን ውል ለማራዘም ተስማማ !

ኒውካስል ዩናይትድ የእንግሊዛዊውን የፊት መስመር ተጨዋች አንቶኒ ጎርደን ኮንትራት ለማራዘም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።

በአሰልጣኝ ኤዲ ሀው የሚመራው ኒውካስል ዩናይትድ የአንቶኒ ጎርደንን ኮንትራት እስከ 2029 ለማራዘም መስማማቱ ተነግሯል።

እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጨዋች አንቶኒ ጎርደን በአዲሱ ውል መሰረት የኒውካስል ዩናይትድ ከፍተኛ ተከፋይ እንደሚሆን ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ የገጠምናቸው ቡድኖች ከሊጉ ግርጌ የነበሩ ናቸው “ አርኔ ስሎት

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ቡድናቸው እስካሁን የገጠማቸው ክለቦች አቋሙን በደንብ የፈተሹ አለመሆናቸውን ገልጸዋል።

“ የገጠምናቸው ቡድኖች በሊጉ ደረጃ ከወገብ በታች ያሉ ነበሩ “ ያሉት አሰልጣኝ አርኔ ስሎት አሁንም ገና ልናረጋግጠው የሚገባን ብዙ ነገር አለ ብለዋል።

አሰልጣኝ አርኔ ስሎት አያይዘውም “ ይህንን የቡድን ስብስብ ከየርገን ክሎፕ መረከብ ትልቅ ክብር ነው “ ሲሉ ተናግረዋል።

“ ጥሩ የውድድር አመት ጅማሬ ነው ነገርግን ፍፁም አይደለም፣ አጨዋወታችን ለአመታት በሊቨርፑል የነበረ ነው ጥሩውን ውጤት ማስቀጠል አለብን።“ አርኔ ስሎት

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አትሌቲኮ ማድሪድ የአቀንቃኟን ዝግጅት ሰረዘ !

አትሌቲኮ ማድሪድ እሁድ በሚደረገው ተጠባቂው የማድሪድ ደርቢ ጨዋታ እንድታቀነቅን ጋብዟት የነበረችውን አቀንቃኝ ዝግጅት መሰረዙ ተገልጿል።

ሜክሲኳዊቷ አቀንቃኝ ዳና ፓኦላ በእሁዱ የማድሪድ ደርቢ ጨዋታ በእረፍት ሰዓት ዝግጅቷን እንደምታቀርብ ተገልጾ ነበር።

አትሌቲኮ ማድሪድ የአቀንቃኟን ዝግጅት የሰረዘው ከጨዋታው አስቀድሞ የሪያል ማድሪድ ደጋፊ መሆኗን ስታናገር በመደመጧ መሆኑ ተነግሯል።

አቀንቃኟ ጨዋታውን ሪያል ማድሪድ 2ለ1 ያሸንፋል ስትልም ግምቷን አስቀምጣለች።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ፕርሚየር ሊግ መሄድ አልፈልግም “ ቦንፌስ

ናይጄሪያዊው የባየር ሌቨርኩሰን የፊት መስመር አጥቂ ቪክቶር ቦኒፌስ የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ምርጫው እንዳልሆነ ተናግሯል።

በባየር ሌቨርኩሰን ቤት ጥሩ ጊዜ በማሳለፍ ላይ የሚገኘው ቪክቶር ቦኒፌስ አንድ ቀን ወደ ፕርሚየር ሊግ ማምራት ይፈልግ እንደሆን ሲጠየቅ “ በፍጹም “ ሲል መልሷል።

ከልጅነቱ ፕርሚየር ሊግ መጫወት ህልሙ እንዳልነበረ የሚገልጸው ተጨዋቹ “ ፕርሚየር ሊግን አልወድም የስፔን እና ጀርመንን እግርኳስ እመርጣለሁ “ ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቼልሲ ተጨዋቹ ወደ ሜዳ ይመለሳል !

ቤልጂየማዊው የቼልሲ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሮሚዮ ላቪያ ካጋጠመው ጉዳት በማገገም ወደ ሜዳ እንደሚመለስ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ገልጸዋል።

ሮሚዮ ላቪያ በቡድናቸው ስብስብ እንደሚካተት የገለፁት አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ መሰለፉን በቀሪ ልምምድ አይተነው እንወስናለን ብለዋል።

እንግሊዛዊው የመስመር ተጨዋች ሬስ ጄምስ በበኩሉ አሁንም ከስብስቡ ውጪ መሆኑን አሰልጣኙ አረጋግጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ራያ ዝግጁ መሆኑን ለማወቅ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገናል “ ሚኬል አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቤን ዋይት እና ጁሪየን ቲምበር ልምምድ መስራታቸውን እና ለጨዋታ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አሰልጣኙ አያይዘውም አዲስ ፈራሚያቸው ሚኬል ሜሪኖ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ሜዳ ሊመለስ እንደሚችል ጠቁመዋል።

ግብ ጠባቂው ዴቪድ ራያ በበኩሉ “ በጥሩ ጤንነት ላይ መሆን አለመሆኑን ለማወቅ ተጨማሪ 24 ሰዓት መጠበቅ አለብን “ ሲሉ ሚኬል አርቴታ ተናግረዋል።

በነገው የሌስተር ሲቲ ጨዋታ ዴቪድ ራያ መድረስ አለመድረሱን ነገ አይተው እንደሚወስኑ ሚኬል አርቴታ ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ሮድሪ ከባድ ጉዳት አጋጥሞታል ! ስፔናዊው አማካይ ሮድሪ በሳምንቱ መጨረሻ ከአርሰናል በነበረው ጨዋታ ያጋጠመው ጉዳት የ “ ACL “ ጉዳት መሆኑን ማንችስተር ሲቲ በይፋ አረጋግጧል። ተጨዋቹ በቀኝ ጉልበቱ ላይ ጉዳቱ እንዳጋጠመው የገለፀው ክለቡ ለተሻለ የህክምና ምርመራ ስፔን እንደሚገኝም አስታውቋል። ሮድሪ በቀጣይ ለምን ያህል ጊዜ ከሜዳ እንደሚርቅ ለማወቅ የህክምና ምርመራዎች መቀጠላቸውን ክለቡ…
ሮድሪ ከውድድር አመቱ ውጪ ሆነ !

ስፔናዊው የማንችስተር ሲቲ አማካይ ሮድሪ በቅርቡ ባጋጠመው ከባድ ጉዳት ምክንያት ከውድድር አመቱ ውጪ መሆኑን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አረጋግጠዋል።

ተጨዋቹ ባለፈው ሳምንት ማንችስተር ሲቲ ከአርሰናል ባደረገው ጨዋታ “ ACL “ ጉዳት እንዳጋጠመው ይታወቃል።

የሮድሪ ጉዳት “ በጣም አስከፊ እና ከባድ ነው በዚህ አመት አንመለከተውም “ሲሉ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በይፋ አሳውቀዋል።

አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አያይዘውም ኬቨን ዴብሮይን ከነገው የኒውካስል ዩናይትድ ጨዋታ ውጪ መሆኑን ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ለማሸነፍ ልክ ነው ያልኩትን አድርጌያለሁ “ አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው ነገ ከሌስተር ሲቲ ጋር ከሚያደርገው ጨዋታ በፊት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ምን አሉ ?

- “ በማንችስተር ሲቲ ጨዋታ ለመፎካከር እና ጨዋታውን ለማሸነፍ ልክ ነው ብዬ ያሰብኩትን አድርጌያለሁ።

- ስለ ቡድኑ ብዙ ጥሩ አስተያየቶችን ስምቻለሁ በመጨረሻው ጨዋታ ባደረግነው ነገር ትችቶች ካሉ ከዚህ ቡድን ስለሚጠበቀው ነገር ይነግረናል።

- ቶሚያሱ ዛሬ በነበረን ልምምድ በከፊል ተሳትፏል በጥሩ ሁኔታ እየተሻሻለ ይገኛል።

- በነበረን አጨዋወት ምክንያት ዩቲዩብ ላይ መተቸት አልፈልግም ግንቦት ላይ የሆነ ነገር ስለማሸንፍ እዛ መሆን እፈልጋለሁ።“ ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/09/27 15:22:40
Back to Top
HTML Embed Code: