Telegram Web Link
ዌስትሀም ካንቴን ለማስፈረም ንግግር ላይ ነው !

የእንግሊዙ ክለብ ዌስትሀም ዩናይትድ የአል ኢትሀዱን የመሀል ሜዳ ተጫዋች ንጎሎ ካንቴን ለማስፈረም በንግግር ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

ዌስትሀም ዩናይትድ ለ 33ዓመቱ የመሀል ሜዳ ተጫዋች ንጎሎ ካንቴ 20 ሚሊየን ፓወንድ የዝውውር ሒሳብ እንዳቀረቡም ታውቋል።

ፈረንሳዊው አማካኝ በ2023 ከቼልሲ በመልቀቅ ወደ ሳውዲ አረቢያ ከተቀላቀለ በኃላ ወደ እንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የመመለሱ ነገር የተቃረበ መሆኑ እየተዘገበ ነው።

የለንደኑ ክለብ ዌስትሀም ዩናይትድ ፈረንሳዊውን የመሀል ሜዳ ተጫዋች ንጎሎ ካንቴ የካልቪን ፊሊፕስ ተተኪ ለማድረግ እንዳሰቡ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አንቾሎቲ ምባፔን በቡድናቸው እንዴት ይጠቀማሉ ?

ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ በነፃ ዝውውር ያስፈረሙት ሎስ ብላንኮዎቹ በቀጣይ በቡድናቸው ካሉ ኮከቦች ጋር ይጣመራል።

ኪሊያን ምባፔ በቡድኑ ከቤሊንግሀም ፣ ቪንሰስ እና ሮድሪጎ ጋር እንዴት ይጣመራል የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ቢሆንም አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ የራሳቸው እቅድ እንዳላቸው ተገልጿል።

ጣልያናዊው አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ በሚቀጥለው አመት አጥቅተው ለመጫወት በሚመርጡበት ወቅት ምባፔን በዘጠኝ ቁጥር ቦታ በማሰለፍ 4-3-3 የጨዋታ አሰላለፍ እንደሚጠቀሙ ተነግሯል።

በተጨማሪም ተከላክለው ለመጫወት ሲመርጡ ሮድሪጎን ወደ ኋላ በመመለስ የ4-4-2 የጨዋታ አሰላለፍ ለመጠቀም ማሰባቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
Photo
" ጥያቄዬ ካልተመለሰ ለውይይት አልቀመጥም ጥሪውን አልተቀበልኩም " ኃይሌ

" ቢመጣ ጥሩ ነው ይመጣል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ " ዶ/ር አሸብር

ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት ለውይይት ያቀረበለትን ጥሪ እንደማይቀበል በሰጠው አስተያየት አረጋግጧል።

ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ከሸገር ኤፍ ኤም ጋር ባደረገው ቆይታ ኮሚቴው በዝግ ያደረገው ምርጫ ካልተሰረዘና ወደ ነበረበት ካልተመለሰ ለውይይት አልቀመጥም በማለት ተናግሯል።

" የጠየቅኩት ሁሉም በነበረበት እንዲመለስ ነው " ያለው ኃይሌ " ጥያቄዬን አሁን ቢያስተካክሉትና ሁሉም በነበረበት ቢመለስ ደስ ይለኛል ይህ ካልሆነና ምን ያመጣሉ በሚል ከቀጠሉ ነገሩ በማንፈልገው አቅጣጫ ሊሄድ ይችላል " ብሏል።

ሻለቃ ኃይሌ አያይዞም " ኦሎምፒክ ኮሚቴው ሁሉንም በነበረበት የሚመልስ ከሆነ ስለወደፊቱ ምርጫ አደራረግ እና ቀጣይ ስራዎች ለመወያየት ዝግጁ ነኝ በደስታ እቀበላለሁ " በማለት ገልጿል።

" የኢትዮጵያ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር በዚህ ጉዳይ ለምን አቅም እንዳጣ አይገባኝም ?" ሲል የጠየቀው ኃይሌ " በጣም አዝናለሁ አቅም ማጣት አልነበረበትም ወይስ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከስፖርት ሚንስቴሩ በላይ ሆኖ ነው " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው ከስፖርት ዞን ጋር በነበራቸው ቆይታ " ኃይሌ አልገኝም ብሎ ምላሽ ሰጥቶናል " ብለው በጉዳዩ ላይ ማረጋገጫ ሲሰጡ በግላቸው ውሳኔው እንዳላስደሰታቸውም ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ ቀጥለውም " ቢመጣ ጥሩ ነው ይመጣል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ተስፋ አልቆረጥኩም ከውይይት የዘለለ ነገር የለም በመወያየት ብቻ ነው መፍታት የሚቻለው " ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ የሚገኘው የአርሰናል ታዳጊ ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ከ 18ዓመት በታች ቡድን የፊት መስመር ተጨዋች የሆነው ኦቢ ማርቲን በርካታ ግቦች እያስቆጠረ ድንቅ ጊዜ ማሳለፉን ቀጥሏል። የ 16ዓመቱ ኦቢ ማርቲን ቡድኑ ዛሬ የኖርዊች ሲቲ አቻውን 9ለ0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ #ሰባት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል። ማርቲን ቡድኑ ባለፉት ሰባት የ 18ዓመት በታች ፕርሚየር ሊግ ጨዋታዎች…
ተስፈኛው የአርሰናል ታዳጊ ወደ ዩናይትድ ?

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ታዳጊ የፊት መስመር አጥቂ ቺዶ ኦቢ ማርቲን ወደ ማንችስተር ዩናይትድ ለማምራት ካሪንግተን ተገኝቶ መነጋገሩ ተገልጿል።

በሚያስቆጥራቸው በርካታ ግቦች መነጋገሪያ የነበረው ኦቢ ማርቲን ከአርሰናል የቀረበለትን ውል እስካሁን አለመቀበሉ ተነግሯል።

ታዳጊው በመድፈኞቹ እንዲቆይ በቅርቡ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አግኝተው አነጋግረውት እንደነበር ተዘግቧል።

የ 16ዓመቱ ታዳጊ ኦቢ ማርቲን በአርሰናል ታዳጊ ቡድን ውስጥ በአንድ ጨዋታ ሰባት ግብ እንዲሁም በሰባት ጨዋታዎች ሀያ አራት ግቦች በማስቆጠር አድናቆት ሲቸረው ነበር።

ተጨዋቹ የናይጄሪያ ፣ እንግሊዝ እና ዴንማርክ ዜግነት እንዳለው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ማድሪድ ለተጨዋቹ አቀባበል ያደርጋል !

ሪያል ማድሪዶች ለአዲሱ ብራዚላዊ የፊት መስመር አጥቂያቸው ኢንድሪክ ይፋዊ አቀባበል እንደሚያደርጉ ይፋ አድርገዋል።

ሎስ ብላንኮዎቹ በሚቀጥለው ሳምንት ቅዳሜ በሳንትያጎ በርናቦ ስታዲየም ይፋዊ አቀባበል እንደሚያደርጉ አሳውቀዋል።

በዕለቱ የክለቡ ፕሬዝዳንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ ለሌሎች ተጨዋቾች እንደሚያደርጉት በክለቡ ማዕከል ተገኝተው ኢንድሪክን የስድስት አመት ውል እንደሚያስፈርሙ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የፓሪስ ኦሎምፒክ 7 ቀን ብቻ ቀረው!

ብርቅዬ አትሌቶቻችንን በፓሪሱ ኦሎምፒክስ ለመቀላቀል ጊዜው አሁን ነው! ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ የአትሌቶቻችንን ብቃት እና ወኔ በጎጆ ፓኬጅ በ350 ብር ይከታተሉ! 

እናሸንፈለን ድሉን እናያለን!

የፓሪስ ኦሎምፒክስን በ350 ብር በጎጆ ፓኬጅ ይከታተሉ! ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/dg1

#ParisOlympics #2024Olympics #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Aarhus - Midtjylland
Sirius - Malmo
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
TIKVAH-SPORT
አልቫሮ ሞራታ ኤሲ ሚላንን ለመቀላቀል ተስማማ ! የስፔን ብሔራዊ ቡድን አምበል አልቫሮ ሞራታ አትሌቲኮ ማድሪድን በመልቀቅ የሴርያውን ክለብ ኤሲ ሚላን ለመቀላቀል ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል። ተጨዋቹ በኤሲ ሚላን ቤት የአራት አመታት ኮንትራት ለመፈረም በቃል ደረጃ ከስምምነት መድረሱ ተነግሯል። ኤሲ ሚላን አልቫሮ ሞራታን የውል ማፍረሻውን 13 ሚልዮን ዩሮ ከፍለው እንደሚያስፈርሙት ተዘግቧል። …
አልቫሮ ሞራታ ወደ አዲስ ክለብ አምርቷል !

የጣሊያኑ ክለብ ኤሲ ሚላን የአትሌቲኮ ማድሪዱን የፊት መስመር ተጨዋች አልቫሮ ሞራታን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

ኤሲ ሚላን የተጨዋቹን የውል ማፍረሻ 13 ሚሊየን ዩሮ በመክፈል በአራት አመታት ኮንትራት አስፈርመውታል።

ስፔናዊው አጥቂ አልቫሮ ሞራታ ወደ ኤሲ ሚላን ያደረገው ዝውውር በእግርኳስ ህይወቱ ስምንተኛው ዝውውር መሆኑ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ዴንማርክ አሰልጣኟ ጋር ተለያይታለች !

የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ካስፐር ሁልማንድ ከአራት አመታት በኋላ ከቡድኑ አሰልጣኝነታቸው መልቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።

አሰልጣኝ ካስፐር ሁልማንድ የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድንን በሀላፊነት እየመሩ በአውሮፓ ዋንጫው ጥሎ ማለፍ ድረስ መጓዝ ችለው ነበር።

" አለም ዋንጫ እየደረሰ ስለሆነ ለዚህ ድንቅ ቡድን አዲስ ፊት እንደሚያስፈልገው ተረድቻለሁ " ሲሉ አሰልጣኝ ካስፐር ሁልማንድ ብሔራዊ ቡድኑን ከለቀቁ በኋላ ተናግረዋል።

የዴንማርክ እግርኳስ ማህበር የአሰልጣኝ ካስፐር ሁልማንድ ተተኪ በማድረግ ሞርተን ዊግሆርስትን እስከ መጪው አዲስ አመት በጊዜያዊነት መሾማቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ባርሴሎና እንደ ምባፔ አይነት ተጨዋች ያስፈልገዋል " ኮማን

የቀድሞ የባርሴሎና አሰልጣኝ ሮናልድ ኮማን ከቅርብ አመታት ወዲህ የታየው የባርሴሎና ትልቅ ችግር የክለቡን ታሪካዊ ሰዎች ባለማክበሩ የመጣ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

" የባርሴሎና ችግር የመጣው ሜሲ ፣ ዣቪ እንዲሁም እኔ በመውጣታችን ነው " ያሉት ሮናልድ ኮማን " ለተጫዋቾች ከመቆም ይልቅ የክለቡን ታሪካዊ ተጨዋች እና ሰዎች ማክበር የተሻለ ይመስለኛል " ብለዋል።

አሰልጣኝ ሮናልድ ኮማን ቀጥለውም በአሁን ሰዓት ሪያል ማድሪድ ከባርሴሎና የበላይ መሆኑን ገልፀው " ባርሴሎና እንደ ምባፔ አይነት ተጨዋች ያስፈልገዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ በአሰልጣኝነት ህይወቴ ያሳለፍኩት ከባዱ አመት ነበር “ ቴንሀግ

የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሀግ ያለፈው የውድድር ዘመን በአሰልጣኝነት ህይወታቸው ያሳለፉት ከባዱ አመት እንደነበር ተናግረዋል።

“ ይህ ቀላል ስራ አይደለም በጣም ከባድ ሀላፊነት ነው " ያሉት ኤሪክ ቴን ሀግ “ በአሰልጣኝነት ህይወቴ ያሳለፍኩት በጣም ከባዱ የውድድር ዘመን ነበር “ ሲሉ ገልጸውታል።

" አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከዘጠኝ አመታት ቆይታ በኃላ አቅሜን ጨርሳለሁ ብለው ሊቨርፑልን ለመልቀቅ መወሰናቸውን አከብረዋለሁ " ሲሉ ኤሪክ ቴንሀግ ተናግረዋል።

አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሀግ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር የኤፌ ካፕ ዋንጫን ሲያሳኩ በሊጉ ስምንተኛ ደረጃን ይዘው ማጠናቀቃቸው ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ስሚዝ ሮው በቀጣይ ወዴት ሊያመራ ይችላል ?

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የመሐል ሜዳ ተጨዋች ኤሚል ስሚዝ ሮው በፕርሚየር ሊግ ክለቦች ክሪስታል ፓላስ እና ፉልሀም እየተፈለገ ይገኛል።

ሁለቱ ክለቦች ተጫዋቹን ለማስፈረም ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸው ሲገለፅ ፉልሀም በቅርቡ ያቀረቡት የዝውውር ጥያቄ በአርሰናል ተቀባይነት አለማግኘቱ ይታወሳል።

አሁን ላይ ክሪስታል ፓላስ ኤሚል ስሚዝ ሮውን ለማስፈረም ለአርሰናል የዝውውር ጥያቄ ለማቅረብ መዘጋጀታቸው ተዘግቧል።

የአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታው ቡድን አርሰናል በቀጣይ ቡድኑን ለማጠናከር ጥሩ ጥያቄ ከቀረበ ለመሸጥ ካሰባቸው ተጨዋቾች መካከል ኤሚል ስሚዝ ሮው አንዱ ነው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ሴስክ ፋብሪጋስ ውሉን ሊያራዝም ነው ! የጣልያኑን ክለብ ኮሞ በሀላፊነት እየመራ የሚገኘው ስፔናዊው አሰልጣኝ ሴስክ ፋብሪጋስ በክለቡ የረጅም ጊዜ ኮንትራት ለመፈረም መቃረቡ ተገልጿል። ሴስክ ፋብሪጋስ ቡድኑን እየመራ በዚህ አመት ከሀያ ሁለት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ጣልያን ሴርያ ውድድር ማሳደጉ አይዘነጋም። የቀድሞ የአርሰናል እና ቼልሲ ተጨዋች ሴስክ ፋብሪጋስ በተጨማሪም በክለቡ የአክስዮን…
ሴስክ ፋብሪጋስ በዋና አሰልጣኝነት ተሾሟል !

የጣልያኑን ክለብ ኮሞ በጊዜያዊ አሰልጣኝነት እየመራ ከሀያ ሁለት አመታት በኋላ ወደ ሴርያው ማሳደግ የቻለው ሴስክ ፋብሪጋስ አሁን ላይ የክለቡ ዋና አሰልጣኝ በመሆን ተሾሟል።

ስፔናዊው አሰልጣኝ ሴስክ ፋብሪጋስ ኮሞን ለሚቀጥሉት አራት የውድድር አመታት ለማሰልጠን ፊርማውን ማኖሩ በይፋ ተገልጿል።

የቀድሞ የአርሰናል እና ቼልሲ ተጨዋች ሴስክ ፋብሪጋስ ከፊርማው በኋላ " አመቱን በዋና አሰልጣኝነት መጀመሬ አስደስቶኛል የክለቡ ባለድርሾች ስላመኑኝ አመሰግናለሁ " በማለት ተናግሯል።

ሴስክ ፋብሪጋስ እንዲሁም የቀድሞ ፈረንሳዊ ኮከብ ቴሪ ሄንሪ በኮሞ እግርኳስ ክለብ የአነስተኛ አክስዮን ድርሻ ባለቤት ናቸው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
🤯 400,000 ብር?? በዛ ላይ ደግሞ አስቡት የእናንተ ሙዚቃ በመላው ኢትዮጵያ ሲደመጥ...እናንተ ችሎታው ይኑራችሁ የቀረውን በእኛ ጣሉት! አሁኑኑ የአንድ ደቂቃ ቪዲዮአችንን እንላክ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷
#1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ
@Safaricomet ታግ እናድርግ

እንዝፈን! እንላክ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!

#SafaricomEthiopia #1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
ዩኤፋ ምርመራ መጀመሩን ይፋ አደረገ !

የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር የስፔን ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች ከቀናት በፊት በማንችስተር ሲቲው ተጨዋች ሮድሪ እየተመሩ ያሰሙትን ዝማሬ እየመረመረ እንደሚገኝ ገልጿል።

ዩኤፋ ምርመራውን የከፈተው ስፔን የአውሮፓ ዋንጫ ድሏን ማድሪድ ውስጥ በምታክብርበት ወቅት ተጨዋቾቹ " ጂብላርታር ስፔን ነው " እያሉ እንግሊዞች ላይ ቀልደዋል በሚል መሆኑ ተነግሯል።

በሰዓቱ ሮድሪ በድምፅ ማጉያ ዝማሬውን ሲያሰማ ሞራታ በበኩሉ " የእንግሊዝ ቡድን አጋሮች አሉህ " ብሎ ሲጠይቀው የሚደመጥ ሲሆን ሮድሪ " ግድ የለኝም " ሲል ተደምጧል።

የጂብላርታር እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከቀናት በፊት በጉዳዩ ላይ ቅሬታውን ለአውሮፓ እግርኳስ ማህበር አስገብቶ ነበር።

ዩኤፋ በተለይም ዝማሬውን ያሰማውን ሮድሪ እንዲሁም የቡድኑ አምበል ሞራታን በመመርመር ላይ መሆኑን አስታውቋል።

በስፔን ደቡባዊ ጫፍ የምትገኘው ጂብላርታር ከ18ኛው መቶ ክፍለዘመን ጀምሮ በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ስር የነበረች ሲሆን ስፔኖች እንድትመለስ እንደሚፈልጉ ይነገራል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" በኒውካስል መቆየት እፈልጋለሁ " ኤዲ ሀው

ስማቸው ከእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ጋር እየተያያዘ የሚገኘው የኒውካስል ዩናይትድ ዋና አሰልጣኝ ኤዲ ሀው በክለቡ መቆየት እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።

" በኒውካስል ዩናይትድ መቆየት እፈልጋለሁ " የሚሉት አሰልጣኝ ኤዲ ሀው " ነገርግን ለመቆየት ነገሮች ለእኔም ለክለቡም ትክክለኛ መሆን አለባቸው " ብለዋል።

ስማቸው ከእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ስለመያያዙ የተጠየቁት አሰልጣኝ ኤዲ ሀው " እኔ ክለቡን እና ደጋፊውን እንዲሁም አሁን ያለንበትን ነገር እወደዋለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።

አሰልጣኝ ኤዲ ሀው ኒውካስል ዩናይትድን ከተረከቡ በኃላ ባለፈው የውድድር አመት ክለቡን የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ ማድረጋቸው አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" አንድ ሙከራ ብቻ ነበር የተሞከረብን " አርኔ ስሎት

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ዛሬ በልምምድ ማዕከሉ ከፕሬስተን ጋር በዝግ የወዳጅነት ጨዋታ አድርጎ የነበረ ሲሆን ጨዋታውን 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።

ከጨዋታው በኋላ አስተያየታቸውን የሰጡት አዲሱ የሊቨርፑል አሰልጣኝ አርኔ ስሎት " ውጤቱ የፈለግነው አልነበረም ነገርግን ሁሉም ተጨዋቾች ብቁ ሆነው ቆይተዋል።

ወጣት ተጨዋቾችን ጨምሮ አብዛኞቹ ተጨዋቾች የመጫወቻ ጊዜ አግኝተዋል ይህ በጣም ጥሩ ነው ፣ አንድ የግብ ሙከራ ብቻ አስተናግደናል እሱም ግብ ነበር " ሲሉ ተደምጠዋል።

በወዳጅነት ጨዋታው ሀያ ስድስት የሊቨርፑል ተጨዋቾች ተሳታፊ እንደነበሩ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጊኒ በወዳጅነት ጨዋታ አርጀንቲናን አሸንፋለች !

የጊኒ ከ 23ዓመት በታች ኦሎምፒክ ብሔራዊ ቡድን ከአርጀንቲና አቻው ጋር ያደረገውን የወዳጅነት ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

በአሰልጣኝ ዣቪየር ማሼራኖ የሚመራው የአርጀንቲና ኦሎምፒክ ብሔራዊ ቡድን በጨዋታው ኒኮላስ ኦታሜንዲ ፣ ቲያጎ አልማዳ እና ሩሊን በቋሚነት አሰልፏል።

ጊኒ በፓሪሱ ኦሎምፒክ ውድድር ከፈረንሳይ ፣ ኒውዝላንድ እና አሜሪካ ጋር ስትደለደል አርጀንቲና ከሞሮኮ ፣ ኢራቅ እና ዩክሬን ጋር ተደልድላለች።

አፍሪካ በዘንድሮው የ2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር በወንዶች በጊኒ ፣ ሞሮኮ ፣ ግብፅ እና ማሊ ብሔራዊ ቡድኖች ትወከላለች።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ተስፈኛው የአርሰናል ታዳጊ ወደ ዩናይትድ ? የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ታዳጊ የፊት መስመር አጥቂ ቺዶ ኦቢ ማርቲን ወደ ማንችስተር ዩናይትድ ለማምራት ካሪንግተን ተገኝቶ መነጋገሩ ተገልጿል። በሚያስቆጥራቸው በርካታ ግቦች መነጋገሪያ የነበረው ኦቢ ማርቲን ከአርሰናል የቀረበለትን ውል እስካሁን አለመቀበሉ ተነግሯል። ታዳጊው በመድፈኞቹ እንዲቆይ በቅርቡ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አግኝተው አነጋግረውት…
ዩናይትድ ተጨዋች ለማስፈረም እያነጋገረ ነው !

ማንችስተር ዩናይትድ የአርሰናሉን ታዳጊ የፊት መስመር አጥቂ ቺዶ ኦቢ ማርቲን ለማስፈረም ንግግር ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

የ 16ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ቺዶ ኦቢ ማርቲን አርሰናል በክለቡ እንዲቆይ ያቀረበለትን ጥያቄ አለመቀበሉ እና ክለቡን ለመልቀቅ መወሰኑ ታውቋል።

ተጨዋቹ በዚህ ሳምንት ካሪንግተን ተገኝቶ እንደነበር መዘገቡ የሚታወስ ሲሆን ቀያዮቹ ሴጣኖች በአሁን ሰዓት ተጫዋቹን ለማስፈረም በንግግር ላይ መሆናቸው ተነግሯል።

በተጨማሪም ማንችስተር ሲቲ ወጣቱን የፊት መስመር አጥቂ ቺዶ ኦቢ ማርቲን ለማስፈረም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እጥፍ ድርብ አሸናፊነት!

በቤቲካ ያሸነፉትን ገንዘብ በACCA እስከ 300% ከፍ ያድርጉ!

አሁኑኑ Betika.et ላይ አሸናፊነትን ይጀምሩ!

ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!
2024/10/04 01:31:35
Back to Top
HTML Embed Code: