Telegram Web Link
Forwarded from HEY Online Market
Play More and Spend less!

•PS4 Slim, 34,999 Birr
•PS4 PRO, 41,999 Birr
•Original Controller 6,499 Birr

Contact Us
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Netherlands - England
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
" ዋንጫውን በድጋሜ ለማሸነፍ እንጥራለን " ሜሲ

የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ትላንት ሌሊት ከካናዳ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረገውን የኮፓ አሜሪካ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ 2ለ0 በማሸነፍ ለፍፃሜ አልፈዋል።

በጨዋታው ለአርጀንቲና አንድ ግብ ያስቆጠረው ሊዮኔል ሜሲ ኮፓ አሜሪካ ከባድ ውድድር መሆኑን ከጨዋታው በኋላ በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" ኮፓ አሜሪካ በጣም ከባድ ውድድር ነው ከአስቸጋሪ ሙቀት ጋር ከባድ ነበር ፣ በድጋሜ ለፍፃሜ መድረሳችን የሚያስደስት ነው ቡድኑ እየሰራ ያለው ነገር አስደናቂ ነገርነው ነው።" ሲል ሜሲ ተናግሯል።

ለኮፓ አሜሪካ ፍፃሜ መብቃት ቀላል አለመሆኑ አያይዞ የገለፀው ሊዮኔል ሜሲ " ቡድኑ አራተኛ ፍፃሜው ነው በቀጣይ በድጋሜ ሻምፒዮን ለመሆን ከፍተኛ ጥረት ማድረግ አለብን " ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" አውሮፓ ዋንጫ ለእኔ ጥሩ አልነበረም " ምባፔ

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ለእሱ ጥሩ እንዳልነበረ ከቡድኑ ስንብት በኋላ በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" የአውሮፓ ዋንጫውን ማሸነፍ ፈልጌ ነበር " የሚለው ኪሊያን ምባፔ በእግርኳስ አንድ ጊዜ ጥሩ ትሆናለህ ሌላ ጊዜ ደግሞ ተቃራኒ ይህ አውሮፓ ዋንጫ ለእኔ ጥሩ አልነበረም ሲል ተደምጧል።

በቀጣይ ብዙ ነገሮች እንደሚጠብቁት ያስታወሰው ኪሊያን ምባፔ " አሁን ራሴን የተወሰነ ማዝናናት እና ለአዲሱ ህይወቴ መዘጋጀት አለብኝ " ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የፍፃሜ ተፋላሚያችን ማንም ቢሆን ለውጥ የለውም " ሮድሪ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሮድሪ በአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ጠንካራ ተጋጣሚ እንደሚጠብቃቸው ከምሽቱ ጨዋታ በኋላ በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።

" የፍፃሜ ተፋላሚያችን ቡድን ማንም ይሁን ማን ለውጥ የለውም " ያለው ሮድሪ ነገርግን በፍፃሜው የሚጠብቀን ተጋጣሚ ጠንካራ እንደሚሆን እናውቃለን ብሏል።

በላሚን ያማል እንቅስቃሴ መኩራቱን የገለፀው ሮድሪ በቀጣይ እሱ የሚጠብቀው የወደፊት እግርኳስ ህይወት አስደናቂ ነው በማለት ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባርሴሎና ብዙ የካሳ ክፍያ ያገኛል !

የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በዘንድሮው የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ከዩኤፋ ለለቀቃቸው ተጨዋቾች የሚያገኘው የካሳ ክፍያ ከዚህ በፊት ካገኘው የበለጠ እንደሚሆን ተገልጿል።

የባርሴሎናን አራት ተጨዋቾች የያዘችው ስፔን ለአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ መድረሷን ተከትሎ ክለቡ ከአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ከ3.1 ሚልዮን ዩሮ በላይ እንደሚያገኝ ተነግሯል።

የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ተጨዋቾቹ በአውሮፓ ዋንጫ ውድድር በቆዩበት ቀን ልክ በአንድ ቀን 10,000 ዩሮ ለክለባቸው ካሳ የሚከፍል ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
Photo
" ጥያቄ ጠይቀህ መልስ የማታገኝለት ሀገር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን " አትሌት ጽጌ ገ/ሰላማ

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ጽጌ ገ/ሰላማ በቀጣዩ የፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር አትሌት ምርጫ ላይ ላቀረበችው ቅሬታ ምላሽ አለማግኘቷን በማህበራዊ ትስስር ገጿ ገልፃለች።

አትሌቷ በ 5000 ሜትር 14፡18 የሆነ የአመቱ ፈጣን ሰዓት ማስመዝገቧን ገልፃ ወቅታዊ ብቃቴ ታይቶ ሁለተኛ ፊልዴ ተደርጎ እንድመረጥ ስትል የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴን በደብዳቤ ጠይቃ እንደነበር አሳውቃለች።

አትሌቷ ያቀረበችው ቅሬታ ተቀባይነት አለማግኘቱን በማህበራዊ ትስስር ገጿ ያሳወቀች ሲሆን " ተገቢ ጥያቄ ጠይቀህ መልስ የማታገኝለት ሀገር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፍትህ እፈልጋለሁ " ስትል መልዕክቷን አስፍራለች።

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ትላንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ " ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች የመጨረሻ ዝርዝር ሰኞ ዕለት ለአለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተልኳል።"ሲሉ አረጋግጠዋል።

ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም " ለቀሩ አትሌቶች ልባቸው እንዳይሰበር እንመኛለን ይቅርታም እንጠይቃለን።"ሲሉ ተናግረዋል።

አትሌት ጽጌ ገ/ሰላማ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባሳወቀው የኦሎምፒክ ተሳታፊ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ በ10000 ሜትር መመረጧ ይታወሳል።

የ 2024 የፈረንሳይ ፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ሊጀምር አስራ ስድስት ቀናቶች ቀርተውታል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ግብ ጠባቂ ለማስፈረም አነጋግሯል ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል እንግሊዛዊውን ግብ ጠባቂ ዳንኤል ቤንትሌይ ለማስፈረም ክለቡ ዎልቭስን ማነጋገራቸው ተገልጿል። በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት መድፈኞቹ ተጨዋቹ ለአርሰናል ጥሩ አማራጭ ግብ ጠባቂ ይሆናል የሚል እምነት እንዳላቸው ተነግሯል። ዎልቭስ የ 31ዓመቱን ግብ ጠባቂ ዳንኤል ቤንትሌይ ስለመሸጥ የሚያስበው ጥሩ የሚባል የዝውውር…
አርሰናል ለዎልቭስ ስንት አቅርቦ ነበር ?

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል እንግሊዛዊውን ግብ ጠባቂ ዳንኤል ቤንትሌይ ከዎልቭስ ለማስፈረም የመጀመሪያ የዝውውር ሒሳብ አቅርበው ውድቅ ተደርጎባቸዋል።

መድፈኞቹ ዳንኤል ቤንትሌይን ለማስፈረም አቅርበው ውድቅ የሆነባቸው ሒሳብ 50,000 ፓውንድ እንደነበር ለዎልቭስ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ዘግበዋል።

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት አርሰናሎች የ 30ዓመቱን ግብ ጠባቂ ዳንኤል ቤንትሌይ ለክለቡ ሶስተኛ አማራጭ ግብ ጠባቂ አድርገው ለማስፈረም እየሰሩ ይገኛሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሙለር ራሱን ከብሔራዊ ቡድኑ ሊያገል ነው !

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ቶማስ ሙለር ራሱን ከብሔራዊ ቡድኑ ለማግለል ከውሳኔ መድረሱ ተገልጿል።

የ 34ዓመቱ ተጨዋች ቶማስ ሙለር ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን አንድ መቶ ሰላሳ አንድ ጨዋታዎችን ማድረግ ችሏል።

ቶማስ ሙለር ከጀርመን ብሔራዊ ቡድን ጋር አንድ የአለም ዋንጫን ማሸነፍ ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ኢትዮጵያ የምድብ ተጋጣሚዎቿን አውቃለች ! የ2025 የሞሮኮ አፍሪካ ዋንጫ ውድድር ማጣሪያ ምድብ ድልድል ከደቂቃዎች በፊት በደቡብ አፍሪካ ጁሀንስበርግ በተደረገ የእጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት ይፋ ተደርጓል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ ስምንት - #ታንዛኒያ - #ጊኒ እና - #ኮንጎ ጋር ተደልድሏል። በደርሶ መልስ በሚደረግ ጨዋታ የምድቡን አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ይዘው…
ዋልያዎቹ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ከሜዳ ውጪ ያደርጋሉ !

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የሞሮኮ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከሜዳው ውጪ ከታንዛኒያ አቻው ጋር እንደሚያደርግ ይፋ ሆኗል።

በምድብ ስምንት ከታንዛኒያ ፣ ጊኒ እና ኮንጎ ጋር የተደለደለው ብሔራዊ ቡድኑ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታውን በሜዳው የሚያደርግ ይሆናል።

የኢትዮጵያ መርሐ ግብሮች ምን ይመስላሉ ?

- የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ :- ታንዛኒያ ከ ኢትዮጵያ

- የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ :- ኢትዮጵያ ከ ከ ኮንጎ

- የምድብ ሶስተኛ ጨዋታ :- ጊኒ ከ ኢትዮጵያ

- የምድብ አራተኛ ጨዋታ :- ኢትዮጵያ ከ ጊኒ

- የምድብ አምስተኛ ጨዋታ :- ኢትዮጵያ ከ ታንዛኒያ

- የምድብ ስድስተኛ ጨዋታ :- ኮንጎ ከ ኢትዮጵያ

* የምድብ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ጨዋታዎች ከወራት በኋላ ከነሐሴ 27 እስከ ጳጉሜ 5 / 2016 ዓ.ም ባሉት ቀናት የሚደረጉ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኑኖ ታቫሬዝ በውሰት ወደ ላዝዮ ሊያቀና ነው !

ያለፈውን የውድድር አመት በውሰት በኖቲንግሀም ፎረስት ቤት ያሳለፈው የአርሰናል የግራ መስመር ተከላካይ ኑኖ ታቫሬዝ በውሰት ውል ላዝዮን ሊቀላቀል መሆኑ ተገልጿል።

ላዝዮ ፖርቹጋላዊውን ተጫዋች ኑኖ ታቫሬዝ በውሰት ከአርሰናል ለማስፈረም ያቀረቡት ጥያቄ ከመድፈኞቹ ተቀባይነት ማግኘቱ ተነግሯል።

በውሰት ውሉ ውስጥ 8 ሚልዮን ዩሮ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ በቋሚነት የማስፈረም አማራጭ እንደሚካተት ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
📢 ለቸኮለ ቀላል ዘዴ ከ #ዋናው!

🏃🏾‍♂ #ይምጡ#ትጥቅዎን ይውሰዱ!

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 09011382830910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WanawSportBot ይዘዙን።

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
ኬር ስታርመር የእንግሊዝን ጨዋታ በወረቀት ይከታተላሉ !

አዲሱ የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስቴር ኬር ስታርመር የምሽቱን የእንግሊዝ እና ኔዘርላንድ የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ በወረቀት ፅሁፍ እየቀረበላቸው እንደሚከታተሉ ተገልጿል።

ጠቅላይ ሚንስቴር ኬር ስታርመር በአሁን ሰዓት በ2024 የኔቶ አመታዊ ስብሰባ በመካፈል ላይ ሲሆኑ በስብሰባው ስልክ እና መሰል ኤሌክትሮኒክሶች መታገዳቸው ተነግሯል።

ይህንንም ተከትሎ ጠቅላይ ሚንስቴሩ የጨዋታውን ውጤቶች ሰራተኞቻቸው በወረቀት ፅሁፍ እያመጡ እንዲያስመለክቷቸው ትዕዛዝ መስጠታቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ኪሊያን ምባፔ መቼ አቀባበል ይደረግለታል ? በቅርቡ በይፋ ሪያል ማድሪድን የተቀላቀለው ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ በክለቡ ደማቅ አቀባበል እንደሚደረግለት ተገልጿል። ሎስ ብላንኮዎቹ ለኪሊያን ምባፔ ሐምሌ 9/2016 ዓ.ም ይፋዊ አቀባበል በሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም ማዘጋጀታቸው ተነግሯል። ከአውሮፓ ዋንጫው ፍፃሜ ሁለት ቀናት በኋላ በሚደረገው ይፋዊ አቀባበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ…
ማድሪድ ለኪሊያን ምባፔ አቀባበል ያደርጋል !

ሪያል ማድሪድ በቅርቡ ወደ ቡድናቸው የቀላቀሉትን ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ቀጣይ ሳምንት ደማቅ አቀባበል እንደሚያደርጉለት ይፋ አድርገዋል።

ሎስ ብላንኮዎቹ ለኪሊያን ምባፔ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ ሐምሌ 9/2016 ዓ.ም ይፋዊ አቀባበል በሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም ማዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

ኪሊያን ምባፔ ከይፋዊ ትውውቁ በኋላ በሳንቲያጎ በርናቦ የጋዜጣዊ መግለጫ ክፍል ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

በኪሊያን ምባፔ የአቀባበል ስነስርዓት እስከ 80,000 የክለቡ ደጋፊዎች ሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም ሊገኙ እንደሚችሉ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ማድሪድ ለኪሊያን ምባፔ አቀባበል ያደርጋል ! ሪያል ማድሪድ በቅርቡ ወደ ቡድናቸው የቀላቀሉትን ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ቀጣይ ሳምንት ደማቅ አቀባበል እንደሚያደርጉለት ይፋ አድርገዋል። ሎስ ብላንኮዎቹ ለኪሊያን ምባፔ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ ሐምሌ 9/2016 ዓ.ም ይፋዊ አቀባበል በሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም ማዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። ኪሊያን ምባፔ ከይፋዊ ትውውቁ በኋላ በሳንቲያጎ…
ምባፔ የዘጠኝ ቁጥር ማልያ ይለብሳል !

ሪያል ማድሪዶች ለሚቀጥለው የውድድር ዘመን ለስድስት ተጨዋቾች አዲስ ቁጥር ማልያ አስተዋውቀዋል።

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ የዘጠኝ ቁጥር ማልያ እንደሚለብስ ሲገለፅ ከነገ ጀምሮ በማድሪድ የሽያጭ ሱቅ በገበያ ላይ ይቀርባልም ተብሏል።

በተጨማሪም በሚቀጥለው አመት :-

ካማቪንጋ 6 ቁጥር ፣ ቫልቬርዴ 8 ቁጥር ፣ ቹዋሜኒ 14 ቁጥር ፣ አርዳ ጉለር 15 ቁጥር እና ጄሱስ ቫሌሆ 18 ቁጥር ለብሰው እንደሚጫወቱ ይፋ ሆኗል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አስቶን ቪላ የኩቲንሆን ኮንትራት ሊያቋርጥ ነው ! አስቶን ቪላ የብራዚላዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፊሊፔ ኩቲንሆ ኮንትራት ለማቋረጥ በንግግር ላይ መሆናቸው ተገልጿል። ያለፈውን የውድድር አመት በውሰት በኳታሩ ክለብ አል ዱሀይሊ ያሳለፈው ፊሊፔ ኩቲንሆ በአስቶን ቪላ ቤት እስከ 2026 የሚያቆይ ኮንትራት አለው። የ 32ዓመቱ ተጨዋች ፊሊፔ ኩቲንሆ በቀጣይ ወደ ቀድሞ ክለቡ የብራዚሉ ክለብ ቫስኮ ዳጋማ…
ፊሊፔ ኩቲንሆ የቀድሞ ክለቡን ተቀላቀለ !

ብራዚላዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፊሊፔ ኩቲንሆ ከፕርሚየር ሊጉ ክለብ አስቶን ቪላ በመልቀቅ የቀድሞ ክለቡ የብራዚሉ ቫስኮ ዳጋማን ተቀላቅሏል።

ያለፈውን የውድድር አመት በውሰት በኳታሩ ክለብ አል ዱሀይሊ ያሳለፈው ፊሊፔ ኩቲንሆ የቀድሞ ክለቡን በረጅም ጊዜ የውሰት ውል መቀላቀሉ ተገልጿል።

ተጨዋቹ ከአስቶን ቪላ ጋር ያለውን ውል በማቋረጥ የቀድሞ ክለቡን ለመቀላቀል ንግግር ላይ የነበረ ቢሆንም ከደሞዝ ክፍያ ጋር በተያያዘ ባለመሳካቱ በውሰት መቀላቀሉ ተገልጿል።

የ 32ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ፊሊፔ ኩቲንሆ በአስቶን ቪላ ቤት እስከ 2026 የሚያቆይ ኮንትራት አለው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጁቬንቱስ ተጨዋች አስፈርመዋል !

የጣልያን ሴርያው ክለብ ጁቬንቱስ ፈረንሳዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሄፍረን ቱራም ከኒስ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

የ 23ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሄፍረን ቱራም በጁቬንቱስ እስከ 2029 የሚያቆየውን የአምስት አመት ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል።

ጁቬንቱስ ለተጨዋቹ ዝውውር 20 ሚልዮን ዩሮ ወጪ እንደሚያደርግ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የእንግሊዝ ደጋፊዎች እንዲጠነቀቁ ጥሪ ቀረበላቸው !

ከሰዓታት በኋላ ተጠባቂ የአውሮፓ ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታቸውን የሚያደርጉት እንግሊዝ እና ኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች ፀብ ውስጥ መግባታቸው ተገልጿል።

ጨዋታው በሚደረግበት ዶርትመንድ ከተማ ከ100,000 በላይ የኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች እንደሚገኙ ተነግሯል።

የኔዘርላንድ ደጋፊዎች ከጨዋታው አስቀድሞ ከእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች ፀብ ውስጥ መግባታቸውን እና ትንኮሳ ማድረጋቸው በማህበራዊ ሚዲያዎች ተዘዋውሯል።

በስፍራው የፀጥታ ስራውን በማገዝ ላይ የሚገኙ የዩናይትድ ኪንግደም ፖሊሶች የኔዘርላንድ ደጋፊዎች የእንግሊዝ ደጋፊዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ እየሞከሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

አምስት የእንግሊዝ ደጋፊዎች መጠነኛ ጉዳት እንዳጋጠማቸው ሲገለፅ ሌሎች ደጋፊዎች ያሉበትን ቦታ እንዲያውቁ እና በአካባቢያቸው የጀርመን ፖሊሶች መኖራቸውን እንዲያረጋግጡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ንግድ ባንክ እና ቡናማዎቹ ተጋጣሚያቸውን መቼ ያውቃሉ ?

ሀገራችን ኢትዮጵያን በመወከል በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግ እና ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውድድሮች የሚሳተፉት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ ቡና የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚያቸውን የሚያውቁበት ቀን ታውቋል።

ይህንንም ተከትሎ የውድድሮቹ የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚዎች በነገው ዕለት ግብፅ ካይሮ በሚደረግ የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

በምድብ ድልድሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቋት አንድ እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና በቋት ሁለት ይገኛሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/03 15:32:32
Back to Top
HTML Embed Code: