Telegram Web Link
ጣልያን ከአውሮፓ ዋንጫ ውጪ ሆነች !

በአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ጥሎ ማለፍ የስዊዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን ከጣልያን ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል።

የስዊዘርላንድን የማሸነፊያ ግቦች ራሞ ፍሩለር እና ሩበን ቫርጋስ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ውጤቱን ተከትሎ የወቅቱ የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር ሻምፒዮን ጣልያን ብሔራዊ ቡድን ከውድድሩ ውጪ ሆነዋል።

ስዊዘርላንድ በሩብ ፍፃሜው የእንግሊዝ እና ስሎቫኪያን አሸናፊ ቀጣይ ሳምንት ቅዳሜ የሚገጥሙ ይሆናል።

ያለፉት ሶስት የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር አሸናፊ ሀገራት ስፔን ፣ ፖርቹጋል እና ጣልያን በቀጣዩ ውድድር በጥሎ ማለፉ ተሸንፈው ተሰናብተዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ደጋፊዎችን ይቅርታ እንጠይቃለን " ዶናሩማ

ከአውሮፓ ዋንጫ የተሰናበተው ጣልያን ብሔራዊ ቡድን አምበል ጂያንሉጂ ዶናሩማ ከጨዋታው በኋላ በሰጠው አስተያየት ደጋፊዎችን ይቅርታ ጠይቋል።

" በጨዋታው ጥሩ አልነበርንም የሆነው ነገር ተቀባይነት የሌለው ነው ፣ እውነታውን መቀበል ያስፈልጋል ደጋፊዎቻችንን ይቅርታ መጠየቅ እንፈልጋለን።" ሲል ዶናሩማ ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ተጨዋቾቹን ለማወቅ በቂ ጊዜ አልነበረኝም " ስፓሌቲ

የጣልያን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሉቺያኖ ስፓሌቲ ተጨዋቾቻቸውን ለማወቅ በቂ ጊዜ አለማግኘታቸውን ከአውሮፓ ዋንጫው ከተሰናበቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።

" ተጨዋቾቹን ለማወቅ በቂ ጊዜ አልነበረኝም " ያሉት አሰልጣኝ ሉቺያኖ ስፓሌቲ የበፊት አሰልጣኞችን ብንመለከት ከሀያ በላይ ጨዋታዎች ሞክረው ነበር ተጨማሪ ጨዋታዎች ያግዙኝ ነበር።"ብለዋል።

ጥሩ ቡድን ለመገንባት የተወሰነ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው የጠቆሙት አሰልጣኝ ሉቺያኖ ስፓሌቲ የቡድኑን መሰናበት ሀላፊነቱን እኔ እወስዳለሁ በማለት ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ብራይተን ተጨዋች ሊያስፈርሙ ነው !

ብራይተን ጋምቢያዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ያንኩባ ሚንቴህ በ33 ሚልዮን ፓውንድ ከኒውካስል ዩናይትድ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።

የ 19ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ያንኩባ ሚንቴህ በግል ጥቅማጥቅም ዙሪያ ከብራይተን ጋር እንዲነጋገር ፍቃድ እንደተሰጠው ተገልጿል።

ኒውካስል ዩናይትድ የነጥብ ቅነሳ ቅጣት ሊያጋልጣቸው የሚችለውን የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ህግ ለማስተካከል በቀጣይ ሰዓታት ተጨዋቾችን ለመሸጥ እንደሚገደዱ ተነግሯል።

ይህንንም ተከትሎ ኒውካስል ቀነ ገደቡ ሳይጠናቀቅ ለማስተካከል ከተለያዩ ክለቦች ጋር በርካታ የዝውውር ግብይቶችን ለመፈፀም እና ለማስተካከል በንግግር ላይ መሆናቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጀርመን እና ዴንማርክ ጨዋታ ተቋርጧል !

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ከዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን ጋር እያደረጉ የነበረው የአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ተቋርጧል።

ጨዋታው የተቋረጠበት ምክንያት በጀርመን ዶርትመንድ ባለው አስቸጋሪ የአየር ንብረት ለውጥ መሆኑ ይፋ ተደርጓል።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ተጨዋቾች ወደ መልበሻ ቤት ያመሩ ሲሆን እሰካሁን ጨዋታው ስለመቀጠሉ የተገለፀ ነገር የለም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#እረፍት

ጀርመን  0 - 0 ዴንማርክ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
50 '

ጀርመን  0 - 0 ዴንማርክ

- የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን አስቆጥሮ የነበረው ግብ ከጨዋታ ውጪ በሚል በቫር ተሽሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
53 '

ጀርመን  1 - 0 ዴንማርክ

ሀቨርትዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
70 '

ጀርመን  2 - 0 ዴንማርክ

ሀቨርትዝ
ሙሲያላ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጀርመን ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል !

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ከዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረገውን የአውሮፓ ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን መቀላቀል ችለዋል።

ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን የማሸነፊያ ግቦች ካይ ሀቨርትዝ እና ጀማል ሙሲያላ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ጀማል ሙሲያል በአውሮፓ ዋንጫው ያስቆጠራቸውን ግቦች ሶስት ማድረስ ችሏል።

ጀርመን በሩብ ፍፃሜው የስፔን እና ጆርጂያን አሸናፊ አርብ ምሽት 1:00 ስዓት የምትገጥም ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
Stock Clearance Discount 2

📞 0925927457 @eBRO4
📞 0953964175 @heymobile

•iP 7+, Black, 128GB, 99% 12K
•iP X, Black, 256 GB, 100%,12K ⚠️
•iP XS, White, 64 GB, 100% 19K
•iP XS Max, Gold, 64GB, 83%, 25K
•iP XS Max, Gold, 256GB, 88% 29K
•iP 11, Red, 64GB, 100% 28K ⚠️
•iP 11, Black, 128GB, 85%, 33K
•iP 11, Purple, 128GB, 88% 33K
•11 Pro, Black, 64GB, 100% 39K ⚠️
•11 Pro, White, 64GB, 87% 36K
•11 Pro Max, Black, 64GB, 86%, 46K

•11 Pro Max, Black, 256GB, -% 40⚠️
•iP 12, Red, 128GB, 88%, 42K
•iP 12, White, 128GB, 88% 42K
•iP 12, Green, 128GB, 86% 42K
•12 Pro, Blue, 128GB, 89% 49K
•12 Pro Max, Blue, 512GB, 84% 64K
•iP 13 Min, Pink, 256GB, 92% 34K
•iP 13, Blueback, 128GB, 90% 56K
•iP 13, Black, 128GB, 92% 49K ⚠️

•iP 13, Red, 128GB, 86%, 56K
•iP 13, Black, 128GB, 89%, 58K
•13 Pro, Golden, 256GB, 87% 69K
•13 Pro, Blue, 512GB/88% 69K ⚠️
•13 ProMax, Black, 128 GB, 87% 74K
•13 ProMax, 256GB, 86%, 64K⚠️
•13 ProMax, 256GB, 85%, 74K⚠️
•13 ProMax, Gold, 256GB, 86%, 79K
•13 Pro Max, Gold, 256 GB,88% 79K
•13 Pro Max, Blue, 256GB, 94% 79K
•13 Pro Max, 1TB, 88%, 69K ⚠️
•13 Pro Max, Blu, 256GB/ -% 70K ⚠️

Exchange Available!
Free Delivery 🚚

@heyonlinemarket
https://heymobile.store/catalogue
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
#CopaAmerica2024

የኮፓ አሜሪካ ውድድር የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ሲደረጉ አርጀንቲና ፔሩን በላውታሮ ማርቲኔዝ ሁለት ግቦች 2ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ምድቧን በበላይነት አጠናቃለች።

ካናዳ በበኩሏ የምድቡን የመጨረሻ ጨዋታ በአቻ ውጤት ማጠናቀቋን ተከትሎ ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ ሩብ ፍፃሜውን መቀላቀል ችለዋል።

ፔሩ ከአስራ ዘጠኝ አመታት በኋላ ከምድቧ ማለፍ ሳትችል የቀረች ሲሆን በተጨማሪ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በምድብ ጨዋታ ግብ ሳታስቆጥር አጠናቃለች።

ላውታሮ ማርቲኔዝ በምድብ ጨዋታዎች አራት ግቦችን በማስቆጠር የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃውን እየመራ ይገኛል።

አርጀንቲና ምድብ ሁለትን ሁለተኛ ደረጃ ይዞ የሚያጠናቅቀውን ቡድን በሩብ ፍፃሜው ስትገጥም ካናዳ አንደኛ ደረጃ ይዞ የሚያጠናቅቀውን ቡድን ታገኛለች።

እስካሁን ሩብ ፍፃሜውን እነማን ተቀላቀሉ ?

- አርጀንቲና

- ካናዳ

- ዩራጓይ

- ቬንዙዌላ

- ኮሎምቢያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ቫር እግርኳሳችንን ፍትሀዊ አድርጎታል " ኔግልስማን

የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን በምሽቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ቫር የነበረው ሚና ፍትሀዊ እንደነበር ከጨዋታው በኋላ ገልጸዋል።

" ቫር ስፖርታችንን ፍትሀዊ አድርጎታል " ሲሉ የገለፁት አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን ዴንማርኮች ለምን እንደተናደዱ ይገባኛል ነገርግን ህጉ ነው አንደርሰን ፈልጎ አልነበረም እኛ ላይ ቢሆንም ቅር እሰኝ ነበር ግን መቀበል አለብኝ ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
" ቫር እግርኳሳችንን ፍትሀዊ አድርጎታል " ኔግልስማን የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን በምሽቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ቫር የነበረው ሚና ፍትሀዊ እንደነበር ከጨዋታው በኋላ ገልጸዋል። " ቫር ስፖርታችንን ፍትሀዊ አድርጎታል " ሲሉ የገለፁት አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን ዴንማርኮች ለምን እንደተናደዱ ይገባኛል ነገርግን ህጉ ነው አንደርሰን ፈልጎ አልነበረም እኛ ላይ ቢሆንም ቅር…
" የቫር ውሳኔ ጨዋታውን ቀይሮታል "

የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ካስፐር ሁልማንድ በምሽቱ የጀርመን ጨዋታ በቫር የተወሰነባቸው ውሳኔ እንዳበሳጫቸው ከጨዋታው በኋላ ገልፀዋል።

" ሁለት የቫር ውሳኔዎች ጨዋታችንን ቀይረውብናል " ያሉት አሰልጣኙ " ያስቆጠርነው ግብ አንድ ሴንቲሜትር ከጨዋታ ውጪ ነበር ግቡን ለመሻር ጥቂት ነገር ተመልክተዋል ይህ የጨዋታ ውጪ ህግ አሰልችቶኛል ።"ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አትሌቲኮ ማድሪድ ከተጨዋቾቹ ጋር ተለያየ !

የስፔን ላሊጋው ክለብ አትሌቲኮ ማድሪድ ኮንትራታቸው ከተጠናቀቀ ሶስት ተጨዋቾቹ ጋር መለያየቱን በይፋ አስታውቋል።

ሜምፊስ ዴፓይ ፣ ማርዮ ሄርሞሶ እና ጋብሬል ፖሊስታ ኮንትራታቸው መጠናቀቁን ተከትሎ ክለቡን በነፃ መልቀቃቸው ይፋ ሆኗል።

ብራዚላዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጋብሬል ፓውሊስታ በቀጣይ የቱርኩን ክለብ ቤሺክታሽ ለመቀላቀል ከስምምነት ደርሷል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አዝፕሉኬታ በአትሌቲኮ ማድሪድ ውሉን አራዝሟል !

ባለፈው ክረምት የዝውውር መስኮት ከቼልሲ በአንድ አመት ውል አትሌቲኮ ማድሪድን የተቀላቀለው ስፔናዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሴሳር አዝፕሉኬታ በክለቡ ዉሉን አራዝሟል።

የ 34ዓመቱ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሴሳር አዝፕሉኬታ በአትሌቲኮ ማድሪድ ቤት ለተጨማሪ አንድ የውድድር አመት ለመቆየት ውሉን ማራዘሙ ይፋ ተደርጓል።

ሴሳር አዝፕሉኬታ ባለፈው አመት ለአትሌቲኮ ማድሪድ ሰላሳ አራት ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ መጫወት ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቶተንሀም ተጨዋች ለማስፈረም አነጋግረዋል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሀም እንግሊዛዊውን ወጣት የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች አርቼ ግሬይ ከሊድስ ዩናይትድ ለማስፈረም ንግግር ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

የ 18ዓመቱ ተጨዋች አርቼ ግሬይ ቶተንሀምን መቀላቀል እንደሚፈልግ የተገለፀ ሲሆን በቀጣይ ክለቦቹ ከስምምነት ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሊድስ ዩናይትድ ተጨዋቹን ለማስፈረም ከብሬንትፎርድ የቀረበላቸውን ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እጥፍ ድርብ አሸናፊነት!

በቤቲካ ያሸነፉትን ገንዘብ በACCA እስከ 300% ከፍ ያድርጉ!

አሁኑኑ Betika.et ላይ አሸናፊነትን ይጀምሩ!

ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!
2024/10/01 16:26:18
Back to Top
HTML Embed Code: