Telegram Web Link
ስማኝ ልጄ!!!!!!! ተነቦ ሼር ይደረግ

1. ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!!!!

2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!!!!

3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!!!!

4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!!!!

5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ!!!!

6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ!!!

7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ማለት አይደለም ባለህ ነገር ደስ ይበልህ ማለት እንጂ!!!!

8. ስራህን ውደድ ማለት የምትሰራው ስራ ጥሩ ነው ማለት አይደለም ነገ ጥሩ ስራ እንዲኖርህ ዛሬ የምትሰራውን ስራ ውደድ ማለት እንጂ!!!!

9. ወረኛ አትሁን ማለት አታውራ ማለት አይደለም ምንም ስለማታውቀው ነገር አታውራ ማለት እንጂ!!!!

10. ትሞታለህ ማለት አትስራ ማለት አይደለም ምንም ቁም ነገር ስትሰራ አትሙት ማለት እንጂ!!!!

11. ብቸኛ አትሁን ማለት ሮጠህ ትዳር ያዝ ማለት አይደለም ልብህን ግዜህን ያለህን ሁሉ አሳልፈ ለመስጠት ዝግጁ ሁን ማለት እንጂ!!!!

12. እውነተኛ ሁን ማለት ሰዎች ባሉበት ብቻ እውነትተናገር ማለት አይደለም ለራስህም የእውነት ኑሮ ኑር ማለት ማለት እንጂ!!!!

13. አትጣላ ማለት ከሰው ጋር አትኑር ማለት አይደለም ቂም ይዘህ አትቆይ ማለት እንጂ!!!!

14. ኩራተኛ አትሁን ማለት አትዘንጥ ማለት አይደለም ሌሎችን አትናቅ ማለት እንጂ!!!

15. ቆንጆ ነህ ማለት ከሌሎች የተሻልክህ ነህ ማለት አይደለም አምሮብሃል ማለት እንጂ!!!!

16. አዋቂ ሁን ማለት እንደገና ት/ቤት ሂድ ማለት አይደለም ብልህ ሁን ማለት እንጂ!!!
©ከFb የተገኘ
እንኳን ለብርሀነ ትንሳዬው በሰላምና በጤና አደረሳችሁ
በቴሌግራም @psychoet
#ውሸት

ለምን እንዋሻለን ??? ውሸት ተናጋሪዎችን እንዴት እናውቃለን???
ለምን እንዋሻለን ??

ሀ. ግላዊ ጥቅም ለማግኘት፡–  ለምሳሌ ለስራ ስንወዳደር ቃለ መጠየቅ ላይ የተሻለ ደመወዝ እንዲከፈለን አሁን የሚከፈለንን የደመወዝ መጠን ከፍ አድርገን እንናገራለን፡፡

ለ.ቅጣትን ለማስቀረት፡– ህፃናት በወላጆቻቸው እንዳይቀጡ ያጠፉትን ነገር አይናገሩም ወይም አልሰራንም ይላሉ፡፡

ሐ. ሌሎች ስለኛ መልካም እይታ እንዲኖራቸው ፡- ሰዎች ስለኛ ጥሩ የሆነ ግንዛቤ ይኖራቸው ዘንድ ያልሆነውን ሆንን፣ ያላደረግነውን አደረግን ብለን እንናገራለን፡፡

ከላይ የተጠቀሱት የውሸት ዓይነቶች  በእኛ ዙሪያ ያጠነጠኑ እና  እራሳችንን ለመጥቀም የታለሙ  (self oriented) ናቸው፡፡ ሆኖም ግን ለሌላ ሰው  ተብለው የሚዋሹ ውሸቶችም አሉ ለምሳሌ፡-

ሀ. ሌሎች ሰዎችን ለመጥቀም፡– እናት ልጇን ከፍርድ ቤት ቅጣት ለመጠበቅ ስትል ወንጀሉ በተፈፀመበት ሰዓት ልጄ እቤት ነው ብላ ልትመሰክር ትችላለች፡፡

ለ. ሰዎች ለማህበራዊ ግንኙነት ሲባልም ይዋሻሉ፡– ጎረቤት እራት ተጋብዘን እዚህ ግባ የማይባለውን  ምግብ ጣት ያስቆረጥማል ብለን የምንወጣው ቀጣይ የሚኖረንን ግንኙነት ከግምት ውስጥ በማሰገባት ነው፡፡

ሐ. ሰዎችን ለመጉዳት እንዋሻለን :- ይህ ደግሞ በሌሎች እንዲቀጡ ባልሰሩት ነገር ላይ በሀሰት በመመስከር የሚደረግ ውሸት ነው ፡፡

ሰዎች እንደሁኔታው ዓይነት ውሸቶችን ይዋሻሉ ለምሳሌ #ሮቢንሰን ባጠናው ጥናት ላይ ስራ ለማግኘት ተብሎ ቃለ ምልልስ ላይ የሚዋሽ ውሸትን #83% የሚሆኑ የጥናት ተሳታፊዎች የነበሩት የኮሌጅ ተማሪዎች እንደ ውሸት አይቆጥሩትም፡፡
#ሮዋት ባጠናው ጥናት ደግሞ #40% የሆኑት የጥናቱ ተሳታፊዎች ወደፊት የፍቅር አጋር ይሆናል ብለው ላሰቡት ሰው በመጀመሪያ ግንኙነት ላይ እንደሚዋሹ አረጋግጠዋል፡፡
ሆኖም ግን ምን ያህል የሚሆነው የተሳካ የፍቅር ግንኙነት ኖሮት እንደቀጠለ ጥናቱ የሚለው ነገር ባይኖርም ከላይ በተቀስነው የውሸት ዓይነት ማለትም ሰዎች ስለ እኛ መልካም እይታ እንዲኖራቸው ለማድረግ በሚዋሽ ውሸት ፍፃሜው ያማረ የፍቅር ግንኙነት ሊኖረን አይችልም፡፡

ሌላው በጥናቱ ላይ የተመለከተው ነጥብ ጾታን በተመለከተ የታየ ልዩነት የለም ይህም ማለት ሁለቱም ወንዶችም ሴቶችም በእኩል መጠን ይዋሻሉ፡፡ በእኛስ ሀገር የትኛው የበለጠ ይዋሻል?? #ወንድ ወይስ #ሴት?? መልሱን ለእናንተ ተውኩት፡፡ ተጨማሪ በሌሎች ጥናቶች ላይ እንደተመለከተው ተጫዋች (ማህበራዊ) (Extraverts) ግላዊ (Introvert) ከሆኑት በበለጠ ውሸት እንደሚያዋሹ አመልክተዋል፡፡

ውሸትን እና ውሸታሞኝችን ለመለየት ሰዎች በጥናት የተደገፉ ከቤተ ሙከራ እስከ ውሸትን የማወቂያ መሳሪያ (polygraph) ድረስ ያሉ የተለያዩ ዓይነት ዘዴዎችን ይጠቀማሉ፡፡ ፖሊግራፍን ውሸትን ለማወቅ የሚለካው እንደ ልብ ምትና የመሳሰሉትን አካለዊ ለውጦችን እንደመሆኑ መጠን እንደየ ግለሰቡ ባህሪ ትክክለኝነቱ ሊወሰን ይችላል፡፡ ስሜታቸውን በቀላሉ የሚቆጣጠሩ ሰዎች ውጤቱን ሊያሳስቱ ሲችሉ፤ ድንጉጥ፤ ስሜታዊና ለነገሩ አዲስ የሆኑ ግለሰቦች ደግሞ በተቃራኒው የቀጣፊነት ባህሪ ሊሰጣቸው ይችላል፡፡ አሁን አሁን ግን ከጎንዮሽ ጉዳቱና ከውጤቱ እርግጠኝነት ጋር በተያያዘ ፖሊግራፍ እየቀረ ያለ ቴክኖሎጂ ነው፡፡

ለጊዜው ግን ለእኛ ይሆነን ዘንድ የሰዎችን ባህርይ በማየት እንዴት ውሸታሞችን መለየት እንችላለን የሚለውን እንመለከት፡፡ የተደረጉት ጥናቶች በዋናነት መሰረት ያደረጉት
#ስሜታዊነትን (emotional state)፣
#የወሬያቸውን (የመልዕክቱን) ይዘት (content complexity)  እና
#ባህርይን ለመቆጣጠር ከሚደረግ ጥረት (attempted behavioral control) በመነሳት ነው፡፡ ስሜታዊነት ላይ ሰዎች ውሸት ሲያወሩ አንደኛ ውሸት እያወሩ ስለሆነ የጥፋተኝነት ስሜት ይሰማቸዋል፣ ሁለተኛ በውሸቱ ምክንያት ወደፊት በሚያገኙት ጥቅም ደስተኛ ይሆናሉ ወይም ደግሞ ይታወቅብኝ ይሆን በማለት ይፈራሉ፡፡ ከወሬያቸው ይዘት ጋር በተገናኘ ውሸት ተናጋሪዎችን ለመለየት ተናጋሪውን ተደጋጋሚ ጥያቄ በመጠየቅ ተመሳሳይ መልስ እንደመለሰልን ማረጋገጥ እና ለምላስ ወለምታዎች ትኩረት መስጠት እንደ ዘዴ ተቀምጠዋል፡፡

የሰዎችን ባህርይ በማየትም ውሸት ተናጋሪዎችን መለየት እንችላለን #ዲፓውሎ_እና_ሮዘንሀል በጥናታቸው እንዳረጋገጡት ከሆነ ውሸት የሚያወሩ ሰዎች በሚያውሩበት ጊዜ እነዚህን ባህሪዎች አሳይተዋል መረጃውን  የሚያስተላልፉለትን ወይም የሚነግሩትን ሰው ዓይን ላለማየት የተለያየ ጥረት ደርጋሉ፣ አላስፈላጊ በሆነ ቦታ ላይ ሊስቁ እና ፈገግ ሊሉ ይችላሉ፣ ተደጋጋሚ የሆነ መንገድ በእጅ ለማስረዳት የእጅ እንቅስቃሴ ያደርጋሉ (ውሸት የማይናገሩ ሰዎች በእጃቸው እንቅስቃሴ ለማስረዳት እንደሚሞክሩ ልብ ይሏል)፣ ፊታቸውን እና  ፀጉራቸውን ያካሉ ወይም ይነካሉ፣ በተለያዩ ፊት ለፊት በተቀመጡ ግዑዝ ነገሮች ይጫወታሉ፣ በፍጥነት ያወራሉ፣ ግንባራቸውን እና እጃቸውን ያልባቸዋል፣ ጥያቄ ሲጠየቁ እስኪመልሱ ድረስ ባንጻራዊነት ሰፊ ጊዜ ይወስዳሉ፣ በመሀል አ……ኧ….እም……ያበዛሉ፣ መንተባተብ (ቃላትን መደጋገም፣ ዐረፍተ-ነገሮችን አለመጨረስ፣ የምላስ ወለምታ)እንዲሁም  ድንገተኛ የሆነ የድምጽ መጨመርና መቀነስ ይታይባቸዋል፡፡

ሰዎች በተለያየ መንገድ ግንኙነት ፈጥረው ሲያወሩልን ወይም መልዕክት ሲያስተላልፉልን ከላይ ከጠቀስናቸው ምክንያቶች መካከል አንዳንድ ነገሮችን ካየን ውሸታም ብለን ከመፈረጃችን በፊት በእራሳችን መንገድ እና ለምን እንደዋሹን ደግሞ ማጣራት ይኖርብናል፡፡ በዚህች ባጭር ጽሁፍ መሸፈን አልችልም እንጂ ስለ Pathological liars (ህይወታቸው በሙሉ በውሸት ስለተሞላና ውሸት መናገርና ማቆም ስለማይችሉ ውሸት በሽታ ስለሆነባቸው ሰዎች) ጥቂት ባወራ ደስ ባለኝ ነበር፡፡ ነገር ግን ወደፊት ይዤላችሁ እንደምቀርብ ቃል በመግባት የዛሬውን በዚህ ልቋጨው፡፡

ሰላማችሁ ይብዛ………..

(በቁምላቸው ደርሶ)
©Zepsychologist
@psychoet
መልካም የሰራተኛ ቀን ይኹንላችሁ። ግን ደግሞ በተሰማራችሁበት ሥራ ስትለፉና ስትደክሙ ይሄንን 👆 እንዳትረሱ።
@psychoet
በፍቅር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ዋና ዋና መገለጫቸው አነዚህ ናቸው፡፡

❤️መቀበል፡ ሰዎችን፣ ሁኔታዎችን፣ ራሳቸውን ያለ ምንም ተጨማሪ ሃሳብ አሁን ባሉበት ላይ መቀበል የሚችሉ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ከማንም ሰው ጋር በምንም ሁኔታ ውስጥ መኖር እንደሚችሉ የሚሰማቸው ሰዎች ናቸው፡፡

❤️መረዳት፡ ሰዎችም ሃሳባቸውን እንዲገልጹ፣ አይታቸውን እንዲያካፍሉ፣ ምክንያታቸውን እንዲገልጹ እድል የሚሰጡ ናቸው፡፡ የተፈጠሩት ነገሮችም ለምን አላማ እንደሆነ ለማወቅ የበኩላቸውን ጥረት የሚያደርጉ ሰዎች ናቸው፡፡ የራሳቸወን ሃሳብ ከመወርወራቸው በፊት መረዳትን  ማስቀደም ይችሉበታል፡፡

❤️ተፈጥሮን መውደድ፡ በፍቅር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች እንደ ተፈጥሮ የሚመስጣቸው ሌላ ነገር ያለ አይመስለኝም፡፡ በሰው አፈጣጠር፣ በውሃ፣ በእጽዋት፣ በእንስሳት፣ በአየር፣ በደመና፣ በዝናቡ ወዘተ እጅግ ይደመማሉ፡፡

❤️ለሁሉም፡ ማንን ታፈቅራላችሁ ብትባሉ ማንን ትላላችሁ? በፍቅር የሚኖሩ ሰዎች ሁሉንም የሚል መልስ ነው ያላቸው፡፡ ሁሉም ነገር ፍቅር አለው፤ ፍቅር ይገባዋል ይላሉ፡፡ ለቀረባቸው፣ ላገኙት፣ ለገጠማቸው ሁሉ መልሳቸው ፍቅር ነው፡፡

❤️መፍቀድ፡ ራሳቸውን እንዲያፈቅርና ነጻ እንዲሆን ይፈቅዱለታል፡፡ በዙሪያቸው ያሉ ሰዎችን በነጻነት ይቀርባሉ፡፡ ሰዎች የፈቀዱትን እንዲያደርጉ ይተዋቸዋል፡፡ በዙሪያቸው ያለ ነገር ሁሉ የፈቀደውን እንዲሆን መፍቀድ፣ እገዛቸውንም መለገስ ይችሉበታል፡፡ በዚህም ምክንያት በሰዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተርፋሉ፡፡

❤️ራስን መሆን፡ በፍቅር የሚኖር ሰው ትኩረቱ ራሱን በመሆን ላይና በማሳደግ ላይ ነው፡፡ ሌሎች ሰዎችም ራሳቸውን እንዲሆኑ ያግዟቸዋል፡፡ ትክክለኛ ፍቅር ራስን በመሆን ውስጥ እንደሆነ ያውቃሉ፡፡

ታዲያ የፍቅር ሰው ናችሁ .. ጻፍልን

ተመስገን አብይ (Psychologist)
@psychoet
ለእያንዳንዱ ጉዳይ መብከንከናችንን እናቁም

በዙሪያዬ ያሉ ጥቂት ሰዎች ኑሯቸው እንዲህ ነው፡፡ ለረባውም ላረባውም፣ ለትንሽ ትልቁ፣ ለሚለከታቸውም ለማይመለከታቸውም ነገር ትኩረት የሚሰጡ ናቸው፡፡ ለእያንዳንዷ ጥቃቅን ጉዳይ ትኩረት ከሰጠንና ከተጨነቅን ኑሯችን ጤናማ አንሆንም፡፡

እንዴት አንድ ሰው ስለሁሉም ነገር ሊጨነቅ ይችላል? ለራሳችን ጉዳይመ ተጨንቀን፣ ለሰዎች ተጨንቀን፣ ሊሆን ይችላል እያልን ተጨንቀን እንዴት እንችለዋለን? 

በጣም የሚገርመው እንዲህ አይነት ባህሪ ያላቸው ሰዎች፡
✍️ የመፍትሄ ሰዎች አለመሆናቸው ላይ ነው፡፡
✍️ አንድን ጉዳይ ለረጅም ግዜ ይተክዙበታል፡፡ 
✍️ነገሮችን በአሉታዊ መንገድ መረዳት ይቀናቸዋል፡፡
✍️ሲታመሙ አንኳን የሚድን አይመስላቸውም፡፡
✍️በህይወታቸው ውስጥ ያሉትን መልካም እድሎችን  መጠቀም አይችሉበትም፡፡

ከዚህ ባህሪ ለመላቀቅ፡

1️⃣ መፍትሄ መስጠት የምንችለውን መፍትሄ መስጠትና መተው ያለብን ደግሞ መተው መለማመድ
2️⃣ ሌሎች ሰዎች እንዴት እንደሚኖሩ ማየት፣ መጠየቅና ትምህርት መውሰድ
3️⃣ ጓደኞችን ማፍራትና ከእነሱ ጋር ግዜ ማሳለፍ ተቃሚ መፍትሄዎቸ ናቸው፡፡

@ተመስገን አብይ Psychologist

@psychoet
መልካም የእናቶች ቀን
❖አንባቢ እናት ጥሩ ትውልድን ትገነባለችና ይቺን የመሰሉ እናቶች ይብዙልን ፡፡ ፎቶው የተላከልኝ ከወደ አዋሳ ነው ፡፡
📚📚📚📚📚📖📖📖📖📖📖
ከ"ሜሎሪና" መጽሐፍ የተወሰዱ የሕይወት ምክሮችና እውነታዎች
📚📚📚📚📚📖📖📖📖📖📖

📕ያለፍክበት የሕይወት መንገድ አስሮ ሊይዝህ አይገባም ፤ ነገህን መወሰን የራሳህ ምርጫ ነው፡፡

📕በሕይወትህ የደስታ ምንጭ መኾን ባትችል ለሌሎች የሐዘን ምክንያት አትኹን፡፡

📕በምድር ላይ ምንም ፍጹም ነገር የለምና አንተም ፍጹም ለመሆን አትሞክር ሰዎችም ፍጹም እንዲሆኑ አትጠብቅ ነገር ግን ኹሉን በመልካምነትና በቅን ልቦና አከናውን ፡፡

📕ያለህን ችሎታ ፣ አቅም ፣ ዕውቀት አንተ ካላከበርከውና ካላወጣኸው ማንም መቶ ሊያከብርልህና ሊያወጣልህ አይችልም ፡፡ ስለዚህ ከተቀምጥክበት ተነሳና ከምኞት ወተህ ወደ ተግባር ተሻገር ፡፡

📕ዝምታ ፣ በውስጡ ትልቅ ጩኸት የያዘ የማይጠየቅ ጠያቂ ፣ የማይመረመር መርማሪ ነውና ከዙሪያህ ካለ የሰዎች ጫጫታ በላይ በላይ የውስጥ ዝምታህን አድምጥ ፡፡

📕በሕይወትህ ትልቅ መከራ ፣ ችግር ፣ ሀዘን ደርሶ ሊሆን ይችላል ፤ "ሰው እንዴት በዚህ ውስጥ ያልፋል?" ብለህ አዝነህ ፣ ተክዘህ ሊሆንም ይችላል ፡፡ ግን በሕይወት ዘመን መዘንጋት የሌለብህ ነገር "ተስፋ" የሚባል ነገር መኖሩን ነው ፡፡

ሜሎሪና አንብቡ አስነብቡ❤️❤️❤️

መልካም የእናቶች ቀን

www.tg-me.com/psychoet
ዝምታ

ለምን ዝም እንላለን ? ዝምታ ይጠቅማል ወይስ ይጎዳል? መልሱን ቀጥሎ ታገኙታላችሁ፡፡

ዝምታ ሁለት አይነት መልኮች አሉት፡፡

አንዱ ስህተትን በመፍራት፣ ላለመሞከር፣ በሰዎች አይን ውስጥ ላለመግባት፣ ድፍረት የማጣት፣ የፍርሃት ምልክት ነው፡፡ እንዲህ አይነት ሰዎች ሌሎችን ማድመጥ ብቻ እንጂ የራሳቸውን ማጋራት፣ መጠየቅ፣ በቂ ምላሽ መስጠት አይችሉበትም፡፡ በዚህም ምክንያት ለራሳቸው ሳይሆኑ ይቀራሉ፡፡ የሰዎች ሁሉ ሃሳብ ማጠራቀመሚያ ቋት ይሆናሉ፡፡ የራሳቸውን ሃሳብ በድፍረት መግለጽ አይችሉበትም፡፡ የሚረዳቸው ሰው እንደሌለም ይሰማቸዋል፡፡

ሁለተኛው ዝምታ ደግሞ ባለመቻል ሳይሆን ፈልገን የምናደርገው ነው፡፡ ለማዳመጥ፣ ለመረዳት፣ ለማሰብ፣ ለራሳችን ግዜ ለመስጠት፣ ተራችንን ለመጠበቅ፣ ወዘተ. ስንፈለግ ዝምታን እንመርጣለን፡፡ አንዳንዴም ሁኔታው ልክ እንዳልሆነ እያወቅን ጭቅጭቁን ለማስወድ ወይም ጉዳዩ በኛ ብቻ ሊፈታ እንደማይችል ስለተረዳንና ለማሳለፍ ስንል ዝምታን እንመርጣለን፡፡

ራሳችሁን የትኛውን ዝምታ ስትጠቀሙ አስተውላችሁ ታውቀላችሁ? የመጀመሪያውን ወይንስ ሁለተኛውን? ጻፉልን፡፡

©ተመስገን አብይ Psychologist
@psychoet
በእራስህ ህይወት ላይ ሹፌር ካልሆንክ
በሌሎች ህይወት ተሳፋሪ ትሆናለህ

@psychoet
#Share አድርጉ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2016 ዓ.ም ለድኅረ- ምረቃ ትምህርት አመልካቾች

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2016 ዓ.ም ለድህረ ምረቃ ትምህርት በቀን መርሃ ግብር ለሁለተኛ እና ለሶስተኛ ዲግሪ እንዲሁም በማታ እና በርቀት መርሃ ግብር ለሁለተኛ ዲግሪ ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ስለዚህም በዩኒቨርስቲዉ ድረ-ገጽ (http://aau.edu.et) ላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች በማሟላት ማመልከት እንደምትችሉ ያሳስባል፡፡

የአ.አ.ዩ የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) የማመልከቻና መፈተኛ ቀናት ከግንቦት 15 እስከ ነሐሴ 06 ቀን 2015 ዓ.ም ሲሆን፤

የአ.አ.ዩ የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና ላለፉ በ(https://portal.aau.edu.et) ላይ የማመልከቻና የትምሕርት ማስረጃዎችን የማስገቢያ ቀናት ከግንቦት 18 እስከ ነሐሴ 10 2015 ዓ.ም፤

የትምሕርት ማስረጃዎችን በማስገባት የማመልከቻ ቦታ ሬጅስትራር ቢሮ ቁጥር 203 መሆኑን ያሳዉቃል፡፡

@Psychoet
ትስማማላችሁ?
ጀምሮ መጨረስ መቻል

ብዙ ነገሮችን እንጀምራለን ነገር ግን የጀመርናቸውን ሁሉ አንጨርስም፡፡ በጣም በጉጉት፣ በተነሳሽነት፣ በፉከራ እንጀምርና ከጥቂት ቀናት በኋላ ስንቀጥለው አይታይም፡፡ ለምን ይመስላችኋል?

አንድ ሰው አንድን ነገር ጀምሮ የማይጨርስ ከሆነ ቀጥሎ ካሉት ውስጥ የማይችላቸው ነገሮች አሉት ማለት ነው፡፡

1️⃣ ፍላጎት፡ ፍላጎቱን ለይቶ የማያውቅ ሰው በጀመረው ነገር ላይ መጽናት አይችልም፡፡ ምክንያቱም በራሱ ፍላጎት ሳይሆን በሌሎች ሰዎች ፍላጎትና ግፊት ስለሚጀምሩ ከጊዜ በኋላ ያስጠላቸውና ይተውታል፡፡
2️⃣ ውሳኔ፡ ውሳኔ ማለት የጀመርኩትን ነገር መጨረሻውን ሳላይ አላቆምም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ከጫፍ እስከምደርስ ድረስ ጉዞዬን እቀጥላለሁ ማለት ነው፡፡ ውሳኔ የአንድን ሰው ሙሉ ህይወት የማስተካከል ሀይል ያለው ትልቅ ችሎታ ነው፡፡
3️⃣ ትኩረት፡ ትኩረቱን የሚፈልገው ነገር ላይ ማድረግ ያልቻለ ሰው የሚጀምረው ብቻ እንጂ የሚጨርሰው ነገር የለውም፡፡ ትኩረታችን በፈለግነው ነገር ላይ ብቻ ለማድረግ ከወሰንንና ከጠበቅን የጀመርነውን ለመጨረስ እንችላን፡፡
4️⃣ ከሌሎች ሰዎች ጋር በህብረት መስራት መቻል፡ አንዳንዶቻችን የጀመርነውን ነገር ያለማንም እርዳታ ብቻችንን ለማድረግ እንለፋለን በኋላም ከአቅማችን በላይ ይሆንብንና እንተወዋለን፡፡ ሰዎችን የመያዝ ጥበብ የሌለው ሰው የጀመረውን ማንኛውንም ነገር ለመጨረስ ይከብደዋል፡፡ በህብረት መስራት መቻል የጀመርነውን ለማሳክት በጣም ቁልፍ ችሎታ ነው፡፡
5️⃣ በለውጥ ውስጥ መማር መቻል፡ ሁሉም ነገሮች እኛ በምንፈልገው ፍጥነትና መንገድ ብቻ አይሄዱም፡፡ አንዳንዴም ከጠበቅናቸው ውጪ የሆኑ ጉዳዮች ይገጥሙናል፡፡ ስለዚህ የጀመርነውን ነገር በማሳካት ሂደት ውስጥ ለሚገጥሙን ማንኛውን ነገር ራስን ማዘጋጀትና ራስን ማሻሻል አስፈላጊ ነው፡፡
©Temu
ራስን መግለጽ መቻል

እስቲ ራሳችሁን ግለጹት? ተብለው ሲጠየቁ ብዙ ሰዎች “እንዴት እኔ ራሴን እገልጻለሁ ሌሎች ሰዎች ይግለጹኝ እንጂ” ይላሉ፡፡ ይህ ትክክለኛ መልስ አይደለም፡፡ ምክንያቱም እኛ በእኛ ውስጥ ነው የምንኖረው እንጂ በሌሎች ሰዎች ውስጥ አይደለም፡፡ ሲቀጥል ሌሎች ሰዎች የራሳቸው ጉዳይና ህይወት ያለባቸው ናቸው ስለዚህ እኔን በደንብ መግልጽ አይችሉም፡፡

ሰዎች ስለኛ የሚናገሩት ያሳየናቸውን ባህሪ ብቻ ነው፡፡ ይህን ሊያዉቁ የሚችሉት ደግሞ ለጅም ግዜ አብረናቸው ካሳለፍን ነው፡፡ አንዳንድ ባህሪያቶች ደግሞ የተለዩ ሁኔታዎችን ጠብቀው ነው የሚገለጹት ስለዚህ ሰዎች ስለኔ ይናገሩ የሚለው የሚያዋጣ አይደለም፡፡
ስለራስ መናገርም በኩራት መንፈስ ራስን መካብ አይደለም፡፡ እኛ ምን አይነት ሰው እንደሆንን ስለራሳችን የምናውቀውን መንገር ማለት ነው እንጂ ራስን መስቀል ማለት አይደለም፡፡

ለምሳሌ አንድ ሰው እኔ ስሜቴ ቶሎ ቶሎ የምቀያየር አይነት ሰው ነኝ ብሎ ራሱን ቢገልጽ ተገቢነት አለው፡፡ ምክንያቱም አሁን ያለውን ማንነቱን ነው የነገረን፡፡ ስለዚህ ራስን መግለጽ አሁን ላይ ያለንን ባህሪና ማንነት መንገር ማሳየት መቻል ነው፡፡

በእርግጥ ከራሱ ጋር ያልተገናኘና ስለራሱ ማንነት አስቦ ለማያውቅ ሰው ይህ ጥያቄ ከባድ ነው፡፡ የዘወትር ትኩረቱ በሰዎችና በሁኔታዎች ላይ ብቻ ለሆነ ሰውም ቢሆን ይህን ጥያቄ መመለስ አይችልም፡፡

ራስን መግለጽ ራስን ከማወቅ ከጥሎ የሚመጣ ችሎታ ነው፡፡ ስለዚህ ራሱን ያወቀ ሰው ብቻ ነው ራሱን መግለጽ የሚችለው ማለት ነው፡፡ ሌሎች ሰዎች እኛ ለተናገርነው ማንነታችን ማረጋገጫ የሚሰጡ አካላቶች ናቸው እንጂ ስለኛ ከእኛ የተሻለ የሚገልጹ አይደሉም፡፡
ራሰን መግለጽ መቻል በጣም ጤናማና ትክክል የሆነ ችሎታ ነው፡፡


©ተመስገን አብይ
15 ወርቃማ #አባባሎች! ሼር
ቴሌግራም ቻናል - @PSYCHOET

1) ምቀኞች መብዛታቸው በስኬት መንገድ ላይ የመሆንህ ምልክት ነው!

2) #ወንድ #ልጅ እናቱ በሕይወት እስካለች ድረስ #ሕፃን ነው..ለእናቱ!

3) በፈተና ላይ አለመታገስ ሌላ #ፈተና ነው!

4) #ፈገግታ ቃላት የሌለው መልካም ንግግር ነው!

5) ካንተ የባሰ አለና አመስግን ፈገግ በል!

6) ትንሽን ለመስጠት አትፈር ምንም አለመስጠት ከሱ የባሰ ነውና!

7) የተሸናፊዉ #ፈገግታ ያሸናፊውን #ደስታ ይቀንሳል!

8) የሁሉን #ሰው ውዴታ ማግኘት ሊደረስበት የማይቻል ግብ ነው!

9) #ነፍስ በኩራት ስትሞላ ጎደሎ የመሆኗ መገለጫ ነው!

10) ኩራተኛ ሰው ተራራ ጫፍ ላይ ሆኖ ሌሎችን ትንሽ አድርጎ እንደሚያይ ነው ነገርግን እሱንም ትንሽ አድርገው እንደሚያዩት አያውቅም!

11) ብዙ ጊዜ በጉጉት ከምንጠብቀው ይልቅ ድንገት የምናገኛቸው ነገሮች ውብ ናቸው እኛ ከለፋነው ጌታ የፃፈው መልካም ነውና!

12) ግኡዝ የሆኑት ውሃና አፈር ለእፅዋት አግልጋይ ናቸው ፤ እፅዋቶች ደግሞ ለእንስሳት ያገለግላሉ እንስሳት ፣እፅዋትና ግኡዛን ደግሞ የሰውን ልጅ ያገለግላሉ ... በተቃራኒው የሰው ልጅ ወደታች ወርዶ ለግኡዛን አገልጋይ (አምላኪ) መሆን ከጀመረ ያኔ ከነሱ የባሰ ይሆናል።

13) ብዙ ሰው ልጅ ለዘለዓለም እንደሚኖር ሆኖ ይለፋል አንድ ቀን ሳያልፍለት ይሞታል!

14) በሕይወት ትልቁ ስኬት የሕይወትን ትርጉም ማግኘትና አላማ ያለው ኑሮ መኖር ነው፡፡

15) በዚህ ቦታ .... ካነበባችሁት ፣ ከሰማችሁት ፣ ከምትከተሉት እምነት የምትወዱትን አባባል በcomment አሳውቁኝና ሌሎችም ያንብቡት፡፡

ሜሎሪና መጽሐፍ
#Share ይደረግ

ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ
#ሃያ አንዱ ማኅበራዊ ሕግጋት
መልዕክቱን አንብበው ሲጨርሱ #Share ያድርጉት

(Social Rules ተብለው የተዘረዘሩ የማኅበራዊ ሕይወት ሕግጋትን ስመለከት ለኛስ አትጠቅምም ወይ ብዬ ነው ወዲህ ማምጣቴ)
==================
1. ይሰለቹሃል
አስሬ አትደውል፤ ሰዎች ጋር ከሁለቴ በላይ አይደወልም። ተሰልቺ ትሆናለህ!

2. 'ሼም ነው' ነው
የሚከፍለው ሌላ ሰው ነው ብለህ ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ምግብና መጠጥ አትዘዝ!

3. አይባልም
"... እንዴ እስካሁን አላገባሕም? ለምንድነው እስካሁን ያልወለድሽው? እንዴት ዲግሪሽን እስካሁን ሳትይዢና ሳትይዝ ወዘተ..." አይባልም።

4. ክፈል
አብሮህ ላለው ሰው ታክሲ ላይም ሆነ የትም ቦታ አግባብ ነው ብለህ ስታምን ቀድመህ ክፈል። ገና ለገና ይከፍላል ብለህ ከሱ ስትጠብቅ ደምህን እያሯሯጥክ ትሰቃያለህ።

5. ነውር ነው
ሰው እየበላም ይሁን በማንኛውም ሰዓት ከሰዎች ጋር ካለህ ጥርስህን አትጎርጉር፣ አፍንጫህንና ሌሎች ያልተገቡ ቦታዎችንም አትነካካ።
============

6. አታቋርጥ
ግዴለህም አብሮህ ያለው ሰው አውርቶ ይጨርስ። ጥልቅ እያልክ አታቋርጥ። ከባሕልም ከስልጣኔም ውጪ ነው።

7. አታብሽቅ
ሆን ብለህ የማናደድ ባሕሪ ካለህ ተው። ሰዎች ለመባል የማይወዱትን ተው። ሰዎች ብዙ የማይናገሩትና የተሸከሙት የራሳቸው ብሽቀት ስላለባቸው ለተሻለውና ለሚበረቱበት ሕይወታቸው አድናቆት ስጥ።

8. አመሥግን
ለተደረገልህ ማንኛውም ቅንጣት ነገር አመሥግን።
9. ያለስስት አድንቅ
ሰዎችን በይፋ አድንቃቸው፣ መልካም ያልሆነ ነገራቸውን ግን በግል አውራቸው።

10. ክፉ አስተያየትህን ቆጥብ
ያልሆነ ነገር ብታይ እንኳን አፍህ በበጎ ቃላት ይቀይረው። ወፍሮ ያየኸውን ሰው ኤጭ ተዝረጠረጥክ ከማለት ተቆጠብ።
===================

11. ካልሆኑ ጥያቄዎች ታቀብ
ሰዎች የሕክምና ቀጠሮ ሄደው መምጣታቸውን ነግረውህ ይሆናል። የውጤቱን ምንነት ለማወቅ ግን በጥልቀት አትጠይቅ። በነገሩህ ልክ መልካሙን ተመኝላቸው። በቻልከው መጠን በመረጃና በጥቆማ አግዛቸው እንጂ ድንበር አትዝለል።

12. ስነ ስርዓት
ሰዎች ከስልካቸው ላይ ፎቶ እንድታይ ቢሰጡህ ከፈቀዱልህ ውጪ ሌላ ፎቶ ካላየሁ ብለህ ስልክ አትፈትሽ። ሁሉም ሰው ታልፎ እንዲገባበት የማይፈልገው የራሱ አጥር አለው።

13. ክብር ለሁሉም
ከላይ ጫፍ ላለ የሥራ ኃላፊና ከታች ዝቅ ባለ ስራ ላይ ለሚገኘው ሰው እኩል ክብር ስጥ። እንደውም ከላይ ካለው ይልቅ ታች ላለው ሰው የሰጠኸው ክብር ብዙ እውቅና አለው። ለንቀትህ ግን የማንንም አድናቆትና ጭብጨባ አታገኝም።

14. ስልክህን አስቀምጥ
ሰዎች በቀጥታ ላንተ እያወሩ ስልክህን የምትነካካ ከሆነ ቀሽምነት ነው። ከሰው ሰራሹ ይልቅ ራሱ ሰው ትልቅ ዋጋ አለው።

15. አድብ
ሰዎች ካልጠየቁህና ካልፈቀዱልህ በስተቀር በራሳቸው ሕይወትና ሥራ ጣልቃ አትግባባቸው።
==========================

16. ተቆጠብ
ከረጅም ጊዜ በኋላ ያገኘሃቸውን ሰዎች አስጨናቂ ጥያቄ አትጠይቃቸው። ሰዎች ቆይታቸውን እንዲሁም ዕድሜና ደሞዛቸውን ጨምሮ የመናገርና ያለመናገር ብቸኛ ባለመብት ራሳቸው እንደሆኑ እወቅ።

17. መነጽርህን አውልቅ 
ከሰዎች ጋር በዓይንህ አውራ። ከማንም ጋር በመንገድ ላይ ተገናኝተህ ስታወራ መነጽርህን ከዓይንህ ማንሳት እንዳለብህ አስታውስ። ክብርም ነው!

18. አትሳሳት
በድኅነት አስተሳሰብ ሆነህ ስለሀብታሞች ምንነትና ማንነት አታውራ፤ ልጅ ሳይኖርህ ስለልጅና ልጅ ስላላቸው ሰዎች ባሕሪ አትፍረድ።

19. ለስልክ መልዕክት ምላሽ መስጠት
በስልክህ የጽሑፍ መልዕክት ሲደርስህ አንብበህ ዝም ማለት ነውር ነው። ተገቢውን ምላሽ በበጎነት ቃል መመለስን ልማድህ አድርገው።

20. ዕቃ መልስ
የወሰድከውን ማንኛውም ቁስ ባለቤቱ ሳይጠይቅህ በፊት ቶሎ መልስ።

21. አማራጭ ሐሳቦች ሁሌም አሉ
የያዝከውን ሐሳብ ሳትፈራ አውጣው። ሌሎች እንዲወያዩበትና እንዲተቹት ክፍት አድርገው፤ አንተም ሐሳብህም ትጎለብታላችሁ። ነገርህን ደገፉትም አልደገፉት ምንጊዜም ቢሆን ላነሳኸው ሐሳብ ጥሩ ግብዓት አይጠፋም። ልክ አልሆን ወይ እያልክ ወይም ሐሳቤ ያንስ ይሆን ወይ ብለህ አትሸማቀቅ፤ ተሸማቀህ ትቀራለህ!

ሳይኮሎጂ  ፔጅን #Like በማድረግ ቤተሰብ ኹኑ

@psychoet
©Abraham Tsehaye
ትስማማላችሁ?
2024/09/29 18:24:07
Back to Top
HTML Embed Code: