Telegram Web Link
ትስማማላችሁ?
ሀምሌ 3፣ 2015
ሜሎሪና መጽሐፍ ከወጣ ዛሬ ድፍን 3 ዓመት ኾነው።😃
በመጀመሪያ፥ በብዙ ሰዎች በመነበቡ እግዚአብሔርን አመሠግናለሁ። በመቀጠልም፥ አንብባችሁ መልካም አስተያየትና ትችታችሁን ለለገሳችሁኝ በሙሉ እግዚአብሔር ክብረት ይስጥልኝ ማለት እፈልጋለኹ።

በቀረው፥ ሜሎሪና ቁጥር ሦስትን በዚህ ዓመት ክረምት ላይ የማውጣት እቅድ እንደነበረኝ በተለያዩ ሚዲያዎች ስገልጥ የነበረ ቢኾንም፣ በተለያዩ ከመጽሐፋ ጋር ተያያዥነት ባላቸው ግላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ምክንያት ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ወደ ቀጣዩ ዓመት ከገና በዓል አካባቢ ለማውጣት ወስኛለሁ። እወዳችኋለሁ ❤️
@psychoet
……… በጣም ገራሚ ታሪክ

      😍 ትንሿ ቆንጅዬ ልጅ ሁለት አፕል እንደያዘች እናቷ መጣች ።
        እናትም " የኔ ጣፋጭ አንዱን ለኔ ለእናትሽ ትሰጪኛለሽ ?" ስትል በትህትና ትጠይቃታለች ።
      ልጅም ትኩር ብላ ከተመለከተቻት በኋላ አንዱን አፕል ግምጥ አደረገችው ። ቀጠለችና ሁለተኛውንም ደገመችው 😳 እናት በልጇ ሁኔታ ደንግጣ ፍዝዝ ብላ ቀረች ።
             ስሜቷን በቁጣ ልታሳያት ብትሞክርም ድንጋጤው ከለከላት ☺️እንዴት በእኔ በእናቷ ትጨክናለች …? ብላ አሰበች ።
   
           በዚህ መሀከል ልጅ የገመጠችውን አንዱን ለእናቷ እያቀበለቻት "እንኪ ማሚ ይበልጥ የሚጣፍጠው ይሄኛው ነው ።" አለቻት ። እናት ያልጠበቀችውን ክስተት በማየቷ ልጇን አቅፋ ተንሰቅስቃ አለቀሰች 😍

መልካም ቀን 💕

@psychiet
አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ⛔️⛔️⛔️
ሁላችሁም በየግሩፑ #ሼር አድርጉት

በእነዚህ ሳምንታት በጓደኞቻችሁ ወይም በግሩፕ የሚላኩ ይሄን የመሰሉ መልዕክቶች ቴሌግራማችሁን ከሚጠልፉ ሰዎች የሚላኩ ሲኾን Linkun ከፍታችሁ ከገባችሁ የእናንተንም ቴሌግራም ጠልፈው ለሌሎች ወዳጆቻችሁ መልዕክት ይልካሉ። ስለዚህ እንደዚህ አይነት መልዕክት ከደረሳችሁ
1. Linkun እንዳትከፍቱት
2. የላከውን ሰው ካወቃችሁት ደውላችሁ ቴሌግራሙ እንደተጠለፈ ንገሩት

እባካችሁ ብዙ ሰው በዚህ እየተሸወደ ስለኾነ ይሄንን ማስጠንቀቂያ በየግሩፑ #ሼር አድርጉ።

@psychoet
ግጭትን ማስተናገድ መቻል

“እኔ ከማንም ሰው ጋር መጣላትም ሆነ መቀያየም አልፈልግም!” ሲሉ የምንሰማቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ከሰዎች ጋር አብረን እስከኖርን ድረስ ደግሞ ከግጭት መራቅ አንችልም፡፡

ግጭት እንዳይፈጠር ከመታገል ይልቅ ግጭትን የምናስተናግድበትን አቅም መፍጠር ነው ያለብን፡፡

ግጭት ለምን ያስፈልጋል?

1️⃣ ግንኙነትን ለማደስ ያስፈልጋል፡፡
2️⃣ ልዩነትን ለማወቅና ለማክበር ያስፈልጋል፡፡
3️⃣ ያመንበትን ነገር እንድናሳይ እድል ይሰጠናል፡፡
4️⃣ መተማመንን ይፈጥርልናል፡፡
5️⃣ አቅማችንን ለመፈተሸ ይረዳናል፡፡
6️⃣ ሁሌም የሚፈጠር ጉዳይ መሆኑን እንድንረዳ ይጠቅመናል፡፡ 

ከግጭት ለመሸሽ ከመመሞከር ይልቅ ያመንበትን ነገር ለማሳየት መሞከር የተሻለ ደስታን ይፈጥርልናል፡፡

ግጭት ሁሌም ያለ መልካም ነገር ነው፡፡

ጠቃሚ ሆኖ ካገኛችሁት ሼር አድርጉት!

ተመስገን አብይ Psychologist
#በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፕላን የተሳፈረ ሰውዬ የበረራ አስተናጋጇ በሰጠችው ጥቆማ መሰረት የአውሮፕላኑ መጸዳጃ ቤት ውስጥ መጠቀም ይጀምራል። ታዲያ በመሐል አንዲት ቀይ ማብሪያና ማጥፊያ የምትመስል ነገር ያይና ነካ ያደርጋታል። በዚህ ቅፅበት አውሮፕላኑ በሐይል መንገጫገጭና ወደ ጎን ማጋደል ይጀመራል። ሰውዬውም ደንግጦ ወይኔ ሳላውቅ የማይነካ ነገር ነክቼ ሕዝብ ጨረስኩኝ ብሎ በነካት ቀይ ነገር ይጸጸታል። ከጥቂት ቆይታ በኃላ ግን መንገጫገጩ ይቆምና ጨርሶ ከመጸዳጃ ቤት ይወጣል። ሁሉም ሰው "አንተ የማትረባ! ጨርሰኸን ነበር እኮ!" ብሎ ይጮህብኛል ብሎ ቢጠብቅም ዞር ብሎ ያየው ሰው እንኳን አልነበረም።
መቀመጫው ላይ እንደደረሰም አጠገቡ የተቀመጠውን ሰው ቀስ እና ስቅቅ ብሎ "ይቅርታ የማይነካ ነገር ነክቼ ጨርሻቹ ነበር አይደል?" ይለዋል። ሰውዬውም "አረ በፍጹም እንደዛ እንዳታስብ! ይህን ያሕል ጥንቃቄ የሚፈልጉ ነገሮች እኮ መፀዳጃ ቤት ውስጥ አይደረጉም ...ካፒቴኑ ያለበት ክፍል ውስጥ ነው ያሉት። አጋጣሚ ነው ትንሽ የአየሩ ሁኔታ አስቸጋሪ ስለሆነ ነው አውሮፕላንኑ የተንገጫገጨው" ይለዋል።
ብዙ ጊዜ ሰዋች እንደዚህ ያስባሉ። የሆነች ነገር ነክተው ሕይወትህን የሚያንገጫግጩ እና መጨረሻህን የሚወስኑ ይመስላቸዋል። የረሱት ነገር ቢኖር ይህን ያክል ጥንቃቄ የሚፈልገው ነገር እነሱ አጠገብ ሳይሆን የሕይወትህ ካፒቴን ጋር እንዳለ ነው። እንደዛማ ባይሆን ኖሮ ቀይዋን ነገር እየጠቀጠቁ ሕይወታችንን መንገጫገጭ ብቻ ያደርጉት ነበር። ምስጋና ለካፒቴኑ ይሁንና እንደዚሕ አይነት ጥንቃቄ የሚፈልጉ ነገሮችን በሱ እጅ ብቻ እንዲገኙ አድርጓቸዋል።
ዋና ነገሬ ያለው እኔና ፈጣሪ ጋር ነው በማለት በእረፍት እንኑር።

© ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ
@psychoet
‹‹ በዚኽች ምድር በቢሊዮን የሚቈጠር ሰው አለ፤ ፈጣሪ አንዱንም ሰው ያለ ምክንያት አልፈጠረም፡፡ ኹሉም ሰው በዐላማ መልካም ሥራ እንዲሠራ በዚኽም ምድር ላይ ተደስቶ እንዲኖር ተፈጥሯል፡፡ ሕይወታችንም የሚለካው በኖርንበት ዐላማ እንጂ በኖርንበት ዕድሜ ብዛት አይደለም፡፡››

ሜሎሪና ቴሎስ
አንተ የአላማ ሰው ነህ!
አንቺ የአላማ ሰው ነሽ!
"... የህይወትን አላማ የተረዳ ሰው የሚኖረው ለመብልና ለመጠጥ ሳይሆን ለህሊናው ነው።

ብዙ ሰው #ህሊናውን_ሸጦ #ለሆዱ_ያድራል

በዚህ አለም የሚኖርበትን አላማ የተረዳ ሰው ህሊናውን ከሆድ ፣ ከስልጣን ፣ ከዝና ጋር አያወዳጅም ።
ህሊናው የሚገዛው ስለተፈጠረለት አላማ ፣
#ለእውነትና_ለፍትህ ብቻ ነው ። ..."

ሜሎሪና - ቴሎስ

መልካም ቀን 💚


መልዕክቱን ቢያንስ ለ5 ጓደኞቻችን እናጋራ
የምትወዱትን ለማግኘት

በጠላችሁት ላይ ትዕግስት

ይኑራችሁ።
@psychoet
ትስማማላችሁ?
በህይወታችሁ ትልቅ የምትሉት ነገር ምንድነው?
እኔ: ጌታዬ ጥያቄ ልጠይቅህ?

ፈጣሪ: ትችላለህ፤ ጠይቀኝ ።

እኔ: ዛሬ ይሄ ኹሉ ችግር እንዲደርስብኝ ለምን ፈቀድክ? ዛሬ እንደማትወደኝ ገባኝ

ፈጣሪ: ልጄ፣ ዛሬ ምን መጥፎ ነገር ደረሰብህ?

እኔ: ዛሬ ስንት የስራ ቀጠሮ እያለኝ አርፍጄ ተነሳሁ ይሄ ሳያንስ እየሮጥኩ ታክሲ ለመያዝ ስከቹል መኪና ጭቃውን ረጭቶኝ ልብሴ ተበላሸ፡፡ በፍጥነት ወደ ቤት ተመልሼ ልብሴን ቀይሬ ስመጣ ደግሞ የታክሲው ሰልፍ እረጅም ኹኖ ጠበቀኝ ።

ፈጣሪ: እሺ ሌላስ?

እኔ: በመንገድ እያለሁ ስልኬ ዘጋ?

ፈጣሪ : እሼ ልጄ አሁን ሁሉንም ላብራራልህ ፡፡ ዛሬ ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነሳ የሞት መልአክ በቤት መጥቶ ነበር እኔ ግን በሕይወት እንድትኖር አንዱን መልአኬን ልኬ ላንተ እየተዋጋልህ ነበር፡፡ ይሄ እስኪያልፍ እንቅልፍ ጣልኩብህ

እኔ : እሺ 😔

ፈጣሪ፡ ታክሲ ቶሎ እንዳትይዝ ያረኩት ደግሞ የምትሄድበት ቦታ ቀድመክ ከደረስክ ሊደበድቡህ ስለነበር ያስረፈድኩህ ብዙ ሰዎች እስኪሰበሰቡ ድረስ ነው፡፡

እኔ : እሺ 😔

ፈጣሪ: ስልክህ እንዲዘጋ ያረኩት ደግሞ ለአንተ በሀሰት ደውለው ከዛ ንግግርህን በመቅዳት በፍርድ ቤት ሊከሱህ የፈለጉ ሰዎች ስለነበሩ ከነሱ ልጠብቅህ ነው፡፡

እኔ: ጌታ ሆይ እባክህ ይቅር በለኝ😢

ፈጣሪ: እሺ ልጄ ግን በማረገው ነገር ኹሉ እኔን እመነኝ ፡፡ ላንተ የማደርገው ኹሉ ለመልካም ነው፡፡

እኔ: አምንሀለው ጌታዬ

ፈጣሪ: እኔ ላንተ ያለኝ ሀሳብ ካንተ ሀሳብና እቅድ በላይ እንደሆነ አትጠራጠር፡፡

እኔ: አልጠራጠርም ጌታዬ ዛሬ ስለሆነው ነገር ኹሉ አመሠግናለሁ ፡፡ እንደምትወደኝ አሁን አወኩ።

ስለመልካምነቱ ፈጣሪያችንን እናመስግን!
መልዕክቱን ለሌሎችም እናጋራ
www.tg-me.com/psychoet
ሶሻል ፎቢያ (Social phobia)
---------------------------------------
ሶሻል ፎቢያ  ያለባቸው ሰዎች ሌሎች ሰዎች ባሉበት ዘና ማለት አይችሉም፡፡ ሌሎች ሰዎች የእነሱን ንግግር ወይም ድርጊት የሚገመግሙና የሚተቹ ስለሚመስላቸው ይፈራሉ፡፡ስህተት እንዳይሰሩና እንዳይዋረዱ ስለሚፈሩ ዘና ብለው እንደሚፈልጉት ከሰዎች ጋር መጫወት ይከብዳቸዋል ፡፡

አብዛኛው ሰው ካልለመደው ሰው ጋር ሲሆን የአለመመቸት ስሜት ይፈጠርበታል፡፡ ሶሻል ፍቢያ ሲሆን ግን ፍርሀቱ በጣም የበዛ ይሆናል፡፡ ሶሻል ፎቢያ ያለባቸው ሰዎች አብሯቸው ያሉ ሰዎች ሲጫወቱ ፣ሲስቁ ፣ሲያወሩ እነሱ መሣተፍ ስለማይችሉ ብቸኝነት ይሰማቸዋል፡፡
ብቻቸውን ግን አይደሉም፡፡ ከአስር ሰው አንዱ ተመሣሣይ ሁኔታ ውስጥ ነው፡፡ ነገ መንገድ ላይ ሲሄዱ አስር ሰዎች ይቁጠሩ ከዛ ውስጥ አንዱ ሶሻል ፍቢያ አለበት/አለባት፡፡

የሶሻል ፎቢያ ምልክቶች በጥቅቱ፦

-ከቤት ውጪ ምግብ ባይበሉ ይመርጣሉ፡፡ለብቻቸው ሬስቶራንት ገብተው፣ ባዶ ጠረጴዛ ፈልገው፣ 'ያ ሁሉ ሰው' እያያቸው መመገብ ይከብዳቸዋል፡፡
-ዝግጅቶች ላይ በግድ ነው የሚገኙት (እሱንም ከተገኙ!)-እስከቻሉት ድረስ ምክኒያት ፈጥረው ለመቅረት ይሞክራሉ፡፡
-በአብዛኛው የድካም ስሜት ይሰማቸዋል፡፡
-ሰዎች ሲሰበሰቡ ከመጨነቅ ጋር ተያይዞ ልብ ቶሎ ቶሎ መምታት፣ ትንፋሽ ቁርጥ-ቁርጥ ማለት፣ ማላብ
- ነገሮች እጅግ አስከፊ ሊሆኑ እንደሚችሉ በማሰብ መጨናነቅ ፣እንቅልፍ ማጣት
- የፍቅር ቀጠሮች ላይ (በተለይ የመጀመሪያዎቹ ላይ) ምን እንደሚባል አለማወቅ...

ከላይ የተዘረዘሩትን ሶሻል ፎቢያ ያለባቸው ሰዎች ይረዱታል፡፡ ሌሎች ግን ቀለል አድርገው ሊያዩት ይችላሉ፡፡ ሶሻል ፎቢያ ተማሪዎች እውቀት እያላቸው ጥሩ ውጤት እንዳይኖራቸው፤ ሰራተኞች ችሎታ እያላቸው የሚገባቸውን እድገት እንዳያገኙ፣ እንዲሁም ለሚወዱት ሰው ፍቅራቸውን መግለፅ እንዳይችሉ ያደረጋል፡፡

ሶሻል ፎቢያን ማሸነፍ ይቻላል ነገር ግን ትዕግስትና ቁርጥኝነት ይጠይቃል፡፡

በራሳችን ልናደረግ የምንችለው
1. ሀሣብን መገምገም፦ በሶሻል ፎቢያ የሚቸገሩ ሰዎች ጭንቀትን የሚያባብሱ ሀሳቦች አላቸው፡፡
ለምሳሌ ፡- ፡"እንደ ሞኝ መቆጠሬ አይቀርም፡፡" "መናገር ስጀምር ድምፄ ይንቀጠቀጥና ራሴን አዋርዳለሁ፡፡ " "አንደፈራሁ ሰዎች ያውቁብኛል፡፡" እነዚህን ሀሣቦች መገመገምና መሞገት ጭንቀቱን ይቀንሣል፡፡
2. ከሰዎች ጋር ሲሰበሰቡ ሌሎች ላይ ማተኮር፤ በራስ ጭንቀት ከመጠመድና ፍርሃትን ስለመሸፈን ከመጨነቅ ሌሎች ሰዎች የሚያደርጉትና  የሚናገሩት ነገር ላይ ማተኮር ጭንቀትን ይቀንሳል ፡፡ ሰዎች በአብዘኛው የሚያስቡት ስለራሳቸው ስለሆነ የሚገምተውን ያህል መፍራታችንም አያውቁም፡፡
3. አተነፋፈስን ማስተካከል - በፍርሃት ጊዜ በአብዛኛው  ከላይ-ከላይና ቶሎ-ቶሎ ነው የሚተነፈሰው ፡፡ ይህ ጭንቀትን ያባብሳል ፡፡- በቀስታ በጥልቀት መተንፈስ  ረጋ ያለ ስሜትን  ይፈጥራል ፡፡
4. አነቃቂ ነገሮች የጭንቀት ስሜትን ስለሚያባብሱ እነሱን መቀነስ፡፡
እነዚህ ተደረገው አሁንም ስሜቱ ካለ የህክምና እርዳታ ያስፈልገዋል፡፡

ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!!!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው
ሰዎች ስለእኛ በሚያስቡት ነገር ላይ መጨነቅን ለማቆም ቀላል ዘዴዎች
Telegram www.tg-me.com/psychoet

‘’የማይባል ነገር ተናገርሁ እንዴ? እንዴት እንደዚህ አደርጋለሁ? ሰዎች እኮ መሃይም :ገገማ:የሚያናድድ ሰው ነው/ነች ይሉኝ ይሆናል’’  እያልን ራሳችንን የምናስጨንቅ ስንቶቻችን ነን! ሌሎች ሰዎች ስለእኛ በሚያስቡት ነገር ላይ በመጨነቅ አእምሯችንን በጨለማ ቦታ እንዲንከራተትና ራሳችንን በመጠራጠር የስጋት ስሜት እንዲሰፍንብንና እንዳንረጋጋ እያደረግን መሆኑን ልናውቅ ይገባል:: ለነገሩ ሁላችንም ሰዎች ስለእኛ ያላቸው ሃሳብ/አስተያየት ምን ይሆን ብለን መጨነቅ እንደሌለብን እናውቃለን ወደ ተግባር ለመቀየር  ግን ስንቸገር እንታያለን:: ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዘዴዎች ብንጠቀምባቸው ይረዱናል!

1. የሰዎችን አዕምሮ ማንበብ እንደማንችል መረዳት፡- እስኪ ሰዎች ስለእኛ የሚያስቡትን በእርግጠኛነት ማወቅ እንችላለን? ብዙ ጊዜ ነገራትን ሳናጣራ ይሆናል በማለት ብቻ ማወቅ እንደምንችል ነው የምናስበው ይህ አስተሳሰባችን ደግሞ ለህይወታችን ፀር ወደሆኑ ድምዳሜዎች/ዉሳኔዎች ይመራናል::ስለዚህ እነዛ ሰዎች ሃሳባቸውን የሚገልጹበትን ዕድል አግኝተው ሃሳባቸውን እስካልገለጹልን ድረስ ስለምን እንደሚያስቡ ማወቅ በፍጹም አንችልም፡፡

2. በቋሚነት ለሚጠቅመን ነገር መስራት:- ከሌሎች  ሰዎች የሚሰነዘሩ  የኩነኔ አስተያየቶች በእርግጥም እኛን ይጎዱናል ነገር ግን ከእነዚህ ሰዎች የሚመጣውን አሉታዊ ምላሽ በመፍራት የምናጣቸው/የምናሳልፋቸው መልካም ዕድሎች ጥለውብን ከሚያልፉት የአእምሮ ጠባሳ አይበልጥም፡፡ እነዚህ የኩነኔ/አሉታዊ አስተያየቶች የሚያደርሱብን ጉዳት ቅጽበታዊ ሲሆን ባጣናቸው/ባመለጡን መልካም ዕድሎች ምክንያት የሚደርስብን ጸጸትና ቁጭት ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ስር እየሰደደና እያደገ ነው የሚሄደው፡፡ ስለዚህ በቋሚነት የሚጠቅመንን ነገር ለማግኘት ጊዜያዊ የሆኑ ተቀባይነት ማጣትን ለመቀበል ፈቃደኞች እንሁን::

3. ራስን ከመኮነን/በራስ ላይ ከመፍረድ መቆጠብ:- እስኪ ሰዎች ምን ይሉን ይሆን ብለን የምንጨነቅበትን ሃሳብ ለሰከንድ ቆም ብለን እናስበው! በእርግጠኝነት እኛ ለራሳችን የምናስበውን ነገር ላይ ነው ሌሎችም እንደዚ ያስባሉ ብለን የምንሰጋ፡፡ ስለዚህ በራሳችን ላይ መፍረድን አቁመን(ራስን ከመኮነን ተቆጥበን) እኛነታችንን ከተቀብለነው ወይም ለራሳችን ጥሩ ግምት ከሰጠን ሌሎቹ ስለእኛ ለሚሰጡት/ለሚያስቡት ሃሳብ ፍርሃትና ስጋት አይኖረንም ማለት ነው፡፡

4. ሌሎች ሰዎችን መኮነንን/በሌሎች ላይ መፍረድን ማቆም፡- ሰዎችን እየገመገምን፡እየኮነንና እየፈረድንባቸው የምንኖር ከሆነ እነሱም በተመሳሳይ ሁኔታ እንደሚፈርዱብን ነው የምናስበው፤ ስለዚህ በእነሱ ላይ ከመፍረድ ይልቅ ህይወታችንን ለማሻሻልና ለማደራጀት እንደሚያግዙን ቆጥረን ብናደንቃቸውና ብናበረታታቸው የበለጠ ተጠቃሚዎች መሆን እንችላለን፡፡

5. ስለእኛ አለመሆኑን መረዳት፡- ሰዎች በራሳቸው እይታ ከደረሰባቸው ክስተት፡ ቁስል፡ ፍራቻና እንከን የተነሳ ለነገሮች የተለያዩ አሉታዊ ምላሾችን ይሰጣሉ ነገር ግን የእነሱ ምላሽ ከእኛ ጋር የሚገናኝ እንዳልሆነ ልብ ልንል ይገባናል፡፡ ለምሳሌ የሆነ ቢዝነስ ለመጀመር ብንወስንና አንድ ሰው ”እመነኝ ይህንን ስራ ከጀመርህ በሚቀጥሉት ወራት አሊያም ዓመታት ምንም  ዓይነት የእረፍት ጊዜ አይኖርህም” ቢል ሰውዬው የተናገረው ቢዝነስ መጀመር ላይ ያለውን ሃሳብ/አመለካከት እንጂ እኛን በተመለከተ እንዳልሆነ ለይተን መረዳት ይጠበቅብናል::

6. በሚያስደስተን ነገር ላይ ትኩረት ማድረግ:- ይህን ባደርግ ሰዎች ይፈርዱብኛል በማለት የሚያስደስቱንን ተግባራት ከማድረግ የምንገደብ ከሆነ(የማኅበረሰቡን እሴቶች በጠበቀ መልኩ) ጊዜያችንን ምንም ዓይነት ጥቅም በሌለው ጭንቀት እያባከንነው መሆኑን እናስተውል፡፡ ስለዚህ በህይወታችን ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት የሚችለውን ብርቅ የሆነውን አቅምና ኃይላችንን በመሸርሸር ፈንታ እኛን በሚያስደስቱን ነገራት ላይ ትኩረት ልናደርግ ይገባል፡፡

7. የሚያውኩንን ነገሮች መለየት፡– ሌሎች ሰዎች አሉታዊ በሆነ መልኩ ይገመግሙናል/ይፈርዱብናል ብለን የምንጨነቀው ምናችንን በተመለከተ ነው? በስራችን ሁኔታ: ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነት: ምናልባትም በክህሎታችንና ነገሮችን በመመርመር ባለን አቅም ሊሆን ይችላል:: ስለዚህ በውስጣችን መረጋጋት እንዳይኖር የሚቀሰቅሱ ነገሮችን መለየትና ማሻሻል ከቻልን ማሻሻል አሊያም እንዳሉ መቀበል ያስፈልጋል:: ምክንያቱም ከሁኔታዎች ጋር ሰላም መፍጠር ከቻልን የሰዎች አጸፋዊ ምላሽ አያስጨንቀንም ማለት ነው::

8. ራሳችንን መቀበል:– ፍጹም አለመሆናችንን፡ እንከንና ድክመቶች እንዳሉን መቀበል ነገር ግን አቻ የሌለን(ልዩ) በዓለም ላይ እኛን የሚመስል ሰብዕናና ተሰጥኦ የታደለ ሰው እንደሌለና ወደፊትም እንደማይኖር ልናስተውል ይገባል፡፡

9. አጸፋዊ ምላሾችን መጠበቅ/ተስፋ ማድረግ፡- በሰዎች ዘንድ የሚፈጠረውን አጸፋዊ መልስ በመፍራት ፈንታ ያ ምላሽ ሊፈጠር እንደሚችል አስቀድመን ተስፋ ማድረግ አለብን(የሰዎችን ስሜት ለመቀስቀስ መፍራት የለብንም) ምክንያቱም በሰዎች ዘንድ አሉታዊም ይሁን አዎንታዊ ምላሽ መፍጠር ካልቻልን ምናልባትም ራሳችንን የመሆን ድፍረቱን ልናጣ እንችላለንና፡፡

10. እየኮነኑን/እየፈረዱብን ነው ብለን ካሰብናቸው ሰዎች ጋር ማውራት፡- እንዲያው ሁኔታዎች ተመቻችተውልን ስለእኛ መጥፎነት ያስባሉ/እየፈረዱብን ነው ብለን ከምናስባቸው ሰዎቸ ጋር ተቀራርበን ብናወራ እስከምንገረም ድረስ ምንም ባለጠበቅነው ሁኔታ አዕምሯቸው በብዙ ጭንቀቶች እንደተሞላ ልናውቅ እንችላለን፡፡ ማን ያውቃል ልክ እኛ እንደምንጨነቀው እነሱም ሌሎች ሰዎች ስለእነሱ ምን ሊያስቡ/ሊሉ በሚችሉት ሃሳብ እየተጨነቁ ሊሆን ይችላል እኮ፡፡ ስለዚህ ራሳችንን ግልጽ በማድረግ ከእነዚህ ሰዎች ጋር ተቀራርበን ሃሳብ ማንሸራሸር ያስፈልጋል::

በአጠቃላይ ከላይ የተዘረዘሩትን ሃሳቦች ወደ ተግባረ ከቀየርናቸው እኛም መቀየር እንችላለን!

©Zepsychologist
Telegram www.tg-me.com/psychoet
2024/09/29 04:21:28
Back to Top
HTML Embed Code: