Telegram Web Link
🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔

ኦ አባይ  ሀገር በሀኪ ኢትዮጵያ 
ሀገረ  ነጎድጓድ ሀገረ እግዚአብሔር

ተንስኢ ወልበሲ ሀይለ እግዚአብሔር  እስመ ተንስኡ ፀላእትኪ ወአብቀዋ ኦሙ ላይለ ህዝብኪ

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

#መልካም እለተ ይሁንልን

ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ

ከ40 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን አሰርተው ሀገረ ስብከታቸው በዘንድሮ ቀይረዋል በረከትዎ ትድረሰን ተጉህ እረኛ ብፁዕ አባታችን።

@ortodoxtewahedo
† ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል †

የደብረ ገሊላ አማኑኤል ካቴድራል የተተከለው በ1905 ዓ.ም በልጅ ኢያሱ ዘመነ መንግሥት ነው። የመጀመሪያውን መቃኞ ያሰሩት ፊት አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሲሆኑ ጽላቱም በጎንደር ክፍለ ሀገር የነበረና ከዚያ መጥቶም በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የተቀመጠ ነበር።

ታድያ ፊት አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ያሰሩት የመጀመርያው መቃኞ ለአገልግሎት ምቹ ስላልነበር ሁለተኛ መቃኞ ድጋሚ ተሰርቶ ታቦቱ እንዲገባ ተደርጓል።

ንግሥት ዘውዲቱ በግንቦት 28 በ 1914 ዓ.ም የአማኑኤል በዓል ተገኝተው ሲያስቀድሱ ምርጊቱ ተደርምሶ ሲወድቅ በማየታቸው ሦስተኛ መቃኞ እንዲሰራ አዘዙ። የደብሩ አስተዳዳሪ በጊዜው የተክለ ሃይማኖትን ቤተ ክርስትያንም አንድ ላይ ያስተዳድሩ የነበረ በመሆኑ ንግሥቲቷ የቤተ መንግስታቸውን አጣኝ የመጀመርያው አስተዳዳሪ ሆነው ደብሩን እንዲጠብቁ አደረጉ። አለቃው ሦስተኛውን መቃኞ አሰርተው ታቦቱ ወደ ተዘጋጀለት መቃኞ ገባ።

በ1920 ህዝቡ እየበዛ በመምጣቱ አገልግሎቱ እንዲሰፋ ስላስፈለገ በንግሥት ዘውዲቱ አማካኝነት አዲስ ሕንጻ ቤተ መቅደስ ግንባታ ተጀመረ። በ1931 ታህሳስ 28 ቀን ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ታቦቱ ወደ መንበሩ ገብቷል። ንግሥት ዘውዲቱ ፍጻሜውን ሳያዩ ያረፉ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ደግሞ ክብ ቅርጽ ነበረው።

አሁን ያለው ቤተ ክርስቲያን በጥር 28 ቀን 1969 ዓ.ም በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው የተጀመረ ሲሆን የወቅቱ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ በነበሩት በሊቀ ሊቃውንት ንቡረ ዕድ አባ ተፈራ መልሴ አስተባባሪነት በምእመናን ርብርብና በቅዱስ አማኑኤል አከናዋኝነት ግንቦት 28 ቀን 1978 ዓ.ም ተጠናቆ ታቦተ ህጉ ወደ ህንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብቷል።

@ortodoxtewahedo
"የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን" የተባለው ስብሰባ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ማግለሉ ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ አስታውቋል!

@ortodoxtewahedo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ስሙት ብዙ ታተርፉበታላቹ እጮኝነት ላይ ላላቹ እና ገና
ለምትይዙ በእውነት ቃለህይወት ያሰማልን አባታችን ።

@ortodoxtewahedo
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ሰማይና ምድር የረጋበት ቀን

#እርገት

እርገት፦ በአካል፣በመንፈስ እና በነፍስ ወደላይ መውጣት ነው
እርገት፦የነፃነት እና የድል ምልክት ነው
እርገት፦ዘለዓለማዊነት ነው
እርገት፦ናፍቆት ነው
እርገት፦ ተስፋ ነው
እርገት፦ መለኮታዊ ተአምር ነው
እርገት፦ ምስጢር ነው
እርገት፦ ክብር ነው
እርገት፦ የኛ ማረግ ማረጋገጫ ነው
እርገት፦የመንፈሳዊነት እጣነ ሞገር ነው

ሰውየው "ዛሬ የሚከበረው በዓል ትርጓሜው ምንድን ነው" ይለዋል ሰውየው መልሶ ይህንን አታውቅም? ዛሬማ "ሰማይና ምድር የተረጋጋበት ቀን" ነዋ አለው ይባላል ብዙ ጊዜ የኛን ያለማወቅ ወደሌሎቹ ጭምር የምናስተላልፈው በልበ ሙሉነት እና በድፍረት ጭምር ነው"ይህንን አታውቅም?" ማለቱ ሲገርም ያስተላለፈው የተሳሳተ መልእክት ደግሞ ሌላ ትግርምት ይፈጥራል።

በሆነ አጋጣሚ ዐውደ ምሕረቱ ተሰጥቶን ማይክ ከጨበጥን በኋላ ከዐውደ ምሕረቱ ሥር የተቀመጡት ሁሉ ምንም የማያውቁ እየመሰለን የእግዚአብሔር ሳይሆን የግል ስሜታችንን የምንገልጽባቸው አጋጣሚዎች እጅግ ብዙ ናቸው ይህ አጋጣሚ ታላላቅ ስህተቶች የሚፈጽሙበት አጋጣሚ ነውና ለሰሚ ጆሮዎች መጠንቀቅ ይገባል ይኸው ዛሬ ድረስ የእርገት በዓል ሲከበር "ሰማይና ምድር የረጋበት" የሚለው የነ......ትምህርት በልበ ቀሊላን ፀርፆ ግራ እያጋባን ይገኛል።


ሉቃስ 24፦
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵⁰ እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።
⁵¹ ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ።
⁵² እነርሱም፤ ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥
⁵³ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ።

@ortodoxtewahedo
Audio
አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ

Size:-38.8MB
Length:-1:51:17

   በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedo
Audio
የዕርገት መንገድ
        
Size:-54MB
Length:-2:34:56

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedo
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

የአብርሐምን ቤት የባረኩ ሥላሴ እኛንም በህይወታችን በኑሮዋጭን በአገልግሎታችን በትዳርአችን በትምርታችን በሥራችን ይባርኩን ።

ሥሉስ ቅዱስ ለሚታምን ሁሉ እምነትን በረከትን ሀገራችን ኢትዮጽያን ሰላም ያድርጉልን አሜን ::

#መልካም እለተ ይሁንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
.
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው
========================

ሰኔ 7/2016 ዓ.ም (የጋ/አ/ዞ/ሀ/ስ አርባምንጭ )

በጋሞ እና አካባቢው ዞኖች አህጉረ ስብከት በአርባ ምንጭ ከተማ በደብረ መ/መድኃኔዓለም ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ከሰኔ 7-9/2016 ዓ.ም የሚካሄደውን ታላቅ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ ተጋባዥ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና መምህራነ ወንጌል እንዲሁም ዘማሪያን በዛሬው እለት ወደ አርባ ምንጭ ሲገቡ በጋሞ አባቶች እና በርካታ ቁጥር ባላቸው ማህበረ ምዕመናን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

@ortodoxtewahedo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የመምህር ተስፈየ አበራ ትምህርቶች የምትቀበሉ እና ትክክል አይደለም የምትሉ በኦርቶዶክሳዊ ጨዋነትና በመረጃ ሀሳብ ስጡ ????

@ortodoxtewahedo
“በጋሞ የሚገኙ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ለመርዳት፣ ባህሉን ለማጠናከር የምታደገርጉት ሥራ ሁሉ የሚያስመሰግን ነው፡፡ ለሰው በሚገባው በራሱ ቋንቋ ማስተማር የሚያስደስት ነው፡፡”
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል አስተባባሪ የተመሠረተበትን 24ኛ ዓመት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ አከበረ፡፡
ዘጋቢ መ/ር ጌታቸው በቀለ
(#EOTCTV ሰኔ ፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም )
+++++++++++++++++++++++++++++++++++ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር አገልግሎቱን እያካሄደ የሚገኘው የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል ማስተበባበሪያ የተመሠረበት ዋና ዓላማ በጋሞ የሚገኙ የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን ለመርዳት፣ ስብከተ ወንጌል በጋሞኛ ቋንቋ ለማስፋፋት በመሆኑ፤ የተመሠረተበትን ፳፬ ኛ ዓመት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት ሰኔ ፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ አክብሯል፡፡
በዕለቱም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ባስተላለፉት መልእክት “የ፳፬ኛ ዓመት በዓላችሁን ለማክበር በመብቃታችሁ እንኳን አደረሳችሁ፤ እንኳን ደስ አላችሁ” ብለዋል፡፡ ቅዱስነታቸው አያይዘውም “በጋሞ የሚገኙ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ለመርዳት፣ ባህሉን ለማጠናከር የምታደገርጉት ሥራ ሁሉ የሚያስመሰግን ነው፡፡ ለሰው በሚገባው በራሱ ቋንቋ ማስተማር የሚያስደስት ነው፡፡ የጀመራችሁትን የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን መርዳት፣ በጋሞኛ ቋንቋ ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት የምታደርጉትን በጎ ሥራችሁን ቀጥሉበት፤ እግዚአብሔር የሚወደው ይህን ሥራ ነው፡፡ እናንተ አሁን የምትሠሩትን ሥራ ልጆቻችሁም የእናንተን ፈለግ ተከትለው በበጎ ነገር እንዲሠማሩ አስተምሯቸው፡፡” በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላለውፈዋል፡፡
የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል አስተባባሪ ኮሚቴ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊ አገልግሎት እንዲሟላ፣ የአገልጋዮች ደመወዝ በወቅቱ እንዲከፈል፣ ፈዋሽ የጠበል ቦታዎች ይዘታቸውን ጠብቀው እንዲቀጥሉ፣ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃቸውን በጠበቀ በዘመናዊ ሕንጻ እንዲገነቡ እያደረገ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል አስተባባሪ ኮሚቴ በስብከተ ወንጌልም ምእመናን በሚገባቸው በጋሞኛ ቋንቋ ወንጌል በማስተማር፣ መዝሙር በማስጠናት ሰፊ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ በቋንቋው የሚያስተምሩ መምህራን ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ እንዲሁም በየሰንበት ትምህርት ቤቶች የተማሩ ደቀመዛሙርት በየጉባኤያቱ እና ማኅበራት ጋር እየተገኙ እንዲያስተምሩ እየተደረገ መሆኑን በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
በገዳማትና አድባራት በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ጋሞኛ ክፍል በአዲሱ የቤተክርስቲያን ሥርዐተ ትምህርት መሠረት ከ1ኛ-8ኛ ክፍል ከአንድ ሺህ አንድ መቶ በላይ በተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ቤታቸው የፈረሰባቸውን ጉባኤያትና አባላት መልሶ ከማቋቋም አንጻር በዚህ ዓመት እንጦጦ እና አካባቢው አንድ፣ አየር ጤና እና ጀሞ ሦስት፣ ሸገር ከተሞች ሁለት ጉባኤያት መልሰው እንዲቋቋሙ ማድረጋቸውን የቀረበው ሪፖርት ያስረዳል፡፡

@ortodoxtewahedo
2024/07/01 10:06:59
Back to Top
HTML Embed Code: