Telegram Web Link
✞ ተፈጸመ✞

"ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19: 30)

ተፈፀመ የሚለው ቃል ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ነፍሱን ለወዳጆቹ ሲሰጥ ከመሞቱ በፊት የተናገረው የመጨረሻ ቃል ነው። " ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19: 30)። ተፈፀመ በግሪክ "ቴትለስታ'ይ" (τελείωσε /Tetelestai) ማለት ሲሆን ትርጉሙም ወደ ፍፃሜ ማምጣት፣ መጨረሻ መድረሱን፣ ማከናወንን ፣ ማለቅን የሚያሳይ ነው። በእርግጥ አማኑኤል TETELESTAI/ ተፈፀመ ሲል ምኑ ይሆን የተፈፀመው? ብሎ የሚጠይቅ ህሊና ያስፈልገናል።

አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ አባቱ የሰጠውን ስራ ለመስራትና ለመፈፀም አምላክነቱን እንደመቀማት ሳይቆጥር በአባቱ በራሱና በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ወደ ዓለም እንደመጣ አስታውቆናል። ከመጣም በሇላ አባቱን የሚያከብር ስራን ሰርቷል "እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ" (ዮሐ 17: 4) እንዲል። ሊሰራ የመጣው የጠፋነውን የሰው ልጆች ሊፈልግና ሊያድን ዘንድ ነው ። በምድር ሲመላለስ የስራው ፍፃሜ የነበረውንም ነፍሱን ስለወዳጆቹ በመስጠት ፈፀመው ። ክርስቶስ ተፈፀመ ሲል የሽንፈት ቃል አይደለም የድልና የአሸናፊነት እንጂ ወደ ዓለም የመጣሁበትን ስራ በሞት ጨረስኩ፣ ህዝቦቼን በሞት አዳንኩ ፣ የኃጢአትን ኃይል ድል ነሳሁ ፣ በሞቴ ሞትን ገደልኩ ፣ በመከራዬ ለመንግስቴ ህዝብን ማረኩኝ ሲል ተፈፀመ አለ እንጂ!

የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ተፈፀመ ብሎ ስለሞቱ ሲናገር "በሞቱ ሞትን ያጠፋው እርሱ ነው፡፡ ሲኦልንም የበዘበዘው እርሱ ነው" አለ።

የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስና ሐዋርያው የነበረው ቅዱስ አትናቴዎስ ስለዚህ ድንቅ ነገር በድርሳኑ ‹‹ነፍሱን ከሥጋው በለየ ጊዜ ያን ጊዜ በሲኦል ፈጥኖ ብርሃን ታየ፡፡ ጌታችን በአካለ ሥጋ ያይደለ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ሔደ፡፡ ሲኦል ተነዋወጠች፤ መሠረቶቿም እፈርስ እፈርስ አሉ፡፡ ምድርን ያለ ጊዜዋ እንዳታልፍ ክብርት ደሙን በምድር ላይ አፈሰሰ፡፡ ከኅልፈት ጠበቃት በእርሷ ያለውንም ዂሉ ጠበቀ፡፡ ስለ ፍጥረት ዂሉ ሥጋውን በመስቀል እንደ ተሰቀለ ተወው፡፡ ነፍሱ ግን ወደ ሲኦል ወረደች ከዚያ ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን አዳነች፤ ሲኦልንም በዘበዘች፡፡ ፍጥረትንም ዂሉ ገንዘብ አደረገች፡፡ ሥጋውም በመቃብር ያሉ ሙታንን አስነሣ፤ ነፍሱም በሲኦል ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን ፈታች፤›› እያለ ያወሳል።

በአማን ኢየሱስ ክርስቶስ ተፈፀመ ሲል አስቀድሞ የገባው የአድናችኋለሁ ተስፋ አርብ ተፈጸመ ፣ የሴቲቱ ዘር የእባቡን ራስ እንደሚቀጠቅጥ የተነገረው ተስፋ ተፈጸመ ፣ የኩነኔና የእርግማን ዘመን በሞቱ ተፈጸመ (ገላ 4፥4) ፣ የእግዚአብሔፍ ፍቅር በመስቀል ሞት ፍጹም ሆኖ በመገለጥ ተፈጸመ/ ተከናወነ/ ፣ እኛ እንጸድቅ ዘንድ የኃጢአት ቅጣት በመስቀል ላይ ተፈጸመ ፣ ወደ ሰማይ እየወጣ በአምላካችን ፊት ይከሰን የነበረው የዲያቢሎስ የክስ መብት በክርስቶስ ሞት ተፈጸመ። ዛሬ ይከሰን ዘንድ ወደ ሰማይ ቢወጣ በጌታ በኢየሱስ እጆች ላይ የሚታዩ ችንካሮችና በልብሱ ላይ የሚታየው የደም ነጠብጣብ አፉን ይዘጋዋል። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ገብቶ የነበረው ጥል በራሱ በጌታችን አስታራቂነት ለአንዴ ተፈጸመ። የሚሰሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ማለቱ ለእንዴና ለዘላለም የእግዚአብሔርን ምህረት የምናስታውስበት ድምጽ ሆነ ። የበረታ ጌታ ሁላችንንም በቸርነቱ አዳነን እርሱ ተፈፀመ ሲል የኛ ደስታ ፣ የኛ መዳን ፣ የኛ ተስፋ ፣ የኛ መቤዠት በእግዚአብሔር ወልድ በተፈፀመልን የዘላለም ኪዳን ደም መፍሰስ በእውነት ተፈጸመ!!!

ለታረደው በግ ለእርሱ መጀመሪያ ከሌለው አባቱ ጋርና ቅዱስ፣ መልካምና ህይወት ሰጪ ከሆነው መንፈስ ቅዱስ ጋር ክብር ሁሉ ይገባዋል። አሁንና ለዘላለም ለትውልደ ትውልድ አሜን!

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
#ጌታችን በመስቀሉ ከ6-10 ሰዓት በመስቀልላይ ሳለ የተፈጸሙ 7ቱ
ተአምራቶች፤

1ኛ. ፀሐይ ጨለመች
2ኛ. ጨረቃ ደም ሆነች
3ኛ. ከዋክብት ብርሃናቸውን ነሱ
4ኛ. የቤተመቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተከፈለ
5ኛ. ዐለቶች ተሰነጣጠቁ
6ኛ. መቃብራት ተከፈቱ
7ኛ. የሞቱት ተነሡ፤ ማቴ.27፤45-46

ጌታችን ከ6-9 ሰዓት በመስቀል ላይ ሳለ የተናገራቸው 7ቱ የፍቅር
ቃላት

1ኛ.ኤሎሄኤሎሄ ኤልማስላማሰበቅታኒ ማቴ.27፤46
2ኛ. እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትኖራለህ፡፡
ሉቃ.23፤43
3ኛ.አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራእሰጣለሁ፡፡ ሉቃ.23፤46
4ኛ.አባት ሆይየሚያደርጉትን አየውቁምናይቅር በላቸው፤ሉቃ.2334
5ኛ. እናትህ እነኋት፤ እነሆ ልጅሽ፤ዮሐ.19፤26-27
6ኛ. ተጠማሁ፤ ዮሐ.19፤30
7ኛ. ተፈጸመ፤ ዮሐ.19፤30

13ቱ ሕማማተ መስቀል

1ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)
2ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)
3ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይመውደቅ)
4ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድመረገጥ)
5ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋርመላተም)
6ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)
7ኛ. ተቀሰፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)
8ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)
9ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)
10ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)
11ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)
12ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይመሰቀል)
13ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትንመጠጣት)
ስብሐትለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱድንግል
ወለመስቀሉክቡር


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👆👆👆👆👆👆👆👇👇👇
#ሕማሙን ልናገር

#ሊቀ መዘምራን ይልማ ሀይሉ

ሕማሙን ልናገር *አንደበት ቢያጥሩኝም*/2/
መቼም ምንም ቋንቋ *ለዚህ አይገኝም*/2/
ከረጂሙ በጭር *ከሰፊው በጠባብ*/2/
ስለከፈለልኝ *ስለጌታ ላስብ*/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
በጌቴሴማኒ *በአታክልቱ ቦታ*/2/
ምድሪቷ ተሞልታ *በታላቅ ጸጥታ*/2/
የአዳምን ልጅ ስቃይ *በደሉን ሊሸከም*/2/
ጌታችን አዘነ *ተጨለቀ በጣም*/2/
ሐዋርያት ደክመው *ተኝተው ነበረ*/2/
ይሁዳ ከአይሁድ *እንደተማከረ*/2/
ጭፍሮች እየመራ *ጌታውን ሊያስገድል*/2/
የተሠራለትን *ቸርነት ሳይቆጥር*/2/
ፋና እያበሩ *ጭፍሮቹ ሲመጡ*/2/
ጌታን ሊያንገላቱት *እንደዚያ ሲቆጡ*/2/
የአምላኩን ጠላቶች *መንገድ እመራ* /2/
ይሁዳ ብቅ አለ *ከቀያፋ ጋራ* /2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
ላቡ ከግንባሩ *እንደ ውኃ ሲወርድ*/2/
በታላቅ ይቅርታ *ጌታችን ሲራመድ*/2/
ምስኪኖችን ሊያጠግብ *ድሆችን ሊታደግ*/2/
ኢየሱስ ቀረበ *እንደሚታረድ በግ*/2/
ይሁዳ ጉንጮቹን *ሳመው በክህደት*/2/
የተማከረውን *የማያውቅ መስሎት*/2/
የአይሁድም ጭፍሮችም *ያዙት ተናጠቁት*/2/
በታላቅ ጭካኔ *በሰንሰለት መቱት*/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
በጲላጦስ ችሎት *አቁመው ከሰሱት*/2/
ንጹሑ እየሱስ *ይሙት በቃ አሉት*/2/
እጆቹን ቸንክረው *በጠንካራ ብረት*/2/
በእፀመስቀሉ *ቀራንዮ ዋለ*/2/
ወልደ እጓለዕመኅያው *ተጠማሁ እያለ*/2/
ሐሞት እና ከርቤ *ቀላቅለው አጠጡት*/2/
እረ እንዴት ጨከኑ *በምሬት ላይ ምሬት*/2/
------------------------------------------
ሕማሙን ልናገር አንደበት ቢያጥሩኝም
መቼም ምንም ቋንቋ ለዚህ አይገኝም
ከረጂሙ በጭር ከሰፊው በጠባብ
ስለከፈለልኝ ስለጌታ ላስብ
አዝ . . . . . . . . . . . //
ፍጥረታት ተጨንቀው በአይሁድ ክፋት
በየተፈጠሯቸው እርቃሉን ሸፈኑት
ጨረቃ ደም ሆነች ፀሐይም ጨለመች
አልፋና ኦሜጋ ተሰቅሎ ስላየች
ከዋክብት እረግፈው ምድር ተናወጠች
መባርቅትም ታዩ ተቆጣ ባሕሩ
መለሳቸው እንጂ ስለፈጹም ፍቅሩ/2/
ከወንበዴ ጋራ ከመሀል አድርገው
ጌታን አንገላቱት በመስቀል ላይ ሰቅለው
በቀኝ የነበረ ወንበዴው ለመነው
በመንግሥትህ ጌታ አስበኝ እያለው
አዝ . . . . . . . . . . . //
ከመስቀሉ በታች ዮሐንስን አየው
እስከመስቀል ድረስ ስለተከተለው
ታላቋን ስጦታ እናቱንም ሰጠው
ተፈፀመ አለ ጌታ ህይወቱን ሰጠ
ሞትንም ከሕዝቡ በፍጹም ቆረጠ/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
እንደተለመደው ዲያቢሎስ ቀረበ
ነፍሳትን ለመብላት እርሱ እንደተራበ
ፍጡር መስሎት ነበር በመስቀል ላይ ያለው
በአራቱም ማዕዝን በንፋስ ወጠረው
በሲኦል ወረደ በኃይሉ ብርሃን
ማረከ ጌታችን የአዳም ልጆችን
በሦስተኛውም ቀን ጌታችን ተነሳ
ሞትን ድል ያረገው የይሁዳ አንበሳ
በቃ ተወገደ የሰው ልጅ አበሳ /2/


#ሼር_share በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት የጠበቁ ፅውፎች ለማንበብ ሆነ ለመማር፡፡

ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

💠 http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💠
💠 http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💠
💠 http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💠


እግዚአብሔር ሃገራችንን እና ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን የእመቤታችን ምልጃና ጸሎት አይለየን ።
#ጌታ ሆይ

#ሊቀ መ ዘምራን ኪነጥበብ
......
ጌታ ሆይ
አይሁድ አማፅያን ሰቀሉህ ሆይ
የአለም መድሐኒት የአለም ሲሳይ ሰቀሉህ ሆይ
የአለም መድሐኒት የአለም ሲሳይ ሰቀሉህ ሆይl
የአዳም በደል
አደረሰህ አንተን ለመገደል
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት
......
ንፁህ ክርስቶስ
ሆንክ ወንጀለኛ ብለህ ስለኛ
መስቀል አሸክመው አስረው ገረፉህ እያዳፉህ
መስቀል አሸክመው አስረው ገረፉህ እያዳፉህ
ግብዞች
እንደራሳቸው መስሏቸው
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ
......
እጅህና እግርህ
በችንካር ተመታ የአለም ጌታ
የሾህ አክሊል ደፋህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ
የሾህ አክሊል ደፋህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ
በመስቀል ላይ
ተጠማሁ ስትል ታላቅ በደል
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው
......
ይቅር ባይ
ግልፅ በደላችን ሁሉን ሳታይ
አንተው ይቅር በለን በእኛው ሳትከፋ እንዳንጠፋ
አንተው ይቅር በለን በእኛው ሳትከፋ እንዳንጠፋ


👇👇👇👇👇
👉 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 👈
☝️☝️☝️☝️☝️☝️
#እውነት_ስለሆነ

#ሊቀ መ ዘምራን ይልማ ሀይሉ

እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ 
ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ 
የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው 
ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/ 

ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም 
ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም 
ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል 
ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/ 

የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ 
ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ 
እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት 
ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/ 

ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት 
ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት 
ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው 
መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/ 

ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው 
አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው 
ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ 
ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/

💚 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💚
💛 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💛
❤️ https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo ❤️
#አልፋና ኦሜጋ

አልፋና ኦሜጋ ፈጣሪ የሆንክ
በካሃዲዎች እጅ ተይዘህ ቀረብክ

ተገፋህ ተደፋህ በጥፊ ተመታህ
እየደበደቡ ክርስቶስ ሆይ አሉሀ
ጽድቅን ስለ ሠራህ በወንጌል ከሰሱህ
ለአዳም ልጅ ብለህ ብዙ ተንገላታህ
………አዝ…………..
ቅዱሳን እጆችህ የፍጥኝ ታስረው
እንደ በግ ተጎተትክ ልትመራቸው
የትም ቦታ ያለህ ሁሉን የምታውቅ
ፊትህን ሸፈኑህ ለመመጻደቅ
………አዝ…………..
በዓውደ ምኲናን ከጲላጦስ ፊት
አሳልፈው ሰጡህ አጋልጠው ለፍርድ
ከሐና ቀያፋ ከመሳፍንቱ ደጅ
ከሄሮድስም ዘንድ አቀረቡህ በዋጅ
………አዝ…………..
ግርፋት ሕማሙ አልበቃ ብሎህ
በመስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ
ሳዶርና አላዶር ዳናትና አዴራ
ተፈልገው መጡ ለችንካር በተራ
………አዝ…………..
የሰላም ባለቤት ደረትህ ተወጋ
ሊያያዝ በችንካር እጅህ ተዘረጋ
ግፈኞች አሁዶች በአንተ ላይ ቀለዱ
ምራቅን ተፉብህ እራስህን ሊጎዱ፤

👇👇. 👇👇👇
👉 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo👈
☝️☝️☝️☝️☝️☝️
ኦ አርምሞ ዘመጠነ ዝ አርምሞ ?
ኦ ትዕግስት ዘመጠነ ዝ ትዕግስት?
ኦ ሂሩት ዘመጠነ ዝ ሂሩት ?
ኦ ፍቅር ዘመጠነ ፍቅረ ሠብ ?
( ይህን ያህል ትዕግሥት እንደምን ያለ ትዕግሥት ነው ? ይህን ያህል ዝመታ እንደምን ያለ ዝመታ ነው ? ይህን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር ነው ?

ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo
"አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ"

2ኛ ቆሮ 5 : 4

@ortodoxtewahedo
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉኅን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እና የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይ በትናንትናው ዕለት ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚገኙ አሳውቀን ነበር።

በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን እየገለጽን፣ ይህነ ላደረገ ሁሌም ለማይተወን ቸር አምላካችን ምስጋና እናቀርባለን።

በዚህ አጋጣሚ በሂደቱ በቀና መንፈስ ለተባበሩን የተለያዩ አካላት እንዲሁም አጣዳፊ ምላሽ ለሰጡን የመንግሥት የጸጥታ አካላት እናመሰግናለን።

በተጨማሪም በትዕግሥት ስትከታተሉና በጸሎት ስታስቡ ለነበራችሁ አባቶች፣ ምእመናን እና የማኅበረ ቅዱሳን አባላት እያመሰገንን፣ በዓሉ የሰላምና የበረከት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።

ማኅበረ ቅዱሳን!

@ortodoxtewahedo
የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለት (የድኅነት ቀን) በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ቅዱስ ፓትርያርኩ እና አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከናወነ ።

@ortodoxtewahedo
📖ቅዳሜ ቀዳም ስዑር ትባላለች ፦

ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል።
ለምለም ቅዳሜ ይባላል፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል።u

📖ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡-

ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።

   < ወስብሐት ለእግዚአብሔር >

👉 @ortodoxtewahedo
2024/09/27 23:21:08
Back to Top
HTML Embed Code: