Telegram Web Link
ስለ ድንግል ብሎ
ዝማሬ ዳዊት On Telegram
#ስለ_ድንግል_ብሎ

ስለ ድንግል ብሎ ኢትዮጵያን ይጎብኛት
ድሮስ ከአምላክ በቀር ይህች አገር ምን አላት
በሠራዊት ብዛት መች ትጠበቃለች
በቅዱሳን ጸሎት እሳት ካልታጠረች(፪)

ዓለም ሸምቆባት አህዛብ ይስቃል
በልጆችሽ ዕንባ አውሬው ይቀልዳል
ታልቅ ሕዝብ መሆኑን ማን በነገራቸው
ከዘመናት በፊት አምላክ የጎበኘው(፪)
#አዝ
እውነተኛ ዕንባ ፈለቀ ከምድር
በፍጡራን ዋይታ ፍጹም ብትማረር
ዕንባና ደማችን ተደባልቆ ፈሷል
አምላክ ቅጣት ይብቃን አሁን ይቅር በለን(፪)
#አዝ
ቅዱሳንን መንቀፍ ወገኔ ተውና
ይልቅ ስለነሱ የጽድቅ ጎዳና
በረድኤታቸው በክብራቸው ጥላ
እንከተላቸው ከፍቅራቸው ኋላ(፪)

ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ

"ኢትዮጵያ እጆቿን
ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች"
መዝ ፷፯፥፴፩

✥••┈••●◉ ✞ ◉●••┈••✥

@ortodoxtewahedo

✥••┈••●◉ ✞ ◉●••┈••✥
#ስለ_ድንግል_ብሎ

ስለ ድንግል ብሎ ኢትዮጵያን ይጎብኛት
ድሮስ ከአምላክ በቀር ይህች አገር ምን አላት
በሠራዊት ብዛት መች ትጠበቃለች
በቅዱሳን ጸሎት እሳት ካልታጠረች(፪)

ዓለም ሸምቆባት አህዛብ ይስቃል
በልጆችሽ ዕንባ አውሬው ይቀልዳል
ታልቅ ሕዝብ መሆኑን ማን በነገራቸው
ከዘመናት በፊት አምላክ የጎበኘው(፪)
#አዝ
እውነተኛ ዕንባ ፈለቀ ከምድር
በፍጡራን ዋይታ ፍጹም ብትማረር
ዕንባና ደማችን ተደባልቆ ፈሷል
አምላክ ቅጣት ይብቃን አሁን ይቅር በለን(፪)
#አዝ
ቅዱሳንን መንቀፍ ወገኔ ተውና
ይልቅ ስለነሱ የጽድቅ ጎዳና
በረድኤታቸው በክብራቸው ጥላ
እንከተላቸው ከፍቅራቸው ኋላ(፪)

      ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ

       "ኢትዮጵያ እጆቿን
ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች"
         መዝ ፷፯፥፴፩

✥••┈••●◉ ✞ ◉●••┈••✥
      
@ortodoxtewahedo

✥••┈••●◉ ✞ ◉●••┈••✥
#ፈረንሳይ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስትያን ።

@ortodoxtewahedo
አቡነ አብርሃም

የእውነት አባት በረከቶ አትለየን ።

“እስከ ትበጽህ ለሞት ተበዓስ በእንተ ጽድቅ እስመ እግዚአብሔር አምላክከ ይትበአስ
በእንቲአከ”

“እስክትሞት ለእውነት ታገል። እግዚአብሔር ላንተ ይታገልለሀልና”

           ሲራክ 4 ፡ 2

@ortodoxtewahedo
" ሊቀ ካህናት " ጌታቸው ዶኒ ማን ነው ???

የጳጳሱ የአቡነ ጎርጎርዮስ ምስክር ሆኖ በ 250,000 ብር ክፍያ ሊመሰክር የመጣው ሰው ማን ነው ???

ለቤተ ክርስቲያን ከሰይጣን እኩል ጠላቷ የሆነ ሰው ለጳጳሱ ለአቡነ ጎርጎርዮስ ወዳጅ እንዴት ይሆናል ???


#ETHIOPIA | ~ ኦሮምያ ~ ምሥራቅ ሸዋ ~ መቂ

ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ውጭ የሲዳሞ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሆኖ በቀድሞው ፓትሪያርክ በአቡነ ጳውሎስ እስከመሾም የደረሰ ፣ የራሱን ሃይማኖት በኦሮምያ ክልል እስከማቋቋም የደረሰ ፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ ምክትል ሓላፊ ሆኖ ተመድቦ እስከመሥራት የደረሰ ፣ የደብረ ገነት ቁስቋም ማርያምን ጨምሮ በደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል፣ በማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም፣ በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና በአየር ጤና ኪዳነ ምሕረት ተመሳሳይ በዕልቅና ተሹሞ አብያተ ክርስቲያናቱን ለምዝበራና ለትርምስ የዳረገ ግለሰብ ነበር ጌታቸው ዶኒ ።

~ ጌታቸው ዶኒ የቀድሞው ሟቹ ፓትሪያርክ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ወዳጅ የአርቲስት መሀሙድ አህመድ የአንድ ዘመን ሚስት የነበረችው የወሮ እጅጋየሁ አማካሪም ነበር ።

በአሁኑ ወቅትም በቤተክህነት ውስጥ ቁጭ ብሎ ነገር የሚሠራውና በሴራ ፖለቲካ የሚተበትበው የፋንታሁን ሙጬም አማካሪና የሙስና አካፋዩ በመሆን እነ በጋሻው ደሳለኝና ያሬድ አደመንም አባ ጳውሎስ ጋር በማቅረብ እንዲሸለሙ በማድረግ ያንንም ፎቶ በማንሳት ምእመናንን በማደናገር እነ በጋሻውም የምእመናንን ገንዘብ ዘርፈው የሲዲ ፋብሪካ እንዲያቋቁሙ ያደረገ ግለሰብ ነው ።

~ በሽሮሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በነበረበት ወቅት፣ የወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ ተከታይና የእምነቱ አስተማሪ ለመኾን የአባልነት ማመልከቻ የጠየቀበት ደብዳቤ፤ በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በነበረበት ወቅት ደግሞ፣ “የቅን ልቦና መንፈሳዊ የፈውስ አገልግሎት ማኅበር” በተሰኘ የኑፋቄ ተቋም፣ በፍትሕ ሚኒስቴር አስመዝግቦ የሚንቀሳቀስበት የሚኒስትሪ ፈቃድ በግንቦት 2004 ዓ.ም. የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ በማስረጃነት ቀርቦበት፣ ሃይማኖቱ እና ሃይማኖተኝነቱ ጥያቄ ቢነሣበትም ይቅርታ ጠይቋል ተብሎ በሥራ መመደቡ የሚታወስ ግለሰብ ነው ።

~ በቃሊቲ ደብረ ገነት ቁስቋም ማርያም እያለ፣ የቀድሞውን ፓትርያርክ ሐውልት በቦሌ መድኃኔዓለም ካቆሙት ግንባር ቀደም የኮሚቴው አባላት አንዱ በመኾን በጥፋት ተግባሩ ዘወትር ቅድስት ቤተክርስቲያንን ሲያቃጥል ፣ ሲያተራምስና ሲለበልብ ሲያደማትና ሲያቆስላትም የኖረም ግለሰብ ነው ።

~ በመጨረሻም አሁን በቅርቡ ከደብረ ይድራስ ቤቴል ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተባረረ በኋላ ወደ ሀገሩ በመሔድ የአባቴ ቤተክርስቲያን ነው በሚል የመቂ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን ገንዘብ በግልጽ ሲካፈል የኖረም ግለሰብ ነው ።

~ አሁን ይህ ግለሰብ የተያዘበት እና በቁጥጥር ስር የዋለበት መንገድም የእግዚአብሔር ድንቅ ተአምራቱ የተገለጸበትም ነበር ።

~ ከቤተክርስቲያን አካባቢ እንዲርቅ መደረጉ ያንገበገበው ጌታቸው ዶኒ ጥቅሙ ስለተቋረጠበት እረፍት ነስቶት በብዙ መልኩ አዲሱን አስተዳዳሪና በህዝብ የተመረጠውን የሰበካ ጉባኤ አባላት በተለያየ መልኩ ሲረብሽ ይቆያል ።

አንድ ጊዜ የተቃዋሚ አባላት ናቸው እያለ ለመንግሥት ሲከሳቸው እሱ አልሠራና አልይዝ ሲለው ደግሞ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከገጠር ድረስ ገብቶ " ቄሮዎችን " በማምጣት " ኦሮሞ የሆነ አማኝ ከሚካኤል እንዳይቀበር " ኮሚቴዎቹ ከልክለዋል በማለት ኮሚቴዎችን እና ቄሮዎቹን ለማጣላት ያላደረገው ጥረት አልነበረም ።

~ በመጨረሻም የጌታቸው ዶኒን መሠሪ አካሔድ ሲያጠና የቆየው ፖሊስ ጌችን በቁጥጥር ስር አውሎት ነበር ።

~ ሟቹ አባ ጳውሎስ በመቂ ከተማ ከሙዳየምጽዋት ተመዝብሮ በብዙ ሚልየን ብር የተገነባውን የጌታቸው ዶኒን መኖሪያ ቤት ለመመረቅ ያለ አጃቢ ፖሊስ ወደ መቂ ሲሔዱ ሞጆ ላይ የኦሮሚያ ፖሊስ አስቁሞ ለክልሉ ፖሊስ መረጃ ሳይደርሰው እንዴት እንደ ተራ ግለሰብ ብቻዎትን በሹፌር ይመጣሉ በማለት አስጠንቅቆአቸው እንደነበርና በጉዞአቸውም ለሚደርስባቸው ችግር ሓላፊነት እንደማይወስድ ጭምር አሳስቧቸው እንደነበር አይዘነጋም ።

~ አሁን አባ ጳውሎስ የሉም ። በጋሻውና ያሬድ አደመም የሉም ።

~ ጌታቸው ዶኒም የለም ነበር ለጳጳሱ ለአቡነ ጎርጎርዮስ ምስክር ሊሆን 250,000 ብር ተከፍሎት ሊመሰክር መጠራቱ የሚያሳዝን የሚያስለቅስ ነው ንግግሩን ሲጀምር እንኳን አማትቦ መጀመር የማይችል የአይጥ ምስክር ዲንቢጥ ነው ነገሩ የቤተ ክርስቲያን ጠላት የአቡነ የጎርጎርዮስ ወዳጅ መሆኑ እጅግ በጣም አሳፋሪ አሸማቃቂ ከመሆኑ በላይ ጳጳሱ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶችን አደራጅተው አቅፈው በማኖር እሳቸው ላይ ህዝቡ ጥያቄ ሲያነሳ ለራሳቸው የውሸት ክብር ሲሉ እንዲያስጥሏቸው ሲሉ ተዋህዶን ክብሯንና ልዕልናዋን አዋረዱት ዳግመኛ የወጓት ደጋግመው እንዲወጓት ከማድረግ አልፈው አብረው ወጓት ።

~ እንኳን የቅዱስ ሲኖዶስ ልዑክ እድርም ቃለ ጉባኤ አለው!!!!!!!

~ እኛ ሀገረ ስብከቱ በደብዳቤ ነው የወከለን እናንተን ማን ወከላችሁ፤ህዝብ የወከላችሁ መሆኑን መረጃ አቅርቡ------ (ጌታቸው ዶኒ)

~ እኛ የወከልነው ሃይማኖታችንን ነው ፤ደብዳቤያችን መሃተባችን ነው ፤ውክልናችንም ክርስትናችን ነው------ (የሀገር ሽማግሌዎች)

~ ቃለ ጉባኤ እንድንይዝ ቅዱስ ሲኖዶስ አላዘዘንም---- አባ ቃላ ጽድቅ አጣሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ
ውይይት በቃለ ጉባኤ ነው የሚታሰረው ሁለታችሁም ተስማምታችሁ የጋራ ቃለ ጉባኤ ለመያዝ ሞክሩ ---- (የመንግስት ታዛቢ አካል)

~ የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጉዳይ እንዲያጣሩ የተመደቡት አባ ቃለ ጽድቅና ሌሎች አጣሪ ኮሚቴዎች የማጣራት ሂደቱን ያለ ቃለ ጉባኤ እና ቪዲዮ ቀረጻ ካለ ማጣራቱን አናከናውን በማለት የሀገረ ስብከቱን ችግር ያለ ቃለ ጉባኤ በወሬ ብቻ ሰምተው ለመሄድ ማሰብ እንደ ድፍረት ነው የሚታየው፡፡

~ አባ ቃለ ጽድቅ በዛሬው ውሎ የሀገረ ስብከቱን ነገረ ለማጣራት ሳይሆን ችግር ለመፍጠር ሲሞክሩ ነበር የዋሉት ፡፡ በተለይም አቡነ ጎርጎርዮስ ችግራቸውን በጌታቸው ዶኒ ውዥንብር ለማለፍ ቢሞክሩም ጉዳዩ ግን በጽኑዓን ምዕመናን ብርቱ ጥረት በቅድመ ሁኔታው ባለመስማማት ማጣራቱ ሳይከናወን ተለያይተዋል፤ የማጣራት ሂደቱም ተቋርጧል፤በቀጣይ ለቅዱስ ሲኖዶስና ለመንግስት የማሳወቅ ሂደቱ ይቀጥላል፡፡

~ የአቡነ ጎርጎርዮስ የአስተዳደር በደል የሚያሳየው በሀገረ ስብከቱ በአቡኑ በኩል ተወካይ ሆነው የቀረቡት ፓስተር ድጋፌ፤ፓስተር ጌታቸው ዶኒ፤ፓስተር ይታገሱ፤አባ ላይከ ማርያም፤አቶ ግርማ መጎስ እና ሌሎች በምዝበራ እና በአስተዳዳር ችግር የአንበሳውን ድርሻ ሲወጡ የነበሩ ሲሆን ቅድስት ቤተክርስቲያን ምን ያክል በደል እየተፈጽመባት እንዳለ የሚያስረዳ ነው፡፡

~ በቀጣይ በሀገረ ስብከቱ ያሉት ምዕመናን በሁሉም አጥቢያ በመቀናጀት ቤ/ክን ከእንደዚህ አይነቶች ለመታደግ ልንቀናጅ እና ፍትህ ፤ቤ/ክን ለሀገር ሠላም የነበራትን ድርሻ እንድትወጣ ለማድረግ ሁላችንም ኃላፊነት እንዳለብን ልናውቅ ይገባል፡፡

በሀገረ ስብከቱ ስር ያሉት ካህናት እና መነኮሳት በሀገረ ስብከቱ ተስፋ መቁረጣቸውን ሲናገሩ ሰምተናል፡፡
በተለይም ሀገረ ስብከቱ በመናፍቁ ጌታው ዶኒ ሲወከል እና እነ አባ ላይከ ቤ/ክን ሲዘርፉ ኖረው ዛሬ ደግሞ ዓይናቸውን በጨው ታጭበው ከካህናት ፊት ቆመው ሲያስተባብሩ ማዬትን ያክል አሳፋሪ ተግባር የለም ይላሉ አባቶች ፡፡

ከ300 በላይ አጥቢያ ካህናት እና ምዕመናን ባሉበት ለምን ከሌላ ሃይማኖት ደጋፊ ማምጣት አስፈለገ !!!!!!!!!!!!

እውነት እርሳቸው የሁሉም አባት ከሆኑ ፤መልካም አስተዳዳር ከፈጸሙ ፤ለገጠር ቤ/ክን ከተጨነቁ እንደውም የአዱላላ ከሊበን ወረዳ የመጡት ስለቤ/ክን ውይይት አለ ተብለው ነው የመጡት ድጋሜ ቢጠሩ መልካም ነው ጉዱን እናያለን እያሉ ይገኛሉ ፡፡

የውሽት ስራ አስኪያጅ ፡- በሞጆ፤በዝዋይ፤እና በሊበን ታዲያ እውነት መቼ ይገለጥ ለእውነት መቆም ከማን እንማር፤ለቤ/ክን ችግር መድረስ ሲገባችሁ ለሰው ዘብ መቆም እስከ መቼ ይሆን፤ስንት የሚስተምራው በማጣት ከቤ/ክን እየወጣ ውሸት መደገፍ !!!!!!!!

ማስጠንቀቅያ፡- ለአንዳንድ አዳማ ማዕከል ማኅበረ ቅዱሳን አባላት እየተደረገ ያለውን የማጣራት ሂደት አቡነ ጎርጎርዮስ እንዳነሱ ነገሩ በሽምግልና እንዲታይ እያደረጋችሁ ያላችሁትን እንቅስቃሴ እያየን እንገኛለን ይህ ተግባር ዋጋ ያስከፍላችሃል!!!!!!!!

ሰምታችሃል ዋጋ ያስከፍላችሃል !!!!!!

እኛ ከማኅበሩ ጋር ምንም ቅሬታ የለንም አርፋችሁ አገልግሎታችሁን ብቻ አከናውኑ!!!

አለበለዚያ ግን ዋጋ ትከፍላላችሁ፡፡ ቤ/ክን በችግር ውስጥ እያለች፤ፍትህ ጠፍቶ፤ሌብነት ስራ ሆኖ፤በጎጥ ስራ መቀጠር የዕለት ተዕለት ተግባር ሆኖ፤ክብረ ክህነት እየኮሰሰ ፤ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነው መሪ እቅድ እነዳይተገበር እየተደረገ ታዲያ ምን የሚሉት ነው አንዳንድ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ጉዳዩን በሽምግልና አቡነ ጎርጎሪዮስን እንዳይነሱ ለማድረግ የምታደርጉትን አቁም አቁሙ ብለናል !!!!!!!!!


ሁሉም ቤተክርስቲያንን እንዳደሙ አይኖሩም ። አንድ ቀንም አይኖሩም ። ቅድስት ቤተክርስቲያን ግን ሁሉን አሳልፋ እሷ ትኖራለች ። እውነታው ይኸው ነው ።

~ ወዳጄ እግዚአብሔር አይጣላህ ። እሱ ዝም ሲልህ እንደሌለ ልትቆጥር ትችላለህ ። ብታውቅበት ዝምታውና ትእግስቱ አንተን ለንስሃ ሲያዘጋጅህ ፣ ዕድልም ሲሰጥህ ነው። በዕድሉ አልጠቀም ካልክ ግን ያው አርጩሜውን ይቆርጥና ዋጋህን ይሰጥሃል ዛሬ የሳቅከው የውሸት ሳቅ ነገ መቅሰፍትን ማምጣቱን እንዳትረሳ በየ ቤታችሁ መቅሰፍት ይወርድባቹሀል በልጆቻችሁ እና በቤተሰቦቻችሁ ላይ ቁጣው ይደርሳል አከተመ ።

~ ጦማሩን #SHARE በማድረግ በጌቾ የቆሰሉ የተዋሕዶ ልጆች አሁንም ስራችሁን አልጨረሳችሁምና አሁንም ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚያደርሰው በደልና ግፍ እንዲደርሳቸው እናድርግ #COMMENT በመስጠትም የልብ የልባችንን እናውጋ ።


@ortodoxtewahedo
ይህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ምቹ ጊዜ ነው ...ብጹዕ አቡነ ሩፋኤል
***

ይህ ዘመን ለቅድስት ቤተክርስቲያን በአራቱም ማዕዘን የመከራ ዶፍ የሚዘንብባት ምቹነት ርቆ የጸናበት የሰማዕትነት እና የስደት ዘመኗ ነው።

ቅድስት ቤተክርስትያን አሁን ላይ ራሄላዊ ሆናለች። ሄሮድስ የገነነባት የኢየሩሳሌም እናቶችን መስላለች።

መኖኮሳት በበዓታቸው የሚረሸኑበት ዘመን የቤተክርስቲያን ምቹ ዘመን ነው ከተባለ ይህን ምቹነት ከረሻኙ ወገን ላሉ ሰልፈኞች ብቻ ነው።

የእረኝነት መንበር እንደ አሜባ ተፈጥሮ ተበጣጥሶ ባለአስኬማ የሆኑ ኖላውያን በዘር ኩሬ ውስጥ ወድቀው የሚንቦራጨቁበት ዘመን የቤተክርስቲያን ምቹ ዘመን ነው ከተባለ እግዚኦታ ይገባናል።

የመቅደስ መቃጠል፣የምዕመናንን ስደት እና ሞት፣የክብረ ክህነት ሹፈት የበዛበት ይህ ዘመን የቤተክርስቲያን ምቹ ዘመን ነው ከተባለ ቤተክርስቲያን በዘመኗ ምቹ ዘመን አላየችም ማለት ነው።

በጹጹስና ስም ደምወዝ እየበሉ፣ቀሚስ እያጠለቁ፣አስኬማ እየደፉ፣በትረ ሙሴ እየጨበጡ ለቄሳራውያን የሚያደላ የስብከት ከንፈር ለያዙ ሰዎች ይህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ሳይሆን ለእነርሱ ምቹ ነው።

ሟች የበዛበት ዘመን ለገዳይ እና እንጅ ለምስኪኖች ምቹ አይደለም። ርሃብ እና ስደት በጸናበት ትውልድ ለአሳዳጅ እና ለሚያገሳው እንጅ ለተጎሳቃዮች ምቹ አይደለም።

ግፍ የጸናበትን ዘመን ማውገዝ ቢያቅት እንኳን ዝም ማለት ማንን ጎዳ

እግዚአብሔር ይቅር ይበለን !!!

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

@ortodoxtewahedo
ውበቱን አድንቀን የማንጨርሰውን ዓለማት በፈጠረ አምላክ ፊት እንኳ ፥ ቅዱሳን ሲናገሩ የሰማነው “በታላቅ ድምፅም እየጮኹ፦ ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ፥ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም ደማችንንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም?” ሲሉ እንጂ ፥ እፁብ ድንቅ ስለሆነው ውብ ዓለማት ከሚፈሰው ደም በፊት የአድናቆት መዝሙር ሲዘምሩ አይደለም።(ዮሐ ራዕ 6፥10)።

በደም በጨቀየ ሀገር ውስጥ ፥ ንጹሐን እንደ በግ ከሚታረዱበት የተሰበሰቡ አባቶች ስለአንድ ሙዚየም በሀገር መሪ ፊት እንዲህ መናገር ምንኛ ያሳፍራል! ለመንጋው ጠባቂ የተባሉት እረኞች ፥ የልጆቻቸው ስቃይ ሳይሆን በከተማ መኃል ስላዩት ውበት ተናግሮ ዝም ማለት እንደምን አስቻላቸው?! ለመሪውስ መስማት የሚወደውን የሚነግሩት ወይስ እውነትን የሚያጋፍጡት እንደ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የበለጠ ወዳጆቹ ናቸው?

©ሙሉዓለም ጌታቸው

@ortodoxtewahedo
የእረኝነታቸውን ብኩርናቸውን በምስር ያልሸጡ አባት..
***

አሸርጋጅ አጎብዳጅ በበዛበት በእዚህ በእሾህ ዘመን ያለአንዳች አባት ያልተወን ቅድስት ሥላሴ የተመሰገነ ይሁን።

እረኛ ያልነው አካል አስብቶ ለአራጅ የሚሰጥ ሻጫ አጋፋሪ ሆኖ በተገለጠበት በእዚህ ትውልድ እንደ አብርሐም አባትነትን ያልናቀ እረኛ መኖሩ ተመስገን ያስብላል።

ብጹዕ አቡነ አብርሐም

በረከትዎ ትድረሰን !!!


@ortodoxtewahedo
"ይህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ምቹ ጊዜ ነው "የሚሉ ሆድ አደሮች የበዙበት ጊዜ ስለሆነ ይህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ፈታኝ ጊዜ ነው ፡ስለዚ ከምንጊዜውም በላይ ጠንካራ አንድነት ያስፈልገናል ። የቤተ ክርስትያንን ደሞዝ እየበሉ ለመንግስት የሚሰሩ ሆድ አደሮች በዝተዋል ።

@ortodoxtewahedo
ክብረ ክህነት ላይ ማመጽን እንደ ጸጋ የተያያዙ
***

ካህናት የመላእክትን አገልግሎት የተጋሩ የእግዚአብሔር አይኖች ናቸው። የእግዚአብሔር ምህረትን እና ቸርነት የሚመላለስባቸው ነው።

ያለክህነት እና ካህናት ምስጢራት መፈጸም አይቻልም። ያለክህነት እና ካህናት ቤተክርስቲያንንም ጭምር ማሰብ አይቻልም።

በትረ ክህነት የጨበጡ እጆች አጋንንትን እየቀጡ ኀጢአትን የሚያቀልጡ ናቸው፡፡ በዓለም ኖረው ዓለምን የሚያክሙ ሀኪሞች ጭምር ናቸው። ዳሩ ግን እነርሱ እየታመሙ ጤነኛዎችን የሚያመረቅዙ ሆኑ እንጅ።

ካህናት ህዝብ እና አህዛብን ወደ እግዚአብሔር እና ወደ መንግስቱ ያቀርባሉ፤ የመንፈስ ልጆቻቸውን በርህራሄ ይጠብቃሉ፡፡ በለመለመ መስክ፣ በጠራ ውኃ በንጽሁ የዕረፍት ስፍራ ያሠማራሉ፡፡

የኤልያስ መንፈስ በኤልሳዕ እንደሰራ ፣የሙሴ ጸጋ በኢያሱ እንደጸና ዛሬም የሐዋርያት መንፈስ በሀዲስ ኪዳን ካህናት ላይ ይሰራ ዘንድ የታመነ ጸጋ ነው።

በአንብሮተ እድ ፣ በንፍሐት እፍታ መንፈስ ቅዱስ የጸጋዎች ሁሉ ቁንጮን ለሰው ልጆች እያቀበለ ርህራሄውን በክህነት ጸጋ ተመልክተናል

ይህን ጊዜ በምድርም በሰማይም ያስሩ ይፈቱ ዘንድ ስልጣንን ይጨብጣሉ።የአምላክ ሥጋና ደምን በመሰዊው ላይ ያቀርባሉ።

ይህ የክህነት ጸጋ በትውልድ መሃል እንዲረክስ ቆብ ያጠለቁት በትጋት እየሰሩ ነው። እረኞች ጭካኔን ከተኩላ በላይ ገልጠው ክህነት እና ካህናትን አምርረው እንዲጠሉ እየተደረጉ ነው።

በአጭሩ የቅድስት ቤተክርስቲያን አይተኬ ጸጋ ተከርሽሮ እንዲነቀል ቀሚስ ባደረጉ ቆብ ባጠለቁ የስም እንጅ የግብር ካህነት በነጠፈባቸው ሰዎች እየተሰራ ነው።

ይህ ዘመን ግዙፍ የእግዚአብሔር ቸርነት ካልታከበት የሚመጣው ነገር እጅግኑ ያስፈራል።

መሰረት መናድ ላይ ከቤተክህነትም ከቤተመንግስትም እየተሰራ ይገኛል
ደገኛው መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ ስምህን ውሰድ

ምን ጉድ ነው የገጠመን.. .!!
ለመንጋው የማይራራ የቤተክርስቲያን መከራ የማይታየው እንዴት አባት ሊባል ይችላል ::

በሰሜን በደቡብም በምስራቅም በሁሉም አቅጣጫ የሚገደል ኦርቶዶክስ ዘመኑ ምቹ ነው እያላቹ የመንጋው ጠባቂነቱ ዝም ያላቹ አባቶች ታሪክ ይፋረዳቹዋል ። የዝቋላ አባቶች የቆሉ ተማሪዎች ደም ሳይደርቅ በየሰከንዱ ጉድ ምንሰማበት ዘመን ቤተ ክርስትያን በታሪክ ጥቁር በለበሰችበት ዘመን ።

" በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።

ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ። "

ሐዋርያት 20 : 28

@ortodoxtewahedo
2024/09/29 21:37:31
Back to Top
HTML Embed Code: