Telegram Web Link
የዐቢይ ጾም ሳምንታት
(የመጀመሪያው ሳምንት)  

+++++++++++‹ዘወረደ›+++++++++++

ትርጕሙ ‹ከሰማየ ሰማያት የወረደ› ማለት ነው፡፡ ከሰማየ ሰማያት የወረደውን፣ ከድንግል ማርያም የተወለደውን በጥንት ስሙ ወልድ፣ ቃል በኋላ ስሙ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ አማኑኤል የተባለውን ሰው የኾነውን አምላክ ለማመስገን ርደቱን (ከሰማየ ሰማያት መውረዱን) ለመዘከር የሚጾም ጾም ነው፡፡

ጌታችን ጾመ ከማለት አስቀድሞ ከሰማየ ሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን መናገር አስፈላጊ ነውና የመጀመሪያው ሳምንት ‹ዘወረደ› ተብሏል፡፡ ‹‹አንተ በሰማይ ወአንተ በምድር ወአንተ በባሕር ወአንተ በየብስ፤ አንተ በሰማይ አለህ፤ በምድር በባሕርም በየብስም አለህ፤›› የተባለውን በሰማይ በምድር ምሉዕ የኾነውን አምላክ ‹ወረደ፤ መጣ› ብሎ መናገር ‹ሰው ኾነ› ማለት ነው፡፡

ሰው ኾኖ መገለጡን ለማስረዳት ነው እንጂ መውረድ መውጣት የሚባሉ ቃላት በዅሉ ምሉዕ ለኾነው መለኮት አይስማሙትም፡፡ ቃላቱ ሰውኛ አነጋገርን የሚያመለክቱ ናቸውና፡፡ መተርጕማን አበው ‹‹‹ዘወረደ› ማለት ‹ሰው የኾነ› ማለት ነው›› ብለው ይተረጕማሉ፡፡ አምላካችን ሰው ከኾነ በኋላ ‹መጣ፤ ሔደ፤ ወረደ፤ ዐረገ› የሚሉ ቃላት ይስማሙታል፡፡

ምልዓቱን ሳይለቅ በሰው አካል ተወስኖ ታይቷልና፡፡ ስለዚህ ‹ወረደ› እግዚአብሔር ሰው ኾኖ መገለጡን፤ ‹ዐረገ› ደግሞ የሰውነቱን ሥራ መፈጸሙን ያሳያል፡፡ ዐረገ ስንልም ቀድሞ በሰማይ የለም ለማለት አይደለም፤ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመለኮቱ በዓለሙ ዅሉ ምሉዕ ነውና፡፡

ጾሙን ሐዋርያት፣ ስያሜውንና የምስጋናውን ሥርዓት ቅዱስ ያሬድ አዘጋጅተዋል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ነቢያትን በንባብ፤ ሐዋርያትን በስብከት፤ ሊቃውንትን በትርጓሜ፤ መላእክትን በዜማ ይመስላቸዋል፡፡ ቅዱስ ያሬድ የመላእክትን የምስጋና ሥርዓት ወደ ምድር አምጥቷል፡፡

የነቢያትን ትንቢት፣ የሐዋርያትን ትምህርት በሚገባ ተርጒሞ፣ አብራርቶ፣ አመሥጥሮ አዘጋጅቶታል፡፡ ሐዋርያት ጾሙን ጾመው የጾም ሕግ ደንግገዋል፤ ቅዱስ ያሬድም ለጾሙ ስያሜ ሰጥቶ ምስጋና ከነሥርዓቱ አዘጋጅቶ አቅርቧል፡፡ቤተ ክርስቲያናችንም የመጀመሪያው የዐቢይ ጾም ሳምንትን (ዘወረደን) ስያሜ እንደ ቅዱስ ያሬድ ከሐዋርያት ተቀብላ ታስተምራለች፡፡

ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ‹ጾመ ሕርቃል› እየተባለም ይጠራል፡፡ ሕርቃል (ኤራቅሊዮስ) በ፮፻፲፬ ዓ.ም የነበረ የቤዛንታይን ንጉሥ ነው፡፡ ለክርስቲያኖች ባደረገው ርዳታ ምክንያት አንድ ሳምንት ጾመውለት ነበር፡፡ ያላወቁ ‹ጾመ ሕርቃል› ብለው አንድ ጊዜ ጾመው ትተውታል፡፡ ጥንቱን የቅዱሳን ሐዋርያት መኾኑን ያወቁ ምእመናን ግን ዅልጊዜ በየዓመቱ ይጾሙት ነበር፡፡ ዛሬም ድረስ ጾመ ሕርቃል እየተባለ ይጠራል፡፡ ሙሉ ታሪኩ በፍትሐ ነገሥት ትርጓሜ አንቀጽ ፲፭ ላይ ይገኛል፡፡

አምላካችን እግዚያብሔር ሆይ ጾማችንን በሰላም እንድንጨርስ ቅዱስ ፈቃድህ ይሁንልን ። አሜን
        
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
#ዘወረደ ብለን የጀመርንውን ፆም #ሆሳዕና ብለን እንድንጨርስ የእግዚአብሔር ቅዱስ ፍቃድ ይሁንልን አሜን!

ይህ ጾም ከእህል እና ውሃ የምንቆጠብበት ሳይሆን ለቤተክርስቲያናችን ለሃገራችን እና ለህዝቦቿ ምህረትን፣ ሰላምንና ፍቅርን የምናስገኝበት የቀድሞ አንድነቷ የሚመለስበት ከተፈራው ከሚወራው ሃገራችንና ህዝቦቿን የምንታደግበት ጾም ያድርግልን።

የታወረ አይነ ልቦናችን የሚገለፅበት፣ ሰላም የሚወርድበት፣ ሃጢአታችን የሚደመሰስበት፣የጠፋነው የምንገኝበት፣ እርስ በእርሰ ከመበላላት የምንፋቀርበት በዘር በሃይማኖት ተከፋፍለን በዲያብሎስ አይን ከመተያየት አንድ የምንሆንበት ጾም ያድርግልን አሜን ::

#አንድ_ሲኖዶስ
#አንድ_ፓትሪያሪክ
#አንዲት_ቤተክርስቲያን

@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
የዐብይ ጾም ሳምንታት።

#ዘወረደ ብለን የጀመርንውን ፆም #ሆሳዕና ብለን እንድንጨርስ የእግዚአብሔር  ቅዱስ ፍቃድ ይሁንልን አሜን!

ይህ ጾም ከእህል እና ውሃ የምንቆጠብበት ሳይሆን ለቤተክርስቲያናችን ለሃገራችን እና ለህዝቦቿ ምህረትን፣ ሰላምንና ፍቅርን የምናስገኝበት የቀድሞ አንድነቷ የሚመለስበት ከተፈራው ከሚወራው ሃገራችንና ህዝቦቿን የምንታደግበት ጾም ያድርግልን።

የታወረ አይነ ልቦናችን የሚገለፅበት፣ ሰላም የሚወርድበት፣ ሃጢአታችን የሚደመሰስበት፣የጠፋነው የምንገኝበት፣ እርስ በእርሰ ከመበላላት የምንፋቀርበት በዘር በሃይማኖት ተከፋፍለን በዲያብሎስ አይን ከመተያየት አንድ የምንሆንበት ጾም ያድርግልን አሜን ::

#አንድ_ሲኖዶስ
#አንድ_ፓትሪያሪክ
#አንዲት_ቤተክርስቲያን

@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
"በዓቢይ ጾም ሕይወቱን ያልቀየረ ክርስቲያን በሌሎች አጽዋማት ይቀይራል ለማለት ይከብዳል "

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ

@ortodoxtewahedo
Audio
ፍቅርና ትሕትና /ዘወረደ/ 
                                                  
Size:- 26.9MB
Length:-24:56
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedo
መጋቢት ሁለት

በዚህች ዕለት ኦርቶዶክሳውያን ታላቁን ዓቢይ ጾም የሚጀምሩባት የተባረከች ዕለት ነች እና እንኳን በሰላም አደረሰን ያደረሰን አምላክ ከጾሙ ረድኤት በረከት የምናገኝበት ያድርግልን ያጣነውን ሰላም ይመልስልን ።

መጋቢት 2 ታሪክ ሲታወስ በዚህች ዕለት ታላቁ ንጉሠ ኢትዮጵያ አፄ ዮሐንስ ስለ ሀገር ክብር ስለ ዳርድንበር መጣስ ስለ ኢትዮጵያውያን መጠቃት ዘምተው በውጉያ መሀል ሰማዕት ሆነዋል። ዕለቱን ስናስብ ጀግናውን ንጉስ እናስባለን ነፍሰቸውን አምላካችን ከቅዱሳን ማኅበር ይደምርልን ።

@ortodoxtewahedo
ያልመነኑ ሰዎች ከመነኮሱ፤ ክርስቲያን ያልሆኑ ሰዎች ከቀሰሱ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁት ሰዎች ካስተማሩ፤ ደመወዝ፣ቤትና መኪና የሚያጓጓቸው ሰዎች ከጰጰሱ፤ ፍትፍት ያልሰለቻቸው ሰዎች ባሕታውያን ከሆኑ፤ የዘር ዛር ያልለቀቃቸው ሰዎች የሁሉ አባት ከተባሉ፤ ከራሳቸው ጋር ያልታረቁ ሰዎች ለታራቂነትና አስታራቂነት ከተቀመጡ፤ የቤተክርስቲያን ፈተናዋ የሀገርም መከራዋ ገና ይቀጥላል።


@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
2024/09/30 11:43:08
Back to Top
HTML Embed Code: