Telegram Web Link
ይቅር ስላልከኝ
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
ይቅር ስላልከኝ ነው

ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ

@ortodoxtewahedo
#በገዳማት_የምሕላ_ጸሎት_ታውጇል

ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ  በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የሚፈጸመውን የምሕላ ጸሎት አስመልክቶ ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ  አሜን

‹‹ተማሕለሉ ወሰአሉ ኃበ አቡክሙ ሰማያዊ እስመ አብ ይሁበክሙ ኵሎ ዘሰአልክሙ…አባታችሁ የምትለምኑትን ሁሉ  ይሰጣችኋልና ወደ ሰማይ አባታችሁ ለምኑ፣ ምሕላንም አውጁ›› ኢዩኤል 1፤14 ቅዱስ ያሬድ
በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ  በጾም በጸሎት በመወሰን፣ምሕላን በማወጅ ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ ወደሚችለው አምላካችን አግዚአብሔር ምልጃን ማቅረብ የሚያስፈልግ መሆኑን ከሀገራችን ሊቃውንት መካከል የመጀመሪያ  የሆነው  ቅዱስ ያሬድ ከሰማያውያን ዐውደ ማህሌት ሰምቶ በቀሰመው ጣዕመ ዜማ  አበክሮ ይነግረናል፡፡

በመሆኑም ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷልና በእውነት የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ እግዚአብሔር መተላለፋችንን ይቅር እንዲለን፣ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ ለቤተ ክርስቲያናችን ፍቅር አንድነት፣ ለሕዝባችን ደኅንነት እንዲሰጥልን ከአንድነት ገዳማት ኅብረት በቀረበው ጥያቄ መነሻነት ምሕላ ማወጅ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በሁሉም የሀገራችን ክፍልና በሌሎችም አህጉራተ ዓለም የምትገኙ መነኰሳትና መነኰሳይያት  ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ትውፊት መሠረት የገዳማት ኅብረቱን ጥሪ ተቀብላችሁ የምሕላ ጸሎት እንድታደርሱ፣ በጤና ችግር ምክንያት ካልሆነ በስተቀር እስከ ዕርበተ ፀሐይ በመጾም ሱባኤ እንድትይዙ፣ ቋሚ ሲኖዶስ በኅብረተ መንፈስ ቅዱስ ከአደራ ጋር ያሳስባል፡፡

ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና  ምእመናን  ሀገራዊ ሰላምን፣  መረጋጋትንና ፍቅር አንድነትን ለማስፈን ጾምና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን  ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

‹‹እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ››
ሐምሌ 5 ቀን 2016 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ፎቶ Eotc tv

@ortodoxtewahedo
" መሰልቸት የጭንቀት የልጅ ልጅ ነው ስንፍናም ሴት ልጅ ናት ። እሷን ለመልቀቅ ፣ በትጋት መድከም - በጸሎት አትስነፍ ፣ ያኔ መሰልቸት ያልፋል እና ቅንዓት ይመጣል ። እናም በዚህ ትዕግስት እና ትህትና ላይ ከጨመሩ ፣ ከዚያ እርስዎ  ከብዙ ክፋት ያድናል"

ቅዱስ አምብሮስ

@ortodoxtewahedo
📖📖📖📖📖📖📖📖📖

"ወዮ ይኽች ዕለት አብ የቀደሳት ወልድ የባረካት መንፈስ ቅዱስ ከፍ ከፍ ያደረጋት ናት፡፡

በእርሷ ደስ ይበለን፡፡ በእርሷም ኃሤትን እናድርግ ትከብሩባት ዘንድ አክብሯት!

ዘመን ወር ለመባል በእርሷ የታወቃችኹ ሌሎች ዕለታት ኾይ የበዓላትን በኩር ኑ አመስግኗት ይኽችውም የከበረች ሰንበተ ክርስቲያን ናት፡፡"

ቅዳሴ አትናቴዎስ

ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
አረሳውም_ያንን_እለት_አልዘነጋም_ያን_ደግነት_ሰማዕቷ_ቅድስት_አርሴማ_ደጓ_እናቴ።_አሮን_ቤቢ_6a5c
<unknown>
አልረሳውም ያንን ዕለት

አልረሳውም ያንን ዕለት
አልዘነጋው ያን ደግነት
እናቴ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት
እምዬ ሆይ ምልሽ ኪዳነ ምሕረት
ስላለኝ ነው ምክንያት/፪/


ለሠው ተናግሬ ያልተረዳኝ ሰው
ዕንባዬ በምሬት ከዓይኔ የሚፈሰው
የቤቴን ገመና ሁሉን ስነግርሽ
አዛኝ እህት ነሽና እራራልኝ ልብሽ
አረሳው መቼም የአንቺን ደግነት/፪/
ውለታ አለብኝ ኪዳነ ምሕረት

አዝ__

ልቤ በሐዘን ጠቁሮ ውስጤ እየደማ
በቅረዜ ሲጨልም ስጓዝ በጨለማ
በራፌን ዘግቼ ዝምብዬ አለቅሳለሁ
አይኔን አቀርቅሬ እናቴ እልሻለሁ
ዘንበል አልሽልኝ ሠምተሽ ፆሎቴን/፪/
አልተጸየፍሽም ብቸኝነቴን

አዝ__

እናት የለኝ ብዬ ከቶም አልከፋ
እኔስ አይቻለሁ ስትሞይኝ በተስፋ
ምድራዋዊ እናቴ ለጊዜው ነው ፍቅሯ
ያንቺስ ግን ልዩ ነው እረ ስንቱን ላውራ
ማርያም ማርያም ብል አልሠለችሽ/፪/
በልቤ ጽላት ስለ ታተምሽ

አዝ___

ሲረበኝ መጥተሻል ሲጠመኝ ደርሰሻል
ለጎደለው ቤቴ በረከት ሆነሻል
ጭንቄም ቀለለልኝ ሐዘኔም ራቀ
ያስጨነቀኝ ጠላት ራሱ ተጨነቀ
መዳኒት ወልደሽ ዳኩኝ ከመሜ/፪/
ይኸው ዘመርኩኝ በምልጃሽ ቆሜ



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ደጅ ጠናሁ
ዝማሬ ዳዊት
ደጅ_ጠናሁ

ደጅ ጠናሁ ቆይቼ ኪዳነ ምህረትን
ተፅናናሁኝ ረሳሁ ሀዘኔን
የአምላክ እናት እመቤታችንን
ሞገስ ሁኚኝ ቀሪው ዘመኔን

የመከራው ዘመን አለፈ እንደዋዛ
አንቺን ተጠግቼ የአለሟን ቤዛ
የልጅሽ ቸርነት የአንቺ ደግነት
ባርያሽን ሰውሪኝ ከአስጨናቂው ሞት
እናቴ ስምሽን ስጠራ አለፈ ያሁሉ መከራ
እምባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዬ በአንቺ እየታበሰ ሰላም ለኪ

#አዝ

ልቤ ባንቺ ፀና ከፍ ከፍም አለ
በጠላቶቼ ላይ አፌ ተናገረ
በማዳንሽ ስራ ባሪያሽ ደስ ብሎኛል
የኃያላኑን ቀስት ልጅሽ ሰብሮልኛል
እናቴ ስምሽን ስጠራ አለፈ ያሁሉ መከራ
እምባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዬ ባንቺ የታበሰ ሰላም ለኪ

#አዝ

እጄ ባዶ ሲሆን ወዳጆቼም ሸሹኝ
በመርገም ምክራቸው ሊለያዩን ሲሹ
እርሱ የሰጠኝን እሱ ወሰደ አልኳቸው
እመቤቴ አለችኝ ብዬ አሳፈርኳቸው
እናቴ ስምሽን ሰጠራ አለፈ ያሁሉ መከራ
እምባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዬ በአንቺ እየታበሰ ሰላም ለኪ

#አዝ

በአውደ ምሕረቱ ሆኜ ስጠራት
ዘንበል ብላ አየችን ኪዳነ ምህረት
ሀሳብሽን ምንም የለም የሚመስለው
እረፍት ያገኘሁት እናቴ ባንቺ ነው
እናቴ ስምሽን ስጠራ አለፈ ያሁሉ መከራ
እምባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዬ ባንቺ እየታበሰ ሰላም ለኪ



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ኪዳነ ምህረት
Orthodox Mezmur Channel
ኪዳነ ምህረት | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
Audio
✤ ኪዳነ ምህረት

ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ኪዳነምሕረት ልዩ ነሽ ለእኔ
ዝማሬ ዳዊት On Telegram
#ኪዳነ_ምህረት_ልዩ_ነሽ_ለኔ

ኪዳነ ምህረት ልዩ ነሽ ለኔ
ሳዝን ስጨነቅ አትራቂኝ ከጎኔ
የችግሬ ደራሽ እመ እግዚአብሔር
ቃል ኪዳንሽ ይርዳኝ ካንቺ ጋር ልኑር(፪)
#አዝ
የአዳም ተስፋው ነሽ የሴት ቸርነቱ
ኪዳነምህረት ነሽ የኖህ ምልክቱ
አዳም ደጅ የጠናሽ ሲገባ ንስሀ
ኖህም ድኖብሻል ከጥፋቱ ውሃ
#አዝ
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ
ማርያም አንቺ ነሽ የፈጣሪ እናቱ
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ
እመብርሃን ስሚኝ ልመናየን ሁሉ
#አዝ
የሰሎሞን አክሊል የዳዊት ዝማሬ
ድንግል መሆንሽን ትመስክር ከንፈሬ
ለተጠማው ውሻ የሚራራው ልብሽ
ለኔም እራርቶልኝ አስታርቂኝ ከልጅሽ
#አዝ
የአብርሃም ድንኳን ነሽ የሙሴ ፅላቱ
ማርያም አንች ነሽ የፈጣሪ እናቱ
የእስራኤል መሰላል የሴም እጣ ክፍሉ
እመብርሃን ስሚኝ ልመናዬን ሁሉ

ዘማሪት ሲስተር ፋሲካ መኮንን
    



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ኪዳነ ምህረት እመቤት
🌺💠❤️ኪዳነ ምሕረት እመቤት🌺❤️💠

ኪዳነ ምሕረት እመቤት እመቤት/×፪/
ነይልን ነይልን ካለንበት/×፪/



ከሰማያት በላይ ካለው ከማደሪያሽ/፪/
ዝማሬ ከሞላው ከዘለዓለም ቤትሽ
የምድር ፍጥረታት ማርያም ማርያም ሲሉሽ/፪/
የቃል እናት እመቤቴ ነይ በሠረገላሽ/፪/


#አዝማች......................................


ከጸጥታው ወደብ ከፍቅር አውድማ/፪/
ከሰላሙ መንደር ከእውነት ከተማ
ሰአሊለነ ቅድስት ውዳሴሽ ሲሰማ/፪/
ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር ነይልን ከራማ/፪/


#አዝማች.......................................

ዘርፋፋው ቀሚስሽ ይውረድ ከሰማያት/፪/
እንባችን ይታበስ በአንቺ አማላጅነት
የጽዮን ዝማሬ ተሞላች ነፍሳችን/፪/
ንዒ ንዒ ንዒ እንበል እንደ አባቶቻችን/፪/


#አዝማች.......................................

ፍጥረታት ሊድኑ በአማላጅነትሽ/፪/
የዘለዓለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሽ
ትውልድ ይህን አምኖ ብጽእት ይልሻል/፪/
እናቴ መመኪያዬ ምርኩዜ ሆነሻል/፪/


#አዝማች........................................

የልብን ሲያዋዩሽ ሰምተሽ ዝም አትይም/፪/
ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም
ከዓይን ጥቅሻ ፈጥነሽ ትደርሺለታለሽ/፪/
ከሃዘን ከመከራ ታሳርፊዋለሽ/፪/


#አዝማች.......................................


👉 ዘማሪት ለምለም ከበደ



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ኪዳነ ምህረት
Orthodox Mezmur Channel
ኪዳነ ምህረት | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
እንወድሻለን ኪዳነ ምሕረት_ _ ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ(360P)
<unknown>
ኪዳነ ምህረት እንወድሻለን

ለግዚአብሔር ታቦቱ መቅደሱ
ቀርበናል ባንቺ ወደ ንጉሱ
የክብራችን ጌጥ ሽልማት
እንወድሻለን ኪዳነምህት

በጨለማው ላለ ብርሃንን አየ
ለርስቱ ተካፋይ እንዲሆን ተለየ
ወደ ቀድሞ ክብሩ ሊመለስ ዳግመኛ
አንቺ ነበርሽ ተስፍው ለአዳም መዳኛ

አዝ===========
ያንን ሁሉ ዘመናት የፈሰሰው ደም
አለምን ከእስራት ሊፈታ አልቻለም
ወደ ሚሻል ኪዳን በደም ሊያሻግረን
ደምሽን ተዋህዶ መዳኃኒ አለም ዋጀን

አዝ===========
አለን ብዙ ምክንያት አንቺን ምንወድበት
ዓለም ያልተረዳው ያላወቀው እውነት
ያወቀ የተረዳ የመዳኑን ሚስጢር
አያፍርም ክብርሽን ቆሞ ለመናገር

አዝ===========
አውቃለሁ እግዚአብሔር የሰጠሽን ክብር
ላመስግንሽ እኔም ሳልጨምር ሳልቀንስ
ሚባርክሽ ብሩክ ነውና እናቴ
ኪዳነ ምህረት ንገሽ እመቤቴ
አዝ===========         



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
እናት አለኝ
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
እናት አለኝ

እናት አለኝ የምታብስ እንባ
አያታለው ስወጣ ስገባ
ኪዳነ ምህረት /3/ አንባ መጠጊያ ናት

ሔዋን ሰጥታኝ ከበለሱ ፍሬ
እራቆቴን ብቆምም አፍሬ
ልብሴን ይዘሽ ወደ እኔ ቀርበሻል
ደጓ እናቴ ቤቴን አድምቀሻል

ኪዳነ ምህረት /3/ አንባ መጠጊያ ናት/

አዝ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠

ለዘላለም ንጽህይት በመሆኗ
ከኔ ጋር ነው ህያው ቃልኪዳኗ
ደስተኛ ነኝ ሀዘኔን አልፌ
አጽናኝ ሆናኝ የመስቀል ስር ትርፌ

ኪዳነ ምህረት /3/ አንባ መጠጊያ ናት/

አዝ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠

ከጥፋቱ ውሀ ማረፊያዬ
መርከቤ ነሽ ከሞት ማምለጫዬ
የአምላክ እናት ምልጃሽ ሆኖኝ ክብሬ በህይወት አለው ጥልቁን ተሻግሬ

ኪዳነ ምህረት /3/ አንባ መጠጊያ ናት/

አዝ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠

በእናትነት ህይወቴን ጎብኝታ
ልቤ አረፈ ተነቅሎ በሽታ
ሰንሰለቴ ከእጄ ተቆረጠ
መራራዬ በልጅሽ ጣፈጠ



ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

📖📖📖📖📖📖📖📖📖
ሲነግሩሽ ሰሚ ነሽ
@yemezmurgetemoche
ሲነግሩሽ ሰሚ ነሽ

ያለሽ ልዩ ፀጋ ያለሽ ልዩ ክብር
የሁሉ እመቤት በሠማይ በምድር
አቁራሪተ መዓት ምዕራገ ፀሎት
ሲነግሩሽ ሰሚነሽ ኪዳነ ምህረት


በመከራ ላለ ሁኚለት መፅናኛ
ዕንባውን አብሺው አይዘን ዳግመኛ
ጉድለቱን ሙይለት በፈረሰው ቆመሽ
ስለምታስምሪው በልዩ ኪዳንሽ
     ከኪዳንም በላይ ኪዳንሽ ልዩ ነው  
     እናቴ የሚልሽ አምላክሽ ልጅሽ ነው


ይበጠስ ከእጁ የወህኒው ሰንሰለት
የሞቱ ደብዳቤ ይቀየር በህይወት
አዲስ ተስፋ ሞልተሽ አዲስ ሰው አድርጊው
መቅበዝበዙን ይርሳ ድንግል አረጋጊው
     ከኪዳንም በላይ ኪዳንሽ ልዩ ነው  
     እናቴ የሚልሽ አምላክሽ ልጅሽ ነው


በእንባ የመጣው ይመለስ በደስታ
መጠማቱ ይቅር ይሞላ በእርካታ
ስዕለቱ ሰምሮለት ይቁም ለምስጋና
የአብራኩን ክፋይ አሳቅፊዉና
     ከኪዳንም በላይ ኪዳንሽ ልዩ ነው  
     እናቴ የሚልሽ አምላክሽ ልጅሽ ነው


ተይዞ ለሚኖር በአልጋ ቁራኛ
ምቺው እመቤቴ የደዌውን ዳኛ
መንገርስ ላንቺው ነው መማፀን ወዳንቺ
ተስፋን ለምትቀጥይ ሕልምን ለምትፈቺ
     ከኪዳንም በላይ ኪዳንሽ ልዩ ነው  
     እናቴ የሚልሽ አምላክሽ ልጅሽ ነው

            
ኪዳነ ምህረት - አቤል መክብብ - Kidane mihiret - Abel Mekbib
masresham
ኪዳነ ምሕረት የ ረፍቴ እናት

# ዘማሪ አቤል መክብብ

ኪዳነ ምህረት የዕረፍቴ እናት
ሰላም ሆነ ባንች አማላጅነት
ንፅህት ድንኳን በእምነት ያጌጥኩብሽ
ሰላም ሆነ በአማኑኤል ልጅሽ

የብርሀን ዝናር ባይኖረኝም
በንጉስ ፊት ተሸልም ብቆም
በልጅሽ ነው ውበቴ ማማሩ
በምልጃሽ ነው ስሜ መቀየሩ
በልቤ ላይ ተነበበ ልጅሽ
አሁን ስሜ ተጠርቷል በልጅሽ
ከታች በምድር እስከሰማይ ድረስ
ድርሻየ ነው ስምሽን ማወደስ(2)

ኪዳነ ምህረት የእረፍቴ እናት
……………………………………
……………………………………
……………………………………

የከበረ ሁነሽ ንግግሬ
ቅኔ አነሳሁ ለክብርሽ ዘማሬ
እንደ ዝግባ ከፍ ብየ ብታይ
ወጥቶልኝ ነው በሰማይ ፀሀይ
ስለ ምልጃሽ ዘይቱ ፈሰሰ
አንቺን ይዤ ሙሽራው ደረሰ
ቀንዲሌ ነሽ ድንግል አዛኝቱ
በልጅሽ ነው የነፍሴ ፅናቱ

ኪዳነምህረት የእረፍቴ እናት
……………………………………
……………………………………
…………………………………

ከኤልያብ ቢደምቅ ደም ግባቴ
ማን ሊመርጠኝ ያላንች እናቴ
ተዋብኩብሽ ገፄ በአንች አበራ
አንደበቴ ስምሽን ሲጠራ
እንደ ሙሴ እንደ አሮን በትር
ማምለጫየ ከፈርዖን ቀንበር
ከእንግዲማ እኔ እንዴት አዝናለሁ
አማላጀ አንችን ይዠዤሻለሁ

ኪዳነምረት የእረፍቴ እናት
            
#እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ

#እንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት ገዳም

በአዲስ አበባ ከተማ በስተሰሜን ምሥራቅ በጉለሌ ክፍለ ከተማ የምትገኝ ስመጥርና ታሪካዊ ገዳም ስትሆን በተራራ፣በሸለቆና በወንዞች የተከበበች በመሆኑዋ በተፈጥሮ አቀማመጧ አረንጓዴ የተላበሰች ናት፡፡ ይህም ለቤተክርስቲያኗ ውበትና ግርማ ሞገስ ከመስጠት አልፎ በሚያስደስት ፀጥታ የአዕዋፍ ዝማሬ ተሞልታ ጸጋን እንድትላበስ አድርጓታል፡፡
ይህች ቦታ የተቆረቆረችው በ484 ዓ/ም ሲሆን በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተቋቋመች፡፡ አባ ሊባኖስ ወደ ሌላ መንፈሳዊ ተልእኮ ለመሄድ መነኮሳቱን ሲሰናበቱ እንዲህ የሚል ትንቢት ተናግረው ነበር ‹‹ልጆቼ ሆይ በሉ ይህችን ቅድስት ቦታ አደራ ሰጥቻችኋለሁ በኋላ ዘመን ታላቅ ቦታ ትሆናለች' አጋንንት ይወገዱባታል' የብዙ ቅዱሳን አፅም ያርፍባታል' ነገስታት ጳጳሳት ይሰግዱባታል' ብዙ መናንያን መጠጊያ ያደርጋታል ቤተ መቅደሷም በወርቅ በብር ተጊጣ ትታነጻለች የአንድነቱም ገዳም ተሻሽሎ ይቋቋምባታል››፡፡ በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡
በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ለመነኮሳቱ እንዲህ ብለው ነበር ‹‹ይህች ገዳም ታላቅ ስመጥር ገዳም ትሆናለች ከእርሷ በታች የሚታየው ጫካና ዱር መናገሻ ከተማ ይሆናል፡፡››
አፄ ዘርዓ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ በንግስት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡
ይህች ቦታ እንደተነገረላት ትንቢት ብዙ ቅዱሳንና ነገሥታት መጥተው የሰገዱባት የባረኳት' ጸበሏ የአጋንንት ድል መንሻ' የብዙ መነኮሳት መጠጊያ 'የህሙማን መፈወሻ' የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎች አንዷ ናት፡፡ ይህች ደብር በ1957 ዓ/ም የተመሠረተ ሰንበት ት/ቤት ሲኖራት በ1984 ዓ/ም በብፁዓን ጳጳሳት ‹‹መርሶ ሕይወት›› /የሕይወት ወደብ/ የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡ የገዳሟ ስያሜ ሐመረ ኖኅ ( የኖኅ መርከብ ) እንደሆነ ሁሉ መርሶ ሕይወት ( የሕይወት ወደብ ) በመባሉ ሁለቱ ተዛማችነት አላቸው ፡፡ ይህ ሰንበት ት/ቤት ለየት የሚያደርገው በግል መኖሪያ ቤት በጋሞኛ ቋንቋ ይሰጥ የነበረውን ትምህርት ከ1986 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ ስር በማቀፍ የወንጌል ትምህርቱን ከመማር ባሻገር ለጋሞ ሕዝብ መንፈሳዊ እንቅስቃሴን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

አዘጋጅ፡- እህተ ማርያም

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘለአለም ትኑር!!!

ሰው ሁሉ ለመናገር የዘገየ ለመስማት የፈጠነ ይሁን !
(ያዕቆብ 1፥19)

< ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@ortodoxtewahedo
2024/09/29 17:35:15
Back to Top
HTML Embed Code: