Telegram Web Link
ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አቀረበ!

ጥቁር ልብስ!!!

ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ ከቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምህረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላለፈ።

@ortodoxtewahedo
የውሸት ክህነቱን በአንደበቱ ያረጋገጠው ዱርዬ
***

ይህን ምስኪን የጩፋ ዘመዶች ለማሳመን ብሎ ዱርየው ባለቀሚስ ሲናገር አንድ ያላስተዋለው ነገር ከአፉ አምልጦታል።

ክህነት/ቅስናውን ከዬት እንዳገኘ ለማስረዳት ሲመልስ
ከባህር ዳር ሀገረስብከት ከነበሩት ከብጽኡ አቡነ ጴጥሮስ ከሚባሉ ሊቀ ጳጳስ ቅስና ተቀብያለው ይላል።

....ከእዛን ቀጠል አድርጎ ከአቡነ ጴጥሮስ የተቀበልኩት የቅስና ካርድ ስለጠፋ አዲስ አበባ ሀገረስብከት ሄጄ አቡነ ሳሙኤል ከሚባሉ ሊቀ ጳጳስ ይህን ካርድ(ቪዲዮው ላይ የሚያሳየውን ካርድ) ወስጃለው ብሎ ይተርካል።

ይህ ዱርዩ የዘነጋው አንድ ሃቅ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት መሰረት ክህነት ያለው አንድ አካል የክህነት ካርዱ ቢጠፋበት ቀድሞ ክህነት ወደወሰደው ሀገረስብከት በመሄድ ቀድሞ ክህነት ከመውሰዱ በፊት ያመጣቸው ፋይሎች ተጣርተው ማስረጃ ወይም ድጋሚ የክህነት መታወቂያ ካርድ ይሰጠዋል እንጅ ክህነት ካልወሰደበት ሀገረስብከት አይወስድም።

ምክንያቱም ክህነት ያልሰጠው ሀገረስብከት ስለሰውዬው የክህነት ማረጋገጫነት አንዳች ፋይል የለውም።

ቀድሞ ክህነት ያልወሰደበት ሀገረስብከት ይህ ሰው ካህን ይሁን ቦዘኔ የትኛውን ፋይሉን አጣርቶ ነው ድጋሚ የክህነት ካርድ የሚሰጠው ?

በአጭር አማረኛ በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ የተመረቀ መሃንዲስ ዲግሪው ስለጠፋ አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ አመልክቶ የትምህርት ማስረጃውን ወሰደ እንደማለት ነው።

ቀሽም ተውኔት።

ለማንኛውም መኖክሴ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ሲመ*Fiq አዲስ አይደለም። ነገር ግን በውሸት ቄስ ነኝ መኖክሴ ነኝ ብሎ መጋጋጥ ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው?

የመነfeq ሰው ምዕመን ይሁን ፓትርያሪክ በየትኛውም መመዘኛ ውሃ አያነሳም። የሁለቱም መጥፋት ስያሜው ክህደት ይባላል።

ይህ ሰው ክህነት አልባ የሆነ ሞላጫ ዱርዬ መሆኑ የምታረጋግጥበት "ከማርያም ጋር እኔን እኩል ነኝ ፣መላእክት ምንም አያውቁም፣" ማርያም እንዴት የህይወት መብልን ያገኘንባት ትባላለች?" ገለመሌ እያለ እንኳን ለኦርቶዶክስ ለቃለህይወት እና መካነኢየሱስ አማኝ እራሱ የሚሰቀጥጥ ንግግር ሲያበዛ ነበር።

እንግዲህ ጩፊዝም እንዲለመልም ውሸት ማደባሪያ ናት

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

@ortodoxtewahedo
በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።
ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ።

ሐዋርያት 20 : 28-30
✞ኪዳነምህረት እመቤት✞
♡የመዝሙር ግጥሞች♡
✞ኪዳነምህረት እመቤት✞

ኪዳነ ምህረት እመቤት እመቤት(፪)
ነይልን ነይልን ካለንበት (፪)

ከሰማያት በላይ /ካለው ከማደሪያሽ/(፪)
ዝማሬ ከሞላው ከዘላለም ቤትሽ
የምድር ፍጥረታት /ማርያም ማርያም ሲሉሽ/(፪)
የቃል እናት እመቤቴ /ነይ በሰረገላሽ/(፪)
       አዝ= = = = =
ከጸጥታ ወደብ /ከፍቅር አውድማ/(፪)
ከሰላሙ መንደር ከእውነት ከተማ
ሰዐሊ ለነ ቅድስት /ውዳሴሽ ሲሰማ/(፪)
ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር /ነይልን ከራማ/(፪)
       አዝ= = = = =
ዘርፋፋው ቀሚስሽ /ይውረድ ከሰማያት/(፪)
እንባችን ይታበስ ባንቺ አማላጅነት
የጽዮን ዝማሬ /ተሞላች ነፍሳቸን/(፪)
ንዒ ንዒ ንዒ እንበል /እንደ አባቶቻችን/(፪)
       አዝ= = = = =
ፍጥረታት ሊድኑ /በአማላጅነትሽ/(፪)
የዘላለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሽ
ትውልድ ይህን አምኖ /ብፅይት ይልሻል/(፪)
እናቴ መመኪያዬ /ምርኩዜ ሆነሻል/(፪)
       አዝ= = = = =
የልብን ሲያዋዩሽ /ሰምተሽ ዝም አትይም/(፪)
ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም
ከአይን ጥቅሻ /ፈጥነሽ ትደርሽለታለሽ/(፪)
ከሐዘን ከመከራ /ታሳርፊዋለሽ/(፪)

            መዝሙር
          ለምለም ከበደ

"ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ"
                  መዝ፹፱፥፫

@ortodoxtewahedo
#እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት አመታዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ ።

#እንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት ገዳም

በአዲስ አበባ ከተማ በስተሰሜን ምሥራቅ በጉለሌ ክፍለ ከተማ የምትገኝ ስመጥርና ታሪካዊ ገዳም ስትሆን በተራራ፣በሸለቆና በወንዞች የተከበበች በመሆኑዋ በተፈጥሮ አቀማመጧ አረንጓዴ የተላበሰች ናት፡፡ ይህም ለቤተክርስቲያኗ ውበትና ግርማ ሞገስ ከመስጠት አልፎ በሚያስደስት ፀጥታ የአዕዋፍ ዝማሬ ተሞልታ ጸጋን እንድትላበስ አድርጓታል፡፡
ይህች ቦታ የተቆረቆረችው በ484 ዓ/ም ሲሆን በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተቋቋመች፡፡ አባ ሊባኖስ ወደ ሌላ መንፈሳዊ ተልእኮ ለመሄድ መነኮሳቱን ሲሰናበቱ እንዲህ የሚል ትንቢት ተናግረው ነበር ‹‹ልጆቼ ሆይ በሉ ይህችን ቅድስት ቦታ አደራ ሰጥቻችኋለሁ በኋላ ዘመን ታላቅ ቦታ ትሆናለች' አጋንንት ይወገዱባታል' የብዙ ቅዱሳን አፅም ያርፍባታል' ነገስታት ጳጳሳት ይሰግዱባታል' ብዙ መናንያን መጠጊያ ያደርጋታል ቤተ መቅደሷም በወርቅ በብር ተጊጣ ትታነጻለች የአንድነቱም ገዳም ተሻሽሎ ይቋቋምባታል››፡፡ በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡
በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ለመነኮሳቱ እንዲህ ብለው ነበር ‹‹ይህች ገዳም ታላቅ ስመጥር ገዳም ትሆናለች ከእርሷ በታች የሚታየው ጫካና ዱር መናገሻ ከተማ ይሆናል፡፡››
አፄ ዘርዓ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ በንግስት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡
ይህች ቦታ እንደተነገረላት ትንቢት ብዙ ቅዱሳንና ነገሥታት መጥተው የሰገዱባት የባረኳት' ጸበሏ የአጋንንት ድል መንሻ' የብዙ መነኮሳት መጠጊያ 'የህሙማን መፈወሻ' የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎች አንዷ ናት፡፡ ይህች ደብር በ1957 ዓ/ም የተመሠረተ ሰንበት ት/ቤት ሲኖራት በ1984 ዓ/ም በብፁዓን ጳጳሳት ‹‹መርሶ ሕይወት›› /የሕይወት ወደብ/ የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡ የገዳሟ ስያሜ ሐመረ ኖኅ ( የኖኅ መርከብ ) እንደሆነ ሁሉ መርሶ ሕይወት ( የሕይወት ወደብ ) በመባሉ ሁለቱ ተዛማችነት አላቸው ፡፡ ይህ ሰንበት ት/ቤት ለየት የሚያደርገው በግል መኖሪያ ቤት በጋሞኛ ቋንቋ ይሰጥ የነበረውን ትምህርት ከ1986 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ ስር በማቀፍ የወንጌል ትምህርቱን ከመማር ባሻገር ለጋሞ ሕዝብ መንፈሳዊ እንቅስቃሴን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
አዘጋጅ፡- እህተ ማርያም (በሰ/ት/ቤታችን ሰሌዳ መጽሔት ቀርቦ የነበረ)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘለአለም ትኑር!!!

ሰው ሁሉ ለመናገር የዘገየ ለመስማት የፈጠነ ይሁን !
(ያዕቆብ 1፥19)

< ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@ortodoxtewahedo
#ኪዳነ ምህረት

ቢዘገይም… ብዙዎች ድንግል እናቱን ኪዳነ ምህረት ስንል ግራ ሲጋቡ አስተውላለሁ። በእርግጥም ግራ ቢጋቡ አይደንቅም ምክንያቱም ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስን ጠንቅቆ መረዳትና የመንፈስ ቅዱስ ድጋፍ ይፈልጋልና።

በብሉይ አማናዊው መሥዋት ከመሰዋቱ በፊት “የሥርየት መክደኛ”በእንግሊዘኛው ደግሞ “mercy seat` እንዲህም ሲባል “የምህረት ዙፋን" የሚባል ክፍል ያለው የቃል ኪዳኑ ታቦት ነበር። እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ቃል ኪዳን በማድረጉ በታቦቱ ላይ ተገልጦ ሙሴን ያነጋገረው ካህናቱን መሥዋዕታቸውን ይቀበል ነበር።

ይህ መገለጥ ግን ከሰዎች ልጆች ጋር ፍጹም እርቅ መፈጸሙን የሚያሳይ አልነበረም። ነገር ግን በዚህ ሕዝቡ ይጽናና ራሱንም ለበለጠ የትንሣኤ ሕይወት ያዘጋጀው ነበር። ምክንያቱም ለአባታቸው ለአብርሃም የገባውን ቃል ኪዳን እንደማያጥፍ ያምኑ ነበርና።

በሠውና በእግዚአብሔር መካከል እርቅ የወረደው ግን ድንግል እናቱን የቃል ኪዳኑ ታቦት አድርጎ ሥጋና ደም ተካፍሎ ሰው ሲሆን ነው። ያኔ በሰውና በእግዚአብሔር በሰውና በመላእክት በሰውና በሰው መካከል የነበረው ጠብ ፍጻሜ አገኘ። እርቅን ከሰው ጋር በተዋሕዶ ከፈጸመ በኋላ በሰው ልጆች ላይ ሰልጥኖ የነበረውን ዲያብሎስ ከድንግል እናቱ በተካፈለው ሰውነት በመስቀሉ ድል ነሳው። ድል መንሳትንም ለእኛ ሰጠን።

ስለዚህ እርቅ የወረደልን ተስፋ መንግሥተ ሰማያት የተሰጠን እርሷንና ሥጋዋን ለራሱ የቃልኪዳን ታቦቱ በማደረግ ስለሆነ ድንግል እናቱን ኪዳነ ምህረት እንላታለን። ምክንያቱም ምህረትና እርቅ ለሰው ልጆች ሁሉ ሆኖአልና።

እርሱ እግዚአብሔር ቃል ከእርሷ ከድንግል እናቱ ሥጋና ነፍስ ነስቶ ባሕርያችንን ለብሶ በእርሱም ለፍጥረቱ ተገልጦ በእኛ ላይ የተፈረደውን ፍርድ በራሱ ተቀብሎ ዲያብሎስን ድል ነስቶ በእርሱ ያመኑትን እርሱን ተስፋ የሚያደርጉትን ከቅዱሳን
መላእክት ጉባኤ ደመራቸው፡፡ ያመኑትንም በጥምቀት እርሱን ለብሰን እንድንነሣ በማድረግ ከቅዱሳን ጉባኤ እንድንደመር አደረገን፡፡

ሰውነታችንን መቅደሱ በማድረግ ሕጉንም በመንፈስ ቅዱስ በልቡናችን ሰሌዳ ላይ ጻፈልን፡፡ እነዚህንና ሌሎች
በረከቶችን ሊሰጠን የወደደው ከድንግል እናቱ በነሣው ሥጋና ነፍስ ነበር፡፡

ስለዚህም ድንግል እናቱ መንፈስ ቅዱስ አናግሩዋት “በእኔ ታላቅ ሥራን አድርጎአልና እንግዲህ ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይሉኛል” ብላ ከፍ አድርጋ ተናገረች፡፡ ስለዚህ ነው ኪዳነ ምሕረት መባልዋ፤ በእርሷ እርቅ ወርዶአልና።
በነቢዩም “ ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፤ እኔ አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል፡፡

”(ዕብ.8፡10) የሚለው ቃል በእኛ የተፈጸመው በድንግል ማርያም ነው፡፡ እንዲህም ስለሆነ ቅዱስ ጳውሎስ
“እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው”ብሎ ጽፎልናል፡፡

(2ቆሮ.3፡3)ይህን በማን አገኘነው ብንባል በክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ የድንግል እናቱን ሥጋና ደም ሳይካፈል ባይወለድ ኖሮ ይህ የምህረት ቃል ኪዳን በእኛና በክርስቶስ መካከል ባልተፈጸመ ነበር፡፡

እናም አጥርቶ ለመረደት የሚፈለግ ቅድስት እናቱን ኪዳነ ምህረት የማለታችን ዋናው ምክንያት ሰውነቷን የምህረት ቃል ኪዳን ታቦት በማደረግ ከርሷ በነሣው ሥጋ ዓለሙ መዳኑ ነው።...

@ortodoxtewahedo
#ኪዳነ ምህረት #16

ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው፡፡

ከ33ቱ በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው፡፡ እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን አላቋረጠችን እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ ወዳጄ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከ5 ቀን በቻለችህ ማሕጸኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መጥተህ ልምናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ አለች በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውታ ሆነ መቃብራት ተሰነጣጠቀ ጌታችንም እልፍ ከእልፍ መላዕክቱ ጋር መጥቶ ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለሚኚኛለሽ አላት፡፡

እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ የሚራራውን በስሜ ቤተ ክርስቲያን ያነጻውን መባዕ የሰጠውን ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው፡፡

ጌታችንም ይህን ሁለ እንዳደርግልሽ በራሴ በአባቴና በመንፈስ ቅዱስ ስም ቀል እገባልሻለው ብሎ ቃል ገብቶላት አርጓል።

በዚህም የተነሳ እመቤታችን እኛን በምልጃዋ የምታስምርበተ ፣ ጥያቄያችንን የምታስመልስበት ፣ እንቆቅልሻችንን የምታስፈታበት የምህረት ኪዳን የካቲት 16 ተቀብላለች እና ኪዳነ ምህረት እንላታለን ።

@ortodoxtewahedo
2024/09/29 17:40:13
Back to Top
HTML Embed Code: