Telegram Web Link
ወደ ላይ አያዳልጣችሁ!

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን አንድ ጨዋነት የራቀው ሰው ሰደባቸው አሉ። በኋላ ግን ጸጽቶት እግራቸው ላይ ወድቆ “ይማሩኝ፣ አጥፍቻለሁ፣ አድጦኝ ነው” ሲላቸው፣ እርሳቸውም “ታዲያ ወደ ታች ያድጣል እንጂ ወደ ላይ ያድጣል እንዴ?” አሉት ይባላል።

ወደ ላይ የሚያድጣቸውን ብዙ ሰዎች እያየን ነው። ሰሞኑን ዘነበ ወላ የተባለ ግለሰብ፣ ሊነቅፈው ቀርቶ ሊረዳውና ሊያደንቀው እንኳ እጅግ የሚበዛበትን የምናኔ ሕይወት ለመንቀፍ ሲሞክር ሰምተናል (የተነገረው በሕንድኛ ወይም በታይ ቋንቋ አይደለም!)። ይህን የመሰሉ እናውቃለን ከሚሉ አላዋቂዎች ወይም ጭፍን ጥላቻ ካሳወራቸው ሰዎች በኦርቶዶክሳዊነት ላይ በተለያየ መንገድ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች እየበዙ መምጣታቸው ጉዳዩን እንደ ቀላል ለማለፍ የማይቻል ያደርገዋል። ዛሬ ካለው የተከማቸ ኦርቶዶክስ-ጠልነት ያደረሱን ከ20ኛው መ/ዓ መጀመሪያ ጀምሮ ኦርቶዶክስ ጠል በነበሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ይሰነዘሩ የነበሩ የጥላቻ ንግግሮችና ጽሑፎች መሆናቸውን ልብ ይሏል።

ምናኔያዊ ሕይወት፣ ከትንሣኤ በኋላ የምናገኘውን እንደ መላእክት የመሆንን ሕይወት፣ በዚህ ዐለም ገንዘብ የማድረግ ሕይወት ነው። “በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም” እንዳለ ጌታችን። ማቴ. 22፡30 መላእክት በተፈጥሯቸው እንደማያገቡና እንደማይጋቡ ሁሉ፣ ከትንሣኤ በኋላ ደግሞ ለሰዎችም ማግባትና መጋባት እንደማይኖር ሁሉ፣ መላእክት ዛሬ የሚኖሩትን፣ የሰው ልጆች ደግሞ ከሞት በኋላ የሚያገኙትን ሕይወት መናንያን ገዳማውያን በአሁኑ ሕይወት ይኖሩታል። እንደዚሁም ምናኔያዊ ሕይወት አዳም ከመበደሉ በፊት የነበረው ሕይወት ምን ይመስል እንደ ነበረ በመስታወት የሚያሳይ ነው፣ ጌታችን የሰጠውን ሕይወት በምልዓት የሚያሳይ ነው።

ምናኔያዊ ሕይወት በክርስትና ውስጥ ያለውን እጅግ የገዘፈና ዘርፈ-ብዙ የሆነ ነገረ-ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ፋይዳ ለጊዜው ብናቆየው እንኳ፣ ክርስቲያናዊ ገዳማት ለሰው ልጆች ያበረከቷቸው ኢኮኖሚያዊ፣ እውቀታዊና ታሪካዊ ጠቀሜታዎች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ጥቂቶቹን እንኳ ብናስታውስ፤ ዩኒቨርሲቲዎችና አዳሪ ት/ቤቶች በዋናነት የተቀዱት ከገዳማት ነው። የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎች ሲመረቁ የሚለብሱት ጋዋንና የሚደፉት ቆብ የገዳማትን ቀሚስና ሞጣህት እንዲሁም ቆብ የሚመስለው በአጋጣሚ አይደለም።

በአውሮፓ የውኃ ኃይልን ለወፍጮና ለቆዳ ሥራ መጠቀምንና ማዕድናትን ማውጣትንና መጠቀምን በስፋት ያስተዋወቁት ገዳማውያን ናቸው። የአውሮፓን የእርሻ መሬት፣ ሥነ ጥበብና እውቀት ከጥፋት በመጠበቅና በማበልጸግ ረገድ ገዳማት የተጫወቱት ሚና ምትክ አልባ ነው። አንዳንድ ገዳማት በየዓመቱ የአበምኔቶች መደበኛ ስብሰባ ስለነበራቸው፣ የደረሱባቸውን አዳዲስ የቴክኖሎጂ እውቀቶችና ልምዶች ይለዋወጡ ስለነበር በዚህ መንገድ ሥልጣኔ በመላው አውሮፓ እንዲስፋፋ የራሳቸውን ታላቅ ሚና ተጫውተዋል።

ከክርስትና በፊት የጉልበት ሥራ መልካም ክብርና ስም አልነበረውም። በግሪኮች ትምህርት መሠረት የጉልበት ሥራ የዝቅተኞቹ ኅብረተሰብ ክፍል (የድሀውና የባሪያዎች) ሥራ ተደርጎ ይወሰድ ነበር። በሮማውያን ዘንድም ለሥራ የነበረው መንፈስ ተመሳሳይ ነበር። ለጉልበት ሥራ በተለይም ለግብርና ከፍ ያለ ቦታና ከበሬታ የሰጡት ገዳማት ናቸው።

ከዚህም ጋር ገዳማት ለድሆች፣ ለስደተኞች፣ ለወላጅ አልባ ልጆች፣ ለሕሙማንና ለችግረኞች መጠጊያዎች በመሆን አገለግልዋል። ለምሳሌ ያህል፣ በ4ኛው መ/ዓ የነበረው ቅዱስ ባስልዮስ የመሠረታቸው ገዳማት ሐኪም ቤቶች፣ የድሆች መመገቢያዎችና የችግረኞች መርጃ ማዕከሎችም ነበሩ። የዘመናዊ ሆስፒታል ጽንሰ-ሐሳብ መሠረቱ ክርስቲያናዊ ገዳማት ናቸው።

እንደዚሁም ገዳማት የሥነ ጽሑፍና የትምህርት ማዕከላት ነበሩ። ታላላቅ ቤተ መጻሕፍት የነበራቸው ብዙ ገዳማት ነበሩ። ብዙ መጻሕፍት ከእኛ እንዲደርሱ ያደረጉት መጻሕፍትን የሚሰበስቡና ባለሙያዎችን መድበው በእጅ የሚያስገለብጡ ገዳማት ናቸው። ብዙዎቹ መጻሕፍትና የታሪክ መዛግብት ከጥፋት ተርፈው ከዛሬ የደረሱት በገዳማት ተደብቀውና ተጠብቀው ስለኖሩ ነው።

ግሪኮች በኦቶማን ቱርክ በተገዙባቸው ወደ 300 የሚደርሱ ዘመናት ውስጥ እምነታቸውን ብቻ ሳይሆን ቋንቋቸውን፣ ባህላቸውንና ሥነ ጽሑፋቸውን ሕያው አድርገው የጠበቁት በገዳማት ዋና ማዕከልነት ነበር። ገዳማቱ ለካህናት ብቻ ሳይሆን በቱርኮች ግዛት ሥር ለነበሩ መላው ግሪካውያን ስውር ት/ቤቶች ነበሩ። በአገራችንና በሌሎች አገራትም ብዙ ተመሳሳይ ታሪኮች አሉ። ነጻነትን ለሚወዱና ባርነትን ለሚጸየፉ ሰዎች ሁሉ እነዚህ ትርጉማቸው ጥልቅ ነው። የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ገዳማትን ትቁር ጥምድ የሚያደርጓቸውም ለዚህ ነው።

መናንያን አባቶችና እናቶች ለሰው ልጅ ሁሉ ምሕረትን ከእግዚአብሔር የሚለምኑ ናቸው። በአስቄጥስ ገዳም ስለ ነበረ አባ ኢሳይያስ ስለ ተባለ አባት በመጽሐፈ ገነት እንዲህ ተብሎ እናገኛለን፡- “በዋዕየ ፀሐይ ላይ ራቁቱን ቁሞ ስለ መላው ዐለም ሲጸልይ ሳለ ከመነኰሳት አንዱ እንዲህ የሚል ድምጽ ሰማ፡- ‘ከእርሱ ጸሎት የተነሣ ለዐለሙ ሁሉ ምሕረት አድርጌያለሁና ሂድና ለአባ ኢሳይያስ ሰውነቱን የሚሸፍንበት ልብስ ስጠው።’”

ገዳማውያን መናንያን ሌላውን የሚዘርፉና የሚያጠፉ ሳይሆኑ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሕረትን የሚለምኑ ናቸው፣ ሰውን የሚያሳድዱ ሳይሆኑ የተሰደዱትን የሚቀበሉ ናቸው። እንኳንስ የሰው ልጅ እንስሳትና አራዊት እንኳ አዳኞች ሲያሳድዷቸው ሸሽተው የሚጠጉባቸው ናቸው። የፍርሃትና የአጎብዳጅነት መንፈስ ያይደለ የእውነትና የጥብዓት መንፈስ ያለው ሁሉ ይህን ይረዳል።

ምንም እንኳ ምናኔያዊ ሕይወት ዓላማው በዚህ ዐለም ሀብት መበልጸግ ባይሆንም፣ በኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ረገድም ቢሆን ገዳማት በየዘመናቱ የነበራቸው ሚና ቀላል አልነበረም። ለአብነት ያህል በዘመናችን የግብፅን የእንስሳት ተዋጽዖ ምርቶች በከፍተኛ ድርሻ የሚሸፍኑት ኦርቶዶክሳውያን ገዳማት ናቸው። የአስቄጥስ ገዳም ለግብፅ የአየርና የዐፈር ጠባይ ተስማሚ የእህልና የአትክልት ዝርያዎችን በማምረት የአገሪቱን የምግብ አቅርቦት ችግር በመፍታት ረገድ የተጫወተው ሚና ታላቅ ነው።

በተለይም ደግሞ የአስቄጥስ ገዳም መነኰሳት በሳይንሳዊ ምርምር በግብፅ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ ያመረቱት “ፎደር ቢት” (fodder beet) የተሰኘ የስኳር ድንች ዓይነት አዲስ ምርት በእጅጉ ተመስግነውበታል። የአሰቄጥስ ገዳም መነኰሳት በዚህ ረገድ ላበረከቱት አስተዋጽዖ ሙስሊሙ መሪ አንዋር ሳዳት ከታላቅ ምስጋና ጋር ብዙ ሽልማት አበርክቶላቸዋል። ሌሎቹ የግብፅ ገዳማትም ለበረሃው ተስማሚ የሆኑ የዕፅዋትና አዝዕርት ዓይነቶችን በሳይንሳዊ ምርምር በመፈለግ ረገድ ከፍተኛ ሥራ እየሠሩ ናቸው።

ወደ ግብጽ አባ ቢሾይ ገዳም ተጉዞ የነበረ አህመድ ኤል-ጋማል የተባለ የተባበሩት ዐረብ ኤምሬትስ ጋዜጠኛ November 21, 1988 ላይ በወጣ “Khaleeg” በተባለ ጋዜጣ ላይ “A visit to the Depth of the Desert” በሚል ርዕስ እንዲህ ጽፎ ነበር፡-
....“በአባ ቢሾይ ገዳም ከአባቶች መነኰሳት ጋር ተገናኘሁ። በዚያም የቦታውን መንፈሳዊነትም ሆነ የእንግዳ ተቀባይነታቸውን ነገር፣ እንዲሁም ዘርፈ ብዙ የሆነውን ተግባራቸውንና ትምህርታቸውን ተመለከትሁ፤ ሆኖም ግን ካየሁት ሁሉ አንዱንም እንኳ እንደሚገባ አድርጌ አሟልቼ ልገልጸው አልችልም። ሆኖም የክርስትና ገዳማዊ ሕይወት በታሪካችን ውስጥ የነበረውን ሚና መዘንጋት ለእያንዳንዱ ዐረብ ታላቅ ኪሳራ የመሆኑ ነገር ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ማስተዋል ተገቢ መሆኑን ለራሴ ተረድቻለሁ። በእ*ስልምና ሃይማኖት ውስጥ ምንኲስናና ገዳማዊ ሕይወት የሚባል ነገር አለመኖሩን ማሰብ ውስጥን የሚረብሽና የሚያሳዝን ነገር ነው።”

መናንያን በሥራ የሻከሩ እጆች ያሏቸው ብቻ ሳይሆኑ ከርኩሰትና ከነውር ንጹሕ የሆነች ነፍስ ትኖራቸው ዘንድ የሚጋደሉ እውነተኛ ጀግናዎችና ትክክለኛ ፈላስፋዎች ናቸው። ከመብላትና መጠጣት፣ ከማግባትና ከመጋባት ባሻገር ወዳለው ሰማያዊ ሕይወት የሚያመለክቱ አቅጣጫ ጠቋሚዎችና ዐዋጅ ነጋሪዎች ናቸው።

ስለሆነም ሰው ያልደረሰበትን ነገር በመሰላል ወጥቼ ልንቀፍ ማለት ተገቢ አይደለም! ሊታገሡት የሚገባም አይደለም! በዕድሜያቸውም ሆነ በእውቀታቸው ታዳጊ የነበሩት የ1950ዎቹና 60ዎቹ ትውልዶች በኦርቶዶክስ-ጠል መምህራን የተሞሉት ጥላቻ ዛሬ ያፈራውን መራራ ፍሬ እያየን፣ የእነዚያ የመንፈስ ልጆች የሆኑ በዕድሜ እንኳ ባይሆን በአእምሮ ሕፃናት የሆኑ ኦርቶዶክስ-ጠሎች ተገቢ ያልሆኑ ነገሮችን ሲናገሩና ሲጽፉ እያዩ ኦርቶዶክሳውያን ዝም ማለት አይችሉም።

ኦርቶዶክሳውያን፣ ገና ለገና ያሻንን ብንላቸው ለክፉ አይሰጡንም የሚሉ የፈሪዎችና የአጎብዳጆች የብዕር መፈተኛና የአፍ ማሟሻ መሆንን መቀበል ከማይችሉበት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሰዋል። ስለዚህ ወደ ላይ አያዳልጣችሁ! የሚታየውን ብቻ ሳይሆን የማይታየውን መፍራትም ብልህነት ነው!
ቅዱስ አትናቴዎስ -795.pdf
19.9 MB
ቅዱስ አትናቴዎስ ሕይወቱ እና ትምህርቱ በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ
ፍኖተ ቅዱሳን (1).pdf
152.9 MB
ፍኖተ ቅዱሳን

በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
"ዳዊት በቀንም በማዕልትም ሕጉን የሚያነብ ብጹዕ ነው ብሏልና ፡፡ በጎዳናም ቢሆን ፤ በቤትም ቢሆን ፤ ስትተኛም ቢሆን ፤ ከእርሱ ይቅርታንና ቸርነትን ታገኝ ዘንድ ፤ ፈጣርህ እግዚአብሔርን በፍፅም ህሊናህ ፤ በፍፅም አእምሮህ ፤ በፍጹም ልቦናህ ፤ ውደደው" !! ።

       መፅሐፈ ዲዲስቅልያ
+ ስለቅዱሳንና ቅድስና ጥቂት +

በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳን ሲባል፡- ሐዋርያት፣ ነቢያት፣ ሰማዕታት፣ ሊቃውንት፣ መናንያን /ገዳማውያን/፣ ደጋግ ሰብአ ዓለም ይጠቀሳሉ፡፡ ቅዱሳን ዜግነትና ተቋማዊ አጥር ባይኖርባቸውም በልማድ እንደየሚከበሩበት ቦታ ስፋትና ጥበት አካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ እየተባሉ ይለያሉ፡፡ የቅድስና አሰጣጡ አስቀድሞ በጉባኤ ደረጃ አልነበረም፡፡ ሰማዕታት የሆኑ እንደሆነ ምስክርነቱ የአደባባይ ነውና በቶሎ ቅድስና ያገኛሉ፡፡ አንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅና ቅዱስ ባስልዮስ ያሉ በአፍም በመጻፍም የገነኑ አበው ግብርና ቅድስናቸው ከመጉላቱ የተነሣ ከቤተ ክህነቱ ቀድሞ ምዕመኑ በቅድስና ጠርቷቸዋል፡፡ ቅድስናው በገቢረ ተአምርና በራእይ የሚገለጥም አለ፡፡

በዚህ ዘመን ግን ከሞላ ጎደል በሁሉም ሐዋርያዊ ትውፊትን በሚከተሉ አብያተ ክርስቲያናት ቅድስና በቃለ ሲኖዶስ ይሰጣል፡፡ የእኛም አካሄድ ተመሳሳይ ነው፡፡ አንድ አባት ቅዱስ ከተባለ በኋላ ስለሚደረገው ልዩ ልዩ ተግባር በ #ወልታ_ጽድቅ ወይም በዲያቆን ሰሎሞን #የኢትዮጵያ_ቤተ_ክርስቲያን_ወርቃማ_ዘመናት ወይም ደግሞ በዶ/ር ሐዲስ የሻነው የትምህርተ ሃይማኖት መጻሕፍት ማንበብ ይቻላል፡፡ ቅድስና በየጊዜው የሚጨመር ነው፤ አይቆምም፡፡ በሌላ በኩል በበጎ የሚነሣው አባት ላይ ከጊዜ በኋላ የሃይማኖት ህፀፅ የተገኘ እንደሆነ የሚታረምበት ዕድል ስለመኖሩ የአርጌንስ ታሪክና የእኛ ሲኖዶስ የግብፆችን የስንክሳር ስርዋጽ ያረመበት ድርጊት ይጠቁመናል፡፡

በ1960ዎቹ ተጀምሮ ሲካሄድ ቆይቶ እንደ መቀዛቀዝ ባለው የኦሪየንታል-ምሥራቃውያን ኢመደበኛ ንግግር የቅድስና አሰጣጥን፣ ማንና እንዴት ቅዱስ ይባል ማለትን ለነገረ መለኮትና ለታሪክ ምሁራን በመተው በግራ ቀኝ ወገኖች የተላለፈው ግዝት እንዲነሣ ሐሳብ ቀርቦ ነበረ፡፡ ሐሳቡ እስካሁን ዳር አልደረሰም ብቻ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያናችን በ1988 ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ በተቋቋመ የጳጳሳትና የሊቃውንት ኮሚቴ የተዘጋቸው የእምነት፣ ሥርዓትና የውጭ ግንኙነት መጽሐፍ በኬልቄዶናውያን ላይ የተላለፈው ግዝት እንደማይነሣ፣ በእነርሱ ስር ያሉ አበውንም በቅድስና መቀበል እንደማይችል በአጽንዖት ገልጧል፡፡ ቀድመው በስንክሳራችን በገቡት የሃይማኖት ጀርባቸው ከወደ ኬልቄዶን በሚመዘዝ አበው ላይ ግን ያሳረፈው ውሳኔ የለም፡፡
---

( ደብተራ በአማን ነጸረ )

⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
“ንስሐ ሰውን ከፍ የደርጋል”

“ለቅሶ የሰማይ በር ያንኳኳል”

“ቅዱስ ትህትና ይከፍታል”

ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋሰው (St. John Climacus)

⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
"ሳምራዊቷ ሴት ውሃ አጠጭኝ ሲላትም የተጠማው ውሃን ሳይሆን የእርሷን ነፍስ ነበር እርሷ ግን የተጠማው ምን እንደሆነ ሳታውቅ ፣ስለዘር ልዩነት ለመከራከር ተነሳች። መቼም የእግዚአብሔር ን ስጦታና ውሃ አጠጡኝ የሚላቸው ማን እንደሆነ የማያውቁ ሁሉ  ዘርኞች ናቸው። ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ፊት ቆመውም እንኳን ዘር መቁጠራቸውን አያቆሙም። እግዚአብሔር ግን የሚፈልገው የሰዎችን ነፍሳቸውን እንጂ ወደላይ ቢቆጠር ሄዶ ሄዶ አንዱ አዳም ላይ የሚያርፈውን የዘር ሀረጋቸውን አይደለም። "
     --- ሕማማት ----
• ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ


⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
Audio
ሃጢያትን ብቻችሁን አትፍለሙ!
#እግዚአብሔርን ጥሩት!
#እግዚአብሔርን_አናግሩት፥ እንዲህም በሉት:-

👆(ሙሉውን ያድምጡ)

(ብፁዕ አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ)

⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
የኤፍራጥስ ወንዝ @EOTC_library .pdf
56.9 MB
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
የብርሃን እናት ዲያቆን ሔኖክ ሃይሌ.pdf
35.5 MB
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
Orthodoxy can't be comfortable unless it's fake

Fr Seraphim Rose
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተባለው ምስባክ

“ምድርኒ ወሀበት ፍሬሃ፤
ወይባርከነ እግዚአብሔር አምላክነ።
ወይባርከነ እግዚአብሔር፤
ወይፍርህዎ ኵሎሙ አጽናፈ ምድር።”
[መዝሙር ዳዊት 67: 6-7]

በግእዝ አጨናነኳችሁ አ..?? አይዞን እኔም ምስባክ ላይ በአማርኛ ሲሉት ስሰማ ጥቅሱን ይዤው ነው😁😁

“ምድር ፍሬዋን ሰጠች፤
እግዚአብሔር አምላካችንም ይባርከናል።
እግዚአብሔር ይባርከናል፥
የምድርም ዳርቻ ሁሉ ይፈሩታል።”

ከዝናብ በኋላ ምድር ፍሬዋን ትሰጣለች.. እንዲሁ ከእግዚአብሔር በረከት ወይም ጸጋ በኋላ ከምድር የተዘጋጀን እኛ ደግሞ ፍሬን እንሰጣለን.. ሰው ጌታችን ኢየሱስ ከሚሰጠው ከሕይወት ውኃ ሳይጠጣ ፍሬን ማፍራት አይችልም.. እኛ ደግሞ ከዚህ ውኃ ጠጥተናልና እንደ ምድረ በዳ እሾህና አመኬላን እንደሚያበቅል ምድር አንሁን.. ከኃጢአት ሁሉ እየራቅን ከጸጋው የተነሳ ፍሬን እናፍራ..

“እግዚአብሔር አምላካችን ይባርከናል”

መልካም የጌታ ቀን

@Apostolic_Answers
🕯የቤተ ክርስቲያን ካህን ላንተ እንደ መንፈሳዊ አባት ይሁንልህ:: አንድ ሕመምተኛ ስውር በሽታዎቹን በግልጽ ለሐኪም እንደሚያሳይና ከዛም እንደሚድን ሁሉ አንተም ሚስጥሮችህንለካህን በግልጽ ንገር [ ትድንማለህ ]

•ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

መልካም የጌታ ቀን (ሰንበት )!

⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
https://www.tg-me.com/orthodoxzelalemawit
⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
2024/09/29 10:23:23
Back to Top
HTML Embed Code: