የእሁድ ውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ
ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን
👉 የእሁድ (ሰንበተ ክርስትያን)ውዳሴ ማርያም አንድምታ
ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ድምጸ
ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ድምጸ
Audio
ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ክፍል 5
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"በቁም ላለመቀበር መንቂያው ጊዜ አሁን ነው"
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"መቼ ነው?!"
ምንለወጠው🤔
ምንለወጠው🤔
አንዳንድ ሰዎች ልበ ቢሶች ሆነው "እግዚአብሄር ዘወትር ሳቅንና ጨዋታን ይስጠኝ እንጂ ሁልጊዜ ማዘንንስ ከእኔ ያርቅልኝ" ይላሉ። ከዚህ በላይ ምን አላዋቂነት አለ? ዘውትራዊ ሳቅንና ጨዋታን የሚሰጥ ዲያቢሎስ እንጂ እግዚአብሔር አይደለምና። ቢያንስ እስኪ ሳቅንና ጨዋታን ያበዙት ዕጣ ፈንታቸው ምን እንደሆነ አድምጡ። "ሕዝቡም ሊበሉ ሊጠጡም ተቀመጡ ሊዘፍኑም ተነሱ" ይላልና (1ኛ ቆሮ 10:7 ፣ ዘጸ 32:6)። የሰዶም ሰዎችና የኖኅ ዘመን ሰዎች እንደዚህ ነበሩ። የሰዶም ሰዎችን አስመልክቶ ግብራቸውን ሲናገር "ትዕቢት እንጀራን መጥገብ መዝለልና ስራ መፍታት" ይላልና (ሕዝ 16:49)። በኖኀ ዘመን የነበሩ ሰዎችም ለብዙ ዓመታት መርከቢቱ ስትዘጋጅ እንኳ እያዩ ሊመጣ ያለውን መዓት ምንም ሳያስቡ ሲበሉ፣ ሲጠጡና ሲዘፍኑ ነበር(ማቴ 24:38)
ስለዚህ ይህ ከዲያቢሎስ የምትቀበሉትን ነገር እግዚአብሄር ይሰጣችሁ ዘንድ አትለምኑት። እግዚአብሔር የሚሰጠው የተሰበረና ትሑት ልብን፣ በመጠን መኖርንና ራስን መግዛትን፣ ፈሪሐ እግዚአብሔርን፣ ንሰሐን ኹሉና እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የኾነ ኃዘንን ነውና።
ኢየሱስ ክርስቶስ ለአልዓዛርና ለከተማይቱ ዕንባውን አፍስሶአልና፣ በይሁዳ ምክንያትም ውስጡ ታውኮአልና። አንድ ሰው ጌታችን ብዙ ቦታ ላይ እንደዚህ ሲያደርግ በርግጥ ያገኘዋል። አንድም ቦታ ላይ ግን ሳቀ፣ በጥቂቱም ወይም በትንሹም ቢኾን ፈገግ አለ የሚል አያገኝም። ንዑድ ክቡር የሚሆን ጳውሎስም ሶስት አመት ሙሉ ሌሊትና ቀን በዕንባ እነደነበረ እርሱ ራሱ ተናግሯል ሌሎችም ይህንን መስክረውለታል (ሐዋ 20:31)። እንደ ሳቀ ግን እርሱ ራሱም የትም ቦታ አልተናገረም ሌሎችም ቅዱሳንም ስለእርሱም ኾነ እርሱን ስለሚመስሉ ሌሎች ቅዱሳን እንደሳቁ ምንም አልነገሩንም። ሣራ ብቻ እንደ ሳቀች በዚህም አንደተወቀሰች(ዘፍ 18: 12-15) ፣ ነፃ የነበረው የኖኅ ልጅም በመሳቁ ምክንያት የወንድሞቹ ባርያ እንደ ኾነ ግን ይነግሩናል (ዘፍ 9:25)።
እንደዚህ ብዬ ስናገር ግን የልብ አለል ዘሊልነትን ከእናንተ ማራቅ ስለምሻ እንጂ ሳቅን ኹሉ ስነቅፍ አይደለም። ጠቢቡ "ለመሳቅ ጊዜ አለው" እንዲል (መክ 3:4)። ነገር ግን እስኪ ንገሩኝ ብዙ ወቀሳ ሊጠብቀን እንደሚችል፣ በሚያስፈራው የፍርድ ዙፋን ፊት እንደምንቆም፣ በዚኽ ዓለም ለሰራነውም ኹሉ አንድ በአንድ መልስ እንደምንሰጥ እያወቅን ተድላ ደስታን እንዴት እናደርጋለን?? ስለዚህ ዘወትር መሳቅ ፣ ስረአት የለሽና ቅምጥል መሆን ከዲያቢሎስ ጎን ለተሰለፉ ሰዎች ነው እንጂ ለእኛ ለክርስቲያኖች አይደለም።
አሁን የነገርኃችሁን ነገር ሰምታችሁ ካዘናችሁ አመሰግናችኋለው፣ " በእኔ ምክንያት ከሚያዝን በቀር ደስ የሚያሰኘኝ ማን ነው?" ይላልና (2ኛ ቆሮ 2:2) እንዲህ ማዘናችሁንና መፀፀታችሁንም መቼም ቢኾን መች አታቋርጡ። ይህ ሀዘን በበጎ ለመለወጥ መነሻ ይኾናልና። ንግግሬንም ያበረታሁትም በውስጣችሁ ያለው መርዝ ከምንጩ እንዲወጣ አድረጌ እናንተን ከዚያ ለማውጣትና ፅኑ መድኃኒት ጨምሬ ነፍሳችሁን ጤናማ ለማድረግ ነውና። እነደዚህ ብዬ የተናገርኩት ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ ክብርና ጌትነት የባህርይ ገንዘቡ በሚኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱና ሰውን በመውደዱ ኹላችንም እግዚአብሔር የሚሰጠንን ርስቱና ክብሩን እንድንወረስ ነውና አሜን!
ቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ
የማቴዎስ ወንጌልን እንዳስተማረው
ስለዚህ ይህ ከዲያቢሎስ የምትቀበሉትን ነገር እግዚአብሄር ይሰጣችሁ ዘንድ አትለምኑት። እግዚአብሔር የሚሰጠው የተሰበረና ትሑት ልብን፣ በመጠን መኖርንና ራስን መግዛትን፣ ፈሪሐ እግዚአብሔርን፣ ንሰሐን ኹሉና እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የኾነ ኃዘንን ነውና።
ኢየሱስ ክርስቶስ ለአልዓዛርና ለከተማይቱ ዕንባውን አፍስሶአልና፣ በይሁዳ ምክንያትም ውስጡ ታውኮአልና። አንድ ሰው ጌታችን ብዙ ቦታ ላይ እንደዚህ ሲያደርግ በርግጥ ያገኘዋል። አንድም ቦታ ላይ ግን ሳቀ፣ በጥቂቱም ወይም በትንሹም ቢኾን ፈገግ አለ የሚል አያገኝም። ንዑድ ክቡር የሚሆን ጳውሎስም ሶስት አመት ሙሉ ሌሊትና ቀን በዕንባ እነደነበረ እርሱ ራሱ ተናግሯል ሌሎችም ይህንን መስክረውለታል (ሐዋ 20:31)። እንደ ሳቀ ግን እርሱ ራሱም የትም ቦታ አልተናገረም ሌሎችም ቅዱሳንም ስለእርሱም ኾነ እርሱን ስለሚመስሉ ሌሎች ቅዱሳን እንደሳቁ ምንም አልነገሩንም። ሣራ ብቻ እንደ ሳቀች በዚህም አንደተወቀሰች(ዘፍ 18: 12-15) ፣ ነፃ የነበረው የኖኅ ልጅም በመሳቁ ምክንያት የወንድሞቹ ባርያ እንደ ኾነ ግን ይነግሩናል (ዘፍ 9:25)።
እንደዚህ ብዬ ስናገር ግን የልብ አለል ዘሊልነትን ከእናንተ ማራቅ ስለምሻ እንጂ ሳቅን ኹሉ ስነቅፍ አይደለም። ጠቢቡ "ለመሳቅ ጊዜ አለው" እንዲል (መክ 3:4)። ነገር ግን እስኪ ንገሩኝ ብዙ ወቀሳ ሊጠብቀን እንደሚችል፣ በሚያስፈራው የፍርድ ዙፋን ፊት እንደምንቆም፣ በዚኽ ዓለም ለሰራነውም ኹሉ አንድ በአንድ መልስ እንደምንሰጥ እያወቅን ተድላ ደስታን እንዴት እናደርጋለን?? ስለዚህ ዘወትር መሳቅ ፣ ስረአት የለሽና ቅምጥል መሆን ከዲያቢሎስ ጎን ለተሰለፉ ሰዎች ነው እንጂ ለእኛ ለክርስቲያኖች አይደለም።
አሁን የነገርኃችሁን ነገር ሰምታችሁ ካዘናችሁ አመሰግናችኋለው፣ " በእኔ ምክንያት ከሚያዝን በቀር ደስ የሚያሰኘኝ ማን ነው?" ይላልና (2ኛ ቆሮ 2:2) እንዲህ ማዘናችሁንና መፀፀታችሁንም መቼም ቢኾን መች አታቋርጡ። ይህ ሀዘን በበጎ ለመለወጥ መነሻ ይኾናልና። ንግግሬንም ያበረታሁትም በውስጣችሁ ያለው መርዝ ከምንጩ እንዲወጣ አድረጌ እናንተን ከዚያ ለማውጣትና ፅኑ መድኃኒት ጨምሬ ነፍሳችሁን ጤናማ ለማድረግ ነውና። እነደዚህ ብዬ የተናገርኩት ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ ክብርና ጌትነት የባህርይ ገንዘቡ በሚኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱና ሰውን በመውደዱ ኹላችንም እግዚአብሔር የሚሰጠንን ርስቱና ክብሩን እንድንወረስ ነውና አሜን!
ቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ
የማቴዎስ ወንጌልን እንዳስተማረው